text stringlengths 4 267 |
|---|
የውዳሴ መዝሙሩንና በጸሎት ጊዜ የሚቀርበውን ውዳሴ የሚመራው የአሳፍ ልጅ፣ የዛብዲ ልጅ፣ የሚክያስ ልጅ ማታንያህ፣ ከወንድሞቹ ሁለተኛ የሆነው ባቅቡቅያ እንዲሁም የየዱቱን ልጅ፣ የጋላል ልጅ፣ የሻሙአ ልጅ አብዳ። |
በቅድስቲቱ ከተማ የነበሩት ሌዋውያን በአጠቃላይ 284 ነበሩ። |
በር ጠባቂዎቹ አቁብ፣ ታልሞን እና በየበሮቹ ላይ የሚጠብቁት ወንድሞቻቸው ደግሞ 172 ነበሩ። |
ከእስራኤላውያን፣ ከካህናቱና ከሌዋውያኑ የቀሩት ደግሞ በሌሎቹ የይሁዳ ከተሞች ሁሉ እያንዳንዳቸው በውርስ ባገኙት ርስት ላይ ይኖሩ ነበር። |
የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች በኦፌል ይኖሩ የነበረ ሲሆን ጺሃ እና ጊሽፓ የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች ኃላፊዎች ነበሩ። |
በኢየሩሳሌም የነበሩት ሌዋውያን የበላይ ተመልካች ከዘማሪዎቹ ከአሳፍ ልጆች መካከል የሚካ ልጅ፣ የማታንያህ ልጅ፣ የሃሻብያህ ልጅ፣ የባኒ ልጅ ዑዚ ነበር፤ እሱም በእውነተኛው አምላክ ቤት ሥራ ላይ ኃላፊ ነበር። |
እነሱን በተመለከተ የወጣ ንጉሣዊ ትእዛዝ ነበር፤ ለዘማሪዎቹ በየዕለቱ የሚያስፈልገውን ነገር በማቅረብ ረገድም ቋሚ የሆነ ዝግጅት ነበር። |
የይሁዳ ልጅ ከሆነው ከዛራ ልጆች መካከል የመሺዛቤል ልጅ ፐታያህ ከሕዝቡ ጋር የተያያዘውን ማንኛውንም ጉዳይ በተመለከተ የንጉሡ አማካሪ ነበር። |
የሰፈራ መንደሮቹ ከነእርሻ ቦታዎቻቸው የሚከተሉት ናቸው፦ ከይሁዳ ወንዶች ልጆች መካከል የተወሰኑት በቂርያትአርባና በሥሯ ባሉት ከተሞች፣ በዲቦንና በሥሯ ባሉት ከተሞች፣ በየቃብጸኤል እና በሥሯ ባሉት የሰፈራ መንደሮች፣ |
በየሹዋ፣ በሞላዳ፣ በቤትጳሌጥ፣ |
በሃጻርሹአል፣ በቤርሳቤህና በሥሯ ባሉት ከተሞች፣ |
በጺቅላግ፣ በመኮና እና በሥሯ ባሉት ከተሞች፣ |
በኤንሪሞን፣ በጾራ፣ በያርሙት፣ |
በዛኖሃ፣ በአዱላምና በሥሯ ባሉት የሰፈራ መንደሮች፣ በለኪሶና በእርሻ ቦታዎቿ እንዲሁም በአዜቃና በሥሯ ባሉት ከተሞች ይኖሩ ነበር። እነሱም ከቤርሳቤህ እስከ ሂኖም ሸለቆ ባለው አካባቢ ሰፈሩ። |
የቢንያም ሰዎች ደግሞ ከጌባ ጀምሮ በሚክማሽ፣ በጋያ፣ በቤቴል እና በሥሯ ባሉት ከተሞች፣ |
በአናቶት፣ በኖብ፣ በአናንያ፣ |
በሃጾር፣ በራማ፣ በጊታይም፣ |
በሃዲድ፣ በጸቦይም፣ በነባላጥ፣ |
በሎድ እና በኦኖ እንዲሁም በእጅ ጥበብ ባለሙያዎች ሸለቆ ተቀመጡ። |
በይሁዳ ከነበሩት ሌዋውያን መካከል የተወሰኑት ቡድኖች በቢንያም ተመደቡ። |
የሃካልያህ ልጅ የነህምያ ቃል ይህ ነው፦ በ20ኛው ዓመት በኪስሌው ወር በሹሻን ግንብ ነበርኩ። |
በዚህ ጊዜ ከወንድሞቼ አንዱ የሆነው ሃናኒ በይሁዳ ከነበሩ ሌሎች ሰዎች ጋር መጣ፤ እኔም ከምርኮ ስለተረፉት አይሁዳውያን ቀሪዎችና ስለ ኢየሩሳሌም ጠየቅኳቸው። |
