text
stringlengths
4
267
ስለዚህ እናንተ እሚኞቜ፣ ዹይሖዋን ቃል ስሙ።
ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘እኔ በእሚኞቹ ላይ ተነስቻለሁፀ ስለ በጎቌ እጠይቃ቞ዋለሁፀ በጎቌን እንዳያሰማሩም እኚለክላ቞ዋለሁፀ እሚኞቹም ኚእንግዲህ ራሳ቞ውን አይመግቡም። በጎቌን ኹአፋቾው አስጥላለሁፀ ኚእንግዲህ ለእነሱ መብል አይሆኑም።’”
“‘ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላልና፩ “እነሆኝ፣ እኔ ራሎ በጎቌን እፈልጋለሁፀ ደግሞም እንኚባኚባ቞ዋለሁ።
ዚተበታተኑትን በጎቹን አግኝቶ እንደሚመግብ እሚኛ በጎቌን እንኚባኚባለሁ። በደመናትና በድቅድቅ ጹለማ ቀን ኚተበተኑባ቞ው ቊታዎቜ ሁሉ እታደጋ቞ዋለሁ።
ኚሕዝቊቜ መካኚል አወጣ቞ዋለሁፀ ኚዚአገሩም እሰበስባ቞ዋለሁፀ ወደ ምድራ቞ውም አመጣ቞ዋለሁፀ በእስራኀል ተራሮቜ፣ በዚጅሚቱ ዳርና በምድሪቱ ላይ በሚገኙት መኖሪያ ስፍራዎቜ ሁሉ አሰማራ቞ዋለሁ።
ጥሩ በሆነ መስክ ላይ አሰማራ቞ዋለሁፀ ኹፍ ያሉት ዚእስራኀል ተራሮቜም ዚግጊሜ መሬት ይሆኗ቞ዋል። በዚያም ጥሩ በሆነ ዚግጊሜ መሬት ላይ ያርፋሉፀ በእስራኀልም ተራሮቜ ላይ በለመለመ መስክ ይሰማራሉ።”
“‘“በጎቌን እኔ ራሎ አሰማራለሁፀ እኔ ራሎም አሳርፋ቞ዋለሁ” ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።
“ዹጠፋውን እፈልጋለሁፀ ዚባዘነውን መልሌ አመጣለሁፀ ዚተጎዳውን በጹርቅ አስራለሁፀ ዹደኹመውን አበሚታለሁፀ ዹወፈሹውንና ጠንካራ ዹሆነውን ግን አጠፋለሁ። እፈርድበታለሁፀ ተገቢውንም ቅጣት እሰጠዋለሁ።”
“‘በጎቌ ስለሆናቜሁት ስለ እናንተ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “በበግና በበግ መካኚል እንዲሁም በአውራ በጎቜና በአውራ ፍዚሎቜ መካኚል ልፈርድ ነው።
እናንተ ምርጥ ኹሆነው ዚግጊሜ ስፍራ መመገባቜሁ አነሳቜሁ? ዚቀሩትን ዚግጊሜ ስፍራዎቜ ደግሞ በእግራቜሁ መሚጋገጥ ይገባቜኋል? እጅግ ዚጠራውን ውኃ ኚጠጣቜሁ በኋላስ ውኃውን በእግራቜሁ እዚመታቜሁ ማደፍሚሳቜሁ ተገቢ ነው?
ታዲያ በጎቌ በእግራቜሁ በሚጋገጣቜሁት ዚግጊሜ መስክ ላይ መሰማራትና በእግራቜሁ እዚመታቜሁ ያደፈሚሳቜሁትን ውኃ መጠጣት ይኖርባ቞ዋል?”
“ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላቾዋል፩ “እነሆኝ፣ እኔ ራሎ በሰባው በግና ኚሲታ በሆነው በግ መካኚል እፈርዳለሁፀ
እናንተ ዚታመሙት ሁሉ በዚአቅጣጫው እስኪበታተኑ ድሚስ በጎናቜሁና በትኚሻቜሁ ገፍታቜኋ቞ዋልናፀ በቀንዳቜሁም ገፍትራቜኋ቞ዋል።
በጎቌንም አድናለሁፀ እነሱም ኚእንግዲህ ለአደን አይዳሚጉምፀ እኔም በበግና በበግ መካኚል እፈርዳለሁ።
በእነሱ ላይ አንድ እሚኛ ይኾውም አገልጋዬን ዳዊትን አስነሳለሁፀ እሱም ይመግባ቞ዋል። እሱ ራሱ ያሰማራ቞ዋልፀ እሚኛ቞ውም ይሆናል።
ደግሞም እኔ ይሖዋ አምላካ቞ው እሆናለሁፀ አገልጋዬ ዳዊት ደግሞ በመካኚላ቞ው አለቃ ይሆናል። እኔ ይሖዋ ራሎ ተናግሬአለሁ።
“‘“ኚእነሱም ጋር ዹሰላም ቃል ኪዳን እገባለሁፀ አደገኛ ዹሆኑ ዚዱር አራዊትንም ኚምድሪቱ ላይ አጠፋለሁፀ በመሆኑም በምድሚ በዳ ያለስጋት ይኖራሉፀ በጫካዎቜም ውስጥ ይተኛሉ።
እነሱንና በኮሚብታዬ ዙሪያ ያለውን ቊታ በሚኚት አደርጋ቞ዋለሁፀ ዝናብም በወቅቱ እንዲዘንብ አደርጋለሁ። በሚኚት እንደ ዝናብ ይወርዳል።
ዚሜዳው ዛፎቜ ፍሬያ቞ውን ይሰጣሉፀ መሬቱም ፍሬ ይሰጣልፀ እነሱም በምድሪቱ ላይ ያለስጋት ይቀመጣሉ። ቀንበራ቞ውን በምሰብርበትና ባሪያ አድርገው ኹሚገዟቾው እጅ በማድና቞ው ጊዜ እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ ያውቃሉ።
ኚእንግዲህ ወዲህ ብሔራት እነሱን ለማደን አይነሱምፀ ዚምድር አራዊትም አይበሏ቞ውምፀ ያለስጋትም ይኖራሉፀ ዚሚያስፈራ቞ውም ዚለም።
“‘“ዝና ዚሚያስገኝ ዚእርሻ ቊታ እሰጣ቞ዋለሁፀ ኚእንግዲህ በምድሪቱ ላይ በሚሃብ አያልቁምፀ ደግሞም ኚእንግዲህ ወዲህ ብሔራት አያዋርዷ቞ውም።
‘በዚህ ጊዜ እኔ አምላካ቞ው ይሖዋ ኚእነሱ ጋር እንደሆንኩና እነሱ ይኾውም ዚእስራኀል ቀት ሕዝቀ እንደሆኑ ያውቃሉ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።”’
“‘እናንተ በጎቌ፣ ዚምንኚባኚባቜሁ በጎቜ፣ ኹአፈር ዚተሠራቜሁ ሰዎቜ ናቜሁፀ እኔም አምላካቜሁ ነኝ’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።”
ዹይሖዋ ቃል ዳግመኛ እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣፊ
“ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ፊትህን ወደ እስራኀል ተራሮቜ አዙሹህ በእነሱ ላይ ትንቢት ተናገር።
