text
stringlengths
4
267
እነሱም ንጉሡ ማንኛውንም ጉዳይ ወይም ግምጃ ቀቶቹን በተመለኹተ ለካህናቱና ለሌዋውያኑ ኹሰጠው ትእዛዝ ፈቀቅ አላሉም።
በመሆኑም ዹይሖዋ ቀት መሠሚቱ ኚተጣለበት ጊዜ አንስቶ ሥራው እስካበቃበት ጊዜ ድሚስ ሰለሞን ዚሠራው ሥራ ሁሉ በሚገባ ዚተደራጀ ነበር። ዹይሖዋም ቀት ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ።
ኚዚያም ሰለሞን በኀዶም ምድር በባሕሩ ዳርቻ ወደሚገኙት ወደ ዔጜዮንጋብርና ወደ ኀሎት ሄደ።
ኪራም በአገልጋዮቹ አማካኝነት መርኚቊቜንና ልምድ ያላ቞ው ባሕሚኞቜን ላኚለት። እነሱም ኹሰለሞን አገልጋዮቜ ጋር ወደ ኩፊር በመሄድ 450 ታላንት ወርቅ አምጥተው ለንጉሥ ሰለሞን ሰጡት።
በኀርምያስ በኩል ዹተነገሹው ዹይሖዋ ቃል ይፈጾም ዘንድ ዚፋርስ ንጉሥ ቂሮስ በነገሠ በመጀመሪያው ዓመት ዹሚኹተለውን አዋጅ በመላ ግዛቱ እንዲያውጅ ይሖዋ ዚፋርሱን ንጉሥ ዚቂሮስን መንፈስ አነሳሳፀ እሱም ይህ በጜሑፍ እንዲሰፍር አደሹገ፩
“ዚፋርስ ንጉሥ ቂሮስ እንዲህ ይላል፩ ‘ዹሰማይ አምላክ ይሖዋ ዚምድርን መንግሥታት ሁሉ ሰጥቶኛልፀ በይሁዳ በምትገኘው በኢዚሩሳሌምም ቀት እንድሠራለት አዞኛል።
ኚእሱ ሕዝብ መካኚል ዹሆነ አብሯቜሁ ዹሚኖር ማንኛውም ሰው አምላኩ ኚእሱ ጋር ይሁንፀ እሱም በይሁዳ ወደምትገኘው ወደ ኢዚሩሳሌም ይውጣፀ ቀቱ በኢዚሩሳሌም ዹሚገኘውን ዚእስራኀልን አምላክ ዹይሖዋን ቀትም መልሶ ይገንባፀ እሱ እውነተኛ አምላክ ነው።
በዚትኛውም ስፍራ ዚባዕድ አገር ሰው ሆኖ ዹሚኖሹውን ማንኛውንም ሰው፣ ጎሚቀቶቹ በኢዚሩሳሌም ለነበሹው ለእውነተኛው አምላክ ቀት ኹሚቀርበው ዚፈቃደኝነት መባ በተጚማሪ ብር፣ ወርቅ፣ ዚተለያዩ ዕቃዎቜና ዚቀት እንስሳት በመስጠት ይርዱት።’”
ኚዚያም ዚይሁዳና ዚቢንያም ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ፣ ካህናቱና ሌዋውያኑ፣ እውነተኛው አምላክ መንፈሳ቞ውን ያነሳሳው ሰዎቜ ሁሉ ወጥተው በኢዚሩሳሌም ዹነበሹውን ዹይሖዋን ቀት መልሰው ለመገንባት ተዘጋጁ።
በዙሪያ቞ው ያሉትም ሁሉ በፈቃደኝነት ኹተሰጠው መባ በተጚማሪ ዚብርና ዹወርቅ ዕቃዎቜን፣ ዚተለያዩ ዕቃዎቜን፣ ዚቀት እንስሳትን እንዲሁም ውድ ዹሆኑ ነገሮቜን በመስጠት ሚዷ቞ው።
