text
stringlengths
4
267
በቀትህ ውስጥ ተትሚፍርፎ ዹሚገኘውን ነገር እስኪሚኩ ድሚስ ይጠጣሉፀመልካም ነገሮቜ ኚሚፈስሱበት ወንዝህ ታጠጣ቞ዋለህ።
ዚሕይወት ምንጭ ኹአንተ ዘንድ ነውፀበብርሃንህ፣ ብርሃን ማዚት እንቜላለን።
ለሚያውቁህ ታማኝ ፍቅርህን፣ቀና ልብ ላላቾው ደግሞ ጜድቅህን ዘወትር አሳያ቞ው።
ዚትዕቢተኛ እግር እንዲሚግጠኝ፣ወይም ዚክፉዎቜ እጅ እንዲያፈናቅለኝ አትፍቀድ።
ክፉ አድራጊዎቜ ዚት እንደወደቁ ተመልኚትፀተመተው ወድቀዋልፀ መነሳትም አይቜሉም።
ይሖዋን ላወድስ። ይሖዋ አምላኬ ሆይ፣ አንተ እጅግ ታላቅ ነህ። ሞገስንና ግርማን ለብሰሃል።
ብርሃንን እንደ ልብስ ተጎናጜፈሃልፀሰማያትን እንደ ድንኳን መጋሹጃ ዘርግተሃል።
ዚላይኛዎቹን ክፍሎቜ ተሞካሚዎቜ ኹላይ ባሉት ውኃዎቜ ላይ ያኖራልፀደመናትን ሠሹገላው ያደርጋልፀበነፋስ ክንፎቜም ይሄዳል።
መላእክቱን መናፍስት፣አገልጋዮቹን ዚሚባላ እሳት ያደርጋል።
ምድርን በመሠሚቶቿ ላይ መሠሚታትፀእሷም ለዘላለም ኚቊታዋ አትናወጥም።
ጥልቅ ውኃን እንደ ልብስ አለበስካት። ውኃዎቹ ኚተራሮቹ በላይ ቆሙ።
በገሠጜካ቞ው ጊዜ ሞሹፀዚነጎድጓድህን ድምፅ ሲሰሙ በድንጋጀ ፈሚጠጡፀ
ተራሮቜ ወደ ላይ ወጡፀ ሞለቆዎቜም ወደ ታቜ ወሚዱፀሁሉም ወዳዘጋጀህላ቞ው ቊታ ሄዱ።
ውኃዎቹ አልፈው እንዳይሄዱ፣እንደገናም ምድርን እንዳይሞፍኑ ወሰን አበጀህላ቞ው።
ምንጮቜን ወደ ሞለቆዎቜ ይልካልፀበተራሮቜ መካኚል ይፈስሳሉ።
ዚዱር አራዊት ሁሉ ኚዚያ ይጠጣሉፀዚዱር አህዮቜም ጥማ቞ውን ይቆርጣሉ።
ዹሰማይ ወፎቜ ኚእነሱ በላይ ይሰፍራሉፀበለመለሙ ዹዛፍ ቅርንጫፎቜ መካኚል ሆነው ይዘምራሉ።
ኹላይ ካሉት ክፍሎቹ ሆኖ ተራሮቜን ያጠጣል። በሥራህ ፍሬ ምድር ሚካቜ።
ሣርን ለኚብት፣አትክልትንም ለሰው ልጆቜ ጥቅም ያበቅላልፀይህን ዚሚያደርገው ምድር እህል እንድታስገኝ ነውፀ
እንዲሁም ዹሰውን ልብ ደስ ዚሚያሰኝ ወይን፣ፊትን ዚሚያበራ ዘይትናዚሰውን ልብ ዚሚያበሚታ እህል እንዲገኝ ነው።
ዹይሖዋ ዛፎቜ፣ እሱ ዹተኹላቾው አርዘ ሊባኖሶቜ፣ውኃ ጠጥተው ይሚካሉፀ
በዚያ ወፎቜ ጎጇቾውን ይሠራሉ። ራዛ በጥድ ዛፎቜ ላይ ትኖራለቜ።
ሚጃጅሞቹ ተራሮቜ፣ ዚተራራ ፍዚሎቜ መኖሪያ ና቞ውፀቋጥኞቹ ዚሜኮኮዎቜ መሞሞጊያ ና቞ው።
ጊዜያትን ለመለዚት ጹሹቃን ሠራፀፀሐይ ዚምትጠልቅበትን ጊዜ በሚገባ ታውቃለቜ።
