text
stringlengths
4
267
ኚዚያም ኚሪሞንጰሬጜ ተነስተው በሊብና ሰፈሩ።
ኚሊብናም ተነስተው በሪሳ ሰፈሩ።
በመቀጠልም ኚሪሳ ተነስተው በቀሄላታ ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚቀሄላታ ተነስተው በሾፈር ተራራ ሰፈሩ።
በኋላም ኹሾፈር ተራራ ተነስተው በሃራዳ ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚሃራዳ ተነስተው በማቅሄሎት ሰፈሩ።
ቀጥሎም ኚማቅሄሎት ተነስተው በታሃት ሰፈሩ።
ኚዚያ በኋላም ኚታሃት ተነስተው በታራ ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚታራ ተነስተው በሚትቃ ሰፈሩ።
በኋላም ኚሚትቃ ተነስተው በሃሜሞና ሰፈሩ።
ኚሃሜሞናም ተነስተው በሞሎሮት ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚሞሎሮት ተነስተው በብኔያዕቃን ሰፈሩ።
በኋላም ኚብኔያዕቃን ተነስተው በሆርሃጊድጋድ ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚሆርሃጊድጋድ ተነስተው በዮጥባታ ሰፈሩ።
ኚዮጥባታም ተነስተው በአብሮና ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚአብሮና ተነስተው በዔጜዮንጋብር ሰፈሩ።
በኋላም ኚዔጜዮንጋብር ተነስተው በጺን ምድሚ በዳ በምትገኘው በቃዎስ ሰፈሩ።
ኚቃዎስም ተነስተው በኀዶም ምድር ወሰን ላይ በሚገኘው በሆር ተራራ ሰፈሩ።
እስራኀላውያን ኚግብፅ ምድር በወጡ በ40ኛው ዓመት በአምስተኛው ወር ኚወሩም በመጀመሪያው ቀን ካህኑ አሮን ይሖዋ በሰጠው ትእዛዝ መሠሚት ወደ ሆር ተራራ ወጣፀ በዚያም ሞተ።
አሮን በሆር ተራራ ላይ በሞተበት ጊዜ ዕድሜው 123 ዓመት ነበር።
በኹነአን ምድር በኔጌብ ይኖር ዹነበሹው ኹነአናዊው ዚአራድ ንጉሥ ዚእስራኀላውያንን መምጣት ሰማ።
ኹጊዜ በኋላም ኹሆር ተራራ ተነስተው በጻልሞና ሰፈሩ።
ኚዚያም ኚጻልሞና ተነስተው በጱኖን ሰፈሩ።
በመቀጠልም ኚጱኖን ተነስተው በኊቊት ሰፈሩ።
ኚኊቊትም ተነስተው በሞዓብ ድንበር ላይ በምትገኘው በኢዬዓባሪም ሰፈሩ።
በኋላም ኚኢይም ተነስተው በዲቊንጋድ ሰፈሩ።
በመቀጠልም ኚዲቊንጋድ ተነስተው በአልሞንዲብላታይም ሰፈሩ።
ኚአልሞንዲብላታይም ተነስተው ደግሞ በነቩ ፊት ለፊት በአባሪም ተራሮቜ ሰፈሩ።
በመጚሚሻም ኚአባሪም ተራሮቜ ተነስተው በኢያሪኮ በሚገኘው በዮርዳኖስ አጠገብ ባለው ዚሞዓብ በሹሃማ ሜዳ ሰፈሩ።
በሞዓብ በሹሃማ ሜዳ ኚቀትዚሺሞት እስኚ አቀልሺቲም በሚገኘው ስፍራ በዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ ሰፈሩ።
