text
stringlengths
707
989
### Text: 1 2019 31 2019 ነገር ሲደጋገም ይሰለቻል ግን እውነታው ይሄ ነው በተመላላሽ ህክምና ክፍል የጡት ካንሰር እንዳለባቸው የሚነገራቸው ሴቶች ቁጥር ቀላል አይደለምአይነተኛ የጡት ካንሰር ምልክቶችን የማያውቁ ነገሩ ከረፈደ በኋላ ወደጤና ተቋማት የሚመጡ ሴቶች ቁጥር ቀላል አይደለምየጡት ካንሰር0የሞት ፍርድ እንደሆነ የሚያስቡ ሴቶች ቁጥር ቀላል አይደለምነገር ሲደጋገም ይሰለቻልግን ማህበራዊ ገጾችን ትምህርት ልንሰጣጥባቸው እንችላለንነገር ሲደጋገም ይሰለቻልግን እርስዎም ሀላፊነት አለብዎት ነገር ሲደጋገም ይሰለቻል ግን ቮልቴር እንዳለው ላላደረጉት መልካም ነገር ሁሉ ወዳጄ ሆይ ተጠያቂ ነዎት እናም ይስሙ ላልሰማም ያሰሙየጡት ካንሰር በጡት የሚገኙት ህዋሳት ከቁጥጥር ውጪ በሆነ መልክ ሲራቡ የሚፈጠር ነው፡፡ በሀገራችን በሴቶች ላይ ከሚፈጠሩ የካንሰር አይነቶች የጡት ካንሰር አንደኛ ደረጃውን ይይዛል፡፡ አጋላጭ ሁኔታዎች ተብለው ሊጠቀሱ የሚችሉ ነገሮችጾታ ከወንዶች ይልቅ ሴቶች 99 ፐርሰንት ያህል የመያዝ እድል አላቸው እድሜ በለጋ እድሜ ያሉ ማለትም ከ20 አመት በታች ያሉ ተጋላጭነታቸው ያነሰ ሲሆን እድሜ በጨመረ ቁጥር በበሽታው የመያዝ እድል ይጨምራል፣ በቤተሰብ ያለ የጡት ካንሰር የተለያዩ በቤተሰብ የሚተላለፉ የዘረመል ግድፈቶች ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ ይችላሉተጨማሪ ያንብቡ 10143 ሼር ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች ቻይና ባለፉት 24 ሰዓት ተጨማሪ 22 አዲስ ኬዞችን ሪፖርት አድርጋለች። ሀያ አንዱ 21 ከውጭ የገቡ ናቸው። በኳታር ተጨማሪ 643 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 12564 ደርሷል። በኢራን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 93657 ደርሷል ባለፉት 24 ሰዓት 1073 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል በተጨማሪ 80 ሰዎች ሞተዋል። በስፔን የሟቾች ቁጥር ከትላንት ጨምሯል ባለፉት 24 ሰዓት 325 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። በጣልያን የሟቾች ቁጥር ከትላንት ቀንሷል ባለፉት 24 ሰዓት 323 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር ከ27000 በላይ ሆኗል። በሩሲያ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች በፍጥነት እየጨመረ ነው በአንድ ቀን 5841 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 99399 ደርሰዋል። በኩዌት በአንድ ቀን ተጨማሪ 300 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 60000 ደርሷል። የጊኒ ቢሳዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ኑኖ ጎሜዝ ና ቢያም የኮሮና ቫይረስ ምርመራ አድርገው በቫይረሱ መያዛቸውን የሀገሪቱ ፐብሊክ ጤና ሚኒስትር አንቶኒዮ ዲዩና በብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ አስታውቀዋል በዓለም አቀፍ ደረጃ የሟቾች ቁጥር ከ220413 ደርሷል 984425 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል 3173410 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። ### Response:
### Text: በትላንትናው ዕለት ከጋምቤላ ከተማ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ30 አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ 5 ግለሰቦች በከፈቱት ተኩስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የጋምቤላ ክልል የሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቱት አስታወቁ።ጉዳቱን ተከትሎ በከተማው በተከሰተው ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።በግጭቱ ባጠቃላይ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አምስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሷል ብለዋል።ጥፋተኞቹን ወደህግ ለማቅረብ የፀጥታ አካላት ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።ከግጭቱ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አስር የሚደርሱ ግለሰቦች ቀደም ብሎ በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ተገቢውን ማጣራት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።ግጭቱ በተፈጠረበት በጋምቤላ ከተማ ያለው ሰላም ወደ ነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅ ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።ከጋምቤላ ከተማ ወደ ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲገቡ ተደርጓል ለጊዜው በፀጥታ አካላት እጀባ እንዲሄዱ እየተደረገ ነው ብለዋል።መረጃው የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው ### Response:
### Text: የተሰረዘው የአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ነገ ይወጣል።በቅርቡ በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ምክንያት ተሰርዞ የነበረው የአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ በነገው ዕለት እንደሚወጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።በጉዳዩ ላይ በምከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ቢሮ ሃላፊ ያስሚን ወሀቢረቢ እና የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሽመልስ ታምራት ዛሬ በሰጡት መግለጫ የተናገሩት ነገ 25 ሺህ 791 የ4060 እና 2080 ቤቶች ዕጣ ይወጣባቸዋል። በነገው እጣ 146 ሺህ 892 እስከ የካቲት 21 ቀን 2014 ዓም ድረስ በቂ ቁጠባ ያላቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ይሳተፋሉ። በነገው እጣ አወጣጥ ነባርና በ2005 ዓም በባለሶስት መኝታ ቤት የተሰሩ 300 ቤቶችም ይተላለፋሉ። በእጣ አወጣጡ ላይ ከዚህ ቀደም የገጠሙ ችግሮች እንዳይደገሙ አዲስ የእጣ አወጣጥ ስርዓት ተዘርግቷታ። የመረጃ ማጥራት እና ማደራጀት ስርዓቱ ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ ተከናውኗል። የእጣ ማውጫ መተግበሪያውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ያለማው ሲሆን ከፌደራል ተቋማት እና ከከተማ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የእጣ አወጣጡ በቆጣቢዎች የቅድመ ግምገማ ወይም የእጣ አወጣጥ ሙከራ የተካሄደበት ነው። ነገ ከሰዓት ላይ የሚካሄደው የእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱም በቴሌቪዠን በቀጥታስርጭት ይተላለፋል። ኤፍ ቢ ሲ ### Response:
### Text: አይካ አዲስ ስራ አቆመ️በቱርካውያን ባለሃብቶች በሠበታ ከተማ የተቋቋመው አይካ አዲስ የጨርታ ጨርቅ ፋብሪካ ከትናንት ጀምሮ ሥራ ማቆሙን ለሠራተኞቹ አስታወቀ፡፡4000 አራት ሺ የሚሆኑ የፋብሪካው ሠራተኞች ከረብዕ ጀምሮ የሥራ ማቆም አድማ ላይ የሠነበቱ ሲሆን አርብ ጠዋት ወደ ፋብሪካው ሲመለሱ በማስታወቂያ ቦርድ ላይ ሳይሰራ የሚከፈል ደሞዝ ስለሌለ፣ ፋብሪካው ለጊዜው ስራ አቁሟል የሚል ማስታወቂያ ተለጥፎ፣ ሠራተኛው እንዲመለስ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡የፋብሪካው ባለቤት ቱሪካዊው ዩሱፍ ሃይዲኒ ፋብሪካውን ጥለው ከተሠወሩ ከ6 ወር በላይ መሆኑን የገለፁት ሠራተኞች ፋብሪካውን የሚያስተዳድረው ልማት ባንክ ነው የሚል መረጃ እንደደረሳቸው ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ፋብሪካውን የሚያስተዳድረው አካል በውል እንደማይታወቅ ተናግረዋል፡፡ሠራተኛው የስራ ማቆም አድማ ላይ የሰነበተውም የፋብሪካው የወደፊት እጣ ፈንታና የስራ ዋስትናችን ይረጋገጥልን በሚል ጥያቄ እንደነበር የገለፁት ሠራተኞቹ ከአርብ ጀምሮ ግን ፋብሪካው ላልተወሰነ ጊዜ ስራ ማቆሙ በማስታወቂያ እንደተገለፀላቸው ተናግረዋል፡፡ላለፉት 6 ወራት የፋብሪካው መደበኛ ስራ ተቀዛቅዞ መቆየቱን የጠቆሙት ሠራተኞቹ ይሁን እንጂ ሠራተኛው የሚያገኘው ወርሃዊ ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም አልተቋረጠም ነበር ብለዋል፡፡ምንጭ አዲስ አድማስ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ነው ፕር ያዕቆብ አርሳኖበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ኢትዮጵያ ታላቁን የህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በመሆኑ የሙሌት ጉዳይ ብዙ የሚያነጋግር እንዳልሆነ ገለፁ።ፕሮፌሰር ያዕቆብ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት ቃል ሁለተኛው ዙር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ጉዳይ ኢትዮጵያውያን እና የዓለምን ፖለቲከኞች ቀልብ በእጅጉ የሳበ ክስተት ነው ብለዋል።በተለይ ግብጽና ወደግብጽ ተለጥፋ ያልተገባ ጭቅጭቅ ውስጥ የምትገኘው ሱዳን በተነዙ የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎችና እና አሳሳች መግለጫዎች የተነሳ የህዳሴው ግድብ ሁለተኛው እርከን ሙሌት በተጋነነ ወሬ ውስጥ ነበር ሲሉ ገልፀዋል።መታወቅ የነበረበትም ሆነ አሁንም መታወቅ ያለበት ጉዳይ ኢትዮጵያ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት መሆኑ ነው ሲሉ አስገንዝበዌ።ይህ እንደሚሆን ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት ጥናት እና ዲዛይን ፣ በድርድሩ ሂደት ፣ በግድቡ ግንባታ ስራና በየጊዜው በሚወጡ በኢትዮጵያ መንግስት መግለጫዎች መገለጹን አስታውሰዋል። ኢፕድ ### Response:
### Text: ፑራቶስ የኢትዮጵያን ገበያ ተቀላቀለ።ፑራቶስ ኢትዮጵያ ዛሬ በአዲስ አበባ የገነባውን ልዩ የፈጠራ ማዕክል ማስመሩቁን ለቲክቫህ በላከው መልዕክት አሳውቋል።ፑራቶስ ኢትዮጵያ ዛሬ ያስመረቀው ወሎ ሰፈር አካባቢ ያስገነባውን የዳቦ፣ ኬክና ሸኮሌት ግብዓት ማምረቻ ፋብሪካ እና ልዩ የምግብ ፈጠራ ማዕከል ነው።የኩባንያው ዋና ስራ አፈፃሚ ዶሚኒክ ኤድዋርዶ በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ባሰሙት ንግግር በዓለም ላይ የታወቀው ፑራቶስ የንግድ ስያሜ የኢትዮጵያን ገበያ በመቀላቀሉ ደስታ እና ኩራት እንደተሰማቸው ገልፀዋል።ዋና ስራ አስፈፃሚው አዲሱ ፋብሪካ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት የፈጠራ ማዕከል እያደገ የመጣውን የደንበኞችን የጥራት ፍላጎት ለማሟላት ቁልፍ ነው ብለዋል።ፑሩቶስ ኢትዮጵያ ሀገር ውስጥ ያሉ የኬክና ዳቦ ባለሞያዎች፣ ዓለም አቀፍ ሆቴሎች ፣ ሱፐር ማርኬቶች እና ሬስቶራንቶችን የሚያገለግል ሲሆን በተጨማሪ የጅቡቲ ፣ ሱዳን ፣ ሱማሊያ እና ኤርትራ ሃገራትን ፍላጎት ለማሟላት ዕቅድ እንዳለው ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል።ፑሩቶስ በእኤአ 1919 ቤልጂየም ውስጥ የተቋቋመ ባለቤትነቱ የቤልጂየም የሆነ የምግብ አቀናባሪ ሲሆን በዓለም ዙሪያ ከ100 በሚበልጡ ሀገራት ውስጥ ቅርንጫፍ አለው በአሁን ሰዓት በአፍሪካ ኬንያ፣ ናይጄሪያ፣ ደአፍሪካ እና አይቮሪኮስት ውስጥ እየሰራ ይገኛል። ### Response:
### Text: ብሄራዊ ቤተ መንግስት️የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመና የቀድሞው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዳኜ መላኩ አሸኛኘት ተደረገላቸው፡፡በዝግጅቱ ላይ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው፣ እርሳቸውም የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድም ዶክተር ሙላቱ ላበረከቱት ያልተቆጠበ የዲፕሎማሲና የመሪነት ሚና ምስጋና አቅርበዋል አዲስ ወደ ስልጣን የመጡ ተሿሚዎች ለአርዓያነት የሚበቃ ስራ እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ሀገራቸውን በማገልገላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይም ባላቸው ልምድ መንግሥትን ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡በብሔራዊ ቤተ መንግሥት በተዘጋጀው የእውቅና እና ክብር ልዩ ፕሮግራም ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከፍተኛ ኒሻንና የክብር ዲፕሎማ አቶ ዳኜ መላኩ ደግሞ የምስጋና ወረቀትና ሜዳልያ ተበርክቶላቸዋል፡፡በዝግጅቱ ላይ የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንቶች፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የተፎካካሮሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: በአንደኛው ሟች ኪስ ውስጥ ተጨማሪ ያልፈነዳ ቦንብ ተገኝቷል ፖሊስአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንበልደታ ክከተማ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ የቦንብ ፍንዳታ የሁለት ግለሰቦች ህይወት ማለፉን የአዲስ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ ነው በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ከሚትሮሎጂ ፊት ለፊትለልማት በተዘጋጀ ቦታ ላይ በተከሰተ የቦንብ ፍንዳታ የሁለት ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ያለፈው።በፍንዳታው አንድ ግለሰብ በፅኑ ተጎድቶ ወደ ሆስፒታል መሄዱን ፖሊስ አሳውቋል።በልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መርማሪ ኢንስፔክተር ዳንኤል ታፈሰ የምርመራ መዝገብ ዋቢ አድርገው ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ አንድ በግምት ዕድሜው ከ50 እስከ 55 የሚገመት ግለሰብ ከሁለት በተመሳይ የዕድሜ ደረጃ ላይ ከሚገኙ 2 ሴቶች ጋር እየተገፈታተረ ወደቦታው ከገባ በኋላ ፍንዳታ ተሰምቷል ጉዳት ደርሷል። የግለሰቦቹ ማንነት እና የፍንዳታው ምክንያት ለማወቅ በምርመራ ሂደት ላይ ነው።በሠዓቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የፌደራል ፖሊስ የቴክኒክ እና የፈንጂ አምካኝ ባለሙያዎች ቦታው ላይ ፈጥነው በመድረስ ተጨማሪ ፍንዳታ እንዳይከሰት አካባቢውን ነፃ የማድረግ ስራ መስራታቸው ተገልጿል።ፖሊስ በአንደኛው ሟች ኪስ ውስጥ ተጨማሪ ያልፈነዳ ቦንብ መገኘቱን አሳውቋል። ### Response:
### Text: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ዕረፍትን በማስመልከት አባታዊ የሐዘን መልዕክት አስተላለፉ።ቅዱስነታቸው የትህትና፣ የጸሎት ሕይወት እና የመልካምነት ምሳሌ የነበሩት ብፁዕ አባ ሰላማ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የሰማነው በታላቅ ሐዘን ነው። ብለዋል። ያለንበትን ፈተና የበዛበት ዘመን በጸሎት የሚያሻግሩ አባቶችን ማጣት0 ቤተ ክርስቲያንን የሚጎዳ ቢሆንም በቅዱስ መጽሐፍ ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ መኖር የሚችል ማን ነው እንደተባለ ሰው በምድር ላይ የሚኖርበት ዘመን በእግዚአብሔር ዘንድ የተቆጠረ እና የተለካ በመሆኑ ብፁዕነታቸው ሃይማኖትን ጠብቀውና መልካሙን ገድል ፈጽመው ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር በክብር ተሸጋግረዋል ሲሉ ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው በዕረፍተ ሥጋ ከእኛ በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘን ቢሰማንም በሰማይ የሚጠብቃቸውን ክብር እያሰብን እንጽናናለን ብለዋል።ቅዱስ ፓትርያርኩ የብፁዕነታቸውን ነፍስ በቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት አጠገብ ያሳርፍልን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውም መጽናናትን ያድልልን ብለዋል። ### Response:
### Text: የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል️በአርባምንጭ ከተማ ዛሬ ጠዋት ላይ በደረሰ የመኪናአደጋ የ5 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ የአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምኢንስፔክተር አባሃጅጉጆ እንደገለጹት የካቲት 192011 ዓም ጠዋት 2 ሰዓት ላይ በአርባምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3 53362 ኢት የሆነ ሲኖ ትራክ መኪና እና ኮድ 415376 ኢት የሆነ ፒካፕ መኪና ከፍጥነት ወሰን በላይ ሲያሽከረክሩ በተፈጠረ አደጋ እስከ አሁን የ5 ሠዎች ሕይወት አልፏል፡፡በቦታው ከነበሩ አይን እማኞች በተገኘ መረጃ አደጋው የተፈጠረው በፍጥነት ሲያሽከረክር የነበረው የሲኖ ትራክ አሽከርካሪ ባለ 3 እግር ባጃጅን ለማትረፍ የቀኝ መስመሩን ትቶ ወደ ግራ በመታጠፍ ፒካፕ መኪናን በመግጨት ከመስመር ያስወጣው ሲሆን በእግረኛ መንገድ ስትጓዝ የነበረች የ13 ዓመት ሕጻንን ጨምሮ በፒካፕ መኪናው ውስጥ የነበሩ 3 ተሳፋሪዎች ሕወታቸው አልፏል፡፡ይሕ በእንዲህ እንዳለ የሲኖ ትራክ አሽከሪው በፀፀት ራሱን ከመብራት ታዎር ላይ በመጣል ሕይወቱ ማለፉን ምኢንስፐክተር አባሃጅ ገልጸው በአደጋው ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል፡፡አሽከርካሪዎች ከተፈቀደ ፍጥነት ወሰን በላይ ባለማሽከርከር በሰው ሕይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ መቀነስ እንደሚጠበቅባቸው የከተማው ፖሊስ አዛዥ ምኢር አባሃጅ ጉጆ አሳስበዋል፡፡ ### Response:
### Text: በሕገ ወጥ መንገድ በቡድን ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኮሚሽኑ ገለፀ፡፡ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን በቡድን በሕገ ወጥ መንገድ የነበሩ ተጠርጣሪዎች፣ መሳሪያና ገንዘብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።በዞኑ ጎዛምን ወረዳ ጭምት በተባለ ቀበሌ ሐምሌ 262011ዓም ነው በሕገ ወጥ መንገድ በቡድን መሳሪያ ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 14 ሰዎችን እና ለጊዜው መጠኑ በግልፅ ያልታወቀ ከፍተኛ ገንዘብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙዩኒኬሽን እና ሚዲያ ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ሰኢድ አህመድ ለአብመድ የገለፁት።ተጠርጣሪዎቹ 4 የጦር መሳሪያ ሁለት ክላሸንኮቭ፣ አንድ አብራራው እና አንድ መትረየስ እና ቁጥሩ ለጊዜው በውል ያልታወቀ በርካታ ገንዘብ ይዘው መገኘታቸውንም ረዳት ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል።በሕገ ወጥ መሳሪያው ምን ሊያደርጉበት ነበር ስለሚለው ጉዳይ አሁንም ተጨማሪ ምርመራዎች እየተደረጉ መሆኑንም ረዳት ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። የኅብረተሰቡን ተደጋጋሚ የሰላም ይከበርልን ጥያቄ ለመመለስ በየደረጃው ያለ የክልሉ የፀጥታ ኃይል የክልሉን ሠላም እና ደኅንነት ለማስከበር በሰፊው እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አስታውቀዋል። ኅብረተሰቡም ትብብሩን እንዲያጠናክር ረዳት ኮሚሽነር ሰይድ ጠይቀዋል፡፡ ### Response:
### Text: የቴፒ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት በፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ሀዘኑን ገልፆ ለደረሰው ጉዳትና እና ህዝብ ላይ ለደረሰው በደል ይቅርታ ጠይቋል።የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ ዛሬ በከተማው በነበረ የሰላም ኮንፈረንስ መድረክ ላይ ንግግር አድርገዋል።ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ ባሰሙት ንግግር ባለፉት ዓመታት በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸው ለደረሰው ጉዳናት፣ የህዝብ በደል ይቅርታ ጠይቀዋል።ከመለያየትና መቃቃር ለውጥ እንደማይመጣ ያነሱት ከንቲባው በመፈቃቀርና በመቻቻል ከሠራን ቴፒ ከተማ እንዲሁም ዞኑ ለሁሉም ይበቃል ብለዋል።በቴፒና አካባቢዋ ሠላም እንዲሰፍን ከፍተኛ ሚና ለተወጡ ባለድርሻ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።በሌላ በኩል በዛሬው ዕለት የጦር መሳሪያ ታጥቀው ጫካ ሸፍተው ከነበሩት ውስጥ ሁለቱ የታጠቁትን መሣሪያ ለፀጥታ ኮማንድ ፖስት አስረክበው በህዝቡ ፊት ቀርበው ይቅርታ ጠይቀው ከህዝቡ ጋር መቀላቀላቸው ተገልጿል።ሌሎችም በዚህ መልኩ የታጠቁትን ለኮማንድ ፖስቱ በሠላም እያስረከቡ ከህዝቡ ጋር እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቀርቧል።ተጨማሪ የዛሬው የሰላም ኮንፈረንስ በተመለከተ ከደቡብ ምዕራብ ክልል ኮሚኒኬሽን የተገኘውን መረጃ በዚህ 1204 መመልከት ይቻላል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኢሰመኮ፣ ከየካቲት 4 ቀን 2015 ዓም ምሽት ጀምሮ በተለያዩ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የተፈጸሙ እስሮችን በተመለከተ የአዲስ አበባን፣ የፌዴራል እና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስና የጸጥታ አካላት፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጽሕፈት ቤትን፣ ምስክሮችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በማነጋገር እንዲሁም በአዲስ አበባ የተለያዩ ማቆያ ቦታዎችን በመጎብኘት ክትትል በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አሳውቋል።የተወሰኑ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች በፍርድ ቤት ወይም በፖሊስ ጣቢያ ዋስትና እየተለቀቁ መሆናቸውን ኮሚሽኑ ያረጋገጠ ቢሆንም አሁንም ብዙ ሰዎች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ በተለያየ ዓይነት ወንጀል ተጠርጥረዋል በሚል ዋስትናም ተከልክለው በእስር ላይ ይገኛሉ ተብሏል።ከተፈጠረው ሁኔታ ጋር ተያይዞ የዚህ ዓይነቱ እስር የዘፈቀደ እስር ሊሆን ስለሚችል የመንግሥት የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር አካላት በሙሉ በበቂ ምክንያት በወንጀል የተጠረጠረን ሰው በሕጉ መሠረት ሰብአዊ መብቶችን ያከበረ በተለይም በቅድመ ምርመራ ወቅት የዋስትና መብት አጠባበቅ ሥርዓትን ባከበረ መንገድ ምርመራ ከማድረግ ውጪ ተገቢ ያልሆነ እስር እንዲያስወግዱ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶር ዳንኤል በቀለ አሳስበዋል፡፡ ### Response:
### Text: በትግራይ ሰሜን ምእራብ ዞን ታሕታይ ቆራሮና ዛና ወረዳዎች ከባድ ነጎድጓድና ዝናብ ተከትሎ የወደቀ መብረቅ አራት ሰዎችና ሰባት የቤት እንስሳት መግደሉ ተገልፀ። አደጋው የደረሰው በታሕታይ ቆራሮ ወረዳ ቀላቕልና በዛና ወረዳ ዋልካ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነው። በወረዳው ቀላቕል በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር የወደቀው መብረቅ የ18 የ23 የ47 እድሜ ያላቸው ሶስት ሰዎችና ሰባት የቤት እንስሳት ፣ በዛና ወረዳ ዛና ዋልካ ቀበሌ የ15 ዕድሜ እንስት መግደሉ የቀበሌው አስተዳዳሪ አቶ ብርሃነ ገመድህን ገልፀዋል ሲል የ ጋዜጠኛ ኪማርያም በርሃነ ከቦታው ዘግቧል።0000000000000000000000000 በሌላ በኩል በዛው ዞን የኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ ትራንስፎርመር ውስጣዊ አካል የሰረቁ ሶስት ተጠርጣሪዎች እጅ በፈንጅ ተይዘወል።ተጠርጣሪዎቹ ስርቆቱ የፈፀሙት በዞኑ ላዕላይ ቆራሮ ወረዳ መስሕል በተባለ ቀበሌ የሚገኝ የትራንስፎርመር ውስጣዊ አካል ነው። ተጠርጣሪዎቹ ነሃሴ 82015 ዓም ሰርቆቱ ፈፅመው በባጃጅ ጭነው ወደ ሽረ ከተማ ሲጓዙ በህዝብና በፀጥታ አካላት ትብብር እጀ ከፍንጅ ተይዘዋል። የላዕላይ ቆራሮ የፀጥታ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገየሱስ በየነ በአከባቢው ለነበረው የ ቴሌሺዥን ጋዜጠኛ እንደጠቆሙት ተጠርጣሪዎቹ ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው ጥረት የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ ነው ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል። ### Response:
### Text: ጄፍሪ ፌልትማን ኢትዮጵያ ይገኛሉ።የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጄፍሪ ፌልትማን ዳግም ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ከዚህ ቀደም ተገልጾ ነበር።ፌልትማን በአሁን ሰዓት ኢትዮጵያ የሚገኙ ሢሆን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ውይይት አድርገዋል።አቶ ደመቀ መኮንን ህወሃት በሰሜን ዕዝ ላይ ስላደረሰው ጥቃት እንዲሁም ቡድኑ እየፈጸማቸው ያለው አስከፊ ድርጊቶች አሁን ለተፈጠረው ችግር መዳረጉን ገልጸዋል።ህወሓት በአሁኑ ወቅት በአፋርና በአማራ ክልሎች ግልጽ ወረራ ፣ ዝርፊያ እና ግድያ በማካሄድ ከፍተኛ ሰብዓዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ወንጀሎችን እየፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል።ህወሓት እነዚህን ሁሉ ወንጀሎች እና ክህደት በሚፈጽሙበት ጊዜ የአሜሪካ መንግስት ዝምታን መርጧል ብለዋል። ይህ በሁለቱ ወንድማማች ሀገራት ግንኙነት ውስጥ ያልተለመደና የሁለቱን የወንድማማች ሀገሮች ግንኙነት የማይመጥን ነው ብለዋል። አቶ ደመቀ አሜሪካ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በሚመጥን መልኩ የወራሪ ኃይሎችን አጥፊ ድርጊቶች እንደምትኮንነው ኢትዮጵያ ተስፋ ታደርጋለች ብለዋል።ቡድኑ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ቀጠናውን እያወከ መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአንክሮ ሊገነዘበው ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለዋል።ያንብቡ 0817 ### Response:
### Text: ከአርባ ምንጭ️ጤና ይስጥልኝ ፀግሽ ነኝ ከአርባ ምንጭ አስካሁን የክረምት በጎ ፍቃድ አልጀመርንም ለምን እንዳልተጀመረ ለመጠየቅ ከተማ አስተዳደር ብንሄድም ከከተማዋ ከንቲባ በተላለፈ ትዛዝ የቁም ከመባሉ በስተቀር ምናቀው ምንም ነገር የለም ነው ሚሉን የከተማውን ከንቲባን ለማናገር በተደጋጋሚ ወደ ከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ብንሄድም በስብሰባ ላይ ናቸዉ እያሉ ለሁለት ሳምንት ከማመላለስ በስተቀር ትክክለኛ ምላሽ ሚሰጠን አካል አላገኘንም ከተማዋ በምትገኝበት ጋሞ ጎፋ ዛን የሚገኙ ወረዳዎች ስራው እየተሰራ በዛኑ ዋና ከተማ የማይሰራበት ምክኒያት ግልፅ አልሆነልንም ወጣቱ ባለዉ አቅም ከተማዋን ለማገልገል ዝግጁ ቢሆንም የሚያሰራው አካል ባለማግኘቱ በጣም ነው ያዘንነው እኛ ከተማዋን ና ህብረተሰቡን በማገልገል ከምናገኘው እርካታ ባሻገር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተራችን ዶር አብይ አሕመድ እንደተናገሩት ከአገልግሎት በሁዋላ የሚሰጠን የምስክር ወረቀት ስራ በምንቀጠር ወቅት እንደ ስራልምድ እንደሚቆጠረ ሰምተናል። ይህን የበጎ አድራጎት ስራ መስራት ካልቻልን ወደ ስራ ፍለጋ በምንሰማራበት ወቅት እኛ የአርባምንጭ ከተማ ወጣቶች ከሌላው የኢትዮጵያ ወጣቶች ቀርቶ ከዛኑ ወጣቶች ጋር መፎካከር አያስችለንም ይህንን ጉዳይ የሚመለከተው አካል አይቶ መፍትሔ እንድሰጠን እንጠይቃለን አመሰግናለሁ። ### Response:
### Text: አብንየአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን በቅርቡ በሚካሄደው የህዝብና የቤት ቆጠራ ላይ ስጋት እንዳለው ገለጸ። የፊታችን መጋቢት በሚካሄደው አገር አቀፍ የህዝብና ቤት ቆጠራ ላይ ከፖለቲካዊ ተጽዕኖ ነጻ መሆን መቻል አለበት ሲል አብን የገለጸው መጪውን የህዝብና ቤት ቆጠራ አስመልክቶ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነው።የፓርቲው ሊቀመንበር ዶር ደሳለኝ እንዳሉት በመጪው መጋቢት 292011 የሚካሄደው 4ኛው ዙር አገር አቀፍ የህዝብና የቤት ቆጠራ በትክክል እንዲካሄድ ህዝቡ በንቃት መሳተፍና ውጤቱንም መከታተል እንዳለበት ገልጸዋል።ዶክተር ሲሳይምስጋናው በጎንደር ዩኒቨርሰቲ የስነ ህዝብ መምህር እንዳሉት ከዚህ በፊት የተደረጉ ቆጠራዎች በርካታ ችግሮች እንደተስተዋሉባቸው በውይይቱ ላይ ባቀረቡት ጥናታዊ ፅሁፍ ጠቁመዋል።ከዚህ በፊት በተካሄዱ የህዝብና የቤት ቆጠራ የተስተዋሉ ህጸጾች በቀጣዩ ቆጠራ ወቅት እንዳይደገሙ ምሁራን ህዝቡን ማንቃት እዳለባቸው እንዲሁም የአማራ ህዝብም ሁኔታዎችን በንቃት መከታተል እንዳለበት ሊቀመንበሩ አሳስበዋል።የህግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ውብሸትሙላት የህዝብና የቤት ቆጠራ ከህግ ማዕቀፍ በሚል ርዕስ የሌሎችን አገሮች ተሞክሮ በማጣቀስ በአገራችን የሚደረግ ቆጠራ በገለልተኛ አካል መካሄድ እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡ምንጭ ኢፕድ ### Response:
### Text: በራይድ እና ዛይ ራይድ መካከል ውዝግብ ተነስቷል በራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት እና ዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መካከል ከንግድ ስም ባለቤትነት እና ከፈጠራ ባለቤትነት መብቶች ጋር በተያያዘ በተነሳው ውዝግብ ራይድ ባቀረበው አቤቱታ መሰረት በንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ምርመራ ተጀመረ።ከአራት ወራት በፊት ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት የስያሜው የባለቤትነት መብት ይገባኛል በሚል ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት እና ለንግድ ውድድር እና ሸማቾች መብት ጥበቃ ባለሥልጣን ማመልከቻ ማስገባቱን ተከትሎ ነው ምርመራው የተጀመረው።ራይድ የሚለው ቃል በራሱ አገልግሎትን የሚያመላክት ገላጭ ቃል እንጂ ስያሜ መሆን የሚችል ቃል አይደለም ያሉት የዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀብታሙ ታደሰ፣ ከራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት ከአንድ ዓመት ቀድመው ወደ ሥራ መግባታቸውን እና በዘርፉ መጀመሪያው መሆናቸውንም ይናገራሉ።የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ለራይድ ከአንድ ዓመት በፊት የንግድ ስያሜ ባለቤትነት ማረጋገጫ መፍቀዱ አግባብ ያልሆነ መሆኑን እያወቅን፣ ያለው ገበያ ሰፊ መሆኑን ተከትሎ አብሮ ለመሥራት እና ለመነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም ሲሉም ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግረዋል።ተጨማሪ ያንብቡ 09243 ምንጭ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ ተጨማሪ 129 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧልባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5274 የላብራቶሪ ምርመራ 129 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3759 ደርሷል።ቫይረሱ የተገኘባቸው 79 ወንድ እና 50 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ1 እስከ 70 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው።ቫይረሱ የተገኘባቸው 85 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 11 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣ 10 ሰዎች ከሱማሌ ክልል፣ 7 ሰዎች ከደቡብ ክልል፣ 6 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 5 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 4 ሰዎች ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደት እና 1 ሰው ከአፋር ክልል ናቸው።ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርመራ ውስጥ 18 11 ከጤና ተቋም እና 7 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ናሙና የለም።ከዚህ ባለፈ ሁለት 2 በህክምና ማዕከል ውስት ህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸውና ህይወታቸው የለፈ ሰዎች ቁጥር ስልሳ ሶስት 63 ደርሷል።ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ዝርዝር ሁኔታ 1 የ60 ዓመት ወንድ የድሬዳዋ ነዋሪ በህክምና ማዕከል በህክምና ላይ የነበሩ።2 የ30 ዓመት ወንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ በህክምና ማዕከል በህክምና ላይ የነበረ። ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 75 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል ከነዚህ ውስጥ 16 ከለገጣፎ፣ 15 ከቢሾፍቱ፣ 11 ከአዳማና 11 ከምስራቅ ሸዋ ይገኙበታል። በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 19 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል13 ሰዎች ንክኪ ያላቸው፣6 ሰዎች የጉዞ ታሪክ ያላቸውና 3 ሰዎች የጉዞ ታሪክና ንክኪ የሌላቸው ናቸው። በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 19 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 181 ደርሰዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ባለፉት 24 ሰዓት አንድ ሰው በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል። አጠቅላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 219 ደርሰዋል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል ከነዚህ መካከል 14 ሰዎች ከሰሸዋ ዞን ናቸው። በክልሉ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 607 ደርሰዋል። በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 8 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 291 ደርሰዋል። በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 6 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል በቫይረሱ መያቸው የተረጋገጠው ሰዎች ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች አይደሉም። በአዲስ አበባ ባለፉት 24 ሰዓት 329 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 13826 ደርሰዋል። በኢትዮጵያ ከተመዘገበው 7 ሞት ስድስቱ 6 በአአ ከተማ የተመዘገበ ነው 5 ከአስክሬን ምርመራና 1 ከጤና ተቋም ### Response:
### Text: የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በጀት️የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2011 በጀት ዓመት ከፌደራል መንግስት የተመደበ በጀት1 መደበኛ በጀትተቁ የበጀት ኮድ የተመደበለት የሥራ ክፍል የተመደበ በጀት መጠን ምርመራ1 3820101 የበላይ አመራር1074953002 3820201 ለመማር ማስተማር2229163003 3820202 ለተማሪ አገልግሎት798598004 3820302 ለምርምር ህትመት126644005 3820301 ለጥናትና ምርምር 15195006 3820401 ለማህበረሰብ አገለግሎት 988679007 3820402 ለህክምና አገለግሎት 47546800ጠ ድምር 570 870 0002 ካፒታል በጀትተቁ የበጀት ኮድ የተመደበለት ፕሮጀክቶች የተመደበ በጀት መጠን ምርመራ1 01001 ለነባር ፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ755694002 01002 ለዋናው ግቢ ላቦራቶሪ ግንባታ379113003 01004 ለዋናው ግቢ ስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራ ግንባታ15192700401007 ለመማሪያ ክፍልና ላይብረሪ ግንባታ 332345005 01008 ለዶርሚታሪና መምህራን ካፍቴሪያ ግንባታ ማጠናቀቂያ638197006 01009 በዋናና ኦቶና ካምፓስ መምህራን መኖሪያ ግንባታ 44564500701012 ለተርጫ ካምፓስ ፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ 1111074008 01013 ለተማሪዎች መመገቢያ ሕንጻ ግንባታ ማጠናቀቂያ 25531700 ጋንዳባ9 01014 ለኦሞቲክና አባላ ምርምር ማዕከል ግንባታ 1671850010 01015 ለኦቶና ካምፓስ አር ሕንጻ ግንባታ ማጠናቀቂያ 225204001101016 ለኦቶና ካምፓስ ክልኒክ ግንባታ 3 829900ጠድምር 450000 000ማጠቃለያመደበኛ በጀት 570 870 000ካፒታል በጀት 450 000000ጠድምር 1020870000ምንጭ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ### Response:
### Text: 4 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለመገንባት የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ነው አራት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለመገንባት የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ገለጸ። ኮርፖሬሽኑ በፓርኮች ግንባታና ምርት ዙሪያ ከምሁራን፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የሙያ ማህበራት ጋር ተወያይቷል። ውይይቱ በኢትዮጵያ በመስኩ እየተካሄደ ያለው እንቅስቃሴ፣ እየተገኙ ያሉ ውጤቶችና ችግሮች ላይ ያተኮረ ነው።የኮርፖሬሽኑ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ሺፈራው ሰለሞን እንደተናገሩት አሁን ካሉት ኢንዱስትሪ ፓርኮች በተጨማሪ አራት ፓርኮችን ለመገንት የሚያስችል ጥናት እየተከናወነ ነው። አሶሳ፣ አረርቲ፣ አይሻና ሰመራ ከተሞች ላይ ለመገንባት እንደታቀደ ጠቁመው በተለይ ሰመራ ላይ የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት መሻሻልን ተከትሎ የወደብ አማራጭ በመኖሩ የተሻለ እንቅስቃሴ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል። አሶሳ ላይ ደግሞ የቀርከሃ ምርት በስፋት በመኖሩ ለቢሮ፣ ለቤት እቃዎችና መርከብ ግንባታ የሚሆን ግብዓት ለማምረት የሚያስችል የኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት እየተጠና መሆኑን ጠቁመዋል። በቀርከሃ ምርት ለመሰማራት ቻይናዊያን ባለሃብቶች ከፍ ያለ ፍላጎት ማሳየታቸውን ገልጸዋል። የጥናት ሂደቱ እንደተጠናቀቀ በውጤቱ መሰረት ወደ ግንባታ ይገባል ብለዋል። ### Response:
### Text: ነሃሴ 92012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 3448 የላብራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 202 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 32 አአ ከተደረገ ምርመራ 22 ቡራዩ 18 ጉጂ ዞን 18 ገላን 17 ምዕራብ ሸዋ 14 ሞጆ 14 ቢሾፍቱ 12 ሰበታ ይገኙበታል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 645 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 1 ከአሶሳ ዞን አሶሳ ወረዳ 1 ከመተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ 1 ከብልዲግሉ ወረዳ በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 453 የላብራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 13 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።አጠቃላይ በአፋር 409 በቫይረሱ የተያዙ ያገገሙ 191 በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 1384 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 196 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧልአጠቃላይ በትግራይ 1688 በቫይረሱ የተያዙ 11 ሞት 764 ያገገሙ ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 352 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 19 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ሁሉም ከማህበረሰቡ በተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 703 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 75 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 265 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 12 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል። 6 ጅግጅጋ 4 ሞያሌ 2 ጎዴ ### Response:
### Text: ለጅቡቲ ጉምሩክ ደብዳቤ ፅፈናል የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽንበጅቡቲ ጉምሩክ የወደብ ጭነት መዘግየት ችግር የተፈጠረ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አሳውቋል።