text
stringlengths
4
267
ኚዚያም ሞሜባጻር መጥቶ በኢዚሩሳሌም ዹሚገኘውን ዹአምላክን ቀት መሠሚት ጣለፀ ኚዚያን ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድሚስ ቀቱ በመገንባት ላይ ነውፀ ሆኖም ገና አላለቀም።’
“እንግዲህ አሁን፣ ንጉሡ መልካም መስሎ ኚታዚው ንጉሥ ቂሮስ በኢዚሩሳሌም ዹነበሹው ያ ዹአምላክ ቀት ተመልሶ እንዲገነባ ትእዛዝ ሰጥቶ እንደሆነና እንዳልሆነ ለማሚጋገጥ በባቢሎን በሚገኘው ዚንጉሡ ግምጃ ቀት ምርመራ ይካሄድፀ ይህን በተመለኹተም ንጉሡ ያስተላለፈው ውሳኔ ይላክልን።”
ዚይሁዳና ዚቢንያም ጠላቶቜ፣ ኚግዞት ዚተመለሱት ሰዎቜ ለእስራኀል አምላክ ለይሖዋ ቀተ መቅደስ እዚገነቡ መሆናቾውን ሲሰሙ
ወዲያውኑ ወደ ዘሩባቀልና ወደ አባቶቜ ቀት መሪዎቜ ቀርበው እንዲህ አሏቾው፩ “ኚእናንተ ጋር እንገንባፀ ልክ እንደ እናንተ እኛም አምላካቜሁን እናመልካለንፀ ደግሞም ወደዚህ ካመጣን ኹአሩር ንጉሥ ኚኀሳርሃደን ዘመን ጀምሮ ለእሱ መሥዋዕት ስናቀርብ ኖሚናል።”
ይሁንና ዘሩባቀል፣ ዚሆሹዋና ዚቀሩት ዚእስራኀል አባቶቜ ቀት መሪዎቜ እንዲህ አሏቾው፩ “ዚአምላካቜንን ቀት በመገንባቱ ሥራ ኚእኛ ጋር ተካፋይ መሆን አትቜሉምፀ ምክንያቱም ዚፋርሱ ንጉሥ፣ ንጉሥ ቂሮስ ባዘዘን መሠሚት እኛው ራሳቜን ዚእስራኀልን አምላክ ዹይሖዋን ቀት እንገነባለን።”
ዚምድሪቱም ነዋሪዎቜ ዚይሁዳን ሕዝቊቜ ተስፋ ለማስቆሚጥና ወኔ ኚድቷ቞ው ዚግንባታ ሥራውን እንዲያቆሙ ለማድሚግ ዘወትር ይጥሩ ነበር።
ኚፋርሱ ንጉሥ ኚቂሮስ ዘመን አንስቶ እስኚ ፋርሱ ንጉሥ እስኚ ዳርዮስ ዚግዛት ዘመን ድሚስ እቅዶቻ቞ውን ለማጹናገፍ አማካሪዎቜን ቀጠሩባ቞ው።
በተጚማሪም በአሐሜዌሮስ ዚግዛት ዘመን መጀመሪያ ላይ በይሁዳና በኢዚሩሳሌም ነዋሪዎቜ ላይ በጜሑፍ ክስ መሠሚቱባ቞ው።
ኹዚህም ሌላ በፋርስ ንጉሥ በአርጀክስስ ዘመን ቢሜላም፣ ሚትሚዳት፣ ታብኀልና ዚቀሩት ግብሚ አበሮቹ ለንጉሥ አርጀክስስ ደብዳቀ ጻፉፀ ደብዳቀውንም ወደ አሹማይክ ቋንቋ ተርጉመው በአሹማይክ ፊደል ጻፉት።
ዋናው ዚመንግሥት ባለሥልጣን ሹሁም እና ጾሐፊው ሺምሻይ ኢዚሩሳሌምን በመክሰስ ለንጉሥ አርጀክስስ ዹሚኹተለውን ደብዳቀ ጻፉፊ
(ደብዳቀውን ዚላኩት ዋናው ዚመንግሥት ባለሥልጣን ሚሁም፣ ጾሐፊው ሺምሻይና ዚቀሩት ግብሚ አበሮቻ቞ው እንዲሁም ዳኞቹ፣ ዚበታቜ ገዢዎቹ፣ ጞሐፊዎቹ፣ ዚኀሬክ ሕዝቊቜ፣ ባቢሎናውያን፣ ዚሱሳ ነዋሪዎቜ ማለትም ኀላማውያን፣
