text
stringlengths
707
989
### Text: የሲዳማ ብሔር ህዝብ ውሳኔ ውጤት አስመልክቶ ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ወላይታ ሶዶ ህዳር 132012 ዓምየሲዳማ ህዝብ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ የቆየው ራሱን በራስ የማስተዳደር በክልል የመደራጀት ህገመንግስታዊ ጥያቄ ከረጅም ጊዜ ትግልና መስዋትነት በኋላ የተገኘ በመሆኑ የወላይታ ዞን አስተዳደር የተሰማውን ታላቅ ደስታ በዞኑ መንግስትና ህዝብ ስም ይገልጻል፡፡የወላይታና የሲዳማ ወንድም ህዝቦች ለዘመናት አብሮ የኖሩ፣ አንድ ትውልድ በሌላው ትውልድ ስተካ በዘመናት መካከል በመከባበር ላይ የተመሰረተ አንድነት በባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ታሪካዊ ጉዳዮች የተሰናሰሉ ከመሆናቸው ባለፈ የደም ትስስር ጭምር የሚያገናኛቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ በእነዚህ የአብሮነት ጊዜያት በክፉም ደጉም በጋራ በሀገር ግንባታ ሂደት የበኩላቸውን ሚና ሲወጡ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡ የሀገራዊ ለውጥ ሂደት ተከትሎ በ2010 ዓም ሁለቱን ወንድም ህዝቦች በማጋጨት የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት የፈለጉ እኩይ ዓላማ ያላቸው ሀይሎች የተለያዩ ጥረቶች ያደረጉ ቢሆንም በህዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቀው የጋራ እሴት እንዳይሸረሸር ሁለቱ ወንድም ህዝቦች ባደረጉት ጠንካራ ተጋድሎ ሁኔታው ወደ ነበረበት የቀድሞ ሠላማዊ ሁኔታ ተመልሷል፡፡ 11234 ወላይታ ዞን አስተዳደር ### Response:
### Text: በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስትን ወልክለው ፊርማቸውን ያኖሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከዛሬው የናይሮቢው ስምምነት በኃላ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።አምባሳደር ሬድዋን ከዛሬው የቀጠለ ውይይት በወታደራዊ ኃላፊዎች መካከል የዛሬ ወር ገደማ በትግራይ ክልል መዲና መቐለ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ጠቁመዋል።ዋናውና የውይይቶቹ ፍፃሜ ደግሞ በፈረንጆቹ አዲስ አመት አዲስአበባ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ገልፀዋል።የናይሮቢው ውይይት በተጀመረበት ዕለት ኡሁሩ ኬንያታ በፕሪቶሪያ ጀመርን፣ መንገዳችን እየተጠጋ አሁን ናይሮቢ ነን ፣ በሚቀጥለው ጊዜ ስብሰባችን መቐለ እንደሚሆን ተስፋ አድርጋለሁ በመጨረሻም አዲስ አበባ ላይ አብረን እናከብራለን። ይህ ጸሎታችን ፣ ተስፋ የምናደርገው እና የምንፈልገው ነው። ማለታቸው አይዘነጋም።በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው የናይሮቢው ውይይት የተደረገው በፕሪቶርያ የተደረገውን ስምምነትን መሰረት አድርጎ መሆኑን ገልፀዋል።ነገር ግን በዚህ ውይይት የውጭ ኃይሎች ጉዳይ እንደነበር እና ውይይቱ በዛ ሁኔታ የተካሄደ እንደነበር አስረድተዋል።አምባሳደር ሬድዋን እና አቶ ጌታቸው ቃላቸውን የሰጡት በዛው ኬንያ፣ ናይሮቢ ለሚገኘው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ነው ### Response:
### Text: የአቅም ማሻሻያ በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ።የትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና0 ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እና በተመሳሳይ ሁኔታ ፈተናው የተሰጠበትን አግባብ እና ሌሎች ጉዳዮችን ከግምት በመውሰድ ለአንድ ጊዜ ብቻ0 የሚያገለግል የአቅም ማሻሻያ እንዲተገበር መወሰኑ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት በ2015 የትምህርት ዘመን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው በ ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎችን አነስተኛ የመግቢያ ውጤት መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ከላይ የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የ ፕሮግራም ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ።1 በሁሉም አማራጮች በግል እና በመንግስት ተቋማት የ ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም 210 ከ 700፣0 180 ከ 600 እና 150 ከ 500 የተቆረጠ መሆኑን።2 ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ0 በመንግስት ተቋማትወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ የ ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ ይሆናል ተብሏል።የአቅም ማሻሻያ የመቁረጫ ነጥቡን ከላይ ይመልከቱምንጭ ትምህርት ሚኒስቴር ### Response:
### Text: ነገ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ አዲስ አፈ ጉባኤ እንደሚመርጥ ይጠበቃል፡፡ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የሚያቀርቧቸውን እጩ የካቢኒ አባላቶች ሹመት ምክር ቤቱ በነገው እለት እንደሚያጸድቅም ፋና ብሮድካስተንግ ኮርፖሬት ዘግቧል፡፡የምክር ቤቱን መዶሻ ከክቡር አባዱላ ገመዳ እጅ ተረክበው አዲሱ አፈ ጉባኤ በመሆን የሚሰየሙት ወሮ መፍሪሂት ከሚል ስለመሆናቸው ምንጮች ለድሬቲዩብ ገልጸዋል፡፡ በአዲሱ የጠቅላይ ሚንስትሩ ካቢኒ ውስጥ የፌድራል ምክር ቤት ሀላፊ ሁነው የተሾሙት ወሮ ኬሪይ ኢብራሂም ስለመሆናቸውም እየተወራ ነው፡፡ኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር ሁነው በማገልገል ላይ የሚገኙት ዶክተር ነገሪ ሌንጮ በአቶ መለስ አለም ፋንታ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ቃል አቀባይ ሁነው መሾማቸውም ተነግሯል፡፡አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የኢህአዴግ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ሁነው በስራቸው ላይ እንዲቀጥሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ መወሰናቸውንም እንዲሁ፡፡ምክር ቤቱ የካቢኒ አባላትን ሹመት ከማጽደቅ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ የአስፈፃሚ አካላትን አደረጃጀት ስልጣን እና ተግባር እንደገና ለማሻሻል የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅንም ተመልክቶ ያፀድቃል ተብሎም ይጠበቃል።ምንጭ ፋና፣ ድሬ ### Response:
### Text: ሰበር ዜና የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የዶክተር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ የ62 ተከሳሾችን የክስ ሂደት ማንሳቱን አስታወቀ።ተከሳሾቹ የወንጀለኛ መቅጫ ህግን አንቀጽ 464 እና 494 በመተላለፍ ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ ያለና እንዲከላከሉ ብይን የተሰጠባቸው ናቸው።ኢዜአ ከፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ባገኘው መረጃ መሰረት በእነ አበበ የኋላ የክስ መዝገብ የተጠቀሰውን አንቀጽ በመተላለፍ ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ ያሉ 18 ተከሳሾች ክስ እንዲነሳም ተወስኗል።በእነ ማስረሻ ሰጠኝ መዝገብ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት ጉዳያቸው ሲታይ ከነበሩት 38 ተከሳሾች መካከል አራቱ በሰው መግደል ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው እንዲከላከሉ ብይን ተሰቶባቸዋል።ስምንቱ ደግሞ በነጻ መሰናበታቸው የሚታወስ ነው። በተጠቀሰው መዝገብ የወንጀለኛ ህጉን አንቀጽ 464 እና 494 በመተላለፍ እንዲከላከሉ ብይን የሰጠባቸውን ቀሪ 26 ተከሳሾች ክስ ደግሞ እንዲነሳ ተወስኗል።በሰው መግደል ወንጀል እንዲከላከሉ የተበየነባቸው የአራቱ ተከሳሾች የፍርድ ሂደት ግን ባለበት ይቀጥላል ተብሏል።በተመሳሳይ በእነ ቴዎድሮስ ዳንኤል መዝገብ የወንጀለኛ ህጉን አንቀጽ 464 እና 494 በመተላለፍ ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ ያለ የ18 ተከሳሾች ክስ እንዲነሳ መወሰኑንም የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታውቋል።ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: ጊፋታ2012 የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ግፋታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ቅድመዝግጅት መጠናቀቁን የወላይታ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በበዓሉ አከባበር የህዝብ ለህዝብ ትስስር ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡የወላይታ ህዝብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር የነበረውን አንድነት በይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል በዞኑ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የጉዞ ግፋታ ልዑካን ቡድን ወደተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች መጓዛቸውን ተነግሯል፡፡በዚህም የጉዞ ግፋታ አባላት ለትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፂዮን ገብረሚኤልና ለአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ላቀ አያሌው ግብዣ አቅርበዋል፡፡የጉዞ ጊፋታ ልዑካን ቡድን እንቅስቃሴ ዋና ዓላማው የዘንድሮውን የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ግፋታ በዓል ከመላው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በጋራ ለማክበር ያለመ ነው ተብሏል፡፡በመስከረም 15 ቀን በወላይታ ጉተራ አዳራሽ በሚካሄደው ሲምፖዚየም የብሔሩ ባህል፣ ታሪክና ቋንቋ አስመልክቶ በምሁራን የተዘጋጀው ጥናታዊ ጽሑፍ እንደሚቀርብ ደሬቴድ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በዓሉ በዞኑ ማዕከል በመስከረም 18 ቀን 2012 ዓም በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም እንደሚከበር ተጠቁሟል፡፡ ### Response:
### Text: የትንሳኤ ሎተሪ ወጣትንሳኤ ሎተሪ ቅዳሜ ሚያዝያ 23 2013 ዓም በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል 1ኛ 5000000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 01488062ኛ 2500000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 04188753ኛ 1250000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 07795944ኛ 600000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1653940 5ኛ 300000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 01000086ኛ 150000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 03806497ኛ 100000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 02327198ኛ 17 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 3000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 581859ኛ 17 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4956610ኛ 170 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 600 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 767911ኛ 170 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 570912ኛ 170 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 150 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 308513ኛ 1700 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 81914ኛ 1700 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 90 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 10615ኛ 17000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 45 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4616ኛ 170000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 