የጂቡቲ ጉምሩክ ከ20 ሺህ ዶላር በታች የክፍያ ደረሰኝ የያዙ ጭነቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዳያልፉ በሚል መመሪያ እቃዎች እንዳይንቀሳቀሱ እንዳገደ ተነግሯል።የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዘርይሁን አሰፋ በሰጡት ቃል በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ለጅቡቲ ጉምሩክ ደብዳቤ መፃፉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እቃዎችን በጂቡቲ ወደብ በኩል የምታዘዋውር መሆኑን ተከትሎ መሰል ችግሮች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ ይጠበቃል ያሉት አቶ ዘርይሁን እቃ አስመጭዎች ለደረሰባቸው ችግር ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ስራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል። በጂቡቲ 2 ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አሉን ያሉት ዳይሬክተሩ ችግሩ የሚያሳድረው ተጽእኖ ከፍተኛ በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚሻ አስረድተዋል፡፡0 ችግሩ ከ3 ሳምንታት በላይ ያስቆጠረ መሆኑን ተከትሎ ጭነቶች ወደብ ላይ በሚቆዩበት ወቅት ከሚከፈለው ገንዘብ መጠን ጋር ተያይዞ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን አስረድተዋል።ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአሐዱ ኤፍ ኤም 943 ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ያሳውቃል። ### Response:
### Text: ጠቅላይ ሚንስትሩ ትላንት በፓርቲዎች ቃልኪዳን ሰነድ ፊርማ ስነስርዓት ላይ ካስተላለፉት መልዕክት1 ህገ መንግስት የሚሻሻለው በስምምነት ብቻ እንደሆነ ያ ካልተቻለ እያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ ሰጠተውበት አብላጭ ድምፅ ያገኘው ሃሳብ ገዥ እንደሚሆን አስምረው ተናግረዋል።የአንድ ሀገር ህገ መንግስት የመላው ሀገሪቷ እንጂ የአንድ አከባቢ ፍላጎት ብቻ እንደማይሆን እና የትም ሀገር ሁሉም ዜጋ በሁሉም ነገር ላይ ተመሳሳይ አቋም ሊኖረው እንደማይችል አከለው ገልፀዋል።2 አብዛኛዎቹ ዋናዋና ፓርቲዎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የራሳቸው ሚዲያ እንዳላቸው እና እነዚህን ሚዲያዎች በስርዓት እንዲንቀሳቀስ የማድረግ ኃላፍነት እንዳለባቸው አክለው ተናግረዋል።በእሳቸው በኩል ፣ፋና ፣ ዋልታ እና ሌሎችም ስርዓት ይዘው እና ህግን ተከትለው መስራት እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።3 አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዬት እንዳመጡ ባይታወቅም ብዙ ሃብት በሀገ ወጥ መልኩ እንዳከበቱ በመጠቆም ጊዜው የችግግር ጊዜ ስለሆነ ለበጎ ዓላማ እና ለሀገር ግንባታ የሚያውሉት ከሆነ ሰደው ማሰደድ ውስጥ እንደማይገቡ አስታውቀዋል። ነገር ግን አንዳንዶች ይህንን ገንዘብ ተጠቅመው ህዝቡን በዘር እና በሃይማኖት ለማባላት ምልክት እያሳዩ ነው። እሄንን ዝም ብሎ ማየት እንደሚከብድ የሚያሳይ ንግግር አድርገዋል። ### Response:
### Text: ከዚህ በኃላ ውሳኔ፣ ማዕቀብ፣ ተፅእኖ የሚባለው ባዶ መዝሙር ነው አምባሳደር ዲና ሙፍቲበአውሮፓ ህብረት እንዲሁም በአሜሪካ ይቀርቡ የነበሩት ቅሬታዎች መፍታት እንደተቻለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባዳደር ዲና ሙፍቲ በትላንት መግለጫቸው ተናግረዋል።እንደ አምባሳደር ዲና ገለፃ ይቀርቡ ከነበሩ ቅሬታዎች መካከል የመጀመሪያው ወደትግራይ እንዳንገባ በሩን ዘግታችሁብናልአልተፈቀደልንም፣ ህዝቡ ተቸግሯል ፣ ተፈናቅሏል ፣ ተርቧል ፣ ሱዳን የገባ አለ ገብተን እንዳንረዳ ተደርገናል ሲሉ ነበር ግቡ ተብሎ በር ተከፍቷልፍቃድም ተሰጥቷል ሲሉ ገልፀዋል።በሁለተኛ ደረጃ ሰብዓዊ መብት ጥሰት አለ ፣ የሴቶች መደፈር አለ፣ ግድያ አለ ፣ ዘረፋ አለ ፣ ቃጠሎ አለ ብለዋል ይሄንንም ነፃ በሆነ አካል ጭምር ማጣራት ይቻላል ብሎ የኢትዮጵያ መንግስት ፍቃደኝነቱን ገልጿል ብለዋል።ሶስተኛው ደግሞ የሰብዓዊ ድጋፍ ጠንክሮ ይቀጥል የሚል ሲሆን ብቻውን መንግስት 70 እየረዳ ነው ማንኛውም ድጋፍ ለማድረግ ለሚፈልግም በሩን ክፍት አድርጓል ብለዋል አምባሳደሩ።ይህ በተደረገበት ሁኔታ ከዚህ በኃላ ውሳኔ ፣ ማዕቀብ ፣ ተፅእኖ የሚለው ባዶ መዝሙር ነው ሲሉ ተናግረዋል ሲቀርቡ የነበሩት ምክንያቶች ስለሌሉ የአውሮፓ እና የአሜሪካ ተፅእኖ የሚባለው ነገር ሊኖርም አይችልም እየቀለለ ይሄዳል ነው ያሉት። ### Response:
### Text: በትግራይ ክልል ጦርነት ሲቀሰቀስ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ ሱዳን መግባታቸው ይታወሳል።እነዚህ ኢትዮጵያውያን ተፈናቃዮች በነበሩባቸው የሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የግዳጅ የውትድርና ምልመላ ይካሄድ እንደነበረ መረጃ እንዳለው የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ለቢቢሲ በሰጠው ቃል አሳውቋል።ተቋሙ ከወራት በፊት ከስደተኞቹ መካከል አንዳንድ ጊዜ በኃይል ጭምር ተዋጊዎችን ለመመልመል የሚደረጉ ጥረቶች እንደነበሩ ተአማኒ ሪፖርቶች 0 ደርሶኛል ብሏል ለቢቢሲ በሰጠው ቃል።ተቋሙ ይህን ካወቀ በኃላ ምን አደረገ የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ወታደራዊ ምልመላ መኖሩን እንደተገነዘብኩኝ ጉዳዩን ለሱዳን ማዕከላዊ መንግሥትና ለአካባቢ ባለሥልጣናት ስጋቴን ገልጫለሁ ብሏል።0 ይህንም ተከትሎ ሁኔታዎች የተሻሻሉ ይመስሉ ነበር ሲል መልሷል።ምልመላውን ማነው የሚያደርገው ይኸው የተመድ ተቋም ወታደራዊ ምልመላውን ለማካሄድ ከኢትዮጵያ የሚመጡ ሰዎች እንደነበሩ እና ይህንንም ከስደተኞች መረዳቱን ይገልጻል። ነገር ግን የትኛው ወገን ምልመላውን እንዳካሄድ ማረጋገጥ አልቻልኩም0 ብሏል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግሥት ሰደተኛ ነን ብለው ወደ ሱዳን የገቡ ሰዎች ድንበር ተሻግረው ከህወሓት ጋር በመሆን ሲዋጉ እንደነበር መግለፁ ይታወሳል።ያንብቡ 0907 ### Response:
### Text: የሰኔ 16ቱ ጥቃት️የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት የሰኔ 16ቱን የቦምብ ጥቃት አስተባብረዋል በሚል ወንጀል የተጠረጠሩት የብሄራዊ የመረጃና ደህንነት ባልደረባ የነበሩት አቶ ተስፋዬኡርጌ ላይ ፖሊስ የሚያደርገውን ምርመራ እንዲያጠናቅቅ የመጨረሻ ቀጠሮ ሰጠ፡፡ፖሊስ ችሎቱ በፈቀደለት 10 ቀናት የሰው ምስክር መቀበሉን ብሎም ከመስሪያ ቤታቸው የተገኘው ቦምብ ለምርመራ መወሰዱንና ሌሎች ተግባራትን ማከናወኑን ጠቅሷል፡፡ ለተጨማሪ የምርመራ ስራ 10 ቀናት እንዲፈቀድለትም ጠይቋል፡፡የሰኔ 16ቱን የቦምብ ጥቃት አስተባብረዋል በሚል ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በቁጥጥር ስር ከዋሉ 4 ወራት መቆጠሩንና ፖሊስ የሚጠይቃቸው የግዜ ቀጠሮዎች ተገቢነት የላቸውም በማለት ቅሬታችውን አቅርበዋል፡፡አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ቦምብ ከቤቴ ሳይገኝ ከቤቱ ተገኝቷል እያሉ በመዘገባቸው ሰብአዊ መብቴ ተነክቶብኛል የሚለውንም ጠቅሰዋልፍርድ ቤቱ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ለመጨረሻ ግዜ በማለት ትእዛዝ እንዲሰጥም አመልክተዋል፡፡ግራ ቀኙን የመረመረው ችሎቱ ከእውነታው ውጭ የሚዘግቡ መገናኛ ብዙሃን እንደሚጠየቁና ፖሊስ ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ የመጨረሻ ቀጠሮ በማለት 7 ቀናት በመፍቀድ ውጤቱን ለመጠባበቅ ለጥቅምት 12 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: የውድድር ማስታወቂያ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአይቢኤ ኢትዮጲያና ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ አህጉራዊ የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ንቅናቄ አፍሪካ ኢኖቬሽን ሳምንት በሚል ርዕስ ከጥቅምት 17 እስከ ጥቅምት 222012 ድረስ በአዲስ አበባ ያካሂዳል፡፡ስለሆነም ችግር ፈቺ ሀብት ፈጣሪና ወደ ምርትና አገልግሎት ሊቀየር የሚችል የፈጠራ ስራ ያላችሁ በዚህ አህጉራዊ መድረክ ላይ ሀገራችሁን ወክላችሁ እንድትወዳደሩና የፈጠራ ውጤቶቻችሁን ለውጭና ለሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ለቬንቸር ካፒታል ተቋማት እና ለሌሎች የፋይናስ ምንጮች በማስተዋወቅ ወደ ምርትና አገልግሎት እንድትቀላቀሉ ይጋብዛል፡፡0 ትኩረት የሚሰጣቸው ዘርፎች፡ 0ዘመናዊ0 ከተሞች እና አዳዲስ የመኖሪያ ቴክኖሎጂዎች0 0ዲጂታላይዜሽን የኢንተርኔት ንግድ ስርዓት የግብርና0 የጤናና የህክምና0 0ቴክኖሎጂ መስተንግዶና ቱሪዝም0 የማምረቻና እና የማዕድን ኢንደስትሪ ዘርፎች ተወዳድራችሁ ስራዎቻችሁን በኢኖቬሽን ሳምንቱ ማስተዋወቅ የምትፈልጉ አመልካቾች የፈጠራ ስራ ፕሮፖዛላችሁን በኢሜይል አድራሻችን 0 ላይ በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን0ለማመልከቻ ቅፁና ለተጨማሪ መረጃ ድረገፃችን 0 ይመልከቱ፡፡አልያም በስልክ ቁጥራችን 251118592039 ይደውሉ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር00 ሼር ### Response:
### Text: በሀገር አቀፍ ደረጃ ላለፉት አራት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ተጠናቋል፡፡ የፈተናው መጠናቀቅን ተከትሎ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደየመጡበት መመለስ ጀምረዋል። በሌላ በኩል ትላንት ታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ቀኑን ሙሉ በከባድ ተኩስ ስትናጥ እንደዋለች አንድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህር ገልፀውልናል።ከፍተኛ የሆነ የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ የነበረው በከተማ አቅራቢያ ላይ እንደነበር ጠቁመዋል።እሳቸው በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በሚገኝ የመምህራን መኖርያ ወስጥ እንደሚኖሩ አመልክተው በነበረው ግጭት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ብሔራዊ ፈተና የወሰዱት በጠዋቱ ፈረቃ ብቻ እንደነበር ገልጸዋል።ለፈተናው ከተቀመጡት ግማሾቹም ቢሆኑ ጥለው በመውጣታቸው እንዳልተፈተኑ አመልክተዋል።በትላንቱ የጎንደር ሁኔታ ከፍተኛ የሰው ጉዳቶችን እንደተመለከቱ የገለፁት መምህሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችም በከተማው በነበረው ሁኔታ ችግር ላይ ወድቀው እንደነበር ገልጸዋል።ቲክቫህ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ካለው የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ምን ይመስል እንደነበር ተማሪዎች እና መምህራን ላይ ስለደረሱ ጉዳቶች ከትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ ለማግኘት ጥረት ያደርጋል።ፎቶ ወላይታ ሶዶ፣ ወልድያ፣ ጅማ ፣ ዋቸሞ፣ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲዎች ### Response:
### Text: ጉባኤው ተጠናቋል 8ኛው የኦህዴድ መደበኛ ጉባኤ ባለ11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።ጉባኤው በኦሮሚያ ክልል በሰላም በልማት እና በማህበራዊ ዘርፎች ያለውን ለውጥ የበለጠ በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራትበሚቻልበት መንገድ ተወያይቷል።ጉባኤው መጠናቀቁን ተከትሎ ጋዜጣው መግለጫ የሰጡት የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሜቴ ጽቤት ኃላፊ ወይዘሮ አዳነች ሃቤቤ የኦሮሞ ህዝብ ሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ መሰረት ነው ብለዋል።የጽቤት ሃላፊዋ አያይዘውም ክልሉ ያለውን ራዕይ ሃገራዊ በማድረግ በአንድ መንፈስ የመስራት ባህል እንዲዳብርም ጥሪ አቅረበዋል።ጉባኤው ባለ11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡በአቋም መግለጫው ላይም፡ኪራይ ሰብሳቢነትን ከምንጩ ለማድረቅ ያስቀመጣቸውንአቅጣጫዎች ተግባራዊ ለማድረግጎሰኝነትንና አክራሪነትን ለመዋጋት ቁርጠኛ አመራሮችንለማፍራትየህዝቡን የልማት ጥያቄ መመለስ የሚችል ብቁ አመራርለመፍጠር የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ በማድረግ የአብሮነትና ሃገራዊ ስሜት በህብረተሰቡና እና በአመራሩ ዘንድ እንዲጠናከር ለማድረግ፣ የተጀመሩ የልማትና የፖለቲካ ውጤቶች ቀጣይነታቸውን እንዲኖር ለማረጋገጥናየኢኮኖሚ እድገቱ ፍትሃዊና ሁሉን አቀፍ እንዲሆን ለማድረግ ከአመራሩና ህብረተሰቡ ጋር ጠንክሮ እንደሚሰራ ኦህዴድ አስታውቋል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: አዲስ አበባ ዛሬ️1ዛሬም በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ስንደቅአላማ በመስቀልና የከተማዋን ጎዳናዎች በማቅለም ዙሪያ አለመግባባቶች ታይተዋል። አዲሱገበያ አካባቢ የኦነግን አርማ ይሰቀልይቀባ በሚሉና ቀድሞ የተሰቀለው አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ስንደቅ አናስነካም ባሉ ወጣቶች መካከል ግብ ግብ ተነስቶ ፖሊስ ጣልቃ ገብቷል። በአስለቃሽ ጭስ ወጣቶቹን መበተን ያቃተው ፖሊስ ጥይት ወደ ስማይ ተኩሷል ። ኋላም በዶፍ ዝናብ ምክንያት ወጣቶቹ ተበትነዋል ።2የአዲስ አበባ ወጣቶችም ሆኑ የኦነግ ደጋፊዎች ከጠብ አጫሪነት እንዲቆጠቡ ይህ ካልሆነ ግን ፖሊስ የህዝቡን ደህንነት ለማስከበር እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ኮምሽነር ዘይኑ ጀማል አስታወቁ። ባለፉት ሁለት ቀናት ለንብረት ውድመት ምክንያት የሆኑ ግጭቶች መከሰታቸውንና ሁኔታው ተባብሶ በፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጉዳት ለማድረስ ሙከራ መደረጉን የተናገሩት ኮምሽነር ዘይኑ ማናቸውም ዜጋ ያመነበትን የፖለቲካ ድርጅት አርማ ይዞ የመውጣትና ተገቢ በሆኑ አካባቢዎች የመስቀል መብቱ የተከበረ ሲሆን፣ ጎዳናዎችንና የጋራ መገልገያዎችን ቀለም መቀባት ግን ተገቢ አለመሆኑን አስረድተዋል።3 የኦነግ አቀባበል ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ የድርጅቱ ደጋፊዎች ከግጭት እራሳቸውን በማራቅ በሰላማዊ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ አሳስቧል ። ምንጭ ዋዜማ ራድዮ ### Response:
### Text: ኒፕሲ ሐስል ተገደለ️ትውልደ ኤርትራዊው የሎስ አንጀለሱ ታዋቂ ራፐር፣ ኤርምያስአስገዶም ኒፕሲ ሐስል በተከፈተበት ተኩስ ሎስ አንደለስ ውስጥ መገደሉን የአሜሪካ መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል።የ33 ዓመቱ ራፐር በርካታ ቦታዎች ላይ በጥይት መመታቱን እና ሆስፒታል እንደደረሰ ሕይወቱ ማለፉን ሎስ አንጀለስ ታይምስ ዘግቧል። ሌሎች ሁለት ሰዎችም በተተኮሰባቸው ጥይት ቆስለዋል ።ከኤርትራዊ አባት እና ጥቁር አሜሪካዊ እናት የተወለደው ኤርሚያስ አስገዶም በዚህ ዓመት ለሽያጭ ያበቃው አልበሙ በግራሚ የምርጥ ራፕ አልበሞች ምርጫ ላይ እጩ ለመሆን በቅቶ ነበር።ሞቱ ካስደነገጣቸው ታዋቂ ሰዎች መካከል አንዷ ሪሃና ስትሆን በዚህ ዜና መንፈሴ ታውኳል ስትል የቲውተር ገጿ ላይ አስፍራለች።ኤርሚያስ አስገዶም ተወልዶ ያደገው በደቡባዊ ሎስ አንጀለስ ሲሆን በተለያዩ የማህበረሰብ አቀፍ ስራዎችና በኪነጥበብ ስራዎች ላይ በመሳተፍ ይታወቃል።ያደኩት በውንብድና ቡድኖች ውስጥ ነው ሲል ለሎስ አንጀለስ ታይምስ በአንድ ወቅት ቃለ መጠይቅ ሰጥቶ ነበር ሞት፣ ግድያ የየእለት ትዕይንቶቻችን ነበሩ። በጦርነት ቀጠና ውስጥ እንደመኖር ነው ከዚህ መንደር ሰዎች ሲሞቱ ከቁብ አይቆጠርም ነበር።ኤርሚያስ ከመገደሉ በፊት በነበረ አንድ እሁድ አምርሮ የሚጠላህ ሲኖር መባረክ ነው በማለት በቲውተር ገፁ ላይ አስፍሯል። ### Response:
### Text: መስጂድ አሰሪው አባ እና የክርስቲያኖች ተንከባካቢው ሼህ ወዳጅነት በጋዜጠኛ ወንድሙ ሃይሉ ሸገር ኤፍ ኤምአባ ቅዱስ ቁርዓንን ጠንቅቀው ያውቃሉ፣ ሼሁም መፅሐፍ ቅዱስን ያነባሉ አሉ፡፡ አባ አክሊለ ማርያም በአዲስ አበባ መስጂዶች እየተዘዋወሩ ለምስራቅ ሐረርጌው የላንጌ ቢላል መስጂድ መስሪያ 300 000 ብር አሰባስበዋል፡፡ ወዳጃቸው ሼህ አህመድ ነጃሺ ኡስማንም እንደ መስጂዱ ሁሉ የቤተ ክርስቲያን እና የክርስቲያኖች ነገር አይሆንላቸውም፣ ለክርስቲያኖች አባታዊ ምክር የሚለግሱ ናቸው።መልዐከ ሕይወት ቆሞስ አባ አክሊለ ማርያም በኢኦተቤተ ክርስቲያን አገልጋይ፣ በምስራቅ ሐረርጌ፣ ሐረር ዙሪያ ቀርሳ ወረዳ የላንጌ ቢላል መስጂድ አሰሪ ኮሚቴ አባል ናቸው፡፡ ሼህ አህመድ ነጃሺ ኡስማን ደግሞ የላንጌ ቢላል መስጂድ እና መድረሳ ኢማም፣ የቀርሳ ወረዳ ቅዱስ ራጉኤል ምዕመናን ወዳጅ፣ ደጋፊ እና ተንከባካቢ ናቸው፡፡አባ አክሊለ ማርያም እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ሁሉ የመስጂዱ እና የሙስሊሞች ነገር አይሆንላቸውም፡፡ ሼህ አህመድ ነጃሺ ኡስማን ደግሞ እንደ መስጂዱ ሁሉ የቤተ ክርስቲያ እና የክርስቲያኖች ነገር አይሆንላቸውምአባ ቅዱስ ቁርዓንን ጠንቅቀው ያውቃሉ፣ ሼሁም መፅሐፍ ቅዱስን ያነባሉ አሉ፡፡ ሰው በፈጣሪው አምሳል ተፈጥሯል በፈጣሪ ፍቅርም ሊተሳሰር ይገባል ባይ ናቸው ሁለቱም፡፡ ሼር ### Response:
### Text: ኤጀንሲው የሰነድ ማረጋገጫ ማህተም አሰራርን ቀየረ።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ እየተበራከተ የመጣውን ሰነድ አስመስሎ የመስራት ወንጀል ለመቀነስ ኤጀንሲው በሚሰጣቸው የልደት፣ የጋብቻ ፣ የፍቺ ፣ የያላገባ እንዲሁም ሌሎች ማስረጃዎች አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረውን የማረጋገጫ አሰራር በዘመናዊ አሰራር በመተካት ፎርጀሪ እያደረሰ ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳት ለመቀነስ የበኩሉን ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አሳውቋል።ተቋሙ በዋና መስሪያ ቤት የሚሰጠውን ለፖስፖርት አገልግሎት፣ ለውጭ ሃገራት የቪሳ ጥያቄ ፣ ለተለያዩ የውጭ እና የሃገር ውስጥ ጉዳዮች የሚውሉ ማስረጃዎች የሚረጋገጥበትን የቀድሞ የማህተም አሰራር በማስቀረት በውጭ ሃገር አሰርቶ ባስገባው ዘመናዊ የሆሎግራም ማረጋገጫ አሰራር ከዛሬ ህዳር 13 2014 ዓም ጀምሮ በመተካት ተግባራዊ ያደርጋል። ይህ አሰራር ከፖስፖርት እና ከውጭ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ በየቦታው ተመሳስሎ በመስራት ለማለፍ የሚሞከሩ ሌብነቶች ኤጀንሲውን እንዳያልፉ እገዛ የሚያደርግ እንደሚሆን ታምኖበታል። በተያዘው በጀት ተቋሙ የሚሰጣቸውን ሰርተፍኬቶች የደህንነት ደረጃ ከፍ ለማድረግ አዲስ የ ቴክኖሎጂ ባላቸው ፕሪንተሮች ለመተካት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።ምንጭ ወኩምመኤጀንሲ ### Response:
### Text: በአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር ሮበርት ሜንዴዝ የቀረበው 3199 ረቂቅ ህግ ዛሬ ማለፉ ተሰምቷል።ኮሚቴው በኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲ ለማበረታታ በሚል ርዕስ የቀረበው 3199 ላይ ተወያይቶ ማማሻያ ካደረገ በኃላ ነው ማሳለፉ የታወቀው።የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ግንኙነት ኮሚቴ ተመልክቶ ያሳለፈው 3199 ረቂቅ ህግ በጠቅላላ የምክር ቤቱ አባላት እንዲፀድቅ የሚመራ ሲሆን ህግ ሆኖ ለመውጣት የህግ አውጪው ምክር ቤት ድምፅ እና የፕሬዜዳንቱን ፊርማ ማግኘት አለበት።3199 ረቂቅ ህግ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበው ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ላይ ሲሆን ከዚህ ረቂቅ ጎን ለጎንም 6600 የተሰኘ በኢትዮጵያ መረጋጋት፣ ሰላምና ዴሞክራሲ ለማስፈን በሚል ርዕስ የቀረበ የውሳኔ ሃሳብ በህግ አውጪው ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ እንዲያየው መላኩን ቪኦኤ ዘግቧል።የኢትዮጵያ ምክትል ጠሚ አቶ ደመቀ መኮንን ሊፀድቁ በመንገድ ላይ ናቸው የተባሉት 3199 እና 6600 ኢትዮጵያን ከሌሎች አገራት ጋር የሚኖራትን የጸጥታ፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ግንኙነት በሌሎች ኃይሎች በጎ ፈቃድ እንዲንጠለጠል እና ራሷን የማትከላከል ሽባ አገር የሚያደርጋት በመሆኑ በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ረቂቅ ህጎቹ እንዳይፀድቁ ከፍተኛ ዘመቻ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል። ### Response:
### Text: ከአርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ባባ ስርዓተ ቀብር ጋር በተያያዘ ካሜራ ይዘው ቪድዮ ለመቅረፅ እና በየማህበራዊ ሚዲያው ለማስራጨት የሚሞክሩ ከድርጊታቸውን እንዲታቀቡ ስርዓተ ቀብሩን ለማስፈፀም የተቋቋመው ኮሚቴ አሳስቧል።ከኮሚቴው አባላት አንዱና የአርቲስቱ የቅርብ ወዳጅ ዲጄ ቢቢ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር በተለይም ፌክ ኒውስ፣ የተለያዩ ቪድዮ እየቀረፁ ፣ ፎቶዎችን እያነሱ ርዕስ እየሰጡ የሚለጥፉ አሉ ወጣቶቻችን ታናናሾቻችን በዚህ ላይ ጥንቃቄ ያድርጉ። ብሏል።