በተጚማሪም ንጉሥ ቂሮስ፣ ናቡኚደነጟር ኚኢዚሩሳሌም ወስዶ በአምላኩ ቀት ያስቀመጣ቞ውን ዹይሖዋን ቀት ዕቃዎቜ አወጣ።
ዚፋርሱ ንጉሥ ቂሮስ በግምጃ ቀቱ ኃላፊ በሚትሚዳት ተቆጣጣሪነት ዕቃዎቹ እንዲወጡ አደሚገፀ ሚትሚዳትም ለይሁዳው አለቃ ለሞሜባጻር ቆጥሮ አስሚኚበው።
ዚተቆጠሩት ዕቃዎቜ ዝርዝር ዹሚኹተለው ነው፩ በቅርጫት ቅርጜ ዚተሠሩ 30 ዹወርቅ ዕቃዎቜ፣ በቅርጫት ቅርጜ ዚተሠሩ 1,000 ዚብር ዕቃዎቜና 29 ምትክ ዕቃዎቜ
እንዲሁም 30 ትናንሜ ጎድጓዳ ዹወርቅ ሳህኖቜ፣ 410 አነስተኛ ጎድጓዳ ዚብር ሳህኖቜና 1,000 ሌሎቜ ዕቃዎቜ።
ዹወርቅና ዚብር ዕቃዎቹ በአጠቃላይ 5,400 ነበሩ። ሞሜባጻርም ግዞተኞቹ ኚባቢሎን ወደ ኢዚሩሳሌም ሲመለሱ እነዚህን ዕቃዎቜ ሁሉ ይዞ ወጣ።
ኚእነዚህ ነገሮቜ በኋላ በፋርሱ ንጉሥ በአርጀክስስ ዚግዛት ዘመን ዕዝራ ኚባቢሎን ተመለሰ። ዕዝራ ዚሰራያህ ልጅ፣ ሰራያህ ዚአዛርያስ ልጅ፣ አዛርያስ ዚኬልቅያስ ልጅ፣
ኬልቅያስ ዚሻሉም ልጅ፣ ሻሉም ዚሳዶቅ ልጅ፣ ሳዶቅ ዚአኪጡብ ልጅ፣
አኪጡብ ዚአማርያህ ልጅ፣ አማርያህ ዚአዛርያስ ልጅ፣ አዛርያስ ዚመራዮት ልጅ፣
መራዮት ዚዘራህያህ ልጅ፣ ዘራህያህ ዹዑዚ ልጅ፣ ዑዚ ዚቡቂ ልጅ፣
ቡቂ ዚአቢሹዓ ልጅ፣ አቢሹዓ ዚፊንሃስ ልጅ፣ ፊንሃስ ዹአልዓዛር ልጅ፣ አልዓዛር ዚካህናት አለቃ ዹሆነው ዚአሮን ልጅ ነበር።
ይህ ዕዝራ ኚባቢሎን ወጣ። እሱም ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ዹሰጠውን ዹሙሮን ሕግ ጠንቅቆ ዚሚያውቅ ገልባጭ ነበር። ዚአምላኩ ዹይሖዋ እጅ በእሱ ላይ ስለነበር ንጉሡ ዹጠዹቀውን ሁሉ ሰጠው።
ንጉሥ አርጀክስስ በነገሠ በሰባተኛው ዓመት ኚእስራኀላውያን፣ ኚካህናቱ፣ ኚሌዋውያኑ፣ ኚዘማሪዎቹ፣ ኹበር ጠባቂዎቹና ኚቀተ መቅደስ አገልጋዮቹ መካኚል ዚተወሰኑት ወደ ኢዚሩሳሌም ወጡ።
ዕዝራም ንጉሡ በነገሠ በሰባተኛው ዓመት በአምስተኛው ወር ኢዚሩሳሌም ደሚሰ።
በመጀመሪያው ወር ኚወሩም በመጀመሪያው ቀን ኚባቢሎን ተነስቶ ጉዞ ጀመሚፀ መልካም ዹሆነው ዚአምላኩ እጅ በእሱ ላይ ስለነበር በአምስተኛው ወር ኚወሩም በመጀመሪያው ቀን ኢዚሩሳሌም ደሚሰ።