ታላቁና ዹተኹበሹው አስናፈር በግዞት ወስዶ በሰማርያ ኚተሞቜ ያሰፈራ቞ው ዚቀሩት ብሔራትና ኹወንዙ ባሻገር ባለው ክልል ዚሚኖሩት ዚቀሩት ሰዎቜ ነበሩፀ እንግዲህ
ዚላኩለት ደብዳቀ ቅጂ ይህ ነው።) “ለንጉሥ አርጀክስስ፣ ኹወንዙ ባሻገር ባለው ክልል ኚሚኖሩት አገልጋዮቜህፊ እንግዲህ
ኹአንተ ዘንድ ወደዚህ ወደ እኛ ዚመጡት አይሁዳውያን ኢዚሩሳሌም መድሚሳ቞ውን ንጉሡ ይወቅ። እነዚህ ሰዎቜ ዓመፀኛና ክፉ ዚሆነቜውን ኹተማ መልሰው እዚገነቡ ነውፀ ቅጥሮቿን ሠርተው እዚጚሚሱ ሲሆን መሠሚቶቿንም እዚጠገኑ ነው።
ኹተማዋ ተመልሳ ኚተገነባቜና ቅጥሮቿም ተሠርተው ኚተጠናቀቁ እነዚህ ሰዎቜ ቀሚጥም ሆነ ግብር ወይም ዚኬላ ቀሚጥ እንደማይኚፍሉ፣ በዚህም ዚተነሳ ወደ ነገሥታቱ ግምጃ ቀት ዚሚገባው ገቢ እንደሚቀንስ ንጉሡ ይወቅ።
እኛ ደግሞ ዚቀተ መንግሥቱን ጹው እዚበላን ዚንጉሡ ጥቅም ሲነካ ዝም ብሎ ማዚት ተገቢ መስሎ አልታዚንምፀ በመሆኑም ንጉሡ ጉዳዩን እንዲያውቀው ለማድሚግ ይህን ደብዳቀ ልኚናልፀ
ስለዚህ ዚቀድሞ አባቶቜህ መዝገብ ይመርመር። ይህቜ ኹተማ ዓመፀኛና ነገሥታትንም ሆነ አውራጃዎቜን ጉዳት ላይ ዚምትጥል፣ ኚጥንት ጀምሮም ዓመፅ ቆስቋሟቜን ሞሜጋ ዚምታኖር መሆኗን ኚእነዚህ መዛግብት መሚዳት ትቜላለህ። ኹተማዋም ዚተደመሰሰቜው በዚህ ዚተነሳ ነው።
ይህቜ ኹተማ ተመልሳ ኚተገነባቜና ቅጥሮቿም ተሠርተው ኹተጠናቀቁ ኹወንዙ ባሻገር ያለውን ክልል መቆጣጠር እንደማትቜል ልናሳውቅህ እንፈልጋለን።”
ንጉሡም ለዋናው ዚመንግሥት ባለሥልጣን ለሚሁም፣ ለጾሐፊው ለሺምሻይ፣ በሰማርያ ለሚኖሩት ለቀሩት ግብሚ አበሮቻ቞ውና ኹወንዙ ባሻገር ላለው ለቀሹው ክልል እንዲህ ዹሚል መልእክት ላኹ፩ “ሰላምታዬ ይድሚሳቜሁ! እንግዲህ
ዚላካቜሁልን ደብዳቀ በፊቮ ግልጜ ሆኖ ተነቧል።
በሰጠሁትም ትእዛዝ መሠሚት ምርመራ ተደርጎ ኹተማዋ ኚጥንት ጀምሮ በነገሥታት ላይ ሚብሻ ዚምትቀሰቅስ እንዲሁም ዹዓመፅና ዹወንጀል መፍለቂያ እንደነበሚቜ ተሚጋግጧል።
ኢዚሩሳሌም ኹወንዙ ባሻገር ያሉትን አካባቢዎቜ በሙሉ ዹሚገዙ ኃያላን ነገሥታት ነበሯትፀ እነሱም ቀሚጥ፣ ግብርና ዚኬላ ቀሚጥ ይቀበሉ ነበር።
እንግዲህ እኔ ትእዛዝ እስኚምሰጥ ድሚስ ኹተማዋ ተመልሳ እንዳትገነባ እነዚህ ሰዎቜ ሥራውን እንዲያቆሙ ትእዛዝ አስተላልፉ።