ጹለማን ታመጣለህፀ ሌሊትም ይሆናልፀበዚህ ጊዜ በጫካ ዚሚኖሩ አራዊት ሁሉ ወጥተው ይንቀሳቀሳሉ።
ደቩል አንበሶቜ አደን ለማግኘት ያገሳሉፀምግባ቞ውንም ኹአምላክ ይሻሉ።
ፀሐይ ስትወጣ፣ተመልሰው በዚጎሬአ቞ው ይተኛሉ።
ሰውም ወደ ሥራው ተሰማርቶእስኪመሜ ድሚስ ሲሠራ ይውላል።
ይሖዋ ሆይ፣ ሥራህ ምንኛ ብዙ ነው! ሁሉንም በጥበብ ሠራህ። ምድር በፈጠርካ቞ው ነገሮቜ ተሞልታለቜ።
ባሕሩ እጅግ ትልቅና ሰፊ ነውፀበዚያ ስፍር ቁጥር ዹሌላቾው ትናንሜም ሆኑ ትላልቅ ሕያዋን ነገሮቜ ይርመሰመሳሉ።
በዚያም መርኚቊቜ ይጓዛሉፀበዚያ እንዲጫወት ዹፈጠርኹው ሌዋታንም በውስጡ ይሄዳል።
በወቅቱ ምግባ቞ውን እንድትሰጣ቞ው፣ሁሉም አንተን ይጠባበቃሉ።
አንተ ዚምትሰጣ቞ውን ይሰበስባሉ። እጅህን ስትኚፍት መልካም ነገሮቜን ይጠግባሉ።
ፊትህን ስትሰውር ይታወካሉ። መንፈሳ቞ውን ኚወሰድክ ይሞታሉፀ ወደ አፈርም ይመለሳሉ።
መንፈስህን ኹላክ ይፈጠራሉፀዚምድርንም ገጜ ታድሳለህ።
ዹይሖዋ ክብር ለዘላለም ይኖራል። ይሖዋ በሥራው ሐሎት ያደርጋል።
ምድርን ሲመለኚት ትንቀጠቀጣለቜፀተራሮቜን ሲነካ ይጚሳሉ።
በሕይወቮ ዘመን ሁሉ ለይሖዋ እዘምራለሁፀበሕይወት እስካለሁ ድሚስ ለአምላኬ ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁ።
ሐሳቀ እሱን ዚሚያስደስት ይሁን። እኔም በይሖዋ ሐሎት አደርጋለሁ።
ኃጢአተኞቜ ኚምድር ይጠፋሉፀክፉዎቜም ኚእንግዲህ አይገኙም። ይሖዋን ላወድስ። ያህን አወድሱ!
ያህን አወድሱ! ዹይሖዋን ስም አወድሱፀእናንተ ዹይሖዋ አገልጋዮቜ፣ ውዳሎ አቅርቡፀ
በይሖዋ ቀት፣በአምላካቜን ቀት ቅጥር ግቢዎቜ ዚቆማቜሁ ሁሉ አወድሱት።
ይሖዋ ጥሩ ነውና፣ ያህን አወድሱ። ደስ ዚሚያሰኝ ነውና፣ ለስሙ ዚውዳሎ መዝሙር ዘምሩ።
ያህ ያዕቆብን ዚራሱ፣እስራኀልን ልዩ ንብሚቱ አድርጎ መርጧልና።
ይሖዋ ታላቅ መሆኑን በሚገባ አውቃለሁናፀጌታቜን ኚሌሎቜ አማልክት ሁሉ ዹላቀ ነው።
በሰማይና በምድር፣ በባሕሮቜና በጥልቆቜ ውስጥይሖዋ ደስ ያሰኘውን ነገር ሁሉ ያደርጋል።
ደመና ኚምድር ዳርቻዎቜ ወደ ላይ እንዲወጣ ያደርጋልፀበዝናብ ጊዜ መብሚቅን ያበርቃልፀነፋሱን ኹግምጃ ቀቱ ያወጣል።
በግብፅ ዹተወለደውንዹሰውም ሆነ ዚእንስሳ በኩር ገደለ።
ግብፅ ሆይ፣ በፈርዖንና በአገልጋዮቹ ሁሉ ላይ፣በመካኚልሜ ምልክቶቜንና ተአምራትን አደሚገ።
ብዙ ብሔራትን መታፀኃያላን ነገሥታትንም ገደለፀ