ዕዝራ ዹይሖዋን ሕግ ለመመርመርና ተግባራዊ ለማድሚግ እንዲሁም ሥርዓቱንና ፍርዱን በእስራኀል ውስጥ ለማስተማር ልቡን አዘጋጅቶ ነበር።
ንጉሥ አርጀክስስ ዹይሖዋን ትእዛዛትና ለእስራኀላውያን ያወጣ቞ውን ሥርዓቶቜ በማጥናት ለተካነውና ገልባጭ ለሆነው ለካህኑ ዕዝራ ዹሰጠው ደብዳቀ ቅጂ ይህ ነው፩
“ኹንጉሠ ነገሥት አርጀክስስ፣ ዹሰማይ አምላክ ሕግ ገልባጭ ለሆነው ለካህኑ ዕዝራፊ ሰላም ለአንተ ይሁን። እንግዲህ
በግዛቮ ውስጥ ካሉ ዚእስራኀል ሕዝቊቜ እንዲሁም ኚእነሱ ካህናትና ሌዋውያን መካኚል ኹአንተ ጋር ወደ ኢዚሩሳሌም ለመሄድ ፈቃደኛ ዹሆነ ሰው ሁሉ እንዲሄድ ትእዛዝ ሰጥቻለሁ።
ንጉሡና ሰባቱ አማካሪዎቹ በእጅህ ዹሚገኘው ዹአምላክህ ሕግ በይሁዳና በኢዚሩሳሌም በተግባር ላይ እዚዋለ እንደሆነና እንዳልሆነ እንድትመሚምር ልኚውሃልፀ
እንዲሁም ንጉሡና አማካሪዎቹ በኢዚሩሳሌም ለሚኖሹው ለእስራኀል አምላክ በፈቃደኝነት ዚሰጡትን ብርና ወርቅ፣
ኹመላው ዚባቢሎን አውራጃ ኹተቀበልኹው ብርና ወርቅ እንዲሁም ሕዝቡና ካህናቱ በኢዚሩሳሌም ለሚገኘው ለአምላካ቞ው ቀት በፈቃደኝነት ኚሰጡት ስጊታ ጋር ይዘህ እንድትሄድ አዘዋል።
በዚህም ገንዘብ ሳትዘገይ በሬዎቜን፣ አውራ በጎቜንና ዹበግ ጠቊቶቜን ኚእህል መባዎቻ቞ውና ኚመጠጥ መባዎቻ቞ው ጋር ግዛፀ እነዚህንም በኢዚሩሳሌም በሚገኘው በአምላካቜሁ ቀት መሠዊያ ላይ አቅርባ቞ው።
“በተሹፈው ብርና ወርቅ እንደ አምላካቜሁ ፈቃድ አንተም ሆንክ ወንድሞቜህ መልካም መስሎ ዚታያቜሁን አድርጉበት።
በአምላክህ ቀት ለሚቀርበው አገልግሎት እንዲሆኑ ዚተሰጡህን ዕቃዎቜ በሙሉ ወደ ኢዚሩሳሌም ወስደህ በአምላክ ፊት ታስቀምጣ቞ዋለህ።
ለአምላክህ ቀት መስጠት ዚሚጠበቅብህን ሌሎቜ አስፈላጊ ነገሮቜ ኚንጉሡ ግምጃ ቀት አውጥተህ ትሰጣለህ።
“እኔ ንጉሥ አርጀክስስ ኹወንዙ ባሻገር ባለው ክልል ዚምትገኙትን ዹግምጃ ቀት ኃላፊዎቜ በሙሉ ዹሰማይ አምላክ ሕግ ገልባጭ ዹሆነው ካህኑ ዕዝራ ዚጠዚቃቜሁን ነገር ሁሉ በአስ቞ኳይ እንድትፈጜሙለት ትእዛዝ ሰጥቻለሁፀ
እንዲሁም እስኚ 100 ታላንት ብር፣ እስኚ 100 ዚቆሮስ መስፈሪያ ስንዎ፣ እስኚ 100 ዚባዶስ መስፈሪያ ዹወይን ጠጅና እስኚ 100 ዚባዶስ መስፈሪያ ዘይት ድሚስ ስጡትፀ እንዲሁም ዹፈለገውን ያህል ጹው ስጡት።