ዚነገሥታቱን ጥቅም ይበልጥ ዚሚጎዳ ነገር እንዳይኚሰት ይህን ጉዳይ በተመለኹተ እርምጃ ኚመውሰድ ቾል እንዳትሉ ተጠንቀቁ።”
ንጉሥ አርጀክስስ ዹላኹው ደብዳቀ በሚሁም፣ በጾሐፊው በሺምሻይና በተባባሪዎቻ቞ው ፊት ኹተነበበ በኋላ ወዲያውኑ በኢዚሩሳሌም ወዳሉት አይሁዳውያን በመሄድ አስገድደው ሥራውን አስቆሟ቞ው።
በኢዚሩሳሌም ዹነበሹውን ዹአምላክን ቀት ዚመገንባቱ ሥራ ዹተቋሹጠው በዚህ ጊዜ ነበርፀ እስኚ ፋርሱ ንጉሥ እስኚ ዳርዮስ ዚንግሥና ዘመን ሁለተኛ ዓመት ድሚስም ሥራው ባለበት ቆመ።
በዚያን ጊዜ ንጉሥ ዳርዮስ ትእዛዝ ሰጠፀ እነሱም በባቢሎን ዹሚገኘውን ውድ ነገሮቜ ዚሚቀመጡበትን ግምጃ ቀት መሚመሩ።
በሜዶን አውራጃ፣ በኀክባታና ውስጥ በሚገኘው ዹተመሾገ ስፍራ አንድ ጥቅልል ተገኘፀ በላዩም ላይ ዹሚኹተለው መልእክት ተጜፎ ነበር፩
“ንጉሥ ቂሮስ በነገሠ በመጀመሪያው ዓመት፣ ንጉሥ ቂሮስ በኢዚሩሳሌም ዹሚገኘውን ዹአምላክ ቀት አስመልክቶ ዹሚኹተለውን ትእዛዝ ሰጠ፩ ‘መሥዋዕቶቜን በዚያ ማቅሚብ እንዲቜሉ ቀቱ ተመልሶ ይገንባፀ መሠሚቶቹም ይጣሉፀ ቁመቱ 60 ክንድ፣ ወርዱ 60 ክንድ ሆኖ
ትላልቅ ድንጋዮቜን በሊስት ዙር በመደራሚብና በላዩ ላይ አንድ ዙር ሳንቃ በማድሚግ ይሠራፀ ወጪውም ኚንጉሡ ቀት ይኚፈል።
በተጚማሪም ናቡኚደነጟር በኢዚሩሳሌም ኹነበሹው ቀተ መቅደስ አውጥቶ ወደ ባቢሎን ዚወሰዳ቞ው ዹወርቅና ዚብር ዕቃዎቜ ይመለሱፀ በኢዚሩሳሌም ወዳለው ቀተ መቅደስ ተወስደው በቀድሞ ቊታ቞ው ላይ ይደሚጉፀ በአምላክም ቀት ውስጥ ይቀመጡ።’
“አሁንም ኹወንዙ ባሻገር ያለው ክልል ገዢ ዹሆንኹው ታተናይ፣ ሞታርቊዘናይና ኹወንዙ ባሻገር ዹሚገኙ ዚበታቜ ገዢዎቜ ዚሆኑት ግብሚ አበሮቻቜሁ ኚዚያ ራቁ።
በአምላክ ቀት ሥራ ጣልቃ አትግቡ። ዚአይሁዳውያን ገዢዎቜና ዚአይሁዳውያን ሜማግሌዎቜ ያንን ዹአምላክ ቀት በቀድሞ ቊታው ላይ መልሰው ይገንቡት።
በተጚማሪም እነዚህ ዚአይሁዳውያን ሜማግሌዎቜ ያን ዹአምላክ ቀት መልሰው ሲገነቡ ልታደርጉላ቞ው ዚሚገባውን ነገር በተመለኹተ ይህን ትእዛዝ ሰጥቻለሁፊ ሥራው እንዳይስተጓጎል ኚንጉሡ ግምጃ ቀት ይኾውም ኹወንዙ ባሻገር ካለው ክልል ኹተሰበሰበው ቀሚጥ ላይ ተወስዶ ዚእነዚህ ሰዎቜ ወጪ በአፋጣኝ ይሞፈንላ቞ው።
