text stringlengths 4 267 |
|---|
ብረትን እንደ ገለባ፣መዳብንም እንደበሰበሰ እንጨት ይቆጥራል። |
ፍላጻ አያባርረውም፤የወንጭፍ ድንጋይም ለእሱ እንደ ገለባ ነው። |
ቆመጥን እንደ ገለባ ይቆጥረዋል፤ጦር ሲሰበቅም ይስቃል። |
ሆዱ እንደሾሉ የሸክላ ስብርባሪዎች ነው፤እንደ ማሄጃ በጭቃ ላይ ምልክት ትቶ ያልፋል። |
ጥልቁን ውኃ እንደ ድስት ያፈላዋል፤ባሕሩንም እንደ ቅባት መያዣ ይበጠብጠዋል። |
በመንገዱ ላይ የሚያብረቀርቅ ፈለግ እየተወ ያልፋል። ተመልካችም ጥልቁ ውኃ ሽበት ያለው ይመስለዋል። |
በምድር ላይ ያለፍርሃት የተፈጠረ፣እንደ እሱ ያለ ፍጡር የለም። |
ትዕቢተኛ በሆነው ሁሉ ላይ በቁጣ ያፈጣል። ግርማ በተላበሱ የዱር እንስሳት ሁሉ ላይ ንጉሥ ነው።” |
“መንፈሴ ተሰብሯል፤ ዘመኔ አብቅቷል፤መቃብር ይጠብቀኛል። |
ፌዘኞች ከበውኛል፤ዓይኔም የዓመፅ ተግባራቸውን በትኩረት ትመለከታለች። |
እባክህ፣ መያዣዬን ተቀብለህ አንተ ዘንድ አስቀምጥልኝ። እጄን የሚመታና ተያዥ የሚሆነኝ ሌላ ማን ይኖራል? |
ማስተዋልን ከልባቸው ሰውረሃልና፤ከዚህም የተነሳ ከፍ ከፍ አታደርጋቸውም። |
የልጆቹ ዓይን ደክሞ እያለ፣ያለውን ለወዳጆቹ ሊያካፍል ይችላል። |
አምላክ የሰዎች መቀለጃ አደረገኝ፤በመሆኑም ፊቱ ላይ እንደሚተፉበት ሰው ሆንኩ። |
ከሐዘን የተነሳ ዓይኔ ፈዘዘ፤እጆቼና እግሮቼም እንደ ጥላ ሆኑ። |
ቅን የሆኑ ሰዎች በዚህ ነገር በመገረም ትኩር ብለው ይመለከታሉ፤ንጹሕ የሆነውም፣ አምላክ የለሽ በሆነው ሰው ይረበሻል። |
ጻድቅ መንገዱን በጥብቅ ይከተላል፤እጁ ንጹሕ የሆነ ሰውም እየበረታ ይሄዳል። |
ይሁን እንጂ ሁላችሁም ተመልሳችሁ መከራከራችሁን መቀጠል ትችላላችሁ፤ከእናንተ መካከል አንድም ጥበበኛ አላገኘሁምና። |
የሕይወት ዘመኔ አበቃ፤ዕቅዴና የልቤ ምኞት ተንኮታኮተ። |
ሌሊቱን ወደ ቀን ይለውጣሉ፤‘ጨለማ ስለሆነ ብርሃን የሚፈነጥቅበት ጊዜ ቀርቧል’ ይላሉ። |
ዝም ብዬ ብጠብቅ ያን ጊዜ መቃብር፣ ቤቴ ይሆናል፤በጨለማ መኝታዬን እዘረጋለሁ። |
ጉድጓዱን ‘አንተ አባቴ ነህ!’ እለዋለሁ፤ ትሏን ‘አንቺ እናቴና እህቴ ነሽ!’ እላታለሁ። |
እንግዲህ የእኔ ተስፋ የት አለ? ተስፋ እንዳለኝ አድርጎ የሚያስብስ ማን ነው? |
ሁላችንም ተያይዘን ወደ አፈር ስንገባ፣ተስፋዬ ወደተቀረቀሩ የመቃብር በሮች ይወርዳል።” |
“ከዓይኔ ጋር ቃል ኪዳን ገብቻለሁ። ታዲያ ለድንግሊቱ ተገቢ ያልሆነ ትኩረት እንዴት እሰጣለሁ? |