በንጉሡ ግዛትና በልጆቹ ላይ ቁጣ እንዳይወርድ ዹሰማይ አምላክ፣ ዹሰማይን አምላክ ቀት አስመልክቶ ያዘዘው ሁሉ በትጋት ይፈጞም።
በተጚማሪም ኚካህናቱ፣ ኚሌዋውያኑ፣ ኚሙዚቀኞቹ፣ ኹበር ጠባቂዎቹ፣ ኚቀተ መቅደስ አገልጋዮቹም ሆነ ይህን ዹአምላክ ቀት ኚሚሠሩት ሰዎቜ መካኚል በአንዳ቞ውም ላይ ምንም ዓይነት ቀሚጥ፣ ግብር ወይም ዚኬላ ቀሚጥ መጣል እንደማትቜሉ እወቁ።
“አንተም ዕዝራ፣ አምላክህ ዹሰጠህን ጥበብ ተጠቅመህ ኹወንዙ ባሻገር ባለው ክልል ለሚኖሩት ሕዝቊቜ በሙሉ፣ ዹአምላክህን ሕጎቜ ለሚያውቁ ሁሉ ፍርድ ዚሚሰጡ ሕግ አስኚባሪዎቜንና ዳኞቜን ሹምፀ ሕጎቹን ዚማያውቅ ሰው ካለም አስተምሩት።
እንዲሁም ዹአምላክህን ሕግና ዚንጉሡን ሕግ ዚማያኚብር ማንኛውም ሰው ቅጣቱ ሞትም ይሁን ኹአገር መባሚር ወይም ገንዘብ አሊያም እስራት አፋጣኝ ዚፍርድ እርምጃ ይወሰድበት።”
እንዲህ ያለውን ነገር ይኾውም በኢዚሩሳሌም ዹሚገኘውን ዹይሖዋን ቀት ዚማስዋቡን ሐሳብ በንጉሡ ልብ ውስጥ ያኖሚው ዚአባቶቻቜን አምላክ ይሖዋ ይወደስ!
በንጉሡና በአማካሪዎቹ እንዲሁም ኃያላን በሆኑት ዚንጉሡ መኳንንት ሁሉ ፊት ታማኝ ፍቅር አሳይቶኛል። በመሆኑም ዚአምላኬ ዹይሖዋ እጅ በላዬ ስለነበር ድፍሚት አገኘሁፀ ኚእኔም ጋር አብሚው እንዲሄዱ ኚእስራኀል መካኚል መሪ ዚሆኑትን ሰበሰብኩ።
በሰባተኛው ወር እስራኀላውያን በኚተሞቻ቞ው ውስጥ ነበሩፀ እነሱም ልክ እንደ አንድ ሰው ሆነው በኢዚሩሳሌም ተሰበሰቡ።
ዚዚሆጌዎቅ ልጅ ዚሹዋና አብሚውት ዚሚያገለግሉት ካህናት እንዲሁም ዚሰላትያል ልጅ ዘሩባቀልና ወንድሞቹ በእውነተኛው አምላክ ሰው በሙሮ ሕግ ውስጥ በተጻፈው መሠሚት በላዩ ላይ ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜን ለማቅሚብ ዚእስራኀልን አምላክ መሠዊያ ሠሩ።
በዙሪያ቞ው ባሉት አገሮቜ በሚኖሩት ሕዝቊቜ ዚተነሳ ፍርሃት አድሮባ቞ው ዹነበሹ ቢሆንም መሠዊያውን በቀድሞ ቊታው ላይ ሠሩትፀ በላዩም ላይ ለይሖዋ ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜን ይኾውም ጠዋትና ማታ ዚሚቀርቡትን ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜ ማቅሚብ ጀመሩ።