30 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር የማስተዛዘኛ ዕጣ ደግሞ 7 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ### Response:
### Text: ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ️የቀድሞዋ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ አመራር የነበሩት ወት ብርቱካንሚዴቅሳ ቅንጅት የፈረሰበትን ትክክለኛ ምክንያት ለማናገር አልፈልግም አሉ። ወደ አገር ቤት ከተመለሱ በሁዋላ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ሰፋ ያለ ቃለ መጠይቅ ያደረጉት ወት ብርቱካን ቅንጅት የፈረሰበት ትክክለኛ ምክንያት ምንድን ነበር ተብለው ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ እውነት ለመናገር አሁን ይሄንን ጥያቄ ልመልስ አልፈልግም፡፡ ልመልስ የማልፈልገው መልስ ስለሌለኝ ወይም ደግሞ ምክንያቱን ስላማላውቀውና ስለማልችል አይደለም በማለት ምክንያቱን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።ወት ብርቱካን አያይዘውም እስካሁንም የተነሱትን ነገሮች ሚዲያ ላይ አይቻለሁ፡፡ አሁን አገራችን ከሁላችንም አፋጣኝ ምላሽ የምትፈልግበት ወቅት ነው ከዚያ ይልቅ ሌሎች በጣም አንገብጋቢ ጥያቄዎች አሉ በማለት የግል አቋማቸውን ግልጽ አድርገዋል። ከዚህ በፊት በነበረን ነገር ማን ጥፋተኛ ነው ማን የበላይ ነው ማን የበታች ነው ማንነው ያፈረስው ለምን ፈረሰ የሚለውን ነገር የአካዳሚክ ጥናትም ለሚያደርጉ ሰዎች በጣም ጥሩ የጥናት መስክ ሊሆን ይችላል ያሉት ወት ብርቱካን አሁን እኔ በዚያ ንትርክ ላይ የመሰማራት ፍላጎትም የለኝም። ለህብረተሰባችንም ዋና ጉዳይ ነው ብዬ አልወስደውም ሲሉ ገልጸዋል።ምንጭ ### Response:
### Text: 1859 ተማሪዎችን አስመረቀ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 353 ሴት ተማሪዎችን ጨምሮ 1859 ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡በመልዕክታቸውም በዩኒቨርስቲ የሚታዩ በዘርኝነት የሚከሰቱ መጠፋፋቶች ኋላ ቀር አስተሳሰብ በመሆናቸው ይህ ትውልድ መፍቀድ የለበትም ብለዋል፡፡ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደ ማርያም በበኩላቸው ተማሪዎች በተማሩበት መስክ ጠንካራ ሰራተኛ በመሆን የአገልጋይነት ስሜት በመላበስ የተጣለባቸውን አደራ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ ከ25 አመታ በፊት የተቋቋመው ዩኒቨርስቲው በልዩ የመግቢያ ፈተና በዓመት 5ሺህ የሚሆኑ ለፈተና ቢቀርቡም 1500 ብቻ ናቸው ዕድሉን የሚያገኙት ተብሏል፡፡ ዩኒቨርስቲው የምርምር እና የጥናት የልህቀት ስራዎችን የሚያካሂድበት 8 የልህቀት ማዕክል አሉት፡፡በዩኒቨስቲው የሚገኘው ላብቶሪ ለዩኒቨርስቲ ለተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ጭምር አገልግሎቱን እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡ ሙህራን በዘርፉ ላይ ምርምር እና ጥናት ሊያካሂዱበት የሚችል በአይነቱ ለየት ያለ የምርምር ማዕከል በዩኒቨርስቲው ውስጥ እየተገነባ እንደሚገኝም ተነግሯል፡፡ ### Response:
### Text: ዶክተር ቴድሮስ ከዢ ጂንፒንግ ጋር መክረዋልየዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም ወደ ቻይና አቅንተው ከአገሪቱ ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ጋር የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በዛሬው ዕለት መክረዋል።ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ቻይና ሙሉ አቅም እና በራስ መተማመን እንዳላት ለዶር ቴድሮስ አድኃኖም ገልጸውላቸዋል።ዢ ጂንፒንግ እንደተናገሩት ቻይና በአሁኑ ሰዓት ቫይረሱን ለመከላከል ከምንም ነገር በፊት ቅድሚያ ሰጥታ እየሠራች እንደሆነ እና ከዓለም የጤና ድርጅት እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ እንደምትሠራም አረጋግጠውላቸዋል።ኮሮና ቫይረስ ሰይጣን ነው ያሉት የቻይናው ፕሬዝዳንት፣ ይህን ሰይጣን ደግሞ ተደብቆ እንዲቀር አንፈቅድለትም፣ እናጠፋዋለን ማለታቸው ተዘግቧል።የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚደረገው ጥረት የዓለም ጤና ድርጅት ከቻይና ጋር በትብብር እንደሚሠራ እና አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም የዓለም ጤና ድርጅት ቃል አቀባይ ተናግረዋል።በቻይና በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሟቾቹ ቁጥር 106 መድረሱንና ከ4 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መጠቃታቸውን በዛሬው ዕለት የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።ሽንዋ፣ ስትሬት ታይምስ፣ሲጂቲኤን፣ ኢቢሲ ### Response:
### Text: ዛሬ ይፋ በተደረገው የተማሪዎች ምደባ ላይ ቅሬታ አለን ያሉ ወላጆች እና ተማሪዎች መልዕክታቸውን እያደረሱ ይገኛሉ ዛሬ የአዲስ ተማሪዎችን ምደባ ይፋ ያደረገ ሲሆን ምደባቸውን የተመለከቱ አንዳንድ ተማሪዎች እና የተማሪዎቹ ወላጆች ቅሬታ እንዳለባቸው ገልፀዋል። ባስቀመጠው የቅሬታ መቀበያ አድራሻ ድህረገፅ ቅሬታቸውን እንደሚያሳውቁ ገልፀው ተገቢው ምላሻ እንዲሰጣቸውም አሳስበዋል።ከውጤታ ጋር የፈለጉት ምርጫ አልተሰጠኝም ያለ አንድ የቲክቫህ አባል በሀገር አቀፉ ፈተና ከ630 በላይ ቢያመጣም የሚፈልገው የዩኒቨርሲቲ ምርጫ እንዳተጠበቀለት ገልጿል። ይህንንም የሚገልፅ ማስረጃውን ከላይ አያይዟል።በተጨማሪ አንዲ ከ620 በላይ ያመጣች ተማሪም በ400 ቤት ውስጥ ውጤታ ያላቸው ምርጫቸው ሲጠበቅ የእሷ ግን እንዳልተጠበቀ ገልፃ የምደባው ሂደት እንዳሳዘናት ገልፃለች።ይህን መሰል ሌሎች ቅሬታዎች ወደቲክቫህ እየተላኩ ሲሆን በምደባ ላይ ያሉ ችግሮች ጊዜው ሳይሄድ ማስተካከያ እንዲደረግ በወላጆች እና ተማሪዎች ተጠይቋል። ዛሬ የተማሪዎችን ምደባ ይፋ ሲያደርግ በምደባው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ተማሪዎች ካሉ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው 972627 በዚህ ሊንክ በመግባት ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ ብሏል።ተማሪዎች ከላይ በተቀመጠው ቅሬታ መቀበያ ላይ ቅሬታችሁን ማሳወቅ ትችላለችሁ። ### Response:
### Text: የፌዴራል መንግስት የሰብአዊ ዕርዳታ እንዲርደስ ለማስቻል አልሜ ያደረኩት የተናጠል የተኩስ አቁም በሕወሃት ትንኮሳ መደናቀፉን ቀጥሏል ብሏል።በትግራይ ክልል በሚገኙ መጋዘኖች ውስጥ ከ400000 ኩንታል የሚበልጥ ስንዴ እና ከ25 ሚሊዮን ሊትር የሚበልጥ የምግብ ዘይት መቀመጡን ገልጿል።የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ያሉት ዜጎቻችን ደህንነት ያሳስበኛል ያለ ሲሆን ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ በተለይም ደግሞ በትግራይ ድጋፍ በመስጠት ላይ የሚገኙት፣ ህወሓት የአፋርን ክልል መተናኮሱን አቁሞ ሰብዓዊ እርዳታ ለያዙ ተሽከርካሪዎች መንገዱን እንዲከፍት ግፊት ማሳደር አለባቸው ብሏል።ይህ መረጃ ይፋ የሆነው በወቅታዊ ሁኔታ የመረጃ ማጣሪያ ገፅ በኩል ነው።ከሰዓታት በፊት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ባስሌይ ድርጅታቸው ትግራይ ውስጥ የሚያደርሰው የምግብ ድጋፍ አቅርቦት በዚህ አርብ እንደሚያልቅበት ገልፀዋል።ዴቪድ ባስሌይ በአፋር አካባቢ ስላለው ሁኔታ ዝርዝር መረጃዎች ባይሰጡም ለትግራይ ምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ አቅርቦቶች የያዙ 170 ተሽከርካሪዎች በአሁን ሰዓት አፋር እንደሚገኙና መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ ገልፀዋል።ዋና ዳይሬክተሩ ተሽከርካሪዎች አሁኑኑ እንዲንቀሳቀሱ መፈቀድ እንዳለበት በመግለፅ ትግራይ ውስጥ ሰዎች እየተራቡ መሆኑን አሳውቀዋል። ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ተከሄደው ጦርነት መቋጫ የሆነው አልጀርስ ስምምነት እንዲፈረም ሚና የነበራቸው የቀድሞ የአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደላዚዝ ቡተፍሊካ በ84 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።በፈረንጆቹ 1999 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ቦተፍሊካ እጅግ ከባድ የሚባለውን የኢትዮኤርትራ ግጭት አንዲፈቱ ሃላፊነት ተጥሎባቸው ነበር፡፡በሁለቱ ሀገራት መካከልም ስምምነት እንዲፈረም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።