ለመሆኑ ከላይ ከአምላክ የማገኘው ድርሻ ምንድን ነው?ከፍ ባለ ስፍራ ከሚኖረው ሁሉን ቻይ አምላክ የማገኘውስ ውርሻ ምንድን ነው? |
በደለኛ ሰው ጥፋት፣ክፉ ነገር የሚያደርጉስ መቅሰፍት አይደርስባቸውም? |
እሱ መንገዴን ሁሉ አያይም?እርምጃዬንስ ሁሉ አይቆጥርም? |
በውሸት ጎዳና ተመላልሼ አውቃለሁ? እግሬ ለማታለል ተጣድፎ ያውቃል? |
አምላክ በትክክለኛ ሚዛን ይመዝነኝ፤ያን ጊዜ ንጹሕ አቋም እንዳለኝ ይገነዘባል። |
እርምጃዬ ከመንገዱ ወጣ ብሎ፣ወይም ልቤ ዓይኔን ተከትሎ፣አሊያም እጄ ረክሶ ከሆነ፣ |
የዘራሁትን ዘር ሌላ ይብላው፤የተከልኩትም ይነቀል። |
ልቤ ሌላ ሴት ከጅሎ፣በባልንጀራዬም ደጃፍ ላይ አድብቼ ከሆነ፣ |
ሚስቴ ለሌላ ሰው እህል ትፍጭ፤ሌሎች ወንዶችም ከእሷ ጋር ይተኙ። |
ይህ አሳፋሪ ምግባር፣ደግሞም በዳኞች ሊያስቀጣ የሚገባ በደል በሆነ ነበርና። |
ይህ የሚያጠፋና የሚደመስስ፣የፍሬዬንም ሥር ሁሉ የሚፈጅ እሳት በሆነ ነበር። |
ወንድ ባሪያዬ ወይም ሴት ባሪያዬ በእኔ ላይ አቤቱታ ባቀረቡ ጊዜፍትሕ ነፍጌ ከሆነ፣ |
አምላክ ሲከራከረኝ ምን ማድረግ እችላለሁ? ሲጠይቀኝስ ምን መልስ እሰጣለሁ? |
እኔን በማህፀን ውስጥ የሠራኝ እነሱንስ አልሠራም? ከመወለዳችን በፊት የሠራን እሱ ራሱ አይደለም? |
ድሃ የሆኑ ሰዎች የፈለጉትን ነገር ነፍጌ፣ወይም የመበለቲቱ ዓይን እንዲያዝን አድርጌ ከሆነ፣ |
ወላጅ አልባ ለሆኑ ልጆች ሳላካፍል፣የራሴን ምግብ ብቻዬን በልቼ ከሆነ፣ |
(ወላጅ አልባ የሆነውን ልጅ ከወጣትነቴ ጀምሮ እንደ አባት ሆኜ አሳድጌዋለሁና፤ከልጅነቴም አንስቶ መበለቲቱን ስመራት ቆይቻለሁ።) |
ሰው የሚለብሰው አጥቶ በብርድ ሲያልቅ፣ወይም ድሃው ሲታረዝ አይቼ ከሆነ፣ |
ከጠቦቶቼ የተሸለተውን ፀጉር ለብሶ በሞቀው ጊዜ፣ሳይባርከኝ ቀርቶ ከሆነ፣ |
በከተማዋ በር ላይ የእኔን እርዳታ በሚፈልግ ወላጅ አልባ ልጅ ላይእጄን በዛቻ አወዛውዤ ከሆነ፣ |
ክንዴ ከትከሻዬ ይውለቅ፤ክንዴም ከክርኔ ይሰበር። |
ከአምላክ የሚመጣ ጥፋት ያስፈራኛልና፤በግርማውም ፊት መቆም አልችልም። |
ወርቅን መታመኛዬ አድርጌ፣ወይም ምርጥ የሆነውን ወርቅ ‘አንተ መመኪያዬ ነህ!’ ብዬ ከሆነ፣ |
ታላቅ ሀብት በማፍራቴ፣እንዲሁም ብዙ ንብረት በማግኘቴ ደስ ብሎኝ ከሆነ፣ |
ፀሐይ ስትፈነጥቅ፣ወይም ጨረቃ ግርማ ተላብሳ ስትሄድ አይቼ ከሆነ፣ |