እነሱም እንዲህ አሉኝ፦ “ከምርኮ ተመልሰው በአውራጃው ውስጥ የሚገኙት ቀሪዎች በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ፤ መሳለቂያም ሆነዋል። የኢየሩሳሌም ቅጥሮች ፈራርሰዋል፤ በሮቿም በእሳት ተቃጥለዋል።” |
እኔም ይህን ስሰማ ቁጭ ብዬ ማልቀስ ጀመርኩ፤ ለቀናትም በሰማይ አምላክ ፊት ሳዝን፣ ስጾምና ስጸልይ ቆየሁ። |
ከዚያም እንዲህ አልኩ፦ “የሰማይ አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ለሚወዱህ፣ ትእዛዛትህንም ለሚያከብሩ ቃል ኪዳንህን የምትጠብቅና ታማኝ ፍቅር የምታሳይ ታላቅና የምትፈራ አምላክ ነህ፤ |
እባክህ ዛሬ ወደ አንተ የማቀርበውን የአገልጋይህን ጸሎት ለመስማት ጆሮህ ወደ እኔ ያዘንብል፤ ዓይኖችህም ይከፈቱ፤ እኛ እስራኤላውያን በአንተ ላይ የፈጸምነውን ኃጢአት እየተናዘዝኩ ስለ አገልጋዮችህ ስለ እስራኤላውያን ቀን ከሌት እየጸለይኩ ነው። እኔም ሆንኩ የአባቴ ቤት ኃጢአት ሠርተናል። |
ለአገልጋይህ ለሙሴ የሰጠሃቸውን ትእዛዛት፣ ሥርዓቶችና ድንጋጌዎች ባለማክበር በአንተ ላይ መጥፎ ድርጊት እንደፈጸምን ምንም ጥርጥር የለውም። |
“እባክህ አገልጋይህን ሙሴን እንዲህ በማለት ያዘዝከውን ቃል አስታውስ፦ ‘ታማኝነት የጎደለው ድርጊት የምትፈጽሙ ከሆነ በሕዝቦች መካከል እበትናችኋለሁ። |
ወደ እኔ ተመልሳችሁ ትእዛዛቴን ብትጠብቁና ብትፈጽሙ ግን ሕዝቦቻችሁ እስከ ሰማይ ዳርቻ ድረስ ቢበተኑ እንኳ ከዚያ እሰበስባቸዋለሁ፤ እንዲሁም ስሜ እንዲኖርበት ወደመረጥኩት ስፍራ አመጣቸዋለሁ።’ |
እነሱ በታላቅ ኃይልህና በብርቱ እጅህ የዋጀሃቸው አገልጋዮችህና ሕዝቦችህ ናቸው። |
ይሖዋ ሆይ፣ እባክህ የአገልጋይህን ጸሎትና ስምህን በመፍራት ደስ የሚሰኙ አገልጋዮችህን ጸሎት ለመስማት ጆሮህን አዘንብል፤ እባክህ ዛሬ አገልጋይህ እንዲሳካለት አድርግ፤ ይህም ሰው ይራራልኝ።” እኔም የንጉሡ መጠጥ አሳላፊ ነበርኩ። |
እኔም ቅጥሩ እንደገና ተገንብቶ እንዳለቀ መዝጊያዎቹን ገጠምኩ፤ ከዚያም በር ጠባቂዎቹ፣ ዘማሪዎቹና ሌዋውያኑ ተሾሙ። |
በኋላም ወንድሜን ሃናኒን፣ የምሽጉ አለቃ ከሆነው ከሃናንያህ ጋር በኢየሩሳሌም ላይ ሾምኩት፤ ምክንያቱም ሃናንያህ እምነት የሚጣልበትና ከሌሎቹ ሁሉ ይበልጥ እውነተኛውን አምላክ የሚፈራ ሰው ነበር። |
እንዲህም አልኳቸው፦ “የኢየሩሳሌም በሮች ፀሐይ ሞቅ እስከሚል ድረስ መከፈት የለባቸውም፤ ጠባቂዎቹ በጥበቃ ሥራቸው ላይ እያሉ በሮቹን መዝጋትና መቀርቀር ይኖርባቸዋል። እንዲሁም የኢየሩሳሌምን ነዋሪዎች ጠባቂዎች አድርጋችሁ መድቡ፤ የተወሰኑት ሰዎች በተመደቡበት የጥበቃ ቦታ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከቤታቸው ፊት ለፊት ይጠብቁ።” |
ከተማዋ ሰፊና ትልቅ ነበረች፤ በውስጧ የነበሩት ሰዎች ጥቂት ሲሆኑ ቤቶቹም እንደገና አልተገነቡም ነበር። |