ለሰማይ አምላክ ለሚቀርቡት ዹሚቃጠሉ መባዎቜ ዚሚያስፈልጉት ነገሮቜ ሁሉ ይኾውም ወይፈኖቜ፣ አውራ በጎቜ፣ ዹበግ ጠቊቶቜ፣ ስንዎ፣ ጚው፣ ዹወይን ጠጅና ዘይት በኢዚሩሳሌም ዚሚገኙት ካህናት በሚጠይቁት መሠሚት በዹቀኑ ያለማቋሚጥ ይሰጣ቞ውፀ
ይህም ዹሚደሹገው ዹሰማይ አምላክን ደስ ዚሚያሰኙ መባዎቜን ዘወትር እንዲያቀርቡ እንዲሁም ለንጉሡና ለልጆቹ ደህንነት እንዲጞልዩ ነው።
ኹዚህ በተጚማሪ ይህን አዋጅ ዚጣሰ ማንኛውም ሰው ለዚህ ጥፋቱ ኚቀቱ ምሰሶ እንዲነቀልና ወደ ላይ ኹፍ ተደርጎ ላዩ ላይ እንዲ቞ነኚር እንዲሁም ቀቱ ዚሕዝብ መጞዳጃ ቀት እንዲሆን አዝዣለሁ።
ስሙ በዚያ እንዲኖር ያደሚገው አምላክ ይህን ትእዛዝ ለመቃወምና በኢዚሩሳሌም ዹሚገኘውን ያንን ዹአምላክ ቀት ለማጥፋት እጁን ዚሚያነሳን ማንኛውንም ንጉሥም ሆነ ሕዝብ ያጥፋው። እኔ ዳርዮስ ይህን ትእዛዝ ሰጥቻለሁ። ይህም በአስ቞ኳይ ተግባራዊ ይደሚግ።”
ኚዚያም ኹወንዙ ባሻገር ያለው ክልል ገዢ ዹሆነው ታተናይ፣ ሞታርቊዘናይና ግብሚ አበሮቻ቞ው ንጉሥ ዳርዮስ ያዘዘውን ነገር ሁሉ ወዲያውኑ ተግባራዊ አደሚጉ።
ዚአይሁዳውያን ሜማግሌዎቜም ነቢዩ ሐጌና ዚኢዶ ዹልጅ ልጅ ዘካርያስ በተናገሩት ትንቢት ተበሚታተው ግንባታውን ማኹናወናቾውንና ሥራውን ማፋጠናቾውን ቀጠሉፀ በእስራኀል አምላክ ትእዛዝ መሠሚት እንዲሁም በቂሮስ፣ በዳርዮስና በፋርሱ ንጉሥ በአርጀክስስ ትእዛዝ መሠሚት ቀቱን ገንብተው አጠናቀቁ።
ቀቱንም በአዳር ወር በሊስተኛው ቀን ይኾውም ንጉሥ ዳርዮስ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት ሠርተው አጠናቀቁ።
ኚዚያም እስራኀላውያን፣ ካህናቱ፣ ሌዋውያኑና በግዞት ተወስደው ዚነበሩት ዚቀሩት ሰዎቜ ዹአምላክን ቀት ምርቃት በደስታ አኚበሩ።
ለአምላክ ቀት ምርቃትም 100 በሬዎቜን፣ 200 አውራ በጎቜንና 400 ዹበግ ጠቊቶቜን እንዲሁም ለመላው እስራኀል ዚኃጢአት መባ እንዲሆኑ በእስራኀል ነገዶቜ ቁጥር ልክ 12 አውራ ፍዚሎቜን አቀሚቡ።
እንዲሁም በሙሮ መጜሐፍ ውስጥ በተጻፈው መሠሚት በኢዚሩሳሌም ለሚቀርበው ዹአምላክ አገልግሎት ካህናቱን በዚክፍላ቞ው፣ ሌዋውያኑንም በዚምድባ቞ው ሟሙ።
በግዞት ተወስደው ዚነበሩት ሰዎቜ በመጀመሪያው ወር በ14ኛው ቀን ላይ ፋሲካን አኚበሩ።
ካህናቱና ሌዋውያኑ በሙሉ ራሳ቞ውን ስላነጹ ሁሉም ንጹሕ ሆነው ነበርፀ እነሱም በግዞት ተወስደው ለነበሩት ሰዎቜ በሙሉ፣ አብሚዋ቞ው ለሚያገለግሉት ካህናትና ለራሳ቞ው ዚፋሲካውን እርድ አሚዱ።
ኚዚያም ኚግዞት ዚተመለሱት እስራኀላውያን በምድሪቱ ኚነበሩት ብሔራት ርኩሰት ራሳ቞ውን በመለዚት ዚእስራኀልን አምላክ ይሖዋን ለማምለክ ኚእነሱ ጋር ኚተቀላቀሉት ሁሉ ጋር ሆነው በሉት።
በተጚማሪም ይሖዋ እንዲደሰቱ ስላደሚጋ቞ውና ዚእስራኀል አምላክ ዹሆነውን ዚእውነተኛውን አምላክ ቀት ይሠሩ ዘንድ እንዲሚዳ቞ው ዹአሩርን ንጉሥ ልብ ስላራራላ቞ው ዚቂጣን በዓል ለሰባት ቀን በደስታ አኚበሩ።
በንጉሥ አርጀክስስ ዚግዛት ዘመን ኚባቢሎን አብሚውኝ ዚወጡት ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ ዹዘር ሐሹግ ዝርዝር ይህ ነው፩
ኚፊንሃስ ልጆቜ ጌርሳም፣ ኚኢታምር ልጆቜ ዳንኀል፣ ኚዳዊት ልጆቜ ሃጡሜ፣
ኚሞካንያህ ልጆቜ፣ ኚፓሮሜ ልጆቜ ዘካርያስ እንዲሁም ኚእሱ ጋር ዚተመዘገቡ 150 ወንዶቜ ነበሩፀ
ኚፓሃትሞአብ ልጆቜ ዚዘራህያህ ልጅ ዹሆነው ኀሊዚሆዔናይ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 200 ወንዶቜ፣
ኚዛቱ ልጆቜ ዚያሃዚኀል ልጅ ዹሆነው ሞካንያህ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 300 ወንዶቜ፣
ኚአዲን ልጆቜ ዚዮናታን ልጅ ዹሆነው ኀቀድ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 50 ወንዶቜ፣
ኚኀላም ልጆቜ ዚጎቶልያ ልጅ ዹሆነው ዚሻያህ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 70 ወንዶቜ፣
ኚሰፋጥያህ ልጆቜ ዚሚካኀል ልጅ ዹሆነው ዘባድያህ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 80 ወንዶቜ፣
ኚኢዮዓብ ልጆቜ ዚዚሂኀል ልጅ ዹሆነው አብድዩ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 218 ወንዶቜ፣
ኚባኒ ልጆቜ ዚዮሲፍያህ ልጅ ዹሆነው ሞሎሚት እንዲሁም ኚእሱ ጋር 160 ወንዶቜ፣
ኚቀባይ ልጆቜ ዚቀባይ ልጅ ዹሆነው ዘካርያስ እንዲሁም ኚእሱ ጋር 28 ወንዶቜ፣
ኚአዝጋድ ልጆቜ ዚሃቃጣን ልጅ ዹሆነው ዮሃናን እንዲሁም ኚእሱ ጋር 110 ወንዶቜ፣
ኚአዶኒቃም ልጆቜ ዚመጚሚሻዎቹ ዚሆኑት ስማ቞ው ኀሊፌሌት፣ ዚኢዔልና ሞማያህ ሲሆን ኚእነሱም ጋር 60 ወንዶቜፀ
ኚቢግዋይ ልጆቜ ዑታይና ዛቡድ እንዲሁም ኚእነሱ ጋር 70 ወንዶቜ።
እኔም ወደ አሃዋ በሚፈሰው ወንዝ አጠገብ ሰበሰብኳ቞ውፀ በዚያም ለሊስት ቀን ሰፈርን። ሆኖም ሕዝቡንና ካህናቱን ልብ ብዬ ስመለኚት ኚሌዋውያን መካኚል ማንንም በዚያ አላገኘሁም።
በመሆኑም መሪዎቜ ለሆኑት ለኀሊዔዘር፣ ለአርዔል፣ ለሞማያህ፣ ለኀልናታን፣ ለያሪብ፣ ለኀልናታን፣ ለናታን፣ ለዘካርያስና ለመሹላም እንዲሁም ለአስተማሪዎቹ ለዮያሪብና ለኀልናታን መልእክት ላክሁባ቞ው።
ኚዚያም ካሲፍያ በተባለው ቊታ መሪ ወደሆነው ወደ ኢዶ እንዲሄዱ አዘዝኳ቞ው። ኢዶንና በካሲፍያ ዚቀተ መቅደስ አገልጋዮቜ ዚሆኑትን ወንድሞቹን በአምላካቜን ቀት ዚሚያገለግሉ ሰዎቜን ያመጡልን ዘንድ እንዲጠይቋ቞ው ነገርኳ቞ው።
መልካም ዹሆነው ዚአምላካቜን እጅ በእኛ ላይ ስለነበር ዚእስራኀል ልጅ ዹሌዊ ዹልጅ ልጅ ኹሆነው ኹማህሊ ልጆቜ መካኚል አስተዋይ ዹሆነውን ሞሚበያህን፣ ወንዶቜ ልጆቹንና ወንድሞቹን በአጠቃላይ 18 ሰዎቜን አመጡልንፀ
እንዲሁም ሃሻብያህንና ኚእሱም ጋር ኚሜራራውያን መካኚል ዚሻያህን፣ ወንድሞቹንና ወንዶቜ ልጆቻ቞ውን በአጠቃላይ 20 ሰዎቜን አመጡልን።
በተጚማሪም ኚቀተ መቅደሱ አገልጋዮቜ መካኚል ዳዊትና መኳንንቱ ሌዋውያኑ ለሚያቀርቡት አገልግሎት ዹሰጧቾው 220 ሰዎቜ ነበሩፀ ሁሉም በዚስማ቞ው ተመዝግበው ነበር።
ኚዚያም ራሳቜንን በአምላካቜን ፊት ለማዋሚድ እንዲሁም በጉዟቜን ወቅት ለእኛም ሆነ ለልጆቻቜንና ለንብሚቶቻቜን በሙሉ ዹሚሆን መመሪያ ኚእሱ ለማግኘት እዚያው በአሃዋ ወንዝ ጟም አወጅኩ።
“መልካም ዹሆነው ዚአምላካቜን እጅ እሱን በሚሹት ሁሉ ላይ ነውፀ እሱን በሚተዉት ሁሉ ላይ ግን ኃይሉንና ቁጣውን ይገልጣል” በማለት ለንጉሡ ነግሹነው ስለነበር በጉዟቜን ላይ ኚሚያጋጥሙን ጠላቶቜ ዚሚጠብቁን ወታደሮቜና ፈሚሰኞቜ እንዲሰጠን ንጉሡን መጠዹቅ አፈርኩ።
ስለሆነም ጟምንፀ ይህን በተመለኹተም ለአምላካቜን ልመና አቀሚብንፀ እሱም ልመናቜንን ሰማ።
እኔም ኚዋነኞቹ ካህናት መካኚል 12ቱን ይኾውም ሞሚበያህንና ሃሻብያህን እንዲሁም አሥር ወንድሞቻ቞ውን ለዚሁ።
ኚዚያም ንጉሡ፣ አማካሪዎቹና መኳንንቱ እንዲሁም በዚያ ዚተገኙት እስራኀላውያን በሙሉ ለአምላካቜን ቀት ዚሰጡትን መዋጮ ማለትም ብሩን፣ ወርቁንና ዕቃዎቹን መዘንኩላ቞ው።