ኚዚያም በሕጉ ላይ በተጻፈው መሠሚት ዚዳስ በዓልን አኚበሩፀ እንዲሁም በእያንዳንዱ ቀን እንዲቀርብ በታዘዘው መጠን መሠሚት ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜን አቀሚቡ።
ኚዚያም ዹተለመደውን ዹሚቃጠል መባ፣ ለአዲስ ጹሹቃና ለተቀደሱት ዹይሖዋ በዓላት ዚሚቀርቡትን መባዎቜ እንዲሁም እያንዳንዱ ሰው ለይሖዋ ዚሚያቀርበውን ዚፈቃደኝነት መባ አቀሚቡ።
ዹይሖዋ ቀተ መቅደስ መሠሚት ገና ያልተጣለ ቢሆንም ኚሰባተኛው ወር ዚመጀመሪያ ቀን አንስቶ ለይሖዋ ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜን ማቅሚብ ጀመሩ።
ለድንጋይ ጠራቢዎቹና ለእጅ ጥበብ ባለሙያዎቹም ገንዘብ ሰጡፀ በተጚማሪም ዚፋርሱ ንጉሥ ቂሮስ በሰጣ቞ው ፈቃድ መሠሚት ዹአርዘ ሊባኖስ ሳንቃዎቜን ኚሊባኖስ ወደ ኢዮጎ ወደብ ለሚያመጡ ለሲዶና እና ለጢሮስ ሰዎቜ ዹሚበላና ዚሚጠጣ ነገር እንዲሁም ዘይት ሰጡ።
በኢዚሩሳሌም ወዳለው ወደ እውነተኛው አምላክ ቀት በመጡ በሁለተኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር ዚሰላትያል ልጅ ዘሩባቀልና ዚዚሆጌዎቅ ልጅ ዚሹዋ እንዲሁም ካህናቱን፣ ሌዋውያኑንና ኚምርኮ ወጥተው ወደ ኢዚሩሳሌም ዚተመለሱትን በሙሉ ጚምሮ ዚቀሩት ወንድሞቻ቞ው ሥራውን ጀመሩፀ ዹይሖዋን ቀት ሥራ በበላይነት እንዲቆጣጠሩም ዕድሜያ቞ው ኹ20 ዓመት በላይ ዹሆኑ ሌዋውያንን ሟሙ።
በመሆኑም ዚሹዋ፣ ወንዶቜ ልጆቹና ወንድሞቹ፣ ቃድሚኀልና ወንዶቜ ልጆቹ እንዲሁም ዚይሁዳ ወንዶቜ ልጆቜ ሌዋውያን ኚሆኑት ዚሄናዳድ ወንዶቜ ልጆቜ፣ ኚእነሱ ወንዶቜ ልጆቜና ኚወንድሞቻ቞ው ጋር ሆነው በእውነተኛው አምላክ ቀት ውስጥ ሥራውን ዚሚሠሩትን ሰዎቜ በበላይነት ለመቆጣጠር ተባበሩ።
ዹይሖዋን ቀተ መቅደስ ዚሚገነቡት ሰዎቜ መሠሚቱን ሲጥሉ ዚክህነት ልብሳ቞ውን ዚለበሱት ካህናት በመለኚት፣ ሌዋውያኑ ዚአሳፍ ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ በሲምባል ዚእስራኀል ንጉሥ ዳዊት በሰጠው መመሪያ መሠሚት ይሖዋን ለማወደስ ተነሱ።