ሆኖም አምላኬ የተከበሩትን ሰዎች፣ የበታች ገዢዎቹንና ሕዝቡን በአንድነት እንድሰበስብና በየዘር ሐረጋቸው እንዲመዘገቡ እንዳደርግ ይህን ሐሳብ በልቤ ውስጥ አኖረ። ከዚያም መጀመሪያ ላይ የመጡትን ሰዎች የዘር ሐረግ ዝርዝር የያዘ መጽሐፍ አገኘሁ፤ በውስጡም ተጽፎ ያገኘሁት ይህ ነው፦ |
የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር በግዞት ወስዷቸው የነበሩትና ከምርኮ ነፃ ወጥተው፣ በኋላ ላይ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ይኸውም ወደየከተሞቻቸው የተመለሱት የአውራጃው ነዋሪዎች እነዚህ ናቸው፤ |
ከዘሩባቤል፣ ከየሆሹዋ፣ ከነህምያ፣ ከአዛርያስ፣ ከራሚያህ፣ ከናሃማኒ፣ ከመርዶክዮስ፣ ከቢልሻን፣ ከሚስጴሬት፣ ከቢግዋይ፣ ከነሁም እና ከባአናህ ጋር የመጡት እነዚህ ናቸው። የእስራኤላውያን ወንዶች ቁጥር የሚከተሉትን ይጨምራል፦ |
የፓሮሽ ወንዶች ልጆች 2,172፣ |
የሰፋጥያህ ወንዶች ልጆች 372፣ |
የኤራ ወንዶች ልጆች 652፣ |
የየሹዋና የኢዮዓብ ወንዶች ልጆች የሆኑት የፓሃትሞአብ ወንዶች ልጆች 2,818፣ |
የኤላም ወንዶች ልጆች 1,254፣ |
የዛቱ ወንዶች ልጆች 845፣ |
የዛካይ ወንዶች ልጆች 760፣ |
የቢኑይ ወንዶች ልጆች 648፣ |
የቤባይ ወንዶች ልጆች 628፣ |
የአዝጋድ ወንዶች ልጆች 2,322፣ |
የአዶኒቃም ወንዶች ልጆች 667፣ |
የቢግዋይ ወንዶች ልጆች 2,067፣ |
የአዲን ወንዶች ልጆች 655፣ |
የሕዝቅያስ ልጅ የአጤር ወንዶች ልጆች 98፣ |
የሃሹም ወንዶች ልጆች 328፣ |
የቤጻይ ወንዶች ልጆች 324፣ |
የሃሪፍ ወንዶች ልጆች 112፣ |
የገባኦን ወንዶች ልጆች 95፣ |
የቤተልሔምና የነጦፋ ሰዎች 188፣ |
የአናቶት ሰዎች 128፣ |
የቤትአዝማዌት ሰዎች 42፣ |
የቂርያትየአሪም፣ የከፊራና የበኤሮት ሰዎች 743፣ |
የራማና የጌባ ሰዎች 621፣ |
የሚክማስ ሰዎች 122፣ |
የቤቴልና የጋይ ሰዎች 123፣ |
የሌላኛው ነቦ ሰዎች 52፣ |
የሌላኛው ኤላም ወንዶች ልጆች 1,254፣ |
የሃሪም ወንዶች ልጆች 320፣ |
የኢያሪኮ ወንዶች ልጆች 345፣ |
የሎድ፣ የሃዲድና የኦኖ ወንዶች ልጆች 721፣ |
የሰናአ ወንዶች ልጆች 3,930። |
ካህናቱ የሚከተሉት ናቸው፦ ከየሹዋ ወገን የሆነው የየዳያህ ወንዶች ልጆች 973፣ |
የኢሜር ወንዶች ልጆች 1,052፣ |
የጳስኮር ወንዶች ልጆች 1,247፣ |
የሃሪም ወንዶች ልጆች 1,017። |
ሌዋውያኑ የሚከተሉት ናቸው፦ የሆዳውያህ ወንዶች ልጆች የሆኑት የየሹዋና የቃድሚኤል ወንዶች ልጆች 74። |
ዘማሪዎቹ የአሳፍ ወንዶች ልጆች 148። |
በር ጠባቂዎቹ የሻሉም ወንዶች ልጆች፣ የአጤር ወንዶች ልጆች፣ የታልሞን ወንዶች ልጆች፣ የአቁብ ወንዶች ልጆች፣ የሃጢጣ ወንዶች ልጆችና የሾባይ ወንዶች ልጆች 138። |
የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች የሚከተሉት ናቸው፦ የጺሃ ወንዶች ልጆች፣ የሃሱፋ ወንዶች ልጆች፣ የታባኦት ወንዶች ልጆች፣ |
የቀሮስ ወንዶች ልጆች፣ የሲአ ወንዶች ልጆች፣ የፓዶን ወንዶች ልጆች፣ |
የለባና ወንዶች ልጆች፣ የሃጋባ ወንዶች ልጆች፣ የሳልማይ ወንዶች ልጆች፣ |
የሃናን ወንዶች ልጆች፣ የጊዴል ወንዶች ልጆች፣ የጋሃር ወንዶች ልጆች፣ |
የረአያህ ወንዶች ልጆች፣ የረጺን ወንዶች ልጆች፣ የነቆዳ ወንዶች ልጆች፣ |
የጋዛም ወንዶች ልጆች፣ የዑዛ ወንዶች ልጆች፣ የፓሰአህ ወንዶች ልጆች፣ |
የቤሳይ ወንዶች ልጆች፣ የመኡኒም ወንዶች ልጆች፣ የነፉሸሲም ወንዶች ልጆች፣ |
የባቅቡቅ ወንዶች ልጆች፣ የሃቁፋ ወንዶች ልጆች፣ የሃርሑር ወንዶች ልጆች፣ |
የባጽሊት ወንዶች ልጆች፣ የመሂዳ ወንዶች ልጆች፣ የሃርሻ ወንዶች ልጆች፣ |
የባርቆስ ወንዶች ልጆች፣ የሲሳራ ወንዶች ልጆች፣ የተማ ወንዶች ልጆች፣ |
የነጺሃ ወንዶች ልጆችና የሃጢፋ ወንዶች ልጆች። |
የሰለሞን አገልጋዮች ወንዶች ልጆች የሚከተሉት ናቸው፦ የሶጣይ ወንዶች ልጆች፣ የሶፈረት ወንዶች ልጆች፣ የፐሪዳ ወንዶች ልጆች፣ |
የያአላ ወንዶች ልጆች፣ የዳርቆን ወንዶች ልጆች፣ የጊዴል ወንዶች ልጆች፣ |
የሰፋጥያህ ወንዶች ልጆች፣ የሃጢል ወንዶች ልጆች፣ የፖክሄሬትሃጸባይም ወንዶች ልጆችና የአምዖን ወንዶች ልጆች። |
የቤተ መቅደሱ አገልጋዮችና የሰለሞን አገልጋዮች ወንዶች ልጆች በአጠቃላይ 392 ነበሩ። |
ከቴልመላ፣ ከቴልሃርሻ፣ ከከሩብ፣ ከአዳንና ከኢሜር የወጡት ሆኖም ከየትኛው የአባቶች ቤትና የዘር ሐረግ እንደመጡ በውል መለየትም ሆነ እስራኤላዊ መሆን አለመሆናቸውን በትክክል ማረጋገጥ ያልቻሉት የሚከተሉት ናቸው፦ |
የደላያህ ወንዶች ልጆች፣ የጦብያ ወንዶች ልጆችና የነቆዳ ወንዶች ልጆች 642። |
ከካህናቱም መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦ የሃባያ ወንዶች ልጆች፣ የሃቆጽ ወንዶች ልጆች እንዲሁም ከጊልያዳዊው ከቤርዜሊ ሴቶች ልጆች መካከል አንዷን ያገባውና በስማቸው የተጠራው የቤርዜሊ ወንዶች ልጆች። |
እነዚህ የዘር ሐረጋቸውን ለማረጋገጥ በመዝገቡ ላይ የቤተሰባቸውን ስም ለማግኘት ቢጥሩም ሊገኙ አልቻሉም፤ በመሆኑም ከክህነት አገልግሎቱ ታገዱ። |
ገዢውም በኡሪምና በቱሚም አማካኝነት ምክር የሚጠይቅ ካህን እስኪገኝ ድረስ እጅግ ቅዱስ ከሆኑት ነገሮች መብላት እንደማይኖርባቸው ነገራቸው። |
መላው ጉባኤ በአጠቃላይ 42,360 ነበር፤ |
ይህ 7,337 ወንድና ሴት ባሪያዎቻቸውን አይጨምርም፤ በተጨማሪም 245 ወንድና ሴት ዘማሪዎች ነበሯቸው። |
ከዚህም ሌላ 736 ፈረሶች፣ 245 በቅሎዎች |
እንዲሁም 435 ግመሎችና 6,720 አህዮች ነበሯቸው። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.