ትላንት የስርዓተ ቀብሩ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በአርቲስት ታሪኩ ባባ መኖሪያ ቤት በነበሩበት ሰዓት ካልተጠበቁ ሰዎች ቪድዮ ተቅርፆ ርዕስ እየሰጡ በቲክቶክ በማህባዊ ሚዲያ ላይ ሲለጥፉ እንደነበር ይህም የአካባቢውን ልጆች ፣ አብሮ አደጎቹንና የኮሚቴውን አባላት እንዳስደነገጠ ገልጿል።ወጣቶች እንዲያህ ያለውን ነገር እንዳያደርጉ ሲልም ጥሪ አቅርቧል።የአርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ባባ ስርዓተ ቀብር ለማስፈፀመው በወጣው መርሃ ግብር ዛሬ ጥዋት 500 ላይ በብሄራዊ ትያትር አዳራሽ የሽኝት ፕሮግራም ይኖራል ፕሮግራሙ ላይ የሞያ አጋሮቹ፣ ጓደኞቹ ፣0 የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ይገኛሉ።ከዚህ በኃላ ከቀኑ 900 ሰዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት ይፈፀማል። ### Response:
### Text: በሀዋሳ እና በወላይታ ሶዶ ከተማ ያለምንም ጥፋታቸው ያለምንም በደላቸው ህይወታቸውን ባጡት ወንድም እና እህቶቼ የተሰማኝን መሪር ሀዘን ለመግለፅ እወዳለሁ። የሞቱት ኢትዮጵያዊያን ናቸው። ብሄራቸው ምንም ሊሆን ይችላል የሞቱት ወንድሞቻችን እህቶቻችን ናቸው። ማንም ብሄሩን መርጦ አልተወለድም ባነሰ አስተሳሰባቸው የሰው ህይወት እንዲጠፋ ላደረጉት ፈጣሪ የእጃቸውን ይሰጣቸዋል። ሜዳ ላይ የፈሰሰው ምንም በደል የሌለበት ምንም ወንጀል ያልሰራ ንፁህ የለፍቶ አደር ኢትዮጵያዊ ደም ነው። ሀዘኑ የወላይታ የሲዳማ ህዝብ ብቻ አይደለም ሀዘኑ የመላው ኢትዮጵያዊ ነው። የፈሰሰው ደም ቀይ ነው ብሄር አልተፃፈበትም። የንፁህ የወንድሞቻችንን ነብስ ፈጣሪ በገነት ያኑረው። ሁሉም የስራውን ያገኛል የንፁሀንን ደም አደባባይ ላይ ያፈሰሱት በግፍ የሰዎችን ቤት የዘረፉት ያቃጠሉት ሳይውሉ ሳያድሩ የእጃቸውን ያገኛሉ። ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን እመኛለሁ ለተጎዱት ፈጣሪ ምህረቱን ይላክላቸው። ሀዋሳ ላይ የፈሰሰው የኔ ደም ነውሶዶ ላይ የፈሰሰው የኔ ደም ነውበየትኛውም የምድር ክፍል ማንነት ላይ ያነጣጠረን ጥቃት እቃወማለሁየሲዳማ እና የወላይታ ህዝብ አንድነት ዛሬም ይቀጥላልወድ ኢትዮጵያዊያን ሊያባሉን ለተነሱት የሀገራችን ጠላቶች እድል ልንሰጥ አይገባም። ፍቅር ያሸንፋል ### Response:
### Text: 9167 የአጭር የስልክ መስመር 0115527110 የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ስልክ ቁጥር የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር እስካሁ ከ300 ያላነሱ የመቐለ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር መረጃ እንዲለዋወጡ መደረጉን አስታውቋል።የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን አሊ በክልሉ ከሚገኙ አለም አቀፍ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል የሚገኙ ተማሪዎችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማገናኘት እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።እስካሁን ድረስ መቐለ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ከ300 በላይ ተማሪዎችን ደህንነት የሚገልፅ የሰላምታ መልክቶች በመቀበል ለቤተሰቦቻቸው ማስተላለፍ መቻሉን ዶር ሰለሞን ጠቁመዋል፡፡በሚቀጥሉት ጊዚያት በክልሉ ውስጥ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተማሪዎች ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተና የሰላምታ መልክቶችን በመቀበል ለቤተሰቦቻቸው የማድረስ ሂደቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።ዶር ሰለሞን የተማሪ ወላጆች ተረጋግተው በፅናትና በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስበዋል፡፡በ9167 የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የአጭር የስልክ መስመር ላይ የተማሪ ወላጆች ተጨማሪ ማብራሪያ መረጃ ማግኘት ይችላሉ ብለዋል። በተጨማሪ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ስልክ ቁጥር 0115 52 71 10 እና በ 9167 መረጃ መጠየቅ ይችላሉ ሲሉ ለአሃዱኤፍኤም 943 ሬድዮ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: ከ5 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስገልገዋል የአማራ ክልል መንግስትየአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስታና ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ኮሚሽን በክልሉ ህወሓት ወረራ በፈፀመባቸው ዞኖች ማለትም ሰሜን ወሎ ደቡብ ወሎ ከፊል ደቡብ ጎንደር ዋግኽምራ ውስጥ የሚኖሩ እና ተፈናቅለው ያሉትን ጨምሮ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ሲል አሳውቋል።ህወሓት በከፈተው ጦርነት ከ991 ሺ በላይ ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን በወረራ በተያዙ አካባቢዎች ደግሞ ከ5 ሚሊዮን ህዝብ በላይ አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል እነዚህ ነዋሪዎች ለምግብ እጦት ፣ የመጠጥ ውሃ እና የመድሃኒት እጦት ችግር ተጋልጠዋል።በሰሜን ወሎ ሜቄት አካባቢ ብቻ በህክምና እጦት 90 ሰዎች የሞቱ ሲሆን በተመሳሳይ የወለሊድ አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት 13 እናቶች ሞተዋል።በጋዝጊብላና በዝቋላ አካባቢ በመድሃኒት እጥረት ፣ በምግብ እጦት 13 ሰዎች ሞተዋል።በአጠቃላይ በወረራ ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች ቤታቸውን እንደዘጉ በምግብ እና በመድሃኒት እጦት ሞተው የሚገኙበት ሁኔታ ነው እየተፈጠረ ያለው።ከላይ የተገለፀው ቁጥር ሙሉ አይደለም ከዚህ በጣም ሊጨምር ይችላል በየአካባቢው የመንግስት መዋቅር በመፍረሱ በምግብ እና በህክምና እጦት የሞቱ አጠቃላይ ሰዎችን ቁጥር ማወቅ አልተቻለም። ### Response:
### Text: በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚለውን አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ እንቅስቃሴን በዛሬው እለት ተቀላቅለዋል የዛሬው ሰላማዊ ሰልፍ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ እያደረገች ያለውን ጫና ለመቃወም እንደሆነ የፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ገልፀዋል የዛሬው ሰልፍ የተጠራው በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሲሆን የሰልፉ አላማም በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ በተመሳሳይ ቀን የሚካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ አንዱ አካል ነው በማለት የሰልፉ አስተባባሪዎች አስታውቀዋል እዚህ ሰልፍ ላይ ለመሳተፍ ከጠዋቱ ጀምሮ በተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ግዛቶች በተዘጋጁ ትራንስፖርቶች ወደ ጆሃንስበርግ ያቀኑ ኢትዮጵያውያን ኤርትራውያን እና አንዳንድ ሌሎች የአፍሪካ ሃገራት በርካታ ዜጎች በሰልፉ ላይ ተሳትፈዋል በሰልፉ ላይ የተኙት በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን በአሜሪካ መንግስት እና በምዕራቡ አለም ሚዲያዎች ላይ ጠንከር ያለ ተቃውሞ አሰምተዋል በተጨማሪ 29 ደግሞ በተባበሩት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ማህበር አስተባባሪነት የተጠራ የተቃውሞ ሰልፍ በድጋሚ በደቡብ አፍሪካ እንደሚኖር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ፎቶ የኛ ሰው ሚዲያ እና ከማህበራዊ ሚዲያ ገፆች የተሰባሰበ ### Response:
### Text: ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ️ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በያዝነው የትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲው የሚመጡ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፊታችን ጥቅምት 10 እስከ 12 ወደ ዩኒቨርሲቲው የሚገቡ ተማሪዎችን ይቀበላል፡፡ ለዚህም ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አረጋግጧል፡፡የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶር ፍሬውተገኘ እንደተናገሩት ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅት ተደርጓል፡፡ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ልክ እንደ ወላጆቻቸው ቤት እንዲቆጥሩት እና በቆይታቸውም እንዲደሰቱ ለማድረግ የበኩላችንን እንወጣለን ወላጆችም ልጆቻቸውን ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲልኩ በአስተማማኝ ሰላም ላይ እንዳሉ ሊሰማቸው ይገባል ነው ያሉት፡፡ ቃላችን ጠብቀን ተማሪዎችን አስተምረን ወደ ወላጆቻቸው እንመልሳለን ብለዋል ዶክተር ፍሬው፡፡የሀገር ሽማግሌዎች ፣የሀይማኖት አባቶች እና ከማህበረሰቡ የተውጣጡ ግለሰቦች ተማሪዎችን እንደሚቀበሉም በመግለጫው ተመላክቷል፡፡የባሕር ዳር ከተማ ከንቲባ ሙሉቀን አየሁ ህብረተሰቡ ተማሪዎችን ለመቀበል መዘጋጀቱንና የከተማ አስተዳደሩ ጸጥታውን አስተማማኝ አድርጎ እንደሚያስቀጥል ነው የተናገሩት፡፡የከተማው ማህበረሰብም ተማሪዎቹን በእንግዳ ተቀባይነት እንዲያስተናግዳቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ምንጭ አብመድ ### Response:
### Text: ህወሓት️የህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ ህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ የድርጅቱን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ቁጥር ከ11 ወደ ዘጠኝ ዝቅ አደረገ።ማዕከላዊ ኮሚቴው ትናንት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ነው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ቁጥሩን ቀደም ሲል ወደነበረበት የቀነሰው።በድርጅቱ ህገደንብ መሰረት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ቁጥርን የመጨመርም ሆነ የመቀነስ የድርጅታዊ ጉባኤ ስልጣን ነው።ቀደም ሲል ማዕከላዊ ኮሚቴው ከዘጠኝ ወደ 11 ቁጥሩን ከፍ ሲያደርግ በድርጅታዊ ጉባኤ ውሳኔ አለመሆኑም የማስተካከያ ውሳኔው መነሻ እንደሆነ ተመልክቷል።ድርጅቱ በቅርቡ ባካሄደው ድርጅታዊ ጉባኤ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትን መምረጡ ይታወሳል።በምርጫው መሰረትም1 ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል2 ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር3 አቶ ጌታቸው ረዳ4 አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ5 ዶክተር አብረሃም ተከስተ6 ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም7 አቶ ጌታቸው አሰፋ8 ዶክተር አምባሳደር አዲስዓለም ባሌማ9 አቶ ዓለም ገብረዋህድ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆነው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህን ጨምሮ አቶ በየነ መክሩ እና ዶክተር አክሊሉ ሀይለሚካኤል የተካተቱበት የህወሃት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትንም መርጦ ነበር።ምንጭ ፋና ብሮድካስቲንግ ### Response:
### Text: አማሮ ወረዳ️በአማሮ ወረዳ ታጣቂዎች በድጋሚ ጥቃት አደረሱ። በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 4 ሰዎችን ገድለው 1 ማቁሰላቸውን የወረዳው መስተዳድር ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽሕፈት ቤቱ ዋና አዛዥ ኢንስፔክተር ሲዳሞ ማዳሞ ለ እንደገለጹት ጥቃቱ የተፈጸመው በወረዳው የኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞንን በምትዋሰነውና ካርማ ጅላ በተባለች አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው፡፡በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት አራት ሰዎችን ገድለው እንድ ማቁሰላቸውን የወረዳው መስተዳድር ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ዋና አዛዥ ኢንስፔክተር ሲዳሞ ማዳሞ ለዲ ደብሊው እንደገለጹት ጥቃቱ የተፈጸመው በወረዳው የኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞንን በምትዋሰነውና ካርማ ጅላ በተባለች አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው፡፡ በጥቃቱ ከሞቱት ነዋሪዎች መካከል ሶስቱ የሸንኮራ አገዳ ምርት በመሰብሰብ ላይ የነበሩ ሲሆኑ አንዱ ግን በከብት ጥበቃ ላይ የተሰማራ ታዳጊ እንደነበር ዋና አዛዡ ኢንስፔክተር ሲዳሞ ገልጸዋል፡፡ በሥፍራው ነበርኩ ያሉ እንድ የአይን እማኝ በበኩላቸው ጥቃት አድራሾቹ በከፈቱት የተኩስ እሩምታ የተደናገጡ መምህራንና ተማሪዎች ወደ አጎራባች መንደሮች መሸሻቸውን ተናግረዋል፡፡ምንጭ አማርኛው አገልግሌት ### Response:
### Text: ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም አገግመው ወደ ቤታቸው ተመለሱ ተባለ በአስመራ በተደረገባቸው የግድያ ሙከራ ቆስለዋል ተብለው የነበሩት የኤርትራ የማዕድን ምኒስትር ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም አገግመው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን በጃፓን የኤርራ አምባሳደር እስጢፋኖስአፈወርቂ አስታወቁ። ጄኔራል ስብሃት በአስመራ ከተማ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል የተባለው ባለፈው ታኅሳስ 2011 ዓም ነበር። በኤርትራ ላይ የሚያተኩሩ እና በተቃዋሚዎች የሚተዳደሩ ማኅበራዊ ድረገፆች ጄኔራሉ በሽጉጥ ጭንቅላታቸው ላይ ተመተው መቁሰላቸውን ፅፈው ነበር።የኤርትራ መንግሥት በአገሪቱ የትጥቅ ትግል ከፍ ያለ ሚና እንደነበራቸው በሚነገርላቸው ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም ላይ ተሞከረ ስለተባለው ግድያ በይፋ የሰጠው ማብራሪያ አልነበረም። አምባሳደር እስጢፋኖስ አፈወርቂ «ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም በውጭ ሀገር ከተደረገላቸው ስኬታማ ሕክምና በኋላ አገግመው ከውድ ቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ አስመራ መመለሳቸውን በመስማቴ ደስ ብሎኛል» ሲሉ በትዊተር ገፃቸው አስፍረዋል። አምባሳደሩ የማዕድን ምኒስትሩ ሕክምና የተደረገላቸው የት እንደሆነ በይፋ ያሉት ነገር የለም። በአስመራ ከተማ በጄኔራል ስብሃት ላይ ጥቃቱ መፈጸሙ ከተሰማ በኋላ የተሰራጩ መረጃዎች ለሕክምና ያመሩት ወደ ዱባይ እንደነበር ይጠቁማሉ።ምንጭ የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: በጦርነት የደቀቀችውን ከተማ ያበረታቱ የሰሜን ወሎዋ ወልድያ ከተማ በኢንቨስትመንቱ ዘርፉ በሯን ክፍት ማድረጓን አሳውቃል። ከተማዋ ጥር 6 ቀን 2015 ዓም0 የኢንቨስትመንት ፎረም ያዘጋጀች ሲሆን ቢዝነስ ብሔር አልባ መሆኑን የተረዱ እና እራሳቸውን ብቻ ሳይሆን ሕዝብን ለመጥቅም ሁለተናዊ አቅሙና ክህሎቱ ያላቸውን ትክክለኛ0 ባለሀብቶች ጋብዛለች ሲል የከተማው አስተዳደር ገልጿል። የከተማው አስተዳደር ወልድያ በ5 አገር አቋራጭ መንገዶች የምትማከል ዲዛይኑ በተሻሻለው ከጅቡቲ ወደብ አዲስ አበባ እና ከመተማ ወረታ መስመር0 የሚገናኘው የባቡር መስመር ደረቅ ወደቧን ከጎና ያደረገች ለንግድ ማዕከልነት ምቹ እና ተማራጭ ነዋሪዋቿ ብቻ ሳይሆኑ የዓየር ንብረቷም እንግዳ ተቀባይ የበርካታ የቱሪዝም ቦታዎች መዳረሻ ዛሬም እንደጥንቱ ጠላትን በፍቅር ድል የሚነሱ አባቶች መፍለቂያና መገኛ መሆኗን ገልጾ የሚመለከታቸው ሁሉ የኢንቨስትመንት ፎረሙን እንዲታደሙ ጥሪ አቅርቧል። የቢሮክራሲው በር ተሰብሮ አቅም ላላቸው አረንጓዴ መብራት ፈንጥቆ እየጠበቀዎት ነውም ብሏል። በኢንቨስትመንት ፎረሙ ዜጎችን ሀብታቸውን ብቻ ሳይሆን ሀሳብ እውቀታቸውንና በጎ ልምዳቸውን ኢንቨስት በማድግ በጦርነት የደቀቀችው ከተማ እንዲያበረታቱ ይፋዊ ጥሪ ቀርቧል።መረጃው ከወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ነው። ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 800 ማክስ አውሮፕላን ላይ በደረሰው አደጋ ላይ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737800 ማክስ የበረራ ቁጥር 302 አውሮፕላን የገጠመውን አደጋ ተከትሎ የሟቾችን አስክሬን ለመለየት ይቻል ዘንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የፎረንሲክ ምርመራ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡በዚህም መሰረት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንና ከኢትዮጵያ ትራንስፖርት ሚንስቴር የተውጣጣ ቡድን ምርመራ ማድረግ ጀምሯል፡፡ የሟቾች አስክሬን ከተለየ በኋላም ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የሚላክ ይሆናል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመላው አለም ለሚገኙ የሟቾች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች ስለአደጋው ተከታታይ መረጃ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ከቦይንግ፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው ሌሎች አለማቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበርም የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ ምርመራዎች የሚደረጉ ይሆናል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ አባላት፣ ማኔጅመንቱና ሰራተኞች በአደጋው የተሰማንን እጅግ ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን በቀጣይም በአየር መንገዱ ዌብሳይትና ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ተከታታይ መረጃዎችን እንደሚያቀርብ ይገልጻል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ### Response:
### Text: ነሃሴ 142012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 768 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 2 ከማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ 1 ከአሶሳ ወረዳ ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 390 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል።አጠቃላይ በድሬዳዋ 742 በቫይረሱ የተያዘ 20 ሞት 606 ያገገሙ በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1553 ላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 133 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።አጠቃላይ በትግራይ 2527 በቫይረሱ የተያዙ 15 ሞት 1105 ያገገሙ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 4853 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 395 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 120 ከምስራቅ ሸዋ 46 ከምስራቅ ሐረርጌ 39 ከቢሾፍቱ ከተማ 34 ከሻሸመኔ ከተማ 31 ከቄለም ወለጋ 17 ከአዳማ ከተማ 17 ከዱከም ከተማ ይገኙበታል። በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 391 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 30 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል 30 ከጅግጅጋ በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 4738 የላብራቶሪ ምርመራ 110 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 18 ከባህር ዳር ከተማ 11 ከሰሸዋ ዞን 11 ከደሴ ከተማ 8 ከምዕጎንደር ዞን 7 ከደጎንደር ዞን 5 ከጎንደር ከተማ ይገኙበታል። ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና ዜና እረፍት ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የፖለቲካ እስረኛ በእስር ቤት ህይወቱ አለፈ በእነ እስከዳር ይርጋ ክስ መዝገብ በበሽብር ክስ አራት አመት ተፈርዶበት ይፈታል ተብሎ እየተጠበቀ የነበረው 2ኛ ተከሳሽ ገበየሁ ፈንታሁን በእስር ቤት ባጋጠመው የጤና እክል ህይወቱ አልፏል። ተከሳሹ በቂ ሕክምና ባለማግኘቱ ከደከመ በኋላ ወደ ፖሊስ ሆስፒታል ተወስዶ የካቲት 182010 በፖሊስ ሆስፒታል ህይወቱ አልፏል። ገበየሁ ፈንታሁን ማዕከላዊ 8 ቁጥር በሚባል ጨለማ ቤት ታስሮ እንደነበርና በቆይታው ድብደባ እንደደረሰበት በወቅቱ አብሮ ታስሮ የነበረው ጓደኛው ገልፆአል።በተለይ በአንድ ወቅት ከደረጃ ገፍትረው እንደጣሉትና በዚህም ምክንያት የራስ ህመም እንደነበረበት ተገልፆአል። አቶ ገበየሁ ፋንታሁን በታመመበት ወቅት በቂ ህክምና እንዳላገኘ ጓደኛው ገልፆአል።አቶ ገበየሁ ፋንታሁን የአንድ ልጅ አባት እና ባለትደር እንደነበርና ከባህርዳር ተይዞ እስከታሰረበት ጊዜ ድረስ በሾፌርነት ተቀጥሮ ቤተሰቦቹን ያስተደድር እንደነበር ተገልፆአል።በክስ መዝገብ 2ኛ ተከሳሽ የነበረው አቶ ገበየሁ ፋንታሁን አራት አመት ተፈርዶበትየነበር ሲሆን 1ኛ ተከሳሽ እስከዳር ይርጋ ጥር 9 2010 ዓም ተፈትቷል። አቶ ገበየሁ ፋንታሁን ይፈታል ተብሎ እየተጠበቀ እንደነበር ታውቋል።ምንጭ ጌታቸው ሽፈራው ### Response:
### Text: ሰበር ዜና በቅርቡ ከእስር የተፈቱት እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዱአለም አራጌ፣ በፍቃዱ በሀይሉን ጨምሮ ሌሎች 12 ግለሰቦች ዛሬ ምሽት በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰምቷል። ዛሬ በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት ቤት ጀሞ ወጣቶች ከእስር ለተፈቱ ሰዎች የምስጋና እና የስጦታ ፕሮግራም አዘጋጅተው ነበር። ፕሮግራሙ ላይም ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዲለም አራጌ፣ እስክንድር ነጋ፣ ኦልባና ሌሊሳ፣ ናትናኤል መኮንን፣ እማዋይሽ ዘውዱ እና አበበ ቀስቶ ተካፋይ ነበሩ።ወደ ፕሮግራሙ ማለቂያ አካባቢው በፖሊስ ተከቦ 12 የሚጠጉ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ውለው በፖሊስ መኪና ተጭነው ወደ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዳቸውን የተመስገን ደሳለኝ ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ ለቪኦኤ ተናግሯል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከልተመስገን ደሳለኝአንዱአለም አራጌማህሌት ፋንታሁንእስክንድር ነጋበፍቃዱ በሀይሉወይንሸት ሞላዘላለም ወርቃገኘሁአዲስ ጌትነትይድነቃቸው አዲስስንታየሁ ቸኮል ተፈራ ተስፋዬ ይገኙበታል።ቪኦኤ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሰዎች መካከል እስክንድር ነጋን ቃለ መጠይቅ ያደረገ ሲሆን እንደ እስክንድር ነጋ ገለፃ በዋናነት የተያዙትበቁጥጥር ስር የዋሉት በፕሮግራሙ ቦታ ኮከብ የሌለበትን ሰንደቅ አላማ በመስቀላቸው ነው። ቪኦኤ ከፖሊስ መረጃ ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ሊሳካለት አልቻለም። ### Response:
### Text: አካላዊ ጉዳት አልደረሰብኝም አረጋዊ በርሄ ዶርበጄነራል ሰዓረ መኮንን እና ሜጀር ጄነራል ገዛኢ አበራ የቀብር ስነስርዓት ላይ ለመካፈል ወደ መቀሌ ያቀኑት የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ትዴት መሪ አረጋዊ በርሀ ዶር የወጣቶች መንጋ ባሏቸው ሰዎች ጥቃት እንደተሞከረባቸው ተናግረዋል፡፡ ቢሆንም ግን አካላዊ ጉዳት አልደረሰብኝም ብለዋል።የቀብር ስነስርዓቱ ላይ ለመገኘት የሰማእታት ሃውልት ደጃፍ ላይ ሲደርሱ ከውስጥና ከውጭ የነበሩት ወጣቶች መግባት የለበትም ብለው በመቃወማቸውና ጥቃት ለማድረስ በመሞከራቸው የክልሉ ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ ሊታደጋቸው እንደቻለ ገልፀዋል።ይህን ተከትሎ ግርግር በመፈጠሩ ወጣቶቹ በወረወሩት ድንጋይ የፖሊስ ኣባላት ላይ እንዲሁም መኪኖች ላይ ጉዳት መድረሱ ታውቋል፡፡ፖሊስ ግርግሩን ለመቆጣጠርም አስለቃሽ ጭስ ለመጠቀም ተገዶም ነበር ተብሏል። ከግርግሩ በኋላ አረጋዊ በርሀ ዶር ወደ ዞኑ የፖሊስ ጽህፈት ቤት የተወሰዱ ሲሆን ማምሻውን በእንግዳ ማረፍያ ማሳለፋቸውንም ተናግረዋል።ባዶ ስድስት የሚባል እስር ቤት ውስጥ ታስረዋል የተባለው ስህተት እንደሆነና ዛሬ ጧት ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ እንደሆነም ገልጸዋል።ጉዳት የደረሰባቸው የፖሊስ አባላት በዓይደር ሆስፒታል ህክምና እያገኙ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።ምንጭ ቢቢሲ አማርኛ ሰኔ 20102011 ዓም ### Response:
### Text: የጅማ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በ2011 ዓም የትምህርት ዘመን በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት ስነስርዓት አካሔደ፡፡ በዚህ ስነስርዓትም ላይ አራት ነጥብ ያመጡ 53 ተማሪዎች የእውቅና ምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ሲሆን ከነዚሁ መካከል ስምንቱ አስሩንም የትምህርት አይነት ያስመዘገቡ ናቸው፡፡ በዕውቅና ዝግጅቱ ላይ የተገኙት የጅማዩኒቨርሲቲ ፕሬዘደንት ዶር ጀማል አባፊጣ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ተማሪዎች ጠንክረው በመስራት ለወደፊቱም የበለጠ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚችሉና ለሌሎች ተማሪዎች አርዓያ በመሆን ጓደኞቻቸውንም ለጥሩ ውጤት እንዲያበቁ፣ የምክርና የሞራል ድጋፍ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል፡፡ አያይዘውም ተማሪዎቹን ለአመርቂ ውጤት ላበቁ መምህራን ምስጋናቸውን በማቅረብ ወደፊት ትምህርት ቤቱን በማጠናከር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡በዝጅቱ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዩጭ ምፕሬዘደንት ዶር አዱላ በቀለ በበኩላቸው የመምህራንን አቅምና ጥረት መደገፍ የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ባለፍ ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራ እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡ በመጨረሻም በትምህርታቸው ውጤታማ ለሆኑ ተማሪዎችና በተማሪዎቹ ለተመረጡ 3 መምህራን የዕውቅና ሽልማት ተሰጥቷል፡፡ ### Response:
### Text: በተፈጠረ የግለሰቦች አለመግባባት ህይወት ሊጠፋ ችሏል የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ከሰሞኑ በሀዋሳ ከተማ የግብርና ሚኒስቴር0ሜካናይዜሽን የስራ ሂደት መሪ0ስራ አስፈፃሚ አቶ በረከት ፎርሲዶ በአንድ የመዝናኛ ስፍራ በጥይት ተመተው ህይወታቸው አልፏል የሚል መረጃ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደርሶት ተመልክቷል።ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማጣራት ጥረት አድርጓል።በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያዬታቸዉን የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ወንጀሉ የተፈጸመው በመዝናኛ ቦታ በተነሳ የግል ጸብ መሆኑን ገልጸዋል።በወቅቱ በተፈጠረ አለመግባባት ሟች በሽጉጥ ራሳቸዉ አካባቢ ተመተው መውደቃቸዉን ከተመቱ በኋላ ወደሆስፒታል ቢወሰዱም ህይወታቸዉ ሊተርፍ አለመቻሉን አስረድተዋል።ኢንስፔክተሩ ፖሊስ አስክሬኑን ወደአዲስ አበባ ወስዶ ካስመረመረ በኋላ ለቤተሰብ ማስረከቡን ገልጸዋል። አሁን ላይ ጥቃት አድራሹና በወቅቱ ከእሱ ጋር የነበሩት ሁሉ ተይዘዉ እየተመረመሩ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለፁት ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ በአካባቢዉ የነበረ ካሜራ ሁነቱን ሙሉ በሙሉ ሬከርድ ማድረጉ ስራችንን አቅልሏል በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ጉዳዩ ለፍርድ ቤት ይተላለፋል ብለዋል።መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው። ### Response:
### Text: ስለ ጥዋቱ የ ዘገባ ከባሌ ጎባ ነዋሪ️ሰላም ፀግሽ የሰራው ዘገባ አንብቤዋለሁ ዘገባው ሚዛናዊነትን የሳተ እንዲሁም እውነታውን ያላንፀባሩ ነው። እኛ ቀኑን ሙሉ አደባባዩ ሰፈር ነበርን። ቀብሮዋ እንድትፈረስ በደንብ ተጠንቶበት የተሰራ ስራ ነው። ለዚህም ማስረጃ አለን ከጥዋቱ 3 ሷት አካባቢ የዞኑ አስተዳደር ከገጠር የመጣውን ማህበረሰብ ሰብስቦ ስብሰባ ሲያደርግ ነበር ቀሪው ህዝብ እንዳይወጣ ደግሞ የከተማው ከፍተኛ ባለስልጣናት በዚያን ቀን ማለትም ቅዳሜ ምንም አይነት ችግር እንደማይፈጠር እና ህዝቡ እንዲዘናጋ አመራሮችን ሰብስበው ለራሳቸው አላማ አመቻችትቅ ወየቤታቸው ለቀዋቸዋል። አደባባዩ የህዝብ ገንዘብ እስከወጣበት ድረስ መፍረስም ካለበት ህዝቡ አንምኖበት እና በአግባቡ መሆን ሲገባው በተደራጁ ሀይሎች ሲፈርስ የክልሉ ፖሊስ አንድም እርምጃ አለመውሰዱ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል። ሌላው ከከንቲባዋ ንግግር የገረመ ኝ የህዝቡ ጥያቄ ነው መባሉ ነው። ህዝቡ በቂ መሰረተ ልማት ሳያገኝ እንዴት 10 ሚሊዮን የሚያወጣ ሀውልት ይገንባልኝ ብሎ ይጠይቃል ፀግሽ ይሄ ፕሮፖጋንዳ ነው። ህዝቡ ጠቡ ያለው ከሌላ እምነት አማኝ ጋር አይደለም ከአመራሩ ጋር ነው። ስለዚህም የክልሉ ባለስልጣናት በአፋጣኝ አመራሩን እንዲፈትሹ እምፀናለሁ። ሰላምና ፍቅር ከኛ ጋር ይሁን አመሰግናለሁ ከጎባ ### Response:
### Text: የኤርትራ የነጻነት ቀን አዲስ አበባ በሚገኘው የአገሪቱ ኤምባሲ ተከበረ28ኛው የኤርትራ የነጻነት ቀን አዲስ አበባ በሚገኘው አዲሱ የአገሪቱ ኤምባሲ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2011 ዓም ተከብሯል።በበዓሉ የተገኙት የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንደገለጹት በዓሉ በዚህ መልኩ መከበሩ በሁለቱ አገራት ባለፈው አንድ ዓመት ያደረጉት መቀራረብ ውጤት ነው ብለዋል።ባለፈው አንድ ዓመት በከፍተኛ ባለስልጣናት በኩል የተደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶች ለአገራቱ ግንኙነት መሻሻል ማሳያዎች መሆናቸውንም አውስተዋል።የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የአገራቱን ታሪካዊ ትስስር በሚያንጸባርቅ መልኩ የበለጠ ተቋማዊ እንዲሆን ኢትዮጵያ አስፈላጊውን ሁሉ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።በኢትዮጵያ የኤርትራ አምባሳደር ሰመረ ርዕሶም በበኩላቸው ከ20 ዓመት በኋላ የአገሪቱን የነጻነት ቀን በኢትዮጵያ ማክበር በመቻላቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነት በበጎ መልኩ እንዲጎለብትና በቀጣናውም ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እንደምትሰራ አስታውቀዋል።በዝግጅቱ ላይ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደተገኙም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቃል አቀባይ ጽቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ### Response:
### Text: በኳታር ለምትገኙ ኢትዮጵያውያንየኢትዮጵያ ኤምባሲ ዶሃየኳታር የሚኒስትሮች ምቤት የኮሮና ቫይረስ መስፋፋትን ለመግታት ያስችላሉ ያላቸውን ተጨማሪ ውሳኔዎች አሳልፏል። በዚህም መሰረት ሁሉም የአገሪቱ ዜጎች እና ሁሉም ነዋሪዎች ከግንቦት 14 ቀን 2012 ዓም 22 2020 ጀምሮ ከቤታቸው ሲወጡ የቫይረስ ተጋላጭነት ደረጃን የሚያሳየውን የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ በስልኮቻቸው ማውረድ ይጠበቅባቸዋል። በግል መኪናዎች ውስጥ ከ2 ሰው በላይ ሆኖ መጓዝ አይፈቀድም። በታክሲዎች፣ በሊሞዚኖች እና በቤተሰብ ሹፌሮች በሚሽከረከሩ መኪናዎች ውስጥ ከ3 ሰው በላይ ሆኖ መጓዝ አይቻልም። አምቡላንሶችና የጤና ሚኒስቴር መስሪያ ቤት መኪኖች፣ የመከላከያ፣ የፖሊስ እና የደህንነት ተቋማት ተሽከርካሪዎች ውሳኔው አይመለከታቸውም። ከግንቦት 11 22 ቀን 2012 ዓም 19 30 2020 ሁሉም ሱቆች ዝግ ሆነው ይቆያሉ የንግድ እንቅስቃሴዎች ይቆማሉ። ምግብ ቤቶች፣ የምግብ አቅራቢ ድርጅቶች እና ፋርማሲዎች ውሳኔው አይመለከታቸውም። ከግንቦት 11 ቀን 2012 ዓም 19 2020 ጀምሮ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በመኖሪያ ቤቶች አቅራቢያ እና አስፈላጊውን ጥንቃቄ የፊት መሸፈኛ በመጠቀም፣ ርቀትን በመጠበቅ በማድረግ መከናወን ይኖርባቸዋል። ውሳኔዎቹን ተላልፎ የተገኘ ግለሰብ እስከ ሶስት ዓመት እስር እና እስከ 200000 የኳታር ሪያል የሚቀጣ ይሆናል። ### Response:
### Text: ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ ፎርጅድ እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ውይይት አድርጓል።በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶር ቀንአ ያደታ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረት በማድረግ የጊዜያዊ መታወቂያ አሰጣጥ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።መመሪያው ሰላማዊ እና ፀረ ሰላም ኃይሎችን ለመለየት፣ የሐሰት መታወቂያ የሚሰጡ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ለመለየት እንዲሁም የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ሆነው ያለ አግባብ ጊዜያዊ መታወቂያ የሚሰጡትን ለመቆጣጠር ያግዛል ብለዋል።ዶር ቀነዓ እንዳሉት ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ ፎርጅድ እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት ያስቀጣል ያሉ ሱሆን ከህዳር 6 ቀን 2014 እስከ ህዳር 152014 በሚቆየው የጊዜያዊ መታወቂያ አሰጣጥ ሂደት ማህበረሰቡ መታወቂያ ማውጣት እንዳለበት ተናግረዋል።የሎጂስቲክ እና የሰው ኃይል ቅድመ ዝግጅት ተካሂዶ አርብ ህዳር 102014 በየክፍለ ከተማው ጊዜያዊ መታወቂያ ለማህበረሰቡ ለመስጠት ዝግጅት መጀመሩም ተገልጿል።ምንጭ ኢትዮ ኤፍ ኤም 1078 ### Response:
### Text: በድጋሚ ቴሌግራም ላይ ና በሚል በአጭበርባሪዎች የተከፈቱ እንጂ ትክክልኛ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ስር ያሉ አይደሉም።ገፆቹ በመቶ ሺዎች ሚቆጠሩ ሰዎች ያሉባቸው መሆኑን የተመለከትን ሲሆን ሁሉም ድርጊታቸው ከቲክቫህ ጋር የማይገናኝ እና ስራቸውም በስማችን ማጭበርበር ነው።ውድ ቤተሰቦቻችን ከመሰል አጭበርባሪዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ በድጋሚ አደራ እንላለን።በዚሁ አጋጣሚ በየዕለቱን የቲክቫህ አባል እየሆናችሁ ለምትገኙ በሺዎች የምትቆጠሩ ቤተሰቦቻችን በኛ ስር ያሉት ትክክለኛ ገፆች የሚከተሉት ናቸው ከ12 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት ከ240 ሺ በላይ አባላት ያሉት ከ145 ሺህ በላይ አባላት ያሉት ከ103 ሺ በላይ አባላት ያሉት ከ19 ሺ በላይ አባላት ያሉት ቲዊተር =09 ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሆነ አሁን ላይ አገልግሎት የሚሰጥ የ አካውንት በስሙ የለም።ቲክቫህ ተስፋ ኢትዮጵያ ሰብዓዊነትን ያስቀደሙ እና ሀገራቸው ኢትዮጵያን የሚያከብሩ እንዲሁም የሚወዱ ዜጎች መሰባሰቢያ መድረክ ሲሆን በወቅታዊ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ክንውኖች ዙሪያ የእርስ በእርስ መረጃ ልውውጥ ይደረግበታል። ከየትኛውም የፖለቲካ ፣ የብሄር፣ የሃይማኖት ውግንና የራቀ ሲሆን ኢትዮጵያን እንደሀገር ያከበሩና ሀገሪቱን አደጋ ላይ የማይጥሉ የተለያዩ አመለካከቶች እንዲሁም አስተሳሰቦች ያሏቸውን ቤተሰቦቹን የሚያሰባስብ ነው። ### Response:
### Text: ለጥያቄዎቻችሁ መልስ1የ እና 2 በተመለከተከዚህ ቀደም በባንክ እየሄደን ገንዘብ በማሰባሰብ የምንተጋገዝበትን መንገድ በሌላ በተሻለ አማራጭ ለመተካት ብዙ ሲታሰብ ነበር። ለማስጀመርም እንቅስቃሴ ተሞክሯል። ግን ያለው ሁኔታ ምቹ ባለመሆኑ ሊሳካ አልቻለም። አሁን ግን ከሜዳ ቻት ጋር በመተባበር በአሞሌ በኩል ስራዎችን ለመስራት ዝግጅታችንን ጨርሰናል። በቀጣይ እንዴት እንደሚሰራ እናሳውቃለን።2 የ የመማሪያ ቻናላችንን በተመለከተ ብዙ ለመስራት ተሞክሯል። ነገር ግን በፍቃደኝነት ላይ ተመስርተው ለሲሩ የተመዘገቡ ሰዎች ስራቸውን በአግባቡ ሊሰሩ ባለመቻላቸው በተቻለ አቅም ሌሎች አማራጮችን እያፈላለግን ነው።የተለያዩ አስተማሪ ፅሁፎቻቹን በ ለማቅረብ የምትፈልጉአጭርከ30 መስመር ያልበለጠአስተማሪለሀገር ግንባታ ጠቃሚ የሆኑ ፅሁፍ ያላችሁ ማቅረብ ትችላላችሁ።ማስታወቂያ ለማስነገር የምትፈልጉ ፍቃድ ያላችሁ እና በ አሰራር ለመገዛት ፍቃደኛ የሆናችሁ ብቻ መጠቀም ትችላላችሁሌላው የግል ምልከታዬን የማጋራበት፣ ልዩ ልዩ ፅሁፎችን ከተለያዩ ሰዎች መራርጬ የማቀርብበት አባባሎችን የፖለቲካ የማህበራዊና ሌሎች ምልከታዎችን እንዲሁም ከተለያዩ ገፆች የምመርጣቸው ልዩ ልዩ ፅሁፎችን በአማርኛ እና እንግሊዘኛ ለናተ የማጋራበትን የግሌን ቻናል ከፈለጋችሁ መቀላቀል ትችላላችሁ 1 ### Response:
### Text: ዳኛው በአምላክ አለቀሰከላይ ያለድ ምስል የኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር በአምላክ ተሰማ እንባ አዘል ፎቶ ነው። ለመሆኑ በአምላክ ለምን አለቀሰሚያዚያ 52011 በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ የሞሮኮው ዋይዳድ ካዛብላካ ከጊኒው ሆሮያ የመልስ ጨዋታ ሊያደርጉ ሞሮኮ ላይ ተገናኝተው ነበር።ከሳምንት በፊት ሁለቱ ቡድኖች ጊኒ ላይ ያለ ጎል አቻ በመለያየታቸው የመልሱ ጨዋታ ተጠባቂ ሆኗል።ካፍ ደግሞ ኢትዮጵያውያኖቹን በአምላክ ተሰማን የመሀል ዳኛ ተመስገን ሳሙኤልን ደግሞ ረዳት አድርጎ ከኬንያውያን አጋሮቻቸው ጋር መድቧል።በጨዋታው ማብቂያ 85ኛ ደቂቃ ላይ ሴኔጋላዊው የሆሮያ ግብ ጠባቂ ሀዲም ኒዳይ ከራሱ ተጫዋች ጋር ተጋጭቶ እጅግ አሰቃቂ ጉዳት ይደርስበታል። ይህ ከባድ ጉዳት የሁለቱን ክለቦች ተጫዋቾችን ብቻ ሳይሆን ክስተቱን በቅርበት የተመለከተው ዋና ዳኛ በአምላክ ተሰማን ጭምር አስደንግጧል። ኢትዮጵያዊው በአምላክ ስሜቱን መቆጣጠር ተስኖት በምስሉ ላይ እንደሚታየው አልቅሷል።በአምላክን እንዲህ አለ በቅርበት ስለነበርኩ ስሜቱ በጣም ከባድ ነበር ልክ እንደ መኪና አደጋ ነበር አልቻልኩም ከቁጥጥሬ ውጪ ሆኖ አለቀስኩ ብሎኛል።እናም ይህ ምስል ብዙ ይናገራልበአምላክ እንባ ውስጥ ለሰው አዛኝና ሩህሩህ የሆነችውን ኢትዮጵያን እዚህ ቦታ ላይ አየናት።ታምሩ ዓለሙ ### Response:
### Text: የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ዓረፉ።ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ምሽት ላይ በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።ብፁዕ አቡነ አልሳዕ በ1927 ዓም በበጌምደር አውራጃ ደራ ወረዳ አፈር ውሃ እናት የተወለዱ ሲሆን የተለያዩ ሃይማኖታዊ ትምህርቶችን በመከታተል በ1971 ዓም የጵጵስና ማዕረግ ተቀብለዋል።በተሰጣቸው ሃይማኖታዊ ስልጣንና ሃላፊነት ከ40 በላይ ዓመታት ያገለገሉት ብፁዕ አቡነ አልሳዕበህይወት ዘመናቸው በጅማ፣ ከፋ፣ ደቡብ ጎንደር እና ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከቶች በጵጵስና አገልግለዋል።በተጨማሪም በአዲስ አበባ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የካህናት የበላይ ጠባቂ ሆነውም አገልግለዋል።ብፁዕነታቸው እሳከረፉባት ቀን ድረስ በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በጵጵስና ሲያገለግሉ ቆይተዋል።እንደ ኤፍ ቢ ሲ ዘገባ የብፁዕ አቡነ ኤልሳ አስከሬን የፊታችን ሰኞ ግንቦት 19 2011ዓም በጎንደር ከተማ መስቀል አደባባይ አሸኛኘት ይደረግለታል።