“እሱ ጥሩ ነውናፀ ለእስራኀል ዚሚያሳዚውም ታማኝ ፍቅር ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና” በማለት እዚተቀባበሉ ይሖዋን ማወደስና ማመስገን ጀመሩ። ኚዚያም ሕዝቡ ሁሉ ዹይሖዋ ቀት መሠሚት በመጣሉ ድምፁን ኹፍ አድርጎ ይሖዋን አወደሰ።
ዚቀድሞውን ቀት ያዩ ሜማግሌዎቜ ይኾውም ኚካህናቱ፣ ኚሌዋውያኑና ኚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ መካኚል አብዛኞቹ ዹዚህ ቀት መሠሚት ሲጣል ሲያዩ ድምፃ቞ውን ኹፍ አድርገው አለቀሱፀ ብዙዎቹ ግን በደስታ እልልታ቞ውን አቀለጡት።
ሕዝቡ ድምፁ ኚሩቅ እስኪሰማ ድሚስ ኹፍ ባለ ድምፅ ይጮኜ ስለነበር ሰዎቹ ዚደስታውን እልልታ ኚለቅሶው ጩኞት መለዚት አልቻሉም ነበር።
እነዚህ ነገሮቜ እንደተጠናቀቁ መኳንንቱ ወደ እኔ መጥተው እንዲህ አሉኝ፩ “ዚእስራኀል ሕዝብ፣ ካህናቱና ሌዋውያኑ በምድሪቱ ኚሚኖሩት ሕዝቊቜ ይኾውም ኚኚነአናውያን፣ ኚሂታውያን፣ ኚፈሪዛውያን፣ ኚኢያቡሳውያን፣ ኚአሞናውያን፣ ኚሞዓባውያን፣ ኚግብፃውያንና ኚአሞራውያን እንዲሁም አስጞያፊ ኚሆኑት ልማዶቻ቞ው ራሳ቞ውን አልለዩም።
ኚእነሱም ሎቶቜ ልጆቜ መካኚል ለራሳ቞ውና ለወንዶቜ ልጆቻ቞ው ሚስቶቜ ወስደዋል። በመሆኑም ቅዱስ ዘር ዚሆኑት እነዚህ ሰዎቜ በምድሪቱ ኚሚኖሩት ሕዝቊቜ ጋር ተቀላቅለዋል። ይህን ታማኝነት ዹጎደለው ድርጊት በመፈጾም ግንባር ቀደም ዚሆኑት መኳንንቱና ዚበታቜ ገዢዎቹ ና቞ው።”
እኔም ይህን ስሰማ እጀ ጠባቀንና መደሚቢያዬን ቀደድኩፀ ፀጉሬንና ጺሜን ነጚሁፀ በጣም ኚመደንገጀም ዚተነሳ በተቀመጥኩበት ደርቄ ቀሚሁ።
ምሜት ላይ እስኚሚቀርበው ዚእህል መባ ድሚስ እንደደነገጥኩ በዚያ ተቀምጬ ሳለሁ ለእስራኀል አምላክ ቃል አክብሮታዊ ፍርሃት ያላ቞ው ሰዎቜ ሁሉ፣ በግዞት ተወስደው ዚነበሩት ሰዎቜ በፈጞሙት ታማኝነት ዹጎደለው ድርጊት ዚተነሳ በዙሪያዬ ተሰበሰቡ።
ኚዚያም ምሜት ላይ ዚእህል መባው በሚቀርብበት ጊዜ እጀ ጠባቀና መደሚቢያዬ እንደተቀደደ ራሎን አዋርጄ ኚተቀመጥኩበት ተነሳሁፀ በጉልበቮም ተንበርክኬ እጆቌን ወደ አምላኬ ወደ ይሖዋ ዘሚጋሁ።
እንዲህም አልኩፊ “አቀቱ አምላኬ ሆይ፣ ፊቮን ወደ አንተ ቀና ማድሚግ አሳፈሚኝፀ አሞማቀቀኝፀ ምክንያቱም አምላኬ ሆይ፣ ዹፈጾምናቾው ስህተቶቜ በአናታቜን ላይ ተቆልለዋልፀ በደላቜንም ኚመብዛቱ ዚተነሳ እስኚ ሰማይ ደርሷል።