ዚአሞራውያንን ንጉሥ ሲሖንን፣ዚባሳንን ንጉሥ ኊግን፣ዚኚነአንንም መንግሥታት ሁሉ ድል አደሚገ።
ምድራ቞ውን ርስት አድርጎ፣አዎ፣ ርስት አድርጎ ለሕዝቡ ለእስራኀል ሰጠ።
ይሖዋ ሆይ፣ ስምህ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል። ይሖዋ ሆይ፣ ዝናህ ኚትውልድ እስኚ ትውልድ ይዘልቃል።
ይሖዋ ለሕዝቡ ይሟገታልናፀለአገልጋዮቹም ይራራል።
ዚብሔራት ጣዖቶቜ ኚብርና ኹወርቅ ዚተሠሩ፣ዚሰው እጅ ሥራ ና቞ው።
አፍ አላ቞ውፀ መናገር ግን አይቜሉምፀዓይን አላ቞ውፀ ማዚት ግን አይቜሉምፀ
ጆሮ አላ቞ውፀ መስማት ግን አይቜሉም። በአፋቾው ውስጥ እስትንፋስ ዚለም።
ዚሚሠሯ቞ውም ሆኑ ዚሚታመኑባ቞ው ሁሉ፣እንደ እነሱ ይሆናሉ።
ዚእስራኀል ቀት ሆይ፣ ይሖዋን አወድሱ። ዚአሮን ቀት ሆይ፣ ይሖዋን አወድሱ።
ዹሌዊ ቀት ሆይ፣ ይሖዋን አወድሱ። እናንተ ይሖዋን ዚምትፈሩ፣ ይሖዋን አወድሱ።
በኢዚሩሳሌም ዹሚኖሹው ይሖዋ፣ኚጜዮን ይወደስ። ያህን አወድሱ!
አምላኬ ይሖዋ ሆይ፣ አንተን መጠጊያ አድርጌአለሁ። ኚሚያሳድዱኝ ሁሉ አድነኝፀ ታደገኝም።
አለዚያ እንደ አንበሳ ይዘነጣጥሉኛልፀዚሚታደገኝ በሌለበት ነጥቀው ይወስዱኛል።
አምላኬ ይሖዋ ሆይ፣ ዚሠራሁት አንዳቜ ጥፋት ካለ፣አግባብ ያልሆነ ድርጊት ፈጜሜ ኚሆነ፣
መልካም ያደሚገልኝን ሰው በድዬ ኚሆነ፣ወይም ያላንዳቜ ምክንያት ጠላቮን ዘርፌ ኚሆነ፣
ጠላት አሳዶ ይያዘኝፀሕይወ቎ን መሬት ላይ ይጚፍልቃትፀክብሬንም ኹአፈር ይደባልቀው። (ሮላ)
ይሖዋ ሆይ፣ በቁጣህ ተነስፀበእኔ ላይ በቁጣ በሚገነፍሉት ጠላቶቌ ላይ ተነስፀለእኔ ስትል ንቃፀ ፍትሕ እንዲሰፍንም እዘዝ።
ብሔራት ይክበቡህፀአንተም ኹላይ ሆነህ በእነሱ ላይ እርምጃ ትወስዳለህ።
ይሖዋ በሕዝቊቜ ላይ ፍርድ ያስተላልፋል። ይሖዋ ሆይ፣ እንደ ጜድቄ፣እንደ ንጹሕ አቋሜም ፍሚድልኝ።
እባክህ፣ ዹክፉ ሰዎቜ ክፋት እንዲያኚትም አድርግ። ጻድቁን ሰው ግን አጜናፀልብንና ጥልቅ ስሜትን ዚምትመሚምር ጻድቅ አምላክ ነህና።
ቀና ልብ ያላ቞ውን ሰዎቜ ዚሚያድነው አምላክ ጋሻዬ ነው።
አምላክ ጻድቅ ፈራጅ ነውፀበዚቀኑም ፍርዱን ያውጃል።
ማንም ሰው ንስሐ ዚማይገባ ኚሆነ፣ አምላክ ሰይፉን ይስላልፀደጋኑን ወጥሮ ያነጣጥራል።
ገዳይ ዹሆኑ መሣሪያዎቹን ያሰናዳልፀዚሚንበለበሉ ፍላጻዎቹን ያዘጋጃል።
ክፋትን ያሚገዘውን ሰው ተመልኚትፀቜግርን ይፀንሳልፀ ሐሰትንም ይወልዳል።
ጉድጓድ ይምሳልፀ ጥልቅ አድርጎም ይቆፍሚዋልፀሆኖም በቆፈሹው ጉድጓድ ውስጥ ራሱ ይወድቃል።
ዚሚያመጣው ቜግር በራሱ ላይ ይመለሳልፀዚዓመፅ ድርጊቱ በገዛ አናቱ ላይ ይወርዳል።
ይሖዋን ለፍትሑ አወድሰዋለሁፀለልዑሉ አምላክ ለይሖዋ ስም ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁ።
ይሖዋ ሆይ፣ አንተን እማጞናለሁ።
አምላኬ ሆይ፣ በአንተ እታመናለሁፀለኀፍሚት እንድዳሚግ አትፍቀድ። ጠላቶቌ በደሚሰብኝ መኚራ አይፈንድቁ።
አንተን ተስፋ ዚሚያደርግ ሁሉ በፍጹም አያፍርምፀያላንዳቜ ምክንያት ክህደት ዚሚፈጜሙ ግን ለኀፍሚት ይዳሚጋሉ።
ይሖዋ ሆይ፣ መንገድህን አሳውቀኝፀጎዳናህንም አስተምሚኝ።
አንተ አዳኝ አምላኬ ስለሆንክበእውነትህ እንድመላለስ አድርገኝፀ አስተምሚኝም። ז [ዋው] ቀኑን ሙሉ አንተን ተስፋ አደርጋለሁ።
ይሖዋ ሆይ፣ ምንጊዜም ታሳያ቞ው ዚነበሩትንምሕሚትህንና ታማኝ ፍቅርህን አስታውስ።
በወጣትነ቎ ዚሠራኋ቞ውን ኃጢአቶቜና በደሎቜ አታስብብኝ። ይሖዋ ሆይ፣ ለጥሩነትህ ስትልእንደ ታማኝ ፍቅርህ መጠን አስበኝ።
ይሖዋ ጥሩና ቀና ነው። ኃጢአተኞቜን ሊኖሩበት ዚሚገባውን መንገድ ዚሚያስተምራ቞ው ለዚህ ነው።
ዚዋሆቜን በትክክለኛ መንገድ ይመራ቞ዋልፀእንዲሁም ለዚዋሆቜ መንገዱን ያስተምራል።
ዹይሖዋ መንገዶቜ ሁሉ፣ ቃል ኪዳኑንና ማሳሰቢያዎቹን ለሚጠብቁ፣ታማኝ ፍቅር ዚሚንጞባሚቅባ቞ውና እምነት ዚሚጣልባ቞ው ና቞ው።
ይሖዋ ሆይ፣ ኃጢአ቎ ታላቅ ቢሆንም እንኳለስምህ ስትል ይቅር በለኝ።
ይሖዋን ዚሚፈራ ሰው ማን ነው? መምሚጥ ስላለበት መንገድ ያስተምሚዋል።
እሱ ጥሩ ዹሆነውን ነገር ያገኛልፀዘሮቹም ምድርን ይወርሳሉ።
ኹይሖዋ ጋር ዹጠበቀ ወዳጅነት ዚሚኖራ቞ው እሱን ዚሚፈሩ ሰዎቜ ና቞ውፀቃል ኪዳኑንም ያሳውቃ቞ዋል።
ዓይኖቌ ሁልጊዜ ወደ ይሖዋ ያያሉፀእግሮቌን ኚወጥመድ ያወጣ቞ዋልና።
ብ቞ኛና ምስኪን ስለሆንኩፊትህን ወደ እኔ መልስፀ ቞ርነትም አሳዚኝ።
ዚልቀ ጭንቀት በዝቷልፀኚሥቃዬ ገላግለኝ።
ጉስቁልናዬንና መኚራዬን ተመልኚትፀኃጢአ቎ንም ሁሉ ይቅር በል።
ጠላቶቌ ምን ያህል ብዙ እንደሆኑ ተመልኚትፀምን ያህል አምርሹው እንደሚጠሉኝም እይ።
ሕይወቮን ጠብቅፀ አድነኝም። አንተን መጠጊያ ስላደሚግኩ ለኀፍሚት እንድዳሚግ አትፍቀድ።
ንጹሕ አቋሜና ቅንነቮ ይጠብቁኝፀአንተን ተስፋ አድርጌአለሁና።
አምላክ ሆይ፣ እስራኀልን ኚጭንቀቱ ሁሉ ታደገው።