ማክሰኞ ግንቦት 20 ቀን 2011ዓም ደግሞ በተወለዱበት የደራ ወረዳ አፈር ውሃ እናት እና የኑዛዜ ቃል ባሳረፉበት በመካነ ሰማዕት ገላውዴዎስ ቤተ ክርስትያን ቅዱስ ፓትሪያሪኩ በተገኙበት ስርዓተ ቀብራቸው የሚፈፀም ይሆናል። ### Response:
### Text: ነሃሴ 152012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 560 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 14 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 2 ከማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ 1 ከአሶሳ ወረዳ 1 ከጉባ ወረዳ 1 ከአሶሳ ህዳሴ ኤርፖርት 3 ከአሶሳ ከተማ በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1392 ላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 273 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል የ1 ሰው ህይወት አልፏል ከአላማጣ በአስክሬን ምርመራአጠቃላይ በትግራይ 2800 በቫይረሱ የተያዙ 16 ሞት 1227 ያገገሙ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 5046 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 191 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 54 ከምስራቅ ሸዋ 30 ከቄለም ወለጋ 20 ከምዕራብ ወለጋ 16 ከቡራዩ ከተማ 16 ከገላን ይገኙበታል። በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 415 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 24 ሰዎች በኮቪድ19 ተይዘዋል ሁሉም ከጅግጅጋ የነሃሴ 14ነሃሴ 142012 ዓም በደቡብ ክልል በተደረገው 1205 የላብራቶሪ ምርመራ 77 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 29 ከጌዴኦ 24 ወናጎ፣2 ዲላ፣ 2 ይጨፌ፣ 1 ዲላ ዙሪያ 23 ከወላይታ 20 ዳሞት ዎይዴ 3 ሶዶ 17 ከጋሞ 6 ቦረዳ፣ 5 ከአርባ ምንጭ፣ 1 ከቁጫ፣ 4 ከሰላምበር እና 1 ወዜ 5 ከጉራጌ 2 ከአበሽጌ፣ 2 ቡታጅራና 1 ከወልቂጤ፣ 2 ከጎፋ 1 ሳውላ እና 1 ደምባ ጎፋ ### Response:
### Text: የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል የመደፈር ጥቃት የተፈፀመባቸው ሴቶች እና ልጃገረዶች ቁጥር ከ1400 መብለጡን ገለፀ።በፌዴራል መንግስቱ የተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የፍትህ እና የሴቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወሮ ኢተነሽ ንጉሰ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተቋማት የሄዱ ሴቶች እና ልጃገረዶች ቁጥር 1408 መድረሱን ተናግረዋል።እንደትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መረጃ በመቐለ 716 ከዓዲግራት 362 ከአክሱም 85 ከሽረ 48 ከማይጨው 37 ከመሆኒ 18 የተመዘገቡትን ጨምሮ አጠቃላይ 1408 ሴቶች እና ልጃገረዶች ተደፍረዋል።የዓይደር ሆስፒታል ዋና ስቶፕ ሴንተር አስተባባሪ ሲስተር ሙሉ መስፍን በትግራይ ውስጥ በሴቶች ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ከመሻሻል ይልቅ እየተባባሰ መሄዱን አመልክተዋል።ወደ ዓይደር ሆስፒታል ሄደው ስለታከሙ እና በመታከም ላይ ስለሚገኙ ጉዳተኞች ሲስተር ሙሉ መስፍን ሲገልፁ ተሻሽሏ የሚባል ነገር የለም ብለዋል።በኤርትራም በኢትዮጵያም ወታደሮች ተደፍረው ፅንስ ለማቋረጥ ወደሆስፒታሉ የሄዱ 238 ሴቶች እና ልጃገረዶች መኖራቸውን ሲስተር ሙሉ ተናግረዋል።ፅንስ ሲያቋርጡ በደም እና በሌላም የሰውነት ፈሳሽ መፍሰስ ምክንያት የተወሳሰበ የጤና እክል ያጋጠማቸው ፣ በኩላሊት መጎዳት ምክንያት ለዳይለሲስ ህክምና የገቡ ሴቶች መኖራቸውን ጨምረው ገልፀዋል።ያንብቡ 0609 ### Response:
### Text: የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትን በህግተጠያቂ ለማድረግ እየተሰራ ነው ዶር እሸቱ ከበደየ2014 ዓም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ስራ ሙሉ በሙሉ በመጠናቅ ላይ መሆኑን የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ዶር ተናግረዋል፡፡የፈተና ዝግጅቱም የተማሪዎችን ልፋት ሊለካ በሚችል ከደህንነት ስጋት ነፃ እንዲሆን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ለፈተና አሰጣጡ ውጤታማነት ከመፈተኛ ቦታ መረጣ ጀምሮ የፈተና ኮዶችን ብዛት ከፍ የማድረግ ስራ የተሰራ መሆኑም ተገልጿል።ይህንን ተከትሎ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የራሳቸው ጥረት ውጤት ለማግኘት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ያሳሰቡ ሲሆን ለዚህም የህግ ተጠያቂነት እንዲኖር እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ተማሪዎችና ወላጆችም መረጃዎችን ከተቋሙ እና ከታማኝ የመረጃ ምንጮች ብቻ እንዲከታተሉም ጠይቀዋል። የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው። ### Response:
### Text: ዶር ዐብይ ፕሬዚደንት ኢሣያስ አፈወርቂ አወደሱ ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማታቸውን ሲቀበሉ ባደረጉት ንግግር ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ አወደሱ። «ይኽን ሽልማት የምቀበለው በኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ስም ነው። በተለይ ደግሞ ለሰላም ሲሉ ከፍተኛውን መስዋእትነት በከፈሉት ስም። በተመሳሳይ ሽልማቱን የምቀበለው በአጋሬና የሰላም ጓድ በኾኑት ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ ስም ነው» ብለዋል። ይኽ ንግግራቸውም ከታዳሚያን ሞቅ ያለጭብጨባ ታጅቧል። የፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ «መልካም ፈቃድ፣ እምነት እና ቁርጠኝነት ለኹለት ዐስርተዓመታት በሃገሮቻችን መካከል የዘለቀው መቆራረጥ እንዲያበቃ ወሳኝ ነበር።» በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ጦርነቱ ሲከፈት ወጣት እንደነበሩ የተናገሩት ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ በጦርነት አውድማ «ወንድም ወንድሙን ሲገድል» መመልከታቸውን ገልጠዋል። የጦርነት መራራ ገጽታን የሰላምን ወሳኝነት አጉልተው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦርነት የተነሳ ለኹለት ዐሥርተዓመታት ተለያይተው የነበሩ ቤተሰቦች መገናኘታቸውን «ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ እንደ አዲስ መጀመሩንም» ጠቅሰዋል። የአየር እና የቴሌኮሙኒኬሽን ግንኙነት በኹለቱ ሃገራት መጀመሩንም በንግግራቸው አሰምተዋል። 12103 ### Response:
### Text: በ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ለኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ እንዳይሆኑ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ዶር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ለኢቲቪ ገልጸዋል። የቀጣዩ ዓመት ትምህርት ምዝገባ ከነገ ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓም ጀምሮ በመንግሥት እና በግል ትምህርት ቤቶች እንደሚጀመር የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መንገዶችን በመተግበር ምዝገባ እንዲያከናውኑ ተፈቅዷል ብለዋል። የበሽታው ሁኔታ እየተስፈፋ ቢሆንም የትምህርት ዝግጅት እና እንቅስቃሴ መጀመር አስፈላጊ ሆኑ መገኘቱን ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት። ወደ መማር ማስተማር ተግባር በሚገባበት ወቅት ለተማሪዎች ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እንደሚሠራ ገልጸው፣ ማስክ፣ የእጅ ማፅጃ እና መሰል አቅርቦቶችን ከባላድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። በግልም ሆነ በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እንዳይከሰት ተማሪዎች ማስክ በማድረግ፣ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ እና እጅን በመታጠብ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ሚኒስትሩ አሳስበዋል። ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች በ2012 የትምህርት ዘመን በ2ኛ ሴሚስተር ያለፋቸውን ትምህርቶች ማካካሻ ለመስጠት መታሰቡንም ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ገልጸዋል ### Response:
### Text: መቀሌ ለተጨነቃችሁ ቤተሰቦች በሙሉ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ሁሉም ካምፓሶች ሰላም ናቸው።ከባለፈው የወልዲያ ግጭት በኃላ አንዳንድ ስሜታዊ ወጣቶች በተለያዩ ተማሪዎች ላይ ትንኮሳ ለመፍጠር ሞክረው የነበር ቢሆንም ያን ያህል በሶሻል ሚዲያው ተጋኖ እንደተወራው አይደለም።በአሪድ ካምፖስገዳም ሰፈር ተገቢ ያልሆኑ እንቅስቃሴዎች በአንዳንድ ወጣቶች እየታየ እንዳለ የገለፁት ተማሪዎች ድንጋይ የመወርወር እና ተማሪዎችን ማስፈራራት እንቅስቃሴ ነበረ። ግቢውም ጉዳዩን በማጣራት ተገቢውን ፈጣን እርምጃ እንዲወስድ ተማሪዎች ጠይቀዋል።በውጭ ተቀምጠው ይህን ጉዳይ በማጋነን ተማሪዎችን እርስ በእርሳቸው ለማጋጨት እና የጥቂት ሰዎችን መጥፎ ተግባር እንደ አብዛኛው ሰው ድርጊት እንዲቆጠር ለማድረግ እየሞከሩ ያሉ አካላት አሉ። ዛሬ ምሽት በአሪድ ካምፓስ እሳት ተነሳ ተብሎ የተወራው በሴቶች ዶርም አካባቢ ትንሽ የኤሌክትሪክ ኮንታክት ሲሆን ሴቶች ተደናግጠው ነበር። ከዚህ ውጭ ምንም አይነት ነገር አልተከሰተም ውጭ የነበሩ ተማሪዎችም ወደ ዶርማቸው ተመልሰዋል።መጥፎ የሚያስቡትን እና ነፁህ ሰዎችን ለመጉዳት የሚያስቡትን ፈጣሪ ይቅር ይበላቸው።የጥቂት ሰዎችን መጥፎ ተግባር እንዲሁም የግለሰቦችን ፀብ የሁሉም አድርጎ ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት የሚሰራ ስራ እጅግ አደገኛ ነው። ምንጭአላ ### Response:
### Text: የህዳሴ ግድብ️የታላቁ ህዳሴ ግድብ የኤልክትሮ ሜካኒክ ስራዎች በዘርፉ ዓለማቀፍ እውቅና ባላቸው የውጭ ኩባንያዎች በመሰጠቱ ህዝቡ ጥራትን በተመለከተ ሥጋት እንዳይገባው ተገለጸ።ግድቡን አስመልክቶ ዛሬ በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ የተሳታፊዎቹ ዋና ጥያቄ ግድቡን እንዴት እንጨርሰዋለን እና ጥራቱስ እንዴት ይጠበቃል የሚለው ነበር።በዚህ ጉዳይ ላይ መልስ የሰጡት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት በኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ላይ የነበረው የዓቅም ውስንነት እንዲሁም የልምድ ማጣት ችግር ኢትዮጵያ ብዙ ገንዘብ እንድትከስር ማድረጉን ገልጸዋል፡፡አሁን ግን ለሜቴክ ተሰጥቶት የነበረው ይህ ሥራ በዘርፉ ዓለም አቀፍ እውቅና ባላቸው የጀርመን፣ የፈረንሳይና የጣሊያን ኩባንያዎች በመተካቱ ህዝቡ በዚህ ላይ ምንም ዓይነት ሥጋት እንዳይገባው አሳስበዋል።እስካሁን ለግድቡ የወጣው 98 ቢሊዮን ብር ሲሆን ከዚህ ውስጥ 10 በመቶው ከህዝብ በተገኘ ድጋፍ የተሰራ እንደሆነ ተገልጿል።ግድቡን አለመጨረስ አገራዊ ክስረት እንደሚያስከትል የገለጹት ኢንጂነሩ ህዝቡ የኔነት ስሜት ተሰምቶት ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥልጠይቀዋል።እስካሁን ግድቡ 65 በመቶ መጠናቀቁን እና በ4 አመት ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅም ተገልጿል።ምንጭ ### Response:
### Text: አንዳንድ አገራት የሚያወጡትን አሃዝ የሚያምን አለ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት መግለጫ የሰጡት ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኮሮና ቫይረስ በአሜሪካ ሊያስከትለው የሚችለው ጉዳት ጣሪያን በማለፉ አንዳንድ ግዛቶች በዚህ ወር መከፈት እንደሚጀምሩ ተናግረዋል።ፕሬዘዳንቱ ከአሜሪካ ግዛት አስተዳዳሪዎች ጋር ከተወያዩ በኋላ ግዛቶቹ ስለሚከፈቱበት ሁኔታ ዛሬ ምሽት መግለጫ እንደሚሰጥ አሳውቀዋል።አሃዞች እንደሚያሳዩት በመላው አገሪቱ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ ነው በማለት ዶናልድ ትራምፕ ገልፀዋል።አሜሪካ 638000 ዜጎቿ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን በኮቪድ19 ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ30800 በላይ ነው።ከሌሎች አገራት በላይ በአሜሪካ በቫይረሱ የሞቱ እና የተያዙ ሰዎች ቁጥር ለምን ከፍ አለ ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፕሬዝደንቱ ሲመልሱ አንዳንድ አገራት የሚያወጡትን አሃዝ የሚያምን አለ በማለት የቻይናን ስም ጠቅሰዋል።ትራምፕ ጨምረውም ቫይረሱ በቻይዋ ዉሃን ከተማ ሳይሆን ከዉሃን ላብራቶሪ ነው የወጣው ስለሚባለው ያልተረጋገጠ ሪፖርት አሜሪካ ትመለከተዋለች ብለዋል።የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በቤጂንግ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በዉሃን በሚገኙ ሁለት ላብራቶሪዎች የደህንነት ጉዳይ ያሳስበናል ሲል ሪፖርት ስለማድረጉ ዘግበዋል።ምንጭ ቢቢሲ ### Response:
### Text: የትግራይ አብዛኛዎቹ ከተማዎች በጨለማ ተውጠዋል።ከትላንት ሀሙስ ከሰዓት ጀምሮ በትግራይ መቐለን ጨምሮ በበርካታ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል።የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በአብዛኞቹ የትግራይ ክልል ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን ገልፀው ኤሌክትሪክ የተቋረጠው ከመሆኒ 40 ኪሜ ላይ ወደ መቐለ ባለ መስመር ላይ ሊሆን እንደሚችል ነው የተቋሙ ባለሞያዎች የለዩት ብለዋል።ትክክለኛው ቦታ ባይታወቅም የባለሞያዎቹ ግምት ወደዛ መስመር ነው ሲሉ አስረድተዋል።የኤሌክትሪክ መቋረጡን ምክንያት በተመለከተም አቶ ሞገስ ቦታው ተለይቶ ያጋጠመውን ችግር መለየት እስኪቻል ድረስ ምክንያቱ ይሄ ነው ብሎ መግለፅ እንደማይቻል ተናግረዋል።ኤሌክትሪክ በተቋረጠባቸው ከተሞች ኤሌክትሪክ ሚመለሰው ችግሩ ተለይቶ አስቸኳይ የጥገና ስራ እንደተጠናቀቀ ነው ሊመጣ የሚችለው ትክክለኛው ቦታውን የመለየት ስራ ተጀምሯል ብለዋል።መቼ ነው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለሚመለሰው ለሚለው ጥያቄም ችግሩ ስላልተለየ ለመገመት እንደማይቻል ገልፀዋል።በትግራይ ውስጥ ግጭት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተለያየ ጊዜ እና በተለያየ ምክንያት ኤሌክትሪክ እየተቋረጠ የክልሉ ነዋሪዎች ረጅም ጊዜያትን በጨለማ ውስጥ ለማሳለፍ ሲገደዱ እንደነበር አይዘነጋም። ### Response:
### Text: ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ባለ 50 ወለል ህንጻ ሊገነባ ነው።0 ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ይታወቅበት የነበረውን ደቡብ ግሎባል ባንክ የተሰኘውን ስያሜውን እና የንግድ ምልክቱን ከቀየረ በኋላ ዋና መስሪያቤቱን በአዲስ አበባ ለመገንባት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ አስታውቋል።ባንኩ ለዋና መስሪያቤቱ ግንባታ ከ18 በላይ ድርጅቶችን የአርኪቴክቸራል ዲዛይን ያወዳደረ ሲሆን የባንኩን የወደፊት መስሪያ ቤት ዲዛይን ኢላፕስ ቢዝነስ ኃየተየግ ማህበር የሰራውን ዲዛይን አሸናፊ አድርጎ መርጧል፡፡ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሜክሲኮ አካባቢ፣ ለዋና መቤት ግንባታ የሚሆን 5500 ካሬ ቦታ መረከቡን የጠቆመው ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ዲዛይኑ ሁለት መንትያ ህንጻዎች ያሉት ብሏል።በዚህም ትልቁ ህንጻ ከ50 ወለል በላይ ሕንጻ፣ ትንሹ ደግሞ ከ12 በላይ ፎቅ እንደሚኖረው የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተስፋዬ ቦሩዶር ገልፀዋል፡፡ባንኩ አክሎም በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ቅርንጫፍን 152 መድረሱን ገልጾ በአዲሱ በጀት አመት የቅርንጫፎቹን ብዛት 185 ለማድረስ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።በተጠናቀቀው በጀት አመት ግሎባል ባንክ 820 ሚሊዮን ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱንም ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከባንኩ ሰምቷል። ጠቅላላ የሀብት መጠኑም 20 ቢሊዮን ብር መድረሱን ገልጿል። ### Response:
### Text: ጠሚ ዶር አብይ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል አንድ ወደፊት ስንሄድ ሁለት ወደኋላ የሚመልሱንን ሀይሎች ማስቆም እንደሚገባ ጠሚ ዶክተር አብይ አህመድ አሳሰቡ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው እለት ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በመግለጫቸውም ከሰሞኑ በተከሰተው ግጭት የ86 ሰዎች ህይወት አልፏል ያሉ ሲሆን ከሟቾች መካከል 82 ወንድ፣ 4 ሴቶች መሆናቸውምን አስታውቅዋል።በብሄር ደግሞ 50 ኦሮሞ፣ 20 አማራ፣ 8 ጋሞ፣ 2 ስልጤ፣ 1 ጉራጌ፣ 2 ሀዲያ እና አንድ አርጎባ ሲሆኑ የአንዱ ሟች ብሄር እንዳልታወቀም አስታውቀዋል። በሀይማኖት ደግሞ ከሟቾቹ መካከልም 40 ክርስቲያን ሲሆኑ 34 ሙስሊም እና 12 የሌላ እምነት ተከታዮች መሆናቸውንም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በመግለጫቸው ያስታወቁት። ከሟቾቹ መካከል 76 ሰዎች በእርስ በእርስ ግጭት 10 ሰዎች ደግሞ በፀጥታ ሀይሎች ህይወታቸው ማለፉንም ገልፀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በመግለጫው ይህ ክፉ ክስተት በኢትዮጵያ የግጭት እሳት ሲነሳ አንዱን ክፍል አቃጥሎ ሌላውን አሙቆ የሚያልፍ እንዳልሆነ ያሳየ ነው ብለዋል። መንግስት የፖለቲካ እና የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ሆደ ሰፊነቱን አብዝቶ ሲያስታምም ከርሟል ብለዋል።ተጨማሪ ያንብቡ 11034 ### Response:
### Text: የ2014 ዓም የትምህርት ዘመን የብሄራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ መግቢያ ፈተና ነገ ይሰጣል።ነገ ሰኞ ታህሳስ 42014 ዓም የህክምና ስፔሻሊቲ መግቢያ ፈተና የሚሰጥ ሲሆን ፈተናው በአማራ ክልልም የሚሰጥ ይሆናል።የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ለኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ፅፎ በነበረው ደብዳቤ አሸባሪው ህወሓት ወረራ በፈፀመት ወቅት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ ፈተናውን ለመፈተን ተመዝግበው በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ጠቅላላ ሀኪሞች ላይ ጫና በመፈጠሩ መግቢያ ፈተናው ለመፈተን ስለሚቸገሩ እንዲራዘም ወይም ሌላ የተለየ አማራጭ እንዲፈለግላቸው ጠይቆ ነበር።ጤና ሚኒስቴር በደብዳቤ በሰጠው ምላሽ የመግቢያ ፈተናው ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው የፈተና አስተባባሪዎች በአስራ ስምንቱ የመፈተኛ ጣቢያዎች ተሰማርተው ፈተናውን ለመስጠት በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን በመገለፅ ፈተናውን ለማራዘም እንደሚቸገር አሳውቋል።በዚህም የነገው ፈተና በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በአማራ ክልል ጨምሮ የሚሰጥ ይሆናል። ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች እና ለፀጥታ ኃይል አባላት በክልሉ ውስጥ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ምክንያት በወጣው መርሃግብር የመግቢያ ፈተናውን መፈተን የማይችሉ ሀኪሞች ካሉ ጤና ሚኒስቴር በሚደርሰው ማረጋገጫ አማካኝነት ሌላ ፈተና አዘጋጅቶ እንደሚያስፈትን አሳውቋል። ### Response:
### Text: በጎንደር ከተማ ህግ ተላልፈዋል የተባሉ 53 የፀጥታ አካላት እንዲጠየቁ መደረጉን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ገለፀ።መምሪያው ይህ ያሳወቀው በመምሪያው ኃላፊ አቶ ፋሲል ሰንደቁ አማካኝነት ለከተማው ነዋሪዎች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ የመወያያ ፅሁፍ ባቀረበበት ወቅት ነው።በከተማዋ የእገታ ወንደል ህገ ወጥ የጥይት ተኩስ ተጀራጅቶ ዘረፉ ዋና ወና የከተማዋ ወንጀሎች መሆናቸውን አቶ ፋሲል ገልፀዋል።በዚህ የእገታ ወንጀል ተሳትፈዋል የተባሉ 34 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን ተናግረዋል።4 በእገታ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው መሆኑም ጠቅሰዋል።በከተማዋ ኃላፊነታቸውን አልተወጡም የተባሉት 14 በየደረጃው በሚገኙ የፀጥታ አመራሮች 20 የፓሊስ አባላትና 14 የሚኒሻ አባላት ተጠያቂ መሆናቸውም አሳውቀዋል።የመስቀል በዓልን ምክኒያት በማድረግ ጥይት ተኩሰዋል የተባሉ 115 ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።የከተማዋን ፀጥታ በመጠበቅ ረገድም ህብረተሰቡ እያበረከተ ያለውን አስተዋፅዎ የሚበረታታ ነው የተባለ ሲሆን የጀመረውን የሰላም የፀጥታ ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠልና በከተማዋ አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት ድርሻውን ሊወጣ ይገባል ተብሏል።መረጃው የጎንደር ኮሚኒኬሽን ነው። ### Response:
### Text: ፕሬዝዳንት ካቦሬ በወታደሮች ታስረዋል።የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት በሀገሪቱ ወታደሮች መታሰራቸው ተነግሯል።