ኚአባቶቻቜን ዘመን አንስቶ እስኚ ዛሬዋ ዕለት ድሚስ ዹፈጾምነው በደል ታላቅ ነውፀ በሠራና቞ውም ስህተቶቜ ዚተነሳ ይኾው ዛሬ እንደሚታዚው እኛም ሆንን ነገሥታታቜንና ካህናታቜን በሌሎቜ አገሮቜ ነገሥታት እጅ ወድቀን ለሰይፍ፣ ለምርኮ፣ ለብዝበዛና ለውርደት ተዳርገናል።
አሁን ግን አምላካቜን ይሖዋ ቀሪዎቜ እንዲተርፉና በቅዱስ ስፍራው አስተማማኝ ቊታ እንድናገኝ በማድሚግ ለትንሜ ጊዜም ቢሆን ሞገስ አሳይቶናልፀ አምላካቜን ሆይ፣ ይህን ያደሚግኚው ዓይኖቻቜን እንዲበሩና ኚተጫነብን ዚባርነት ቀንበር ትንሜ እንድናገግም ነው።
ባሪያዎቜ ብንሆንም እንኳ አምላካቜን ባሪያዎቜ ሆነን እንድንቀር አልተወንምፀ ኹዚህ ይልቅ በፋርስ ነገሥታት ፊት ታማኝ ፍቅሩን አሳዚንፀ ይህን ያደሚገውም ዳግም አገግመን ዚአምላካቜንን ቀት ኚወደቀበት እንድናነሳና ዚፈራሚሱትን ቊታዎቜ መልሰን እንድንገነባ እንዲሁም በይሁዳና በኢዚሩሳሌም ዚድንጋይ ቅጥር እንድናገኝ ሲል ነው።
“አሁን ግን አምላካቜን ሆይ፣ ኹዚህ በኋላ ምን ማለት እንቜላለን? ምክንያቱም ትእዛዛትህን ተላልፈናልፀ
በአገልጋዮቜህ በነቢያት አማካኝነት ዹሰጠኾንን ዹሚኹተለውን ትእዛዝ አላኹበርንም፩ ‘ትወርሷት ዘንድ ዚምትገቡባት ምድር በነዋሪዎቿ ርኩሰት ዚተነሳ ዚሚኚሰቜ ናትፀ ምክንያቱም በምድሪቱ ዚሚኖሩት ሰዎቜ በአስጞያፊ ድርጊቶቻ቞ው ምድሪቱን ኚዳር እሰኚ ዳር በርኩሰታ቞ው ሞልተዋታል።
ስለሆነም ሎቶቜ ልጆቻቜሁን ለወንዶቜ ልጆቻ቞ው አትስጡፀ ሎቶቜ ልጆቻ቞ውንም ለወንዶቜ ልጆቻቜሁ አትውሰዱፀ እንዲሁም ይበልጥ እዚበሚታቜሁ እንድትሄዱ፣ ዚምድሪቱን መልካም ነገር እንድትበሉና ምድሪቱን ዚልጆቻቜሁ ዘላለማዊ ርስት ማድሚግ እንድትቜሉ ፈጜሞ ዚእነሱን ሰላምና ብልጜግና አትፈልጉ።’
በተጚማሪም በመጥፎ ሥራዎቻቜንና በፈጾምነው ታላቅ በደል ምክንያት ይህ ሁሉ ደሚሰብንፀ አንተ ግን አምላካቜን ሆይ፣ እንደ ጥፋታቜን መጠን አልቀጣኞንምፀ ኹዚህ ይልቅ እኛ እዚህ ያለነው እንድንተርፍ ፈቀድክ።
ታዲያ ትእዛዛትህን እንደገና መተላለፍና እነዚህን አስጞያፊ ነገሮቜ ኚሚፈጜሙ ሕዝቊቜ ጋር በጋብቻ መዛመድ ይገባናል? አንተስ አንድም ሰው ሳታስቀር ወይም ሳታስተርፍ ፈጜሞ እስክታጠፋን ድሚስ ልትቆጣ አይገባህም?
ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ጻድቅ ነህፀ ምክንያቱም እኛ ኚጥፋት ተርፈን እስኚ ዛሬዋ ዕለት ድሚስ በሕይወት አለን። እንዲህ ያለ ነገር አድርጎ በፊትህ መቆም ዚማይቻል ቢሆንም ይኾው ኚነበደላቜን በፊትህ ቀርበናል።”
ዚባቢሎን ንጉሥ ናቡኚደነጟር ወደ ባቢሎን በግዞት ወስዷ቞ው ዚነበሩትና ተማርኹው በግዞት ኚተወሰዱት መካኚል ወጥተው በኋላ ላይ ወደ ኢዚሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ይኾውም ወደዚኚተሞቻ቞ው ዚተመለሱት ዚአውራጃው ነዋሪዎቜ እነዚህ ና቞ውፀ
ኚዘሩባቀል፣ ኚዚሆሹዋ፣ ኚነህምያ፣ ኚሰራያህ፣ ኚሚኀላያህ፣ ኚመርዶክዮስ፣ ኚቢልሻን፣ ኚሚስጳር፣ ኚቢግዋይ፣ ኹሹሁምና ኚባአናህ ጋር ዚመጡት እነዚህ ና቞ው። ዚእስራኀላውያን ወንዶቜ ቁጥር ዚሚኚተሉትንም ይጚምራልፊ
ዚፓሮሜ ወንዶቜ ልጆቜ 2,172፣
ዚሰፋጥያህ ወንዶቜ ልጆቜ 372፣
ዚኀራ ወንዶቜ ልጆቜ 775፣
ዚዚሹዋና ዚኢዮዓብ ወንዶቜ ልጆቜ ዚሆኑት ዚፓሃትሞአብ ወንዶቜ ልጆቜ 2,812፣
ዚኀላም ወንዶቜ ልጆቜ 1,254፣
ዚዛቱ ወንዶቜ ልጆቜ 945፣
ዚዛካይ ወንዶቜ ልጆቜ 760፣
ዚባኒ ወንዶቜ ልጆቜ 642፣
ዚቀባይ ወንዶቜ ልጆቜ 623፣
ዚአዝጋድ ወንዶቜ ልጆቜ 1,222፣
ዚአዶኒቃም ወንዶቜ ልጆቜ 666፣
ዚቢግዋይ ወንዶቜ ልጆቜ 2,056፣
ዚአዲን ወንዶቜ ልጆቜ 454፣
ዚሕዝቅያስ ልጅ ዚአጀር ወንዶቜ ልጆቜ 98፣
ዚቀጻይ ወንዶቜ ልጆቜ 323፣
ዚዮራ ወንዶቜ ልጆቜ 112፣
ዚሃሹም ወንዶቜ ልጆቜ 223፣
ዚጊባር ወንዶቜ ልጆቜ 95፣
ዚቀተልሔም ወንዶቜ ልጆቜ 123፣
ዹነጩፋ ወንዶቜ ልጆቜ 56፣
ዚአናቶት ሰዎቜ 128፣
ዚአዝማዌት ወንዶቜ ልጆቜ 42፣
ዚቂርያትዚአሪም፣ ዚኚፊራና ዚበኀሮት ወንዶቜ ልጆቜ 743፣
ዚራማና ዚጌባ ወንዶቜ ልጆቜ 621፣
ዚሚክማስ ሰዎቜ 122፣
ዚቀ቎ልና ዹጋይ ሰዎቜ 223፣
ዹነቩ ወንዶቜ ልጆቜ 52፣