ቦተፍሊካ በፈረንጆቹ ሚያዚያ 2019 ስልጣናቸውን ከመልቀቃቸው በፊት ሰሜን አፍካዊቷን ሀገር አልጀሪያን ለሁለት አስርት አመታት መርተዋል፡፡የቀድሞውየአልጀሪ ፕሬዝዳንት ቢተፍሊካ፣ በሀገሪቱ የተካሄደውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ ነበር ከሁለት አመታት በፊት ስልጣናቸውን የለቀቁት፡፡ለሁለት አስርት አመታት አልጀሪያን ያስተዳሩጽ ቦተፍሊካ የአልጀሪያ የነጻነት ጦርነት ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን በፈረንጆቹ 2019 የህዝብ ተቃውሞ በመዝዛቱ ስልጣናቸውን ለ6ኛ ዙር የማራዘም እቅዳቸውን ሰርዘው ስልጣን ለቀዋል፡፡ቦተፍሊካ ከፈረንጆቹ 2013 እስሚሞቱበት ጊዜ ድረስ በአደባባይ ብዙም አይታዩም ነበር፡፡ለረጅም ጊዜ ታመው እንደነበር የተነገረላቸው አብደላዚዝ ቦተፍሊካ በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። አል ዓይን ኒውስ ### Response:
### Text: ቃላት እንደሚያድኑት እንደሚያፅናኑት ሁሉ ቃላት ለማጥፋትም ስሜትን መቀስቀስ ይችላሉ ዶክተር ፀደይ ወንድሙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ በ2011 ዓም ላይ እጅግ እየተባባሰ የመጣው የ ጥላቻ ንግግር በሀገሪቱ ላይ ስለሚያመጣው የከፋውድመት በመረዳት በኦሮሚያ ፣ በአማራ ፣ በትግራይ ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ክልሎች በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲሁም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከጥላቻ ንግግሮች እንቆጠብ 0 በሚል ዘመቻ አካሂዶ ነበር።በወቅቱ ወደ ትግራይ ፣ መቐለ ዩኒቨርሲቲ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ባደረጉት የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት ጉዞ እንዲሁም በዛው በተቋሙ በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ0 የመቐለ ዩኒቨርሲቲ መምህርት ዶር ፀደይ ወንድሙ ንግግር አድርገው ነበር።ዶክተር ፀደይ ወንድሙ0 በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መድረክ ላይ የጥላቻ ሀሳብ ንግግር መሆን የሚጀምረው በተለያዩ ሚዲያዎች መሰራጨት ሲጀምር ነው። ንግግሩ ቀስ እያለ ወደመጠፋፋት ደረጃ ያመራል። የቃላት ጉልበት የሚገለጠውም እዚህ ደረጃ ላይ ነው። ቃላት እንደሚያድኑት እንደሚያፅናኑት ሁሉ ቃላት ለማጥፋትም ስሜትን መቀስቀስ ይችላሉ። ስለዚህ በእኔ እሳቤ መዋጋትና ማስቆም ካለብን የጥላቻን ሀሳብ ነው የጥላቻ ንግግር ተብሰልስሎ ወደ ውጪ የወጣ የጥላቻ ሀሳብ መገለጫ ነው ብለው ነበር።2011 ዓም ### Response:
### Text: ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገሪቱ ያሉ ችግሮች በውይይት እና በስምምነት እንዲፈቱ በድጋሚ ጥሪ አቀረበች።ይህ ጥሪ የቀረበው ቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት 2016 ዓም ጉባኤውን ካጠናቀቀ በኃላ ባወጣው መግለጫ ነው።ቅዱስ ሲኖዶስ ትላንት በሰሜኑ ኢትዮጵያ የሀገራችን ክፍል በተካሄደው ጦርነት በጠፋው የሰው ሕይወትና በወደመው ንብረት ከደረሰብን ሐዘን እኛ ኢትዮጵያውያን ገና ሳንጽናና ዛሬም በሀገራችን ኢትዮጵያ በበርካታ አካባቢዎች የተከሰቱት ጦርነቶች፣ ግጭቶችና አለመግባባቶች እያስከተሉት ያለው የንጹሐን የሰው ሕይወት መጥፍትና የንብረት ውድመት በእጅጉ አሳዝኖናል ብሏል።በመሆኑም ችግሩ በውይይትና በስምምነት እንዲፈታ የፌዴራልን የክልል መንግሥታት፣ እንዲሁም በግጭቱ ተሳትፎና ድርሻ ያላቸው በሁሉም አካባቢ የምሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ የበኩላቸው ሚና በመወጣት እናት አገራችን ኢትዮጵያ ሰላሟና አንድነቷ ተጠብቆ ይቀጥል ዘንድ ከአደራ ጭምር በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል።ከዚህ በተጨማሪ ስለ ሀገር ሰላም እና ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት በመላው ዓለም በሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ከህዳር 15 ቀን 2016 እስከ ታህሣሥ 27 ቀን 2016 ዓም ድረስ ጸሎትና ምሕላ እንዲፈጸም ተወስኗል። ### Response:
### Text: በትናንትናው ዕለት በተባበሩት መንግስታት በአቢዬ ጊዜያዊ የደኅንነት ሀይል ግቢ ውስጥ በሂሊኮፍተር አደጋ ህይወታቸው