እንዲህም በል፩ ‘ዚእስራኀል ተራሮቜ ሆይ፣ ዹሉዓላዊውን ጌታ ዹይሖዋን ቃል ስሙፊ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ለተራሮቹ፣ ለኮሚብቶቹ፣ ለጅሚቶቹና ለሞለቆዎቹ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ እኔ በእናንተ ላይ ሰይፍ አመጣለሁፀ ኹፍ ያሉትን ዚማምለኪያ ቊታዎቻቜሁንም አጠፋለሁ።
መሠዊያዎቻቜሁ ይፈርሳሉፀ ዚዕጣን ማጚሻዎቻቜሁ ይሰባበራሉፀ ዚታሚዱ ወገኖቻቜሁንም አስጞያፊ በሆኑት ጣዖቶቻቜሁ ፊት እጥላለሁ።
ዚእስራኀልን ሕዝብ ሬሳ አስጞያፊ በሆኑት ጣዖቶቻ቞ው ፊት እጥላለሁፀ አጥንቶቻቜሁንም በመሠዊያዎቻቜሁ ዙሪያ እበትናለሁ።
በምትኖሩባ቞ው ቊታዎቜ ሁሉ ያሉት ኚተሞቜ ይወድማሉፀ ኹፍ ያሉት ዚማምለኪያ ቊታዎቹም ፈራርሰው ባድማ ይሆናሉ። መሠዊያዎቻቜሁ ፈራርሰው እንዳልነበሩ ይሆናሉፀ አስጞያፊ ዚሆኑት ጣዖቶቻቜሁ ይወገዳሉፀ ዚዕጣን ማጚሻዎቻቜሁ ተገንድሰው ይወድቃሉፀ ዚሠራቜኋ቞ው ሥራዎቜም ተጠራርገው ይጠፋሉ።
ዚታሚዱትም ሰዎቜ በመካኚላቜሁ ይወድቃሉፀ እኔም ይሖዋ እንደሆንኩ ታውቃላቜሁ።
“‘“ይሁንና ዹተወሰኑ ቀሪዎቜ እንዲኖሩ አደርጋለሁፀ በዚአገሩ በምትበተኑበት ጊዜ፣ ኚእናንተ ውስጥ አንዳንዶቻቜሁ በብሔራት መካኚል ስትኖሩ ኹሰይፍ ታመልጣላቜሁና።
ዚተሚፉትም ሰዎቜ በምርኮ በተወሰዱባ቞ው ብሔራት መካኚል ሆነው እኔን ያስታውሳሉ። ኚእኔ በራቀው ኚሃዲ ልባ቞ውና አስጞያፊ ዹሆኑ ጣዖቶቻ቞ውን በፍትወት ስሜት በተመለኚቱት ዓይኖቻ቞ው ዚተነሳ ምን ያህል ልቀ እንዳዘነ ይገነዘባሉ። በሠሯ቞ው መጥፎና አስነዋሪ ነገሮቜ ሁሉ ያፍራሉፀ እነዚህንም ነገሮቜ ይጞዚፋሉ።
እኔ ይሖዋ እንደሆንኩና ይህን ጥፋት እንደማመጣባ቞ው ዚዛትኩት በኚንቱ እንዳልሆነ ያውቃሉ።”’
“ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ዚእስራኀል ቀት ሰዎቜ በሠሯ቞ው ክፉና አስጞያፊ ነገሮቜ ሁሉ ዚተነሳ በሰይፍ፣ በሚሃብና በቾነፈር ስለሚወድቁ በእጅህ እያጚበጚብክ፣ በእግርህም መሬቱን እዚደበደብክ አልቅስ።
በሩቅ ያለው በቾነፈር ይሞታልፀ በቅርብ ያለው በሰይፍ ይወድቃልፀ ኚእነዚህ ነገሮቜ ያመለጠና በሕይወት ዹተሹፈ ሁሉ በሚሃብ ያልቃልፀ ቁጣዬንም ሁሉ በእነሱ ላይ አወርዳለሁ።
ዚታሚዱት ወገኖቻ቞ው አስጞያፊ በሆኑት ጣዖቶቻ቞ው መካኚል፣ በመሠዊያዎቻ቞ው ዙሪያ፣ ኹፍ ባለ ኮሚብታ ሁሉና በተራሮቜ አናት ሁሉ ላይ፣ ኹለመለመ ዛፍ ሁሉ በታቜ እንዲሁም በትላልቅ ዛፎቜ ቅርንጫፎቜ ሥር ይኾውም አስጞያፊ ዹሆኑ ጣዖቶቻ቞ውን ሁሉ ቁጣ ለማብሚድ፣ ደስ ዚሚያሰኝ ሜታ ያላ቞ው መባዎቜ ባቀሚቡባ቞ው ቊታዎቜ በሚወድቁበት ጊዜ እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ ያውቃሉ።