ይሖዋ በኢያሪኮ በሚገኘው በዮርዳኖስ አጠገብ ባለው ዚሞዓብ በሹሃማ ሜዳ ላይ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“እስራኀላውያንን ተናገራ቞ውፀ እንዲህም በላቾው፩ ‘እንግዲህ ዮርዳኖስን ተሻግራቜሁ ወደ ኹነአን ምድር ልትገቡ ነው።
ዚምድሪቱን ነዋሪዎቜ በሙሉ ኚፊታቜሁ አባሯ቞ውፀ ዚተቀሚጹ ዚድንጋይ ምስሎቻ቞ውንም ሁሉ አጥፉፀ ኚብሚት ዚተሠሩ ሐውልቶቻ቞ውንም በሙሉ አስወግዱፀ በኚፍታ ቊታዎቜ ላይ ያሉ ቅዱስ ስፍራዎቻ቞ውን ሁሉ አፍርሱ።
ምድሪቱን ርስት አድርጌ ስለምሰጣቜሁ ምድሪቱን ወርሳቜሁ በዚያ ትኖራላቜሁ።
ምድሪቱንም በዚቀተሰባቜሁ ውርስ አድርጋቜሁ በዕጣ ተኚፋፈሉ። ተለቅ ላለው ቡድን በዛ ያለውን፣ አነስ ላለው ቡድን ደግሞ አነስ ያለውን ውርስ አድርጋቜሁ ስጡት። ሁሉም በወጣለት ዕጣ መሠሚት ዹተሰጠውን ቊታ ይወርሳል። በዚአባቶቻቜሁ ነገዶቜ ርስታቜሁን ውርስ አድርጋቜሁ ትቀበላላቜሁ።
“‘ዚምድሪቱን ነዋሪዎቜ ኚፊታቜሁ ሳታባርሩ እዚያው ኚተዋቜኋ቞ው ግን ዓይናቜሁ ውስጥ እንደገባ ጉድፍ እንዲሁም ጎናቜሁ ላይ እንደተሰካ እሟህ ይሆኑባቜኋልፀ ደግሞም በምትኖሩበት ምድር ያንገላቷቜኋል።
እኔም በእነሱ ላይ ለማድሚግ ያሰብኩትን በእናንተ ላይ አደርግባቜኋለሁ።’”
በዚህ ጊዜ ሕዝቡ፣ ስለደሚሰበት ቜግር በይሖዋ ፊት ክፉኛ ማጉሹምሹም ጀመሚ። ይሖዋ ይህን ሲሰማ ቁጣው ነደደፀ ኹይሖዋም ዚመጣ እሳት በእነሱ ላይ ተቀጣጠለፀ በሰፈሩ ዳርቻ ያሉትን ዹተወሰኑ ሰዎቜም በላ።
ሕዝቡ ወደ ሙሮ መጮኜ ሲጀምር ሙሮ ይሖዋን ተማጞነፀ እሳቱም ኚሰመ።
ኹይሖዋ ዚመጣ እሳት በእነሱ ላይ ስለነደደም ዚዚያ ቊታ ስም ታበራ ተባለ።
እስራኀላውያንም በመካኚላ቞ው ዹነበሹው ድብልቅ ሕዝብ ሲስገበገብ ሲያዩ እንዲህ በማለት እንደገና ያለቅሱ ጀመር፩ “እንግዲህ አሁን ዹምንበላው ሥጋ ማን ይሰጠናል?
በግብፅ እያለን በነፃ እንበላው ዹነበሹው ዓሣ እንዲሁም ኪያሩ፣ ሐብሐቡ፣ ባሮ ሜንኩርቱ፣ ቀይ ሜንኩርቱና ነጭ ሜንኩርቱ በዓይናቜን ላይ ዞሯል!
አሁን ግን ዝለናል። ኹዚህ መና በስተቀር ሌላ ዹምናዹው ነገር ዚለም።”
መናው እንደ ድንብላል ዘር ነበርፀ መልኩም ሙጫ ይመስል ነበር።
ሕዝቡም ሜዳ ላይ ወጥቶ መናውን ኹለቀመ በኋላ በወፍጮ ይፈጹው ወይም በሙቀጫ ይወቅጠው ነበር። ኚዚያም በድስት ይቀቅሉት ወይም እንደ ቂጣ ይጋግሩት ነበርፀ ጣዕሙም በዘይት ተለውሶ እንደተጋገሚ ጣፋጭ ቂጣ ነበር።
ሌሊት በሰፈሩ ላይ ጀዛ በሚወርድበት ጊዜ መናውም በላዩ ላይ ይወርድ ነበር።
ሙሮም ሕዝቡ ይኾውም እያንዳንዱ ሰው በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ሆኖ ኚቀተሰቡ ጋር ሲያለቅስ ሰማ። ይሖዋም እጅግ ተቆጣፀ ሙሮም በጣም አዘነ።
ኚዚያም ሙሮ ይሖዋን እንዲህ አለው፩ “አገልጋይህን ዚምታጎሳቁለው ለምንድን ነው? በፊትህ ሞገስ ያጣሁትና ዹዚህን ሁሉ ሕዝብ ሾክም በእኔ ላይ ዚጫንኚው ለምንድን ነው?