ልቤ በስውር ተታሎ፣አፌም ለእነሱ አምልኮ ለማቅረብ እጄን ስሞ ከሆነ፣ |
ይህ በዳኞች ሊያስቀጣ የሚገባ በደል በሆነ ነበር፤በላይ ያለውን እውነተኛውን አምላክ መካድ ይሆንብኝ ነበርና። |
ጠላቴ በደረሰበት ጥፋት ደስ ብሎኝ ያውቃል?ወይስ ክፉ ነገር ስለደረሰበት ሐሴት አድርጌ አውቃለሁ? |
በእርግማን ሕይወቱን በመሻት፣አንደበቴ ኃጢአት እንዲሠራ አልፈቀድኩም። |
በድንኳኔ የሚኖሩ ሰዎች‘እሱ ካቀረበው ምግብ በልቶ ያልጠገበ ሰው ማግኘት የሚችል ማን አለ?’ አላሉም? |
አንድም እንግዳ ደጅ አያድርም ነበር፤ቤቴን ለመንገደኛ እከፍት ነበር። |
በደሌን በልብሴ ኪስ በመሸሸግ፣እንደ ሌሎች ሰዎች ጥፋቴን ለመሸፋፈን ሞክሬ አውቃለሁ? |
የብዙ ሰዎችን ምላሽ በመፍራት፣ወይም በሌሎች ቤተሰቦች ንቀት በመሸበር፣ዝም ብያለሁ? ደግሞስ ወደ ውጭ መውጣት ፈርቻለሁ? |
ምነው የሚሰማኝ ባገኘሁ! በተናገርኩት ነገር ላይ ስሜን አሰፍር ነበር። ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ መልስ ይስጠኝ! ምነው ከሳሼ ክሱን በሰነድ ላይ ባሰፈረ ኖሮ! |
በትከሻዬ እሸከመው ነበር፤እንደ አክሊልም በራሴ ላይ አስረው ነበር። |
የወሰድኩትን እያንዳንዱን እርምጃ ባሳወቅኩት ነበር፤እንደ አለቃ በልበ ሙሉነት ወደ እሱ እቀርብ ነበር። |
እርሻዬ በእኔ ላይ ጮኻ፣ትልሞቿም በአንድ ላይ አልቅሰው ከሆነ፣ |
ፍሬዋን ያለዋጋ በልቼ፣ባለቤቶቿንም አሳዝኜ ከሆነ፣ |
በስንዴ ፋንታ እሾህ፣በገብስም ምትክ የሚገማ አረም ይብቀልብኝ።” የኢዮብ ቃል እዚህ ላይ ተፈጸመ። |
ኢዮብ እንዲህ ሲል መለሰ፦ |
“እናንተ ሰዎች ነፍሴን የምታበሳጯት፣በቃላት የምትደቁሱኝስ እስከ መቼ ነው? |
ይኸው አሥር ጊዜ ገሠጻችሁኝ፤ከባድ በደል ስትፈጽሙብኝ አላፈራችሁም። |
ስህተት ብፈጽምም እንኳ፣የሠራሁት ስህተት ከእኔ ጋር ይኖራል። |
በእኔ ላይ የደረሰው ነቀፋ ተገቢ እንደሆነ አድርጋችሁ በመከራከር፣በእኔ ላይ ራሳችሁን ከፍ ከፍ ብታደርጉ፣ |
ያሳተኝ አምላክ እንደሆነ እወቁ፤በማጥመጃ መረቡም ይዞኛል። |
እነሆ ‘ግፍ ተፈጸመብኝ!’ ብዬ ብጮኽም መልስ አላገኘሁም፤እርዳታ ለማግኘት ብጣራም ፍትሕ የለም። |
መንገዴን በድንጋይ ግንብ ዘጋ፤ እኔም ማለፍ አልቻልኩም፤ጎዳናዬንም በጨለማ ጋረደ። |
ክብሬን ገፎኛል፤አክሊሉንም ከራሴ ላይ አንስቷል። |
እስክጠፋ ድረስ በሁሉም አቅጣጫ አፈራረሰኝ፤ተስፋዬን እንደ ዛፍ ነቀለው። |
ቁጣው በእኔ ላይ ነደደ፤እንደ ጠላቱም ቆጠረኝ። |
ሠራዊቱ በአንድነት መጥተው ከበቡኝ፤በድንኳኔም ዙሪያ ሰፈሩ። |
የገዛ ወንድሞቼን ከእኔ አራቀ፤የሚያውቁኝም ሰዎች ጥለውኝ ሄዱ። |
የቅርብ ወዳጆቼ ትተውኛል፤በደንብ የማውቃቸውም ሰዎች ረሱኝ። |
በቤቴ ያሉ እንግዶችና ሴቶች ባሪያዎቼ እንደ መጤ ቆጠሩኝ፤እንደ ባዕድ አገር ሰው ተመለከቱኝ። |
አገልጋዬን ጠራሁት፤ እሱ ግን አልመለሰልኝም፤እንዲራራልኝ በአንደበቴ ለመንኩት። |
ሚስቴ ትንፋሼን እንኳ ተጸየፈችው፤ለገዛ ወንድሞቼም መጥፎ ጠረን ሆንኩባቸው። |
ትናንሽ ልጆች እንኳ ናቁኝ፤ስነሳ በእኔ ላይ ያላግጣሉ። |
የቅርብ ወዳጆቼ ሁሉ ተጸየፉኝ፤የምወዳቸውም ሰዎች በእኔ ላይ ተነሱ። |
አጥንቶቼ ከቆዳዬና ከሥጋዬ ጋር ተጣበቁ፤ከሞት ለጥቂት ተረፍኩ። |
ወዳጆቼ ሆይ፣ ማሩኝ፤ እባካችሁ ማሩኝ፤የአምላክ እጅ መታኛለችና። |
አምላክ እንዳሳደደኝ የምታሳድዱኝ ለምንድን ነው?ያለፋታ የምታጠቁኝስ ለምንድን ነው? |
ምነው ቃሌ በተጻፈ!ምነው በመጽሐፍ ላይ በሰፈረ! |
ምነው በብረት ብዕርና በእርሳስ፣በዓለቱ ላይ ለዘላለም በተቀረጸ! |
የሚዋጀኝ ሕያው እንደሆነ በሚገባ አውቃለሁና፤ከጊዜ በኋላ መጥቶ በምድር ላይ ይቆማል። |
ቆዳዬ በዚህ መንገድ ቢጠፋም፣ገና በሥጋ እያለሁ አምላክን አየዋለሁ፤ |
እኔ ራሴ እሱን እመለከተዋለሁ፤የሌላ ሰው ዓይን ሳይሆን የገዛ ዓይኖቼ ያዩታል። ይሁንና በውስጤ እንደዛልኩ ይሰማኛል! |
የችግሩ መንስኤ እኔ ጋ እያለ፣ ‘የምናሳድደው እንዴት ነው?’ ትላላችሁና። |
እናንተ ራሳችሁ ሰይፉን ፍሩ፤ሰይፉ በበደል ላይ ቅጣት ያመጣልና፤ፈራጅ መኖሩን ልታውቁ ይገባል።” |
“አሁን ግን ኢዮብ፣ እባክህ ቃሌን ስማ፤የምናገረውንም ሁሉ አዳምጥ። |
እባክህ ልብ በል! አፌን እከፍታለሁ፤አንደበቴም ይናገራል። |
ቃሌ የልቤን ቅንነት ይገልጻል፤ከንፈሮቼም የማውቀውን ነገር በቅንነት ይናገራሉ። |
የአምላክ መንፈስ ሠራኝ፤ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ እስትንፋስም ሕይወት ሰጠኝ። |
የምትችል ከሆነ መልስልኝ፤የመከራከሪያ ሐሳብህን በፊቴ አቅርብ፤ ቦታህንም ያዝ። |
እነሆ፣ በእውነተኛው አምላክ ፊት እኔም እንደ አንተው ነኝ፤እኔም የተሠራሁት ከሸክላ ነው። |
ስለዚህ እኔን ፈርተህ ልትሸበር አይገባም፤የማሳድርብህ ጫናም ሊደቁስህ አይገባም። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.