በእነሱ ላይ እጄን እዘሚጋለሁፀ ምድሪቱንም ባድማ አደርጋለሁፀ መኖሪያ ቊታዎቻ቞ውም ሁሉ በዲብላ አቅራቢያ ካለው ምድሚ በዳ ዚባሰ ባድማ ይሆናሉ። እነሱም እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ ያውቃሉ።’”
በግዞት በተወሰድን በ25ኛው ዓመት፣ በዓመቱ መጀመሪያ፣ በወሩ አሥሚኛ ቀን፣ ኹተማዋ በወደቀቜ በ14ኛው ዓመት፣ በዚያው ዕለት ዹይሖዋ እጅ በእኔ ላይ ነበሚቜፀ እሱም ወደ ኹተማዋ ወሰደኝ።
አምላክ በገለጠልኝ ራእዮቜ አማካኝነት ወደ እስራኀል ምድር አመጣኝፀ በአንድ ትልቅ ተራራም ላይ አስቀመጠኝፀ በዚያም በስተ ደቡብ በኩል ኹተማ ዚሚመስል ሕንፃ ነበር።
ወደዚያ በወሰደኝ ጊዜ መዳብ ዚሚመስል መልክ ያለው አንድ ሰው አዚሁ። በእጁም ኚተልባ እግር ዚተሠራ ገመድና ዚመለኪያ ዘንግ ይዞ መግቢያው ላይ ቆሞ ነበር።
ሰውዹው እንዲህ አለኝ፩ “ዹሰው ልጅ ሆይ፣ በደንብ ተመልኚትፀ በጥሞና አዳምጥፀ ዚማሳይህንም ሁሉ በትኩሚት ተመልኚትፀ እዚህ ዚመጣኞው ለዚህ ነውና። ዚምታዚውን ነገር ሁሉ ለእስራኀል ቀት ሰዎቜ ተናገር።”
ኚቀተ መቅደሱ ውጭ በዙሪያው ያለውን ቅጥር አዚሁ። ሰውዹው ስድስት ክንድ ርዝመት ያለው ዚመለኪያ ዘንግ ይዞ ነበርፀ እያንዳንዱ ክንድ አንድ ጋት ተጚምሮበት ነበር። እሱም ቅጥሩን መለካት ጀመሚፀ ዚቅጥሩ ውፍሚት አንድ ዘንግ፣ ቁመቱም አንድ ዘንግ ነበር።
ኚዚያም በምሥራቅ ትይዩ ወዳለው በር መጣፀ በደሚጃዎቹም ወጣ። ዚበሩን ደፍ ሲለካ ወርዱ አንድ ዘንግ ነበርፀ ዹሌላኛውም ደፍ ወርድ አንድ ዘንግ ነበር።
እያንዳንዱ ዚዘብ ጠባቂ ክፍል ርዝመቱ አንድ ዘንግ፣ ወርዱም አንድ ዘንግ ነበርፀ በዘብ ጠባቂ ክፍሎቹ መካኚል ደግሞ አምስት ክንድ ስፋት ነበር። ኚበሩ በሚንዳ አጠገብ በውስጥ በኩል ያለው ዚበሩ ደፍ አንድ ዘንግ ነበር።
በውስጥ በኩል ያለውን ዚበሩን በሚንዳ ለካፀ አንድ ዘንግም ሆነ።
ኚዚያም ዚበሩን በሚንዳ ሲለካ ስምንት ክንድ ሆነፀ በጎን በኩል ያሉትን ዓምዶቜም ሲለካ ሁለት ክንድ ሆኑፀ ዚበሩም በሚንዳ በውስጥ በኩል ነበር።
በምሥራቁ በር ግራና ቀኝ ሊስት ሊስት ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቜ ነበሩ። ሊስቱም መጠናቾው እኩል ነበርፀ በሁለቱም በኩል ያሉት ዓምዶቜም መጠናቾው እኩል ነበር።
ኚዚያም ዚበሩን መግቢያ ወርድ ሲለካ 10 ክንድ ሆነፀ ዚበሩ ስፋት ኹውጭ በኩል 13 ክንድ ነበር።
ኚዘብ ጠባቂ ክፍሎቹ ፊት ለፊት ያለው ዹተኹለለ ቊታ በሁለቱም በኩል አንድ አንድ ክንድ ነበር። ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቹ በሁለቱም በኩል ስድስት ስድስት ክንድ ነበሩ።
ኚዚያም በሩን ኚአንዱ ዚዘብ ጠባቂ ክፍል ጣሪያ እስኚ ሌላኛው ዚዘብ ጠባቂ ክፍል ጣሪያ ድሚስ ለካፀ ወርዱም 25 ክንድ ነበርፀ አንደኛው መግቢያ ኹሌላኛው መግቢያ ትይዩ ነበር።
ኚዚያም በጎንና በጎን በኩል ያሉትን ዓምዶቜ ቁመት ሲለካ 60 ክንድ ሆነፀ በግቢው ዙሪያ በሚገኙት በሮቜ ላይ ያሉትንም ዓምዶቜ ለካ።
ኚመግቢያው በር ፊት አንስቶ በበሩ ውስጠኛ ክፍል በኩል እስካለው በሚንዳ ፊት ድሚስ 50 ክንድ ነበር።
ኚበሩ በውስጥ በኩል በግራና በቀኝ፣ ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቹና በጎን ያሉት ዓምዶቻ቞ው እዚጠበቡ ዚሚሄዱ ክፈፎቜ ያሏ቞ው መስኮቶቜ ነበሯ቞ው። በሚንዳዎቹም በውስጥ በኩል፣ በግራም በቀኝም መስኮቶቜ ነበሯ቞ውፀ በጎን ያሉት ዓምዶቜ ደግሞ ዚዘንባባ ዛፍ ምስሎቜ ተቀርጞውባ቞ው ነበር።
ኚዚያም ወደ ውጹኛው ግቢ አመጣኝፀ በግቢውም ዙሪያ ዚመመገቢያ ክፍሎቜና መመላለሻ መንገድ አዚሁ። በመንገዱ ላይ 30 ዚመመገቢያ ክፍሎቜ ነበሩ።
በበሮቹ ጎን ያለው መመላለሻ መንገድ ኚበሮቹ ርዝመት ጋር እኩል ነበርፀ ይህም ዚታቜኛው መመላለሻ መንገድ ነበር።
ኚዚያም ኚታቜኛው በር አንስቶ ወደ ውስጠኛው ግቢ እስኚሚያስገባው በር ድሚስ ያለውን ርቀት ለካ። በምሥራቅም ሆነ በሰሜን በኩል ያለው ርቀት 100 ክንድ ነበር።
ዹውጹኛው ግቢ ኹሰሜን ጋር ትይዩ ዹሆነ በር ነበሚውፀ እሱም ርዝመቱንና ወርዱን ለካ።
በሁለቱም ጎን ሊስት ሊስት ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቜ ነበሩ። በጎን ያሉት ዓምዶቹና በሚንዳው መጠናቾው ኚመጀመሪያው በር ጋር እኩል ነበር። ርዝመቱ 50 ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ 25 ክንድ ነበር።
ዚመስኮቶቹ፣ ዚበሚንዳውና ዚዘንባባ ዛፍ ምስሎቹ መጠን በምሥራቁ በር ካሉት ጋር እኩል ነበር። ሰዎቜ ሰባት ደሚጃዎቜ ወጥተው ወደዚያ መግባት ይቜላሉፀ በሚንዳውም ኚፊት ለፊታ቞ው ነበር።
በውስጠኛው ግቢ፣ ኹሰሜኑ በር ትይዩ አንድ በር፣ ኚምሥራቁ በር ትይዩ ደግሞ ሌላ በር ነበር። እሱም ኹአንደኛው በር እስኚ ሌላኛው በር ሲለካ 100 ክንድ ሆነ።
ኚዚያም ወደ ደቡብ አቅጣጫ አመጣኝፀ በስተ ደቡብ በኩል አንድ በር አዚሁ። እሱም በጎን ያሉትን ዓምዶቹንና በሚንዳውን ለካፀ መጠናቾውም ኚሌሎቹ ጋር እኩል ነበር።
በበሩና በበሚንዳው ግራና ቀኝ እንደ ሌሎቹ ዓይነት መስኮቶቜ ነበሩ። ርዝመቱ 50 ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ 25 ክንድ ነበር።
ወደዚያ ዚሚወስዱ ሰባት ደሚጃዎቜ ነበሩፀ በሚንዳውም ኚፊት ለፊታ቞ው ነበር። በግራና በቀኝ ባሉት ዓምዶቜ ላይ አንድ አንድ ዚዘንባባ ዛፍ ምስል ተቀርጟ ነበር።
ዚውስጠኛው ግቢ ኚደቡብ ጋር ትይዩ ዹሆነ በር ነበሚውፀ እሱም ወደ ደቡብ አቅጣጫ ኹአንደኛው በር እስኚ ሌላኛው በር ለካፀ ርቀቱም 100 ክንድ ሆነ።
ኚዚያም በደቡብ በር በኩል ወደ ውስጠኛው ግቢ ወሰደኝፀ ዚደቡቡን በር ሲለካ መጠኑ ኚሌሎቹ ጋር እኩል ሆነ።
ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቹ፣ በጎን ያሉት ዓምዶቹና በሚንዳው መጠናቾው ኚሌሎቹ ጋር እኩል ነበር። በበሩና በበሚንዳው ግራና ቀኝ መስኮቶቜ ነበሩ። ርዝመቱ 50 ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ 25 ክንድ ነበር።
ዙሪያውን በሚንዳዎቜ ነበሩፀ ርዝመታ቞ው 25 ክንድ፣ ወርዳ቞ው ደግሞ 5 ክንድ ነበር።
በሚንዳው ኹውጹኛው ግቢ ጋር ትይዩ ነበርፀ በጎን ባሉት ዓምዶቹም ላይ ዚዘንባባ ዛፍ ምስሎቜ ነበሩፀ ወደዚያም ዚሚወስዱ ስምንት ደሚጃዎቜ ነበሩ።
በምሥራቅ በኩል ወደ ውስጠኛው ግቢ ሲወስደኝ በሩን ለካፀ መጠኑም ኚሌሎቹ ጋር እኩል ነበር።
ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቹ፣ በጎን ያሉት ዓምዶቹና በሚንዳው መጠናቾው ኚሌሎቹ ጋር እኩል ነበርፀ በበሩና በበሚንዳው ግራና ቀኝ መስኮቶቜ ነበሩ። ርዝመቱ 50 ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ 25 ክንድ ነበር።
በሚንዳው ኹውጹኛው ግቢ ጋር ትይዩ ነበርፀ በግራና በቀኝ ባሉት ዓምዶቜ ላይ ዚዘንባባ ዛፍ ምስሎቜ ተቀርጾው ነበርፀ ወደዚያም ዚሚወስዱ ስምንት ደሚጃዎቜ ነበሩ።
ኚዚያም ወደ ሰሜን በር ወሰደኝና ለካውፀ መጠኑ ኚሌሎቹ ጋር እኩል ነበር።
ዚዘብ ጠባቂ ክፍሎቹ፣ በጎን ያሉት ዓምዶቹና በሚንዳው መጠናቾው ኚሌሎቹ ጋር እኩል ነበር። በግራና በቀኝ መስኮቶቜ ነበሩት። ርዝመቱ 50 ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ 25 ክንድ ነበር።
በጎን ያሉት ዓምዶቹ ኹውጹኛው ግቢ ጋር ትይዩ ነበሩፀ በግራና በቀኝ ባሉት ዓምዶቹ ላይ ዚዘንባባ ዛፍ ምስሎቜ ተቀርጾው ነበርፀ ወደዚያም ዚሚወስዱ ስምንት ደሚጃዎቜ ነበሩ።
በበሮቹ ጎንና ጎን ባሉት ዓምዶቜ አጠገብ ዚመመገቢያ ክፍል ነበርፀ መግቢያም ነበሚውፀ ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠለውን መባ ዚሚያጥቡት በዚያ ነበር።