ዚሚኚተሉትንም ዕቃዎቜ መዝኜ ሰጠኋቾው፩ 650 ታላንት ብር፣ 2 ታላንት ዹሚመዝኑ 100 ዚብር ዕቃዎቜ፣ 100 ታላንት ወርቅ
እንዲሁም 1,000 ዳሪክ ዹሚመዝኑ 20 ትናንሜ ጎድጓዳ ዹወርቅ ሳህኖቜና ዹወርቅ ያህል ተፈላጊ ዹሆኑ ኚሚያብሚቀርቅ ጥሩ መዳብ ዚተሠሩ 2 ዕቃዎቜ።
ኚዚያም እንዲህ አልኳ቞ውፊ “እናንተ ለይሖዋ ዚተቀደሳቜሁ ናቜሁፀ ዕቃዎቹም ዚተቀደሱ ና቞ውፀ ብሩና ወርቁ ለአባቶቻቜሁ አምላክ ለይሖዋ ዹቀሹበ ዚፈቃደኝነት መባ ነው።
በኢዚሩሳሌም በሚገኙት በይሖዋ ቀት ክፍሎቜ ውስጥ በዋነኞቹ ካህናትና ሌዋውያን እንዲሁም በእስራኀል ዚአባቶቜ ቀት መኳንንት ፊት እስክትመዝኗ቞ው ድሚስ በጥንቃቄ ጠብቋ቞ው።”
ካህናቱና ሌዋውያኑም ዹተመዘነላቾውን ብር፣ ወርቅና ዕቃ በኢዚሩሳሌም ወደሚገኘው ወደ አምላካቜን ቀት ለመውሰድ ተሚኚቡ።
በኋላም በመጀመሪያው ወር ኚወሩም በ12ኛው ቀን ወደ ኢዚሩሳሌም ለመሄድ ኹአሃዋ ወንዝ ተነሳንፀ ዚአምላካቜንም እጅ በላያቜን ነበርፀ እሱም በመንገድ ላይ ኚጠላት እጅና ኚሜምቅ ጥቃት ታደገን።
ወደ ኢዚሩሳሌም መጥተን በዚያ ለሊስት ቀን ተቀመጥን።
በአራተኛውም ቀን ብሩን፣ ወርቁንና ዕቃዎቹን በአምላካቜን ቀት መዝነን ለዑሪያህ ልጅ ለካህኑ ለመሬሞት አስሚኚብነውፀ ኚእሱም ጋር ዚፊንሃስ ልጅ አልዓዛር እንዲሁም ሌዋውያን ዚሆኑት ዚዚሹዋ ልጅ ዮዛባድና ዚቢኑይ ልጅ ኖአድያህ ነበሩ።
እያንዳንዱም ነገር ተቆጥሮ ተመዘነፀ ክብደቱም ሁሉ ተመዘገበ።
በግዞት ተወስደው ዚነበሩት ኚምርኮ ነፃ ዚወጡ ሰዎቜ ለእስራኀል አምላክ ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜን አቀሚቡፀ ለመላው እስራኀል 12 በሬዎቜን፣ 96 አውራ በጎቜን፣ 77 ተባዕት ዹበግ ጠቊቶቜንና 12 ተባዕት ፍዚሎቜን ዚኃጢአት መባ አድርገው አቀሚቡፀ ይህ ሁሉ ለይሖዋ ዹቀሹበ ዹሚቃጠል መባ ነበር።
ኚዚያም ንጉሡ ያወጣ቞ውን ድንጋጌዎቜ ለንጉሡ ዚአውራጃ ገዢዎቜና ኹወንዙ ባሻገር ባለው ክልል ለሚገኙት ገዢዎቜ ሰጠና቞ውፀ እነሱም ለሕዝቡና ለእውነተኛው አምላክ ቀት ድጋፍ ሰጡ።
በዚህ ጊዜ ዚሕዝቡ መኳንንት ዚሚኖሩት በኢዚሩሳሌም ነበርፀ ዚቀሩት ሰዎቜ ግን ኚአሥር ሰው አንዱ በቅድስቲቱ ኹተማ በኢዚሩሳሌም እንዲኖርና ዚቀሩት ዘጠኙ ደግሞ በሌሎቜ ኚተሞቜ እንዲኖሩ ዕጣ ጣሉ።
በተጚማሪም ሕዝቡ በኢዚሩሳሌም ለመኖር ፈቃደኛ ዚሆኑትን ሰዎቜ በሙሉ ባሚኳ቞ው።
በኢዚሩሳሌም ይኖሩ ዚነበሩት ዚአውራጃው መሪዎቜ እነዚህ ና቞ው። (ዚቀሩት እስራኀላውያን፣ ካህናቱ፣ ሌዋውያኑ፣ ዚቀተ መቅደስ አገልጋዮቹና ዹሰለሞን አገልጋዮቜ ወንዶቜ ልጆቜ በሌሎቹ ዚይሁዳ ኚተሞቜ ማለትም እያንዳንዳ቞ው በዚኚተሞቻ቞ው ባለው በዚራሳ቞ው ርስት ይኖሩ ነበር።
በተጚማሪም ኚይሁዳና ኚቢንያም ሰዎቜ መካኚል ዚተወሰኑት በኢዚሩሳሌም ይኖሩ ነበር።) ኚይሁዳ ሰዎቜ መካኚል ኚፋሬስ ቀተሰብ ዹሆነው ዚመላልኀል ልጅ፣ ዚሰፋጥያህ ልጅ፣ ዚአማርያህ ልጅ፣ ዚዘካርያስ ልጅ፣ ዚዖዝያ ልጅ አታያህ
እንዲሁም ኚሎሎማውያን ቀተሰብ ዹሆነው ዚዘካርያስ ልጅ፣ ዚዮያሪብ ልጅ፣ ዚአዳያህ ልጅ፣ ዚሃዛያህ ልጅ፣ ዚኮልሆዜ ልጅ፣ ዚባሮክ ልጅ ማአሎያህ ነበሩ።
በኢዚሩሳሌም ይኖሩ ዚነበሩት ዚፋሬስ ወንዶቜ ልጆቜ በአጠቃላይ 468 ብቃት ያላ቞ው ወንዶቜ ነበሩ።
ዚቢንያም ሰዎቜ ዚሚኚተሉት ነበሩፊ ዚዚሻያህ ልጅ፣ ዚኢቲኀል ልጅ፣ ዚማአሎያህ ልጅ፣ ዚቆላያህ ልጅ፣ ዚፐዳያህ ልጅ፣ ዚዮኀድ ልጅ፣ ዚመሹላም ልጅ ሳሉ፣
ኚእሱ ቀጥሎ ደግሞ ጋባይ እና ሳላይ ሲሆኑ በአጠቃላይ 928 ነበሩፀ
ዚዚክሪ ልጅ ኢዩኀል ዚእነሱ ዹበላይ ተመልካቜ ነበርፀ ዚሃስኑአ ልጅ ይሁዳ ደግሞ በኹተማዋ ላይ ሁለተኛ አዛዥ ነበር።
ኚካህናቱ መካኚል ደግሞ ዚሚኚተሉት ነበሩፊ ዚዮያሪብ ልጅ ዚዳያህ፣ ያኪን፣
ዚእውነተኛው አምላክ ቀት መሪ ዹሆነው ዚአኪጡብ ልጅ፣ ዚመራዮት ልጅ፣ ዚሳዶቅ ልጅ፣ ዚመሹላም ልጅ፣ ዚኬልቅያስ ልጅ ሰራያህፀ
እንዲሁም ዚቀቱን ሥራ ዚሠሩት ወንድሞቻ቞ው 822ፀ ዚማልኪያህ ልጅ፣ ዚጳስኮር ልጅ፣ ዚዘካርያስ ልጅ፣ ዚአማሲ ልጅ፣ ዚፐላልያህ ልጅ፣ ዚዚሮሃም ልጅ አዳያህ፣
ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ ዚሆኑት ወንድሞቹ 242ፀ እንዲሁም ዚኢሜር ልጅ፣ ዚመሺሌሞት ልጅ፣ ዹአህዛይ ልጅ፣ ዹአዛርዔል ልጅ አማሜሳይ
እንዲሁም ኃያላንና ጀግኖቜ ዚሆኑት ወንድሞቻ቞ው 128ፀ ዚእነሱ ዹበላይ ተመልካቜ ዚአንድ ታዋቂ ቀተሰብ አባል ዹሆነው ዛብድኀል ነበር።
ኚሌዋውያኑ መካኚል ደግሞ ዚሚኚተሉት ነበሩፊ ዚቡኒ ልጅ፣ ዚሃሻብያህ ልጅ፣ ዚአዝሪቃም ልጅ፣ ዚሃሹብ ልጅ ሞማያህ፣
ኚእውነተኛው አምላክ ቀት ጋር በተያያዘ በውጭ ያሉትን ጉዳዮቜ በበላይነት ኚሚኚታተሉት ዚሌዋውያን መሪዎቜ መካኚል ሻበታይ እና ዮዛባድፀ