ፕሬዝዳንት ሮች ካቦሬ የታሰሩት በአማጺ ወታደሮች ሲሆን በሀገሪቱ መዲና ኡጋዱጉ ባለ አንድ ወታደራዊ ማዘዣ ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል።የቡርኪና ፋሶ መንግስት በትናንትናው ዕለት የወታደሮቹ እንቅስቃሴ መፈንቅለ መንግስት አለመሆኑን ገልጾ ነበር።በቡርኪና ፋሶ ወታደሮች ውስጥ ጥያቄ እንዳነሱ የሚነገርላቸው አማጺ ወታደሮች አዛዦቻቸውን ጨምሮ መሪዎችን ገድለዋል።ይሄንን ተከትሎም የቡርኪና ፋሶ መንግስት ከትናንት ምሽት ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ጨምሮ የሰዓት ገደብ ጥሎም ነበር፡፡በምዕራብ አፍሪካ ሀገራት መፈንቅለ መንግስት ማድረግ የተለመደ ሲሆን አሁን ደግሞ ተራው የቡርኪና ፋሶ ሆኗል።የማሊ ወታደሮች በኮለኔል አስሚ ጎይታ የተመራ መፈንቅለ መንግስት በማድረግ አሁን ላይ የሽግግር ጊዜያዊ መንግስት መስርተው ማሊን በማስተዳደር ላይ ይገኛል።ኢኳቶሪያል ጊኒም መፈንቅለ መንግስት በማድረግ የሀገሪቱን ሲቪል አስተዳድር በማስወገድ ወታደረዊ መንግስት የመሰረተ ሲሆን እነዚህ ወታደራዊ መሪዎች ስልጣናቸውን በህዝብ ለተመረጡ መንግስታት እንዲያስረክቡ ኢኮዋስን ጨምሮ አፍሪካ ህብረት እና ሌሎች ተቋማት በማሳሰብ ላይ ናቸው።ምንጭ አል ዓይን ኒውስ ሮይተርስ ### Response:
### Text: በማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች ተከስቶ በነበረ ግጭት መደበኛ ትምህርታቸውን መከታተል ያልቻሉ ከ7ሺህ 600 በላይ ተማሪዎች ዘንድሮ የሚሰጡትን ክልላዊና አገር አቀፍ ፈተናዎች እንደማይወስዱ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላው አበበ እንደገለጹት በዞኖቹ በነበረው ግጭት በ53 የአንደኛና በአምስት የሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሥራ ተቋርጦ ቆይቷል።በግጭቱ ተማሪዎቹን ጨምሮ የትምህርት ቤቶቹ ማኅበረሰብ አባላት በመፈናቀላቸውና ተማሪዎች በቶሎ ወደ ትምህርት ገበታቸው ሊመለሱ ባለመቻላቸው ፈተናዎቹን እንዳይወስዱ ተወስኗል ብለዋል።ፈተናዎቹን የማይወስዱት ከ4ሺህ በላይ የስምንተኛ ክፍል እንዲሁም ከ3ሺህ 600 የሚበልጡት ደግሞ የ10ኛና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።ተማሪዎቹ በመጪው ዓመት ትምህርታቸውን በአግባቡ ተከታትለውና በቂ ዝግጅት አድርገው ፈተናዎቹን እንደሚወስዱም አመላክተዋል።እንደ ምክትል ቢሮው ኃላፊ ገለጻ ተማሪዎቹ በመጪው ዓመት መደበኛ ትምህርታቸውን በሚገባ ተከታትለው ፈተናዎቹን እንዲወስዱ ለማስቻል ቢሮው ከወዲሁ ዝግጅት እያደረገ ነው።በክልሉ ከ804 ሺህ በላይ የ8ኛ፣ የ10ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተናዎች እንደሚወስዱ ታውቋል።ምንጭ፡ ኢዜአ ### Response:
### Text: ምርጫ2013እናአዲስአበባ በአዲስ አበባ ድምፅ ሰጪው ረጅም ሰልፍ ነበረበት የሚልም ቅሬታ ነበር ይሄ ጉዳይ እንዴት ይታያል ወሪት ሶሊያና ምንም ጥያቄ የለውም በተወሰነ ደረጃ የድምፅ ሰጪዎች መንገላታት ቢያሳዝንም በሌላ በኩል ሲታይ ድምፅ ሰጪዎች በድምፅ መስጠት ሂደቱ ላይ ለመሳተፍ ረጅም ሰዓት ወስደው በከፍተኛ ወጥተው ድምፅ መስጠታቸው በጣም የሚያስደስት ነው ይህም በቦርዱ በጥሩ ጎኑ የታየ ነው። በአጠቃላይ በአአ የነበረው ምርጫ በወሪት ሶሊያና ሽመልስ አዲስ አበባ በጣም ጥቂት ችግር ካለባቸው አብዛኛው የምርጫ ሂደት ሁሉም ማለት ይቻላል ፓርቲዎች ሆኑ የግል ተወዳዳሪዎች ወኪሎቻቸውን ያስቀመጡበት በቆጠራ ሂደቱ ላይ አብዛኛዎቹ ከመጀመሪያው ጀምሮ ሂደቱ እስኪጠናቀ ድረስ ታዝበው ፈርመው የሄዱበት የቆጠራ ሂደት ያካሄድንበት ነው። በእርግጥ በአዲስ አበባ ጣቢያዎቹ ብዙ ቢሆኑም በከፍተኛ ደረጃ የፓርቲ ወኪሎች የተገኙበት ፣ ታዛቢዎች የተገኙበት፣ ዜጎች በጣም በረጅም ሰልፍ ሰዓት ወስደው የመረጡበት ፣ እስከ ለሊቱ 7 ሰዓት ሰፍል ላይ ያለው ሰው እንዳይቋረጥ ብለን ማንኛውም ድምፅ ሰጪ ድምፁን እንዲሠጥ ያደረግንበት ፣ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ከልሎች ቦታዎች በተሻለ ሁኔታ ግልፅ የሆነበት እና ሚዲያን የሲቪክ ማህበራትም ፣ የፓርቲ ወኪሎች እኛም እራሳችን እየዞርን ያየንበት ነው። ### Response:
### Text: ትዴት ተቃዋሚው የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ትዴት ፓርቲ ዛሬ በአዲስ አበባ ባካሄደው ውይይት ትግራይ ውስጥ አሁንም አፈና ቀጥሏል አለ። ህዝብን ከድህነት ለማላቀቅ የሚጥሩ ፓርቲዎች በነጻነት መንቀሳቀስ እንዳልቻሉም ገልጿል። የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ትዴት ትግራይ ውስጥ አሁንም አፈና መቀጠሉን እና ህዝቡን ከድህነት ለማላቀቅ የሚጥሩ ፓርቲዎች በነጻነት የመንቀሳቀስ መብት ለውጥ እንዳልታየበት ገለጸ።0የትግራይ ህዝብ በጠላት ተከብበሃል እየተባለ በህወሓት ሽብር እና ፍርሃት እየተለቀቀበት ለግጭትም እንዲጋበዝ እየተገፋ ነው ያሉት የትዴት ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ ችግሩ የጋራ በመሆኑ በትብብር ልንታገለው ይገባል ሲል በአዲስ አበባው ውይይት ላይ አሳስበዋል። ህዝቡ ህወሓት እንደሚለው ጠላት የለውም ሲሉም ለተሳታፊዎቹ ተናግረዋል።0አብዛኛው የትግራይ ህዝብ ድህነት ውስጥ ነው ያለው ትዴት በትግራይ ያለው ችግር ተባብሶ በመቀጠሉ ሕወሃት በቃንየሚለው ህዝብ ቁጥር እየጨመረ መጥቷል 0ብሏል። ተቃዋሚ ፓርቲው በዛሬው የአዲስ አበባ ስብሰባው ሶሻል ዴሞክራሲ የፖለቲካ መርህን እንደሚከተል ለደጋፊዎቹ እና ለውይይት ተሳታፊዎቹ አስታውቋል። ዴሞክራሲ እና ፍትሃዊነት የሰፈነባት ኢትዮጵያ እንድትገነባም የድርሻዬን እጥራለሁ ሲል ቃል ገብቷል።0 የጀርመን ድምፅ ራድዮ ### Response:
### Text: ነሃሴ 252012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 1 በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 599 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 22 ሰዎች በኮቪድ19 መያቸው ተረጋግጧል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 3343 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 127 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 28 ከአርሲ ዞን 25 ከጉጂ ዞን 14 ከቡራዩ ከተማ 13 ከቢሾፍቱ ከተማ ይገኙበታል።አጠቃላይ በኦሮሚያ 6301 በቫይረሱ የተያዙ 45 ሞት 1953 ያገገሙ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 161 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 22 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ የተያዙት 21 ከደምቤ አጋሎ ወረዳ 1 ከሆምሻ ወረዳአጠቃላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ 651 በቫይረሱ የተያዙ 303 ያገገሙ በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 4894 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 75 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 15 ከሰሸዋ ዞን 12 ከደጎንደር ዞን 10 ከሰወሎ ዞን 9 ከዋግ ብሰብ ዞን 7 ከባህር ዳር ከተማ 6 ከደሴ ከተማ ይገኙበታል።አጠቃላይ በአማራ 2412 በቫይረሱ የተያዙ 22 ሞት 1261 ያገገሙ በሀረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 440 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 4 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል የ1 ሰው ህይወት አልፏል። አጠቃላይ በሀረሪ 1147 በቫይረሱ የተያዙ 21 ሞት 376 ያገገሙ ### Response:
### Text: ጥቅምት 12013 ዓምየኢትዮጵያ ኮቪድ19 መረጃዎች በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 142 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 7 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 104 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 39 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 1154 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 99 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከ99ኙ መካከል 64 ከምዕጎጃም ዞን ፣ 16 ከባህር ዳር ከተማ ይገኙበታል። በድሬዳዋ 142 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 47 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቷል። በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 468 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 19 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 471 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 169 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 3913 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 365 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል። በሐረሪ ባለፉት 24 ሰዓት 120 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 53 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል። በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 645 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 50 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል። በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 184 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 18 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል። ### Response:
### Text: በትላንቱ ስብሰባ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከኢትዮጵያ ጋር የተዋጣ ግንኙነት እንዲኖር ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን አሁንም እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።እንደውም ለኢትዮጵያ መንግስት ታደላለህ በሚል ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሲወቅሱኝ ቆይተዋል ሲሉ ተናግረዋል።ለአምባሳደር ታዬ ባቀረቡት ጥያቄም በኢትዮጵያ መንግስት በኩል እስካሁን ድረስ ለተመድ የገባ ደብዳቤ የለም ከተባረሩት 7 የተመድ ሰራተኞች በአንዱም ላይ ቢሆን አንድም ደብዳቤ ካለ ያቅርቡልኝ የማውቀው ነገር የለም ስለሚባለው ክስ ብለዋል።ገተሬዝ በግልፅ የተመድ ባለስጣናት እና ሰራተኞቹን ኢትዮጵያ የማባረር መብት የላትም ያሉ ሲሆን ግለሰቦቹን በማባረር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግ ጥሳለች ብለዋል።ማንኛውም የተመድ አባል ከስነ ምግባር ውጭ ያደረገው ምንም አድራጎት ካለ እንድናውቅ እንፈልጋለን ሲሉም ተደምጠዋል።አጀንዳችን አንድ ብቻ ነው እሱም የኢትዮጵያ ህዝብ መከራ እንዲያበቃ እንፈልጋለን ይህ ነው አጀንዳችን ሲሉ ተናግረዋል።አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ንግግሮች መደረግ ያለባቸው በኢትዮጵያ እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት መካከል እንዲሆን ጠይቀው አፋጠነው ማስረጃውን ለማቅረብ እንደሚሰሩ ገልፀዋል። እንዲሁም ሀሳብዎት እና ልቦናዎት ከኛ ጋር በመሆኑ እናደንቃለን ብለዋል።የመረጃ ግብአት ቪኦኤና የ ገፅ። ### Response:
### Text: ዶይቼ ቨለ ከአቶ በረከት ጋር️በቅርቡ ከብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው የታገዱት አቶ በረከት ስምዖን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከዶይቼ ቬለው ነጋሽመሐመድ ጋር ዛሬ ቃለ ምልልስ አድርገዋል። ይህ ቃለምልልስ ምሽት 1 ሰዓት በጀርመን ድምፅ ራድዮ የአማርኛ ዝግጅት ላይ የሚቀርብ ይሆናል። ዶቼ ቨለ ከቃለመጠይቁ ቀንጭቦ ለፌስቡክ ተከታዮቹ ይህን አቅርቧል️ ከማዕከላዊ ኮሚቴ ለመታገዴ የውጭ ኃይል እንዳለበት ፍንጭ አለኝ። ሃያ ሰባት ዓመት በስልጣን ስቆይ አንድም ካሬ ሜትር አልወሰድኩም። አሁንም በመንግስት ቤት ነው የምኖረው። ለውጥ እንዲመጣ የመጀመሪያው ታጋይ ነኝ ብልህ ይገርመሃል። የአራቱም የኢህአዴግ አባል ፓርቲ ሊቀመናብርት እና ምክትል ሊቀመናብርት በሙሉ ለዉጥ እንዲደረግ ስጠይቅ ተቃዋሚ ነበሩ። ለውጡን በተመለከተ የእያንዳንዱን የኋላ ታሪክ አውቃለሁ። ከፈለጉ በመገናኛ ብዙሃን ይግጠሙኝ ። ባለፉት ዓመታት ትልቅ ፈተና የነበረው መሪዎች ራሳቸውን ለማብቃት ትኩረት አልሰጡም። የፖለቲካ ውይይት እንኳ ለማድረግ ፍቃደኛ የነበረ አመራር አልነበረም። አጀንዳ ጀምሮ እንኳ ለመጨረስ ፍቃደኛ የነበረ አመራር አልነበረም። ይቺ ሀገር የሚያስጎመጀም፣ የሚያስፈራም ሁኔታ ላይ ነው ያለችው። አሁን የተያዘው ለውጥ ሚዛኑን ጠብቆ ከቀጠለ ኢትዮጵያ ከፍ ወዳለ ደረጃ ትደርሳለች። ### Response:
### Text: ካለብን ታሪካዊ እና ሞራላዊ ኃላፊነት አንጻር ናሚቢያውያን ይቅር እንዲሉን እንጠይቃለን ሄኮ ማስጀርመን ናሚቢያን ቅኝ በገዛችበት ወቅት ጅምላ ጭፍጨፋዎችን መፈጸሟን አመነች፡፡ጀርመን እአአ ከ190408 ባሉት ዓመታት በናሚቢያ ዜጎች ላይ የፈጸመችውን ግድያ በጅምላ ጭፍጨፋነት ለመቀበል ስታቅማማ ቆይታለች፡፡ነገር ግን 5 ዓመታትን በወሰደ ንግግር ጭፍጨፋውን ስለመፈጸሟ አምና ተቀብላለች።ይህን ተከትሎ በተደረሰ ስምምነት መሰረት ለተለያዩ ልማቶች የሚውል የ13 ቢሊዬን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ተስማምታለች።ጄኔራል ሎታር ቮን ትሮታ በሄሬሮ ጎሳዎች የተነሳውን የጸረ ቅኝ ግዛት ተቃውሞ ለማርገብ በማሰብ ሙሉ የጎሳው አባላት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ በማዘዝ 65 ሺ ገደማ የጎሳው አባላት መጨፍጨፋቸውን እና በትንሹ 1 ሺ የናማ ጎሳ አባላት መገደላቸውን የታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ።የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄኮ ማስ ካለብን ታሪካዊ እና ሞራላዊ ኃላፊነት አንጻር ናሚቢያውያን ይቅር እንዲሉን እንጠይቃለን ብለዋል ባወጡት መግለጫ፡፡ማስ በመግለጫቸው ዓላማችን ተጎጂዎቹ የሚታወሱበትን እውነተኛ የእርቅ መንገድ መፈለግ ነው ብለዋል፡፡ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዛሬዋ ናሚቢያ ቅኝ ግዛት ዘመን የተፈጸሙ የጭካኔ ድርጊቶችን በይፋ ጅምላ ጭፍጨፋ ብለን እንጠራቸዋለን ሲሉ ተናግረዋል። አልዓይን ### Response:
### Text: ኢትዮ ቴሌኮም የ4 አገልግሎት ተደራሽነትን እያሰፋ ይገኛል።ከዚህ ቀደም በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞች ተግባራዊ የተደረገው የ4 አገልግሎት በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ ዛሬ ተጀምሯል።ጋምቤላ ከተማ በኢትዮ ቴሌኮም የ ደቡብ ምዕራብ ምዕራብ ቀጠና የሚገኝ ሲሆን የ4 እና የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራውን ተጠናቆ ስራ ጀምሯል።በዚህ ቀጠና 28000 ደንበኞች የዳታ ተጠቃሚዎች ናቸው።በጋምቤላ ከተማ አገልግሎቱን የማስጀመሪያ ስነስርዓት የተካሄደ ሲሆን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሪት ፍሬህይወት ታምሩ ተገኝተው ነበር።በሌላ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በተያያዘ መረጃ ኢትዮ ቴሌኮም ከአፍሪካ የቴሌኮም አገልግሎት ኩባንያዎች ውስጥ በሁለተኛ ደረጃ መቀመጡ ተሰምቷል።በአፍሪካ 195 የቴሌኮም ኦፐሬተሮች ያሉ ሲሆን ኢትዮ ቴሌኮም በግዝፈት፣ በደንበኛ ቁጥር እና በአገልግሎት ደረጃ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ከዓለም ደግሞ 28ኛ ደረጃን ይዟል። ይህን ያሳወቀው ግሎባል ሲስተምስ ፎር ሞባይል ኮሙኒኬሽንስ ወይም በእንግሊዝኛ ምህጻረ ቃል የተባለ ተቀማጭነቱ እንግሊዝ ሀገር የሚገኝ ተቋም ነው። በዓለም ዙርያ ከ750 በላይ የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪ ተቋሞችን በአባልነት አቅፎ የያዘና ኩባንያዎቹን በሥራቸው ልክ ጥራት እና ደረጃ መዝኖ ሪፖርት የሚያድርግ ዓለም አቀፍ ተቋም መሆኑን ሸገር አስነብቧል። ### Response:
### Text: ምዕራባዊ ኦሮሚያ ግጭት መታየቱ ተሰማ️በምዕራባዊ ኦሮሚያ ክልል በሚገኙት አከባቢዎች የኦሮሞ ነፃ አዉጭ ግንባር ኦነግ ስራዊት ናቸዉ በተባሉና በኢትዮጵያ መከላክያ ሰራዊት መካከል ላለፉት ቀናቶች ግጭት መታየቱን የአከባቢዉ የዓይን እማኞች ለዶይቼ ቬሌ ገልጹ። ግጭቱን ተከትሎ የክልሉ ፕሬስዳንት አቶ ለማመገርሳ በትላንትናዉ እለት እንደተናገሩት ሁኔታዉ በጣም እንዳሳዘናቸዉ ገልፀዋል። ወጣቶች መሳርያ በመታጠቅ ዘመናዊ መሳርያ ከታጠቀዉ ከመንግስት ሰራዊት ጋር ለመወጋት ወደ ጫካ መግባታቸዉ ስህተት መሆኑን እና ትክክለኛ የትግል ስልት አለመሆኑን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ለማ መገርሳ ተችተዋል።አከባቢዉ ላይ ባለዉ የፀጥታ አለመረጋጋት ምክንያት የሰዎች እንቅስቃሴን እና የንግድ ሂደቱን ማገቱንም ገልፀዋል። ጫካ የገቡት እነዚህ ወጣቶች ወደ ቀያቸዉ እንዲመለሱ ለማድረግ ከሽማግሌዎች ጋር በመሆን እንደሚሞክሩ እንዲሁም ማህበረሰቡ በጠረጴዛ ዙርያ መወያያት እንደለበት አቶ ለማ አሳስበዋል። ይህ የማይሆን ከሆነ ለተከሰተዉና ለሚከሰተዉ ችግር መፍትሄ መስጠት እንደሚያስቸግር ገልፀዋል። ካለፉት ሁለት ቀናት ጀምሮ በተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች «መንግስት የኦነግ ስራዊት ለማጥቃት ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ» በመቃወም ወጣቶች ሰላማዊ ሰልፎችን እያደረጉ ይገኛሉ።ምንጭ ዶቼ ቨለ ### Response:
### Text: ሲአን ሲዳማዞን ሞረቾ ወተረሬሳ ሀገረሰላም በደቡብ ክልል በሐዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን የገጠር ከተሞች በተከሰቱ ግጭቶች የሞቱት ሰዎች ቁጥር 21 መድረሱን የሲዳማ አርነት ንቅናቄ አስታወቀ። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ኔሳ ዛሬ ለጀርመን ራድዮ እንደተናገሩት በሲዳማ ዞን ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር በነበረ ግጭት 21 ሰዎች መሞታቸው ተናግረዋል። በሲዳማ ዞን ስር ባለው ወተረሬሳ 12 ሰዎች መሞታቸውን የሚናገሩት አቶ ደሳለኝ በሞሮቾ ሶስት እና በሀገረሰላም ደግሞ ሁለት ሰዎች በግጭቱ ህይወታቸው እንዳለፈ አስረድተዋል።በሐዋሳ በነበረው ግጭት አራት ሰዎች መሞታቸውን እና ሌሎች ሰባት ሰዎች በፅኑ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ከንቲባ አቶ ስኳሬ ሾዳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። በግጭቱ የተጠረጠሩ 150 ሰዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ከንቲባው ጠቁመዋል። ግጭቱን ተከትሎ የክልል እና የፌደራል አካላት ባደረጉት የማረጋጋት ስራ በሐዋሳ ከተማ እና በአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ መሻሻሉን አቶ ስኳሬ ገልፀዋል። በሐዋሳ በዛሬው ዕለት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንደታየና የማህበራዊ አገልግሎት መስጫዎች ተከፍተው ስራ መጀመራቸው ተሰምቷል። የኢንተርኔት አገልግሎት እና የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ግን አሁንም ዝግ ናቸው።ምንጭ የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: ብሔራዊ ባንክ ከባንክ ዉጭ ይዞ መንቀሳቀስ የሚቻለዉን የገንዘብ መጠን በድጋሜ ዝቅ ማድረጉ ተገለፀ።ባንኩ ትናንት ካቲት 29 ጀምሮ ይህንንና መሰል ጉዳዮችን የያዙ መመሪዎች ላይ ማሻሻያ አድርጓል።በማሻሻያዉ መሰረት ከባንክ ዉጭ ይዞ መንቀሳቀስ የሚቻለዉ የገንዘብ መጠን ለድርጅቶች ወደ 200000 ብር እንዲሁም ለግለሰቦች ወደ 100000 ብር ዝቅ እንዲል አድርጓል።ባንኩ ተመሳሳይ የገንዘብ መጠን ገደብ የሚጥል መመሪያ ሲያወጣ በ6 ወራት ዉስጥ ለ2ተኛ ጊዜ ሲሆን ከ6 ወራት በፊት የወጣዉና እስካሁን ተግባራዊ ሲደረግ የቆዬዉ መመሪያ ከባንክ ዉጭ ሊኖር የሚችለዉ የገንዘብ መጠን 15 ሚሊዮን ብር የነበረ መሆኑ ይታወቃል፡፡በተመሳሳይም የዳያስፖራ አካዉንት ባለቤቶች የገቢ ንግድ ላይ የሚሳተፉበት አካሄድ እንዲሁ ማሻሻያ ተደርጎበታል።