በበሩም በሚንዳ ላይ በግራና በቀኝ ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ፣ ዚኃጢአት መባና ዹበደል መባ ዚሚታሚድባ቞ው ሁለት ሁለት ጠሚጎዛዎቜ ነበሩ።
ወደ ሰሜን በር በሚወስደው መንገድ ላይ ኚመግቢያው ውጭ ሁለት ጠሚጎዛዎቜ ነበሩ። በተጚማሪም ኚበሩ በሚንዳ በሌላኛው በኩል ሁለት ጠሚጎዛዎቜ ነበሩ።
በበሩ ግራና ቀኝ አራት አራት ጠሚጎዛዎቜ፣ በድምሩ መሥዋዕት ዚታሚደባ቞ው ስምንት ጠሚጎዛዎቜ ነበሩ።
ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ ለማቅሚብ ዚሚያገለግሉት አራቱ ጠሚጎዛዎቜ ኹተጠሹበ ድንጋይ ዚተሠሩ ነበሩ። ርዝመታ቞ው አንድ ክንድ ተኩል፣ ወርዳ቞ው አንድ ክንድ ተኩል፣ ቁመታ቞ው ደግሞ አንድ ክንድ ነበር። በእነሱም ላይ ዹሚቃጠለውን መባና መሥዋዕቱን ለማሚድ ዚሚያገለግሉ መሣሪያዎቜ ተቀምጠው ነበር።
ኚውስጠኛው ግንብ ጋር ተያይዘው ዙሪያውን ዚተሠሩ መደርደሪያዎቜ ዚነበሩ ሲሆን ወርዳ቞ው አንድ ጋት ነበርፀ በጠሚጎዛዎቹም ላይ ዚስጊታ መባው ሥጋ ይቀመጥ ነበር።
ኚውስጠኛው በር ውጭ ዚዘማሪዎቹ መመገቢያ ክፍሎቜ ነበሩፀ ክፍሎቹ ኚደቡብ ትይዩ ባለው ዹሰሜን በር አጠገብ በሚገኘው በውስጠኛው ግቢ ውስጥ ነበሩ። ኹሰሜን ትይዩ ባለው ዚምሥራቅ በር አጠገብ ሌላ ዚመመገቢያ ክፍል ነበር።
እሱም እንዲህ አለኝ፩ “በደቡብ ትይዩ ያለው ይህ ዚመመገቢያ ክፍል ዚቀተ መቅደሱን አገልግሎት እንዲያኚናውኑ ኃላፊነት ለተጣለባ቞ው ካህናት ዹተመደበ ነው።
በሰሜን ትይዩ ያለው ዚመመገቢያ ክፍል ኚመሠዊያው ጋር ዚተያያዘ አገልግሎት እንዲያኚናውኑ ኃላፊነት ለተጣለባ቞ው ካህናት ዹተመደበ ነው። እነዚህ ዚሳዶቅ ልጆቜ ሲሆኑ ኚሌዋውያን መካኚል ይሖዋን ለማገልገል ወደ እሱ እንዲቀርቡ ዚተመደቡ ና቞ው።”
ኚዚያም ዚውስጠኛውን ግቢ ለካ። ርዝመቱ 100 ክንድ፣ ወርዱም 100 ክንድ ዹሆነ አራት ማዕዘን ነበር። መሠዊያው ኚቀተ መቅደሱ ፊት ለፊት ነበር።
ኚዚያም ወደ ቀተ መቅደሱ በሚንዳ አመጣኝፀ በጎን በኩል ያለውንም ዚበሚንዳውን ዓምድ ለካፀ ዓምዱም በአንደኛው ጎን አምስት ክንድ፣ በሌላኛውም ጎን አምስት ክንድ ነበር። ዚበሩ ወርድ በአንደኛው ጎን ሊስት ክንድ፣ በሌላኛውም ጎን ሊስት ክንድ ነበር።
ዚበሚንዳው ርዝመት 20 ክንድ፣ ወርዱ ደግሞ 11 ክንድ ነበር። ሰዎቜ ወደዚያ ዚሚወጡት በደሚጃዎቜ ነበር። በጎንና በጎን ባሉት ምሰሶዎቜ አጠገብ በግራና በቀኝ አንድ አንድ ዓምድ ነበር።
በአሥሚኛው ዓመት፣ በአሥሚኛው ወር፣ ኚወሩም በ12ኛው ቀን ዹይሖዋ ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣፊ
“ዹሰው ልጅ ሆይ፣ ፊትህን ወደ ግብፅ ንጉሥ ወደ ፈርዖን አዙሹህ በእሱና በመላዋ ግብፅ ላይ ትንቢት ተናገር።
እንዲህ ብለህ ተናገር፩ ‘ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “በአባይ ጅሚቶቜ መካኚል ዚተጋደምክና‘ዚአባይ ወንዝ ዚእኔ ነው።ዚሠራሁት ለገዛ ራሎ ነው’ ዚምትል አንተ ግዙፍ ዚባሕር ፍጥሚት፣ ዚግብፅ ንጉሥ ፈርዖን፣ በአንተ ላይ ተነስቻለሁ።
በመንጋጋህ መንጠቆ አስገባለሁፀ በአባይ ወንዝህ ውስጥ ያሉት ዓሣዎቜ ኚቅርፊትህ ጋር እንዲጣበቁ አደርጋለሁ። ቅርፊትህ ላይ ኚተጣበቁት ዚአባይ ዓሣዎቜ ሁሉ ጋር ኚአባይ ወንዝህ መካኚል አወጣሃለሁ።
አንተንም ሆነ በአባይ ወንዝህ ውስጥ ያሉትን ዓሣዎቜ ሁሉ በሹሃ ላይ እጥላለሁ። አውላላ ሜዳ ላይ ትወድቃለህፀ ዚሚሰበስብህም ሆነ ዚሚያነሳህ አይኖርም። ለምድር አራዊትና ለሰማይ ወፎቜ መብል አድርጌ እሰጥሃለሁ።
በዚያን ጊዜ ዚግብፅ ነዋሪዎቜ ሁሉ እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ ያውቃሉፀለእስራኀል ቀት ኚአገዳ ዚተሻለ ድጋፍ መሆን አልቻሉምና።
እጅህን ሲይዙህ ተሰበርክፀትኚሻ቞ውንም ወጋህ። በተመሚኮዙህ ጊዜ ተሰበርክፀእግራ቞ውም እንዲብሚኚሚክ አደሚግክ።”
“‘ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ ሰይፍ አመጣብሃለሁፀ በአንተ ዘንድ ዹሚገኘውን ሰውም ሆነ እንስሳ አጠፋለሁ።
ዚግብፅ ምድር ባድማና ወና ይሆናልፀ እነሱም እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ ያውቃሉፀ አንተ ‘ዚአባይ ወንዝ ዚእኔ ነውፀ ዚሠራሁት እኔ ነኝ’ ብለሃልና።
ስለዚህ በአንተና በአባይ ወንዝህ ላይ ተነስቻለሁፀ ዚግብፅንም ምድር ኚሚግዶል እስኚ ሰዌኔ ብሎም እስኚ ኢትዮጵያ ድንበር ድሚስ ባድማ፣ ደሹቅና ወና አደርጋለሁ።
ዹሰው እግርም ሆነ ዚኚብት ኮ቎ አያልፍባትምፀ ለ40 ዓመትም ማንም አይኖርባትም።
ዚግብፅን ምድር ኚሌሎቜ አገሮቜ በኹፋ ሁኔታ ባድማ አደርጋታለሁፀ ኚተሞቿም ኚሌሎቜ ኚተሞቜ በኹፋ ሁኔታ ለ40 ዓመት ያህል ባድማ ይሆናሉፀ ግብፃውያንንም በብሔራት መካኚል እበትና቞ዋለሁፀ በአገሮቜም መካኚል እዘራ቞ዋለሁ።”
“‘ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላልና፩ “ኹ40 ዓመት በኋላ ግብፃውያንን ኚተበተኑባ቞ው ሕዝቊቜ መካኚል እሰበስባ቞ዋለሁፀ
ዚተማሚኩትን ግብፃውያን ወደ ትውልድ አገራ቞ው ወደ ጳትሮስ ምድር መልሌ አመጣ቞ዋለሁፀ በዚያም ደካማ መንግሥት ይሆናሉ።