ይህን ሁሉ ሕዝብ ዚፀነስኩት እኔ ነኝ? ለአባቶቻ቞ው ለመስጠት ቃል ወደገባህላ቞ው ምድር እንዳስገባ቞ው ‘ዚሚጠባን ሕፃን እንደሚታቀፍ ሞግዚት በጉያህ እቀፋ቞ው’ ዚምትለኝ ዚወለድኳ቞ው እኔ ነኝ?
ለዚህ ሁሉ ሕዝብ ዹሚሆን ሥጋ ኚዚት ነው ዚማመጣው? ይኾው እነሱ ‘ዹምንበላው ሥጋ ስጠን!’ በማለት እያለቀሱብኝ ነው።
ይህን ሁሉ ሕዝብ እኔ ብቻዬን ልሾኹመው አልቜልምፀ ኹአቅሜ በላይ ነው።
እንዲህስ ኚምታደርገኝ እባክህ አሁኑኑ ግደለኝ። በፊትህ ሞገስ አግኝቌ ኹሆነ ኚእንግዲህ መኚራ እንዳይ አታድርገኝ።”
ይሖዋም መልሶ ሙሮን እንዲህ አለው፩ “ኚእስራኀል ሜማግሌዎቜ መካኚል ዚሕዝቡ ሜማግሌዎቜና አለቆቜ ዹመሆን ብቃት አላቾው ዚምትላ቞ውን 70 ሰዎቜ ሰብስብልኝፀ እነሱንም ወደ መገናኛ ድንኳኑ ውሰዳ቞ውና በዚያ ኹአንተ ጋር ይቁሙ።
እኔም ወርጄ በዚያ ኹአንተ ጋር እነጋገራለሁፀ በአንተ ላይ ካለው መንፈስ ወስጄ በእነሱ ላይ አደርጋለሁፀ እነሱም ዚሕዝቡን ሾክም ብቻህን እንዳትሞኚም ይሚዱሃል።
ሕዝቡንም እንዲህ በለው፩ ‘ሥጋ ስለምትበሉ ለነገ ራሳቜሁን ቀድሱፀ ምክንያቱም በይሖዋ ፊት አልቅሳቜኋልፀ ደግሞም “ዹምንበላው ሥጋ ማን ይሰጠናል? በግብፅ ዚነበርንበት ሁኔታ ዚተሻለ ነበር” ብላቜኋል። ይሖዋ በእርግጥ ሥጋ ይሰጣቜኋልፀ እናንተም ትበላላቜሁ።
ዚምትበሉትም ለአንድ ቀን ወይም ለ2 ቀን ወይም ለ5 ቀን ወይም ለ10 ቀን ወይም ለ20 ቀን አይደለምፀ
ኹዚህ ይልቅ በአፍንጫቜሁ እስኪወጣና እስኪያንገፈግፋቜሁ ድሚስ ወር ሙሉ ትበላላቜሁፀ ምክንያቱም በመካኚላቜሁ ያለውን ይሖዋን ትታቜኋልፀ እንዲሁም “ኚግብፅ ዚወጣነው ለምንድን ነው?” በማለት በፊቱ አልቅሳቜኋል።’”
ኚዚያም ሙሮ እንዲህ አለ፩ “እኔ በመካኚሉ ዹምገኘው ሕዝብ 600,000 እግሚኛ ወንዶቜ ያሉበት ነውፀ አንተ ደግሞ ‘ሥጋ እሰጣ቞ዋለሁፀ ወር ሙሉ እስኪጠግቡ ይበላሉ’ ትላለህ።
በጎቹና ኚብቶቹ ሁሉ ቢታሚዱ እንኳ ይበቃቾዋል? ዚባሕር ዓሣዎቜ ሁሉ ቢያዙስ ሊበቃቾው ይቜላል?”
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን “ለመሆኑ ዹይሖዋ እጅ አጭር ነው? እንግዲህ ያልኩት ነገር ይፈጾምልህ እንደሆነና እንዳልሆነ ታያለህ” አለው።
ሙሮም ወጥቶ ዹይሖዋን ቃል ለሕዝቡ ተናገሚ። እንዲሁም ኚሕዝቡ ሜማግሌዎቜ መካኚል 70 ሰዎቜን ሰብስቊ በድንኳኑ ዙሪያ እንዲቆሙ አደሚገ።
ኚዚያም ይሖዋ በደመና ወርዶ አነጋገሚውፀ በሙሮ ላይ ኹነበሹውም መንፈስ ወስዶ በ70ዎቹ ሜማግሌዎቜ ላይ አደሚገ። እነሱም ወዲያው መንፈሱ እንዳሚፈባ቞ው እንደ ነቢያት አደሚጋ቞ውፀ ሆኖም ዳግመኛ እንደዚያ አልሆኑም።
በዚህ ጊዜ ኚሰዎቹ መካኚል ሁለቱ በሰፈሩ ውስጥ ቀርተው ነበር። ስማ቞ውም ኀልዳድና ሞዳድ ነበር። እነዚህ ሰዎቜ ምንም እንኳ ወደ ድንኳኑ ባይሄዱም ስማ቞ው ኚተመዘገቡት ሰዎቜ መካኚል ስለነበሩ መንፈሱ በእነሱም ላይ ወሚደ። በመሆኑም እነሱም በሰፈሩ ውስጥ እንደ ነቢያት ሆኑ።
አንድ ወጣትም እዚሮጠ በመሄድ “ኀልዳድና ሞዳድ በሰፈሩ ውስጥ እንደ ነቢያት እዚሆኑ ነው!” ሲል ለሙሮ ነገሚው።
በዚህ ጊዜ ኚወጣትነቱ ጀምሮ ዹሙሮ አገልጋይ ዹነበሹው ዹነዌ ልጅ ኢያሱ “ጌታዬ ሙሮ ሆይ፣ እነዚህን ሰዎቜ ኹልክላቾው እንጂ!” ሲል ተናገሚ።
ሙሮ ግን እንዲህ አለው፩ “ስለ እኔ ተቆርቁሹህ ነው? አትቆርቆርፀ ዹይሖዋ ሕዝቊቜ በሙሉ ነቢያት ቢሆኑና ይሖዋ መንፈሱን ቢሰጣ቞ው እንዎት ደስ ባለኝ!”
በኋላም ሙሮ ኚእስራኀል ሜማግሌዎቜ ጋር ወደ ሰፈሩ ተመለሰ።
ኚዚያም ነፋስ ኹይሖዋ ዘንድ ወጥቶ ድርጭቶቜን ኚባሕሩ እዚነዳ በማምጣት በሰፈሩ ዙሪያ በተና቞ውፀ ድርጭቶቹም ዚአንድ ቀን መንገድ ያህል በአንድ በኩል፣ ዚአንድ ቀን መንገድ ያህል ደግሞ በሌላ በኩል በሰፈሩ ዙሪያ ሁሉ ተበትነው ነበርፀ መሬት ላይም ሁለት ክንድ ኚፍታ ያህል ተቆልለው ነበር።
ሕዝቡም በዚያን ዕለት ቀኑን ሙሉና ሌሊቱን ሙሉ እንዲሁም በማግስቱ ቀኑን ሙሉ ድርጭቶቹን ሲሰበስብ ዋለ። ኚአሥር ሆሜር ያነሰ ዹሰበሰበ አልነበሚምፀ ዹሰበሰቧቾውንም በሰፈሩ ዙሪያ አሰጧ቞ው።
ሆኖም ሥጋውን ገና ሳያኝኩት፣ በጥርሳ቞ው መካኚል እያለ ዹይሖዋ ቁጣ በሕዝቡ ላይ ነደደፀ ይሖዋም ሕዝቡን ክፉኛ ፈጀ።
እነሱም ሲስገበገቡ ዚነበሩትን ሰዎቜ በዚያ ስለቀበሯ቞ው ዚቊታውን ስም ቂብሮትሃታባ አሉት።
ሕዝቡም ኚቂብሮትሃታባ ተነስቶ ወደ ሃጌሮት ተጓዘፀ በሃጌሮትም ተቀመጠ።
ኚመቅሰፍቱ በኋላ ይሖዋ ሙሮንና ዚካህኑን ዚአሮንን ልጅ አልዓዛርን እንዲህ አላቾው፩
“ኹመላው ዚእስራኀል ማኅበሚሰብ መካኚል ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዹሆናቾውን በዚአባቶቻ቞ው ቀት ቁጠሩፀ በእስራኀል ዹጩር ሠራዊት ውስጥ ገብተው ማገልገል ዚሚቜሉትን ሁሉ ቁጠሩ።”
በመሆኑም ሙሮና ካህኑ አልዓዛር ኚኢያሪኮ ማዶ በዮርዳኖስ አጠገብ በሚገኘው ዚሞዓብ በሹሃማ ሜዳ ላይ ለሕዝቡ እንዲህ ሲሉ ተናገሩፊ
“ይሖዋ ሙሮን ባዘዘው መሠሚት ዕድሜያ቞ው 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዹሆናቾውን ቁጠሩ።” ኚግብፅ ምድር ዚወጡት ዚእስራኀል ልጆቜ ዚሚኚተሉት ነበሩፊ
ዚእስራኀል ዚበኩር ልጅ ሮቀልፀ ዚሮቀል ልጆቜ እነዚህ ነበሩፊ ኹሃኖክ ዚሃኖካውያን ቀተሰብ፣ ኹፓሉ ዚፓላውያን ቀተሰብ፣
ኚኀስሮን ዚኀስሮናውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚካርሚ ዚካርማውያን ቀተሰብ።
ዚሮቀላውያን ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 43,730 ነበሩ።
ዹፓሉ ልጅ ኀልያብ ነበር።
ዚኀልያብ ልጆቜ ደግሞ ነሙኀል፣ ዳታን እና አቀሮን ነበሩ። እዚህ ላይ ዚተጠቀሱት ዳታን እና አቀሮን ቆሬና ግብሚ አበሮቹ በይሖዋ ላይ ባመፁበት ወቅት ኚእነሱ ጋር በማበር በሙሮና በአሮን ላይ ዚተነሱ ዚማኅበሚሰቡ ተወካዮቜ ነበሩ።
ኚዚያም ምድር አፏን ኚፍታ ዋጠቻ቞ው። ቆሬም እሳት ወርዶ 250 ሰዎቜን በበላ ጊዜ ኚነግብሚ አበሮቹ ሞተ። እነሱም ዚማስጠንቀቂያ ምሳሌ ሆኑ።
ይሁንና ዚቆሬ ልጆቜ አልሞቱም።
ዚስምዖን ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚነሙኀል ዚነሙኀላውያን ቀተሰብ፣ ኚያሚን ዚያሚናውያን ቀተሰብ፣ ኚያኪን ዚያኪናውያን ቀተሰብ፣
ኚዛራ ዚዛራውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚሻኡል ዚሻኡላውያን ቀተሰብ።
ዚስምዖናውያን ቀተሰቊቜ እነዚህ ሲሆኑ እነሱም 22,200 ነበሩ።
ዚጋድ ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኹጾፎን ዚጞፎናውያን ቀተሰብ፣ ኹሃጊ ዚሃጋውያን ቀተሰብ፣ ኚሹኒ ዚሹናውያን ቀተሰብ፣
ኹኩዝኒ ዚኊዝናውያን ቀተሰብ፣ ኚኀሪ ዚኀራውያን ቀተሰብ፣
ኚአሮድ ዚአሮዳውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኹአርዔላይ ዚአርዔላውያን ቀተሰብ።
ዚጋድ ልጆቜ ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 40,500 ነበሩ።
ዚይሁዳ ልጆቜ ኀር እና ኩናን ነበሩ። ሆኖም ኀር እና ኩናን በኹነአን ምድር ሞቱ።
ዚይሁዳ ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኹሮሎም ዚሎሎማውያን ቀተሰብ፣ ኚፋሬስ ዚፋሬሳውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚዛራ ዚዛራውያን ቀተሰብ።
ዚፋሬስ ልጆቜ እነዚህ ነበሩፊ ኚኀስሮን ዚኀስሮናውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኹሃሙል ዚሃሙላውያን ቀተሰብ።
ዚይሁዳ ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 76,500 ነበሩ።
ዚይሳኮር ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚቶላ ዚቶላውያን ቀተሰብ፣ ኹፑዋ ዚፑዋውያን ቀተሰብ፣
ኚያሹብ ዚያሹባውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚሺምሮን ዚሺምሮናውያን ቀተሰብ።
ዚይሳኮር ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 64,300 ነበሩ።
ዚዛብሎን ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩፊ ኚሰሬድ ዚሰሬዳውያን ቀተሰብ፣ ኚኀሎን ዚኀሎናውያን ቀተሰብ እንዲሁም ኚያህልኀል ዚያህልኀላውያን ቀተሰብ።
ዚዛብሎናውያን ቀተሰቊቜ እነዚህ ነበሩፀ ኚእነሱም መካኚል ዚተመዘገቡት 60,500 ነበሩ።
ዚዮሎፍ ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ው ምናሮና ኀፍሬም ነበሩ።