በዚህ መሰረት እነዚሁ ደንበኞች በአስመጭነት መሳተፍ የሚችሉት ባንኩ ቅዲሚያ ትኩረት እንዲያገኙ መርጫቸዋለሁ ባላቸዉ ዘርፎች ላይ የተወሰነ የዉጭ ምንዛሬ አቅርቦት እንደሚኖር ተገልጿል፡፡እነዚህ ለተለያዩ የፋብሪካ ምርቶች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ጥሬ እቃዎች ፣ መድሃኒቶች ፣ እንዲሁም በተለዬ አስፈላጊ የተባሉ የምግብ እና ምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ ብቻ እንዲሆን ታስቦ መመሪዉን ማሻሻል እንዳስፈለገ የባንኩ ምክትል ገዥ አስረድተዋል፡፡ምንጭ አሀዱ ቴሌቪዥን ### Response:
### Text: ዎላይታ ታይምስ የተሰኘው ሚዲያ ከመንግስት አካል ይደርስብኛል ባለው ጫና ሥራ ማቋረጡን ገልጿል።በኢትዮጲያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን በሚዲያ ሥራ ለመሰማራት ሕጋዊ ፈቃድ ወስዶ በዞናዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ የነበረው ዎላይታ ታይምስ ሚዲያ በደረሰበት ጫና ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ሥራ ማቆሙን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላከው መረጃ ያሳያል።የሚዲያው መስራች የሆነው ጋዜጠኛ ናትናኤል ጌቾ በሥራው በተደጋጋሚ ለእስርና ለእንግልት፣ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት መዳረጉን ጠቅሶ በቅርቡም ከቀን 19032015 ዓም ጀምሮ በመንግስት ላይ ጥላቻና ሀሰተኛ መረጃ አሰራጭቷል በሚል ተጠርጥሮ በዎላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ እንደነበር ተናግሯል።ጋዜጠኛው በዎላይታ ሶዶ ከተማ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ታስሮ ከቆየበት ትላንት 2832015 ዓም በሰላሳ ሺ 30000 ብር ዋስትና መለቀቁን ተናግሯል። ተመሳሳይ አይነት ጫና በመኖሩም ሌሎች የሚዲያው ጋዜጠኞችም ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰባቸው በመሆኑ ሥራው ተቋርጦ ቢሮው መዘጋቱን አክሎ ገልጿል፡፡ሚዲያው እየደረሰበት ያለውን ከፍተኛ ጫና ለኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት በደብዳቤ ጭምር ማስታወቁን የገለጸ ቢሆንም ምንም አይነት ምላሽ አለማግኘቱን ጋዜጠኛ ናትናኤል ጌቾ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።ያንብቡ 1210 ### Response:
### Text: ነሃሴ 162012 ዓምየኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 2 በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 4442 የላብራቶሪ ምርመራ 121 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 21 ከምዕጎንደር ዞን 18 ከሰወሎ ዞን 17 ከሰሸዋ ዞን 16 ከደሴ ከተማ 15 ከዋግ ብሰብ ዞን 14 ከደወሎ ዞን 8 ከባህር ዳር ከተማ ይገኙበታል።አጠቃላይ በአማራ 1772 በቫይረሱ የተያዙ 19 ሞት 668 ያገገሙ ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 307 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 13 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል። ሁሉም ከማህበረሱ ከተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው።አጠቃላይ በድሬዳዋ 794 በቫይረሱ የተያዘ 20 ሞት 612 ያገገሙ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 766 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 113 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ተያዙት 113 ሰዎች መካከል አንድ መቶ አምስቱ 105 ከሀዋሳ ከተማ ናቸው።አጠቃላይ በሲዳማ 1017 በቫይረሱ የተያዙ 13 ሞት 268 ያገገሙ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 24 ውስጥ በተደረገው 4428 የላብራቶሪ ምርመራ 607 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። እንዲሁም በ24 ሰዓታት ውስጥ የ18 ሰዎች ሰዎች ህይወት አልፏል። 12 ከአስከሬን ምርመራ 6 ከጤና ተቋም በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2177 የላብራቶሪ ምርመራ ሃምሳ አንድ 51 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ ውስጥ በ2021 እአአ በተለያዩ ምክንያቶች የምግብ ርዳታ የሚያስፈልገው ሕዝብ ቁጥር ከፍ ማለቱን የርሃብ ስጋት ማስጠንቀቂያ የሚያመላክተው ዓለም አቀፍ ተቋም አመለከተ። ተቋሙ ባወጣው ሪፖርት በተለይ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝ በተባባሰው የጎሳ እና የፖለቲካ ውጥረት 3 ሚሊየን ገደማ ሰዎች በሀገር ውስጥ ሳይፈናቀሉ እንዳልቀሩ አመልክቷል።ከተፈናቀሉት 3 ሚሊዮን ገደማ ሰዎች አንድ ሚሊየን የሚሆኑት ትግራይ ውስጥ ይገኛሉ ተብሏል።በተጨማሪ ትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ከሚታየው አለመረጋጋት ሌላ ከመጋቢት ወር እስከ ግንቦት ባለው ጊዜ የሚጠበቀው ወሳኝ የዝናብ ወቅት የነበረው የዝናብ እጥረት ሰብል በማምረት የሚታወቁ አካባቢዎች ምርት እንዲቀንስ ማድረጉም ለችግሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጿል። የሀገሪቱ የማክሮ ኤኮኖሚ ይዞታ ዝቅ ማለት የምግብ ዋጋ እንዲንር ማድረጉ የመግዛት አቅምምን መጉዳቱ ሌላው ምክንያት እንደሆነ አስረድቷል።ከላይ የተገለፁት እና ተያያዥ መንስኤዎች አብዛኛው ድሀ ቤተሰብ ምግብ የማግኘት ዕድሉን በመዝጋታቸው ግጭቶቹን ባፋጣኝ በማቆም፣ ሰብዓዊ ርዳታን ከፍ በማድረግ ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ማድረስ የሚቻልባቸውን መንገዶች ማመቻቸት እንደሚያስፈልግ ማመልከቱን ዲ ደብሊዩ አስነብቧል። ### Response:
### Text: መግለጫ በአገሪቱ እየመጡ ያሉ ለውጦችን ለማደናቀፍ እየተሰሩ ያሉ ሴራዎችን የሚመረምሩ ኮሚቴዎች ተቋቋሙ።የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅቤት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ሰኔ16፣ 2010 በጠቅላይ ሚኒስትር ዶር አብይ አህመድ መሪነት በአገሪቱ የተጀመረውን ለውጥ እውቅና ለመስጠት፣አገራዊ አንድነትን ለመገንባትና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን ለመደገፍ በወጣው ህዝብ ላይ ቦምብ ተወርውሯል፣ ሂደቱ እንዲስተጓጎልም ተደርጓል፡፡ሰላማዊ ሰልፉን ለማደናቀፍ ቦምብ ከመወርወር ጀምሮ ሂደቱ እንዲስተጓጎል በወቅቱ መብራትና የቴሌኮም ኔትወርክ ማጥፋት፣ የኢኮኖሚ አሻጥር በተደራጀ አኳኋን በመስራት የኑሮ ውድነትን እንዲባባስ እና የተለያዩ ህዝባዊ አገልግሎት እንዲሰጡ የተቋቋሙ ተቋማት አስፈላጊውን አገልግሎት እንዳይሰጡ እየተደረገ መሆኑን ለማረጋገጥ መቻሉንም ጽቤቱ አመልክቷል፡፡እነዚህን ህገወጥ ተግባራት አጣርቶ ለህግ የሚያቀርብ ከተለያዩ አካላት የተለያዩ ኮሚቴዎች ተቋቁመው ስራቸውን እያከናወኑ መሆኑን ፅቤቱ ገልጿል፡፡ለተልዕኮው ስኬታማነትም መላው ሰላም ወዳድ ህዝብ ከኮሚቴው ጎን በመቆም ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግና አጥፊዎችን ለፍርድ ለማቅረብ እንዲተባበር ተጠይቋል፡፡ውጤቱን ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ፅቤቱ አመልክቷል፡፡© ### Response:
### Text: ሀዋሳ️በሐዋሳ ከተማ የድንገተኛአደጋዎችና የቀዶ ጥገና ስፔሻላይዝድ ህክምና ማዕከል ትናንት ተመረቀ።የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ በስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የክልሉ መንግሥት የኅብረተሰቡን የጤና ፍላጎት ለማሟላት ለባለሀብቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።የግል ባለሀብቶች በዘርፍ ለተገኙ ውጤቶች ድርሻቸው ከፍተኛ ሲሆን÷ ወደፊትም ለዚሁ ተግባር ኢንቨስትመንት የሚውል መሬት እንደሚመቻችላቸውም ነው የተናገሩት።ባለፉት ዓመታት 4ሺህ 670 የጤና ተቋማትን መገንባታቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳደሩ÷ የሰው ኃይልና ቁሳቁስን በማሟላት በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ዕድገት ተምዝግቧል ብለዋል።የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቅናው ካውዛ በበኩላቸው ማዕከሉ በድንገተኛ አደጋዎች የሚከሰተውን ሞትና የአካል ጉዳት ለመቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።የያኔት የድንገተኛ አደጋዎችና የቀዶ ጥገና ስፔሻላይዝድ ህክምና ማዕከል ባለቤት ዶክተር ግርማ አቢ እንዳሉት÷ ማዕከሉ በኢትዮጵያ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሶስተኛ ደረጃ በገዳይነቱ የሚታወቀውን በትራፊክ እና ሌሎች አደጋ ጉዳተኞችን እንደሚስተናግድተናግረዋል፡፡ማዕከሉ ባለ 11 ወለል ህንጻ የህክምና አገልግሎት ለሚሰጥበት ሆስፒታል ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጥሏል።ምንጭ ፡ ኢዜአ ### Response:
### Text: አጫጭር መረጃዎች በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት 1481 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል 48 ሰዎች ሞተዋል። በኢራን ዛሬ መስጊዶች በጊዜያዊነት ተከፍተው ሌሎችም እንቅስቃሴ ላይ የተጣሉ ገደቦች እየተነሱ እንደሚቀጥሉ ተገልጻል በሩሲያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ በልጧል ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 10899 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 232243 ደርሰዋል። የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸው ሆስፒታል ገብተዋል። የቻይናዋ ዉሃን ከተማ አስራ አንድ ሚሊዮን የሚደርስ ነዋሪዋን የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ልታደርግ ዕቅድ እያዘጋጀች መሆኑ ተነግሯል በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት 176 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 26920 ደርሷል። በዩናይትድ ኪንግደም ትላንት ብቻ 627 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 32692 ደርሷል። በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር ከ82000 በላይ ሆኗል። በኳታር በአንድ ቀን 1526 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 25149 ደርሷል። በሳዑዲ አረቢያ በ24 ሰዓት 1911 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ 9 ሰዎች ሞተዋል። በቻይና ትላንት 1 ሰው በቫይረሱ ተይዟል በደቡብ ኮሪያ ደግሞ 27 ሰዎች ተይዘዋል እንዲሁም 2 ሰዎች ሞተዋል። ### Response:
### Text: ለኮቪድ19 የሚሰጠው ትኩረት መቀነስ አሳሳቢ ነው በዶክተር መክብብ ካሳየዓለም ጤና ድርጅት እንደተነበየው የኮቪድ19 ወረርሽኝ ክትባት በስፋት ጥቅም ላይ እስኪውል የሁለት ሚሊየን ሰዎች ህይወት ሊያልፍ ይችላል፡፡በሀገራችን የበሽታው አሳሳቢነት ጨመረ እንጂ አልቀነሰም በየቀኑ የበርካታ ዜጎቻችንን ህይወት እየቀጠፈ ነው፡፡የዓለም ጤና ድርጅት የሚከተሉትን አራት መንገዶች ሀገራት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ይመክራል፡፡ 1 የቫይረሱን ስርጭት ሊያባብሱ የሚችሉ ኘሮግራሞችን መገደብ፡፡2 በቀላሉ ሊጎዱ ለሚችሉ ዜጎች ትኩረት መስጠት፡፡3 ማህበረሰብን ስለ ወረርሽኙ ማስተማርና ማንቃት፡፡4 መመርመር፣ የታመሙት ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ፣ እና ንክኪ ያላቸውን መለየትና መመርመር ናቸው፡፡የሚደረገው ምርመራ መቀነስ ፣ ንክኪ ያላቸውን ግለሰቦች ለይቶ የመመርመር ስራ መቀነስ ፣ አርአያ መሆን የሚችሉ ታዋቂ ግለሰቦች የመንግስት እና የግል ተቋማት ተወካዮች የሚያሳዩት ቸልተኝነት እና የሚድያው መሰላቸት ተደማምሮ ወረርሽኙን በቀላሉ መቆጣጠር እንዳንችል የብዙዎችንም ልፋት መና እንዲቀር ያደርጋል፡፡ትንፋሽ አጥሯቸው የሚሰቃዩትን ወገኖቻችንን እናስባቸው የእኛ ቸልተኝነት ለራሳችንም ለሌሎችም ህይወት ማለፍ ምክንያት ሊሆን ይችላል ሁሉም ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል፡፡ ### Response:
### Text: የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ አደርገዋለሁ ያለውን አዲሱን የደንብ ልብስ እና አርማ ዛሬ በይፋ በመስቀል አደባባይ አስተዋውቋል።አዲሱ የደንብ ልብስ እና አርማ ከላይ በፎቶ ተያይዟል።አዲሱ የፖሊስ አርማ ምን አካቷል የሚሰጠው ትርጉም ምንድነው ጋሻ መከላከልን፣ ጥንካሬን፣ ድፍረትና ጀግንነትን ይወክላል ተብሏል። ቀጥ ያሉ እኩል ጨረሮች ጨረሮቹ የብሄር ብሄረሰቦችን፣ የህዝቦችን እና የሃይማኖት እኩልነትን የሚያሳዩ ናቸው። የተከበበ ክብ መስመር ጋሻነትን ለማመልከት የተቀመጠ ነው። የፍትህ ሚዛን የፍትህ ስርዓትን የሚወክል ነው። ሁሉንም ዜጎችን በእኩል አይን በማየት ፍትህን ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ለማሳየት የተቀመጠ ነው። የዘንባባ ዝንጣፊ የሰላም ምልክት ሆኖ የቀረበ ሲሆን ፖሊስ የሰላም ዘብ መሆኑን ለማሳየት የተቀመጠ ነው ተብሏል። ባለ 5 ጎን ኮከብ የፖሊስን ማዕረግ የሚወክል ነው። በተጨማሪ ኮከቡ የኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ስርኣትን፣ የብሄር ብሄረሰቦችን አንድነት እና እኩልነት ማሳያ ተደርጎ የቀረበ ነው ተብሏል። ቀለማት ሰማያዊ ሰላምን የሚወክል ነው ፣ ወርቃማ ቀለም የክብር እንዲሁም የአሸናፊነት አስተሳሰብን የሚወክል ነው ፣ ብራማ ቀለም በአርማው ዙሪያውን ከቦት የሚገኝ ሲሆን የፖሊስን ጋሻነት እና መከታነት ለማሳየት ነውከአዲስ ቴቪ ያገኘነው መረጃ። ### Response:
### Text: ችሎት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የክስ መዝገብ ተከሳሾች ላይ የዐቃቤ ሕግ መስክሮችን ለመስማት የያዘው ቀጠሮ ተፈጻሚ ሳይሆን ቀርቷል።ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን ሳይሰማ የቀረበው የተከሳሽ ጠበቆች ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረባቸውን ተከትሎ ነው።ከተከሳሽ ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ከድር ቡሎ ለቢቢሲ እንደተናገሩት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጃዋር መሐመድን ጨምሮ አራት ተከሳሾች በሌሉበት የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች ይሰሙ ሲል ያሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርበዋል።ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የቀረበው ይግባኝ መርምሮ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች እንዳይሰሙ ማዘዙንም ጠበቃው ከድር ቡሎሎ ተናግረዋል።የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ በተከሳሾቹ ላይ የዐቃቤ ሕግ መስክሮችን ከዛሬ ሰኞ ጥቅምት 222014 ዓም ጀምሮ ለመስማት ቀጠሮ ይዞ ነበር።ሥራ አስፈጻሚው አካል ሕግ እስካላከበረ ድረስ ፍርድ ቤት አንገኝም በማለታቸው አራቱ ተከሳሾች በሌሉበት ጉዳያቸው እንዲታይ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላልፎ እንደነበረ ይታወሳል።የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተከሳሽ ጠበቆች አቤቱታን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለኅዳር 07 2014 ዓም ቀጠሮ መስጠቱን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል። ### Response:
### Text: የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በዚህ ሳምንት 2 በረራዎችን ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ በማድረግ የህክምና ቁሳቁሶችን አድርሷል።ባለፈው ሳምንት በ5 በረራዎች እጅግ አስፈላጊ የህክምና ቁሳቁሶችን ወደ ትግራይ ክልል መቐለ ማጓጓዙና ማከፋፈል መጀመሩን መግለፁ ይታወሳል።በዚህ ሳምንት ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና ከቀይ መስቀል የቀረቡ መድሃኒቶችና ሌሎች የህክምና አቅርቦቶችን በመያዝ 2 ተጨማሪ በረራዎች ወደ ትግራይ ክልል ተደርገዋል።በዚህ ሳምንት በቀሩት ቀናት እና በሚቀጥሉት ሳምንታት ተመሳሳይ በረራዎች እንደሚደረጉ እና ይህም ቀጣይነት ያለው እርዳታ እንደሚሆን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታውቋል።የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ላለፉት ወራት የህክምና አቅርቦት ማድረግ እንዳልቻለ ገልፆ አሁን እየተደረጉ ያሉት እጅግ በጣም አስቸኳይ ለሰዎች ህይወት አድን የሚሆኑ አቅርቦቶች ናቸው ብሏል።ከዚህ በተሻለ በርካታ የህክምና ቁሳቁሶች እና መድሃኒቶችን ለማድረስ ከአየር ላይ በረራ በተጨማሪ በየብስ ለማጓጓዝ መታሰቡን ይህን ተግባራዊ ለማድረግም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል።የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በአፋር ክልል እና አማራ ክልል ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ገልጿል። ፎቶ ፋይል ### Response:
### Text: የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻችውን አስመረቁ። ዛሬ ተማሪዎቻቸውን ካስመረቁት ዩኒቨርሲቲዎች መካከልም የሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ይገኝበታል። ዩኒቨርሲው በተለያዩ መርሃ ግብር ያስተማራቸውን ከ 5 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን አስመርቋል። በተጨማሪም ለአርቲስት አሊ ሸቦ እና ለዶክተር አበራ ደሬሳ የክብር ዶክተሬት ሰጥቷል። በሌላ በኩልየጎንደር ዩኒቨርሲቱ በተለያዩ የትምህርት መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 365 ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከልም 3 ሺህ 227 ተማሪዎች ሴቶች ናቸው። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ አወል አርባ ተመራቂዎች በራሳቸው አቅምና ሀይል በመተማመን የጋራ ሀገራቸውን እንዲገነቡ ጥሪ አቅርበዋል። እንደ ኤፍ ቢሲ ዘገባ ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት 47 ሺህ 723 ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር አስራት አፀደ ወይን ተናግረዋል።በሌላ በኩል የወልዲያ ዩኒቨርሲቱ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ድግሪ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 627 ተማሪዎችን እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 6 ሺህ 857 ተማሪዎችን አስመርቀዋል። በተጨማሪም ጅማ፣ ወለቂጤ፣ ደብረ ታቦር እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን አስመርቀዋል።ምንጭ ኢፕድ ቀን ሰኔ 292011 ዓም ### Response:
### Text: ሰብሌን ያዳነችልንን ሰብልዬን እናመሠግናለን በቃሉ ወረዳ የ019 የአብቾ ቀበሌ አርሶ አደሮች የቃሉ ወረዳ የ019 የአብቾ ቀበሌ አርሶ አደሮቹ በአምበጣ መንጋው ክፋት እና በሚያደርሰው ጉዳት የተማረሩ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ለ4ኛ ጊዜ በአብቾ በቀበሌ የሠፈረው የበረሀ አንበጣ መንጋ በሰብልና በእንስሳት መኖ ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡ይህን መንጋ ለመከለካል የምስራቅ አፍሪካ አንበጣ መከላከል ድርጅት በተደጋጋሚ በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት ቢያከናውንም እንደዛሬው የተሳካ ርጭት አለማከናወኑን አርሶአደሮቹ ተናግረዋል፡፡ አርሶአደሮቹ እንደሚሉት አውሮፕላኗ ለመሬት ያላት ቅርበት አንበጣው ላይ ኬሚካሉን በቀላሉ ለመርጨት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የኬሚካሉ የመግደል አቅም ከፍተኛ ሲሆን መንጋውን ከመግደል አልፎ ወደተለያዩ አቅጣጫወች እንዲበተን አድርጎታል ብለዋል፡፡ አርሶ አደር ሠይድ መሀመድ የተባሉት ግለሰብ በዛሬው ርጭት ከመደሰታቸውም በላይ ትንሿን ሰብልየን አመስግኑልኝ ብለዋል፡፡የቃሉ ወረዳ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዯች ፅቤት በበኩሉ በአርሶ አደሮቹ ስም የተሠማውን ደስታ ገልጾ ትንሿ ሰብልየን ከልብ እናመሠግናለን ብሏል፡፡ በሁሉም አካባቢዎች እየተደረገ ያለው ድጋም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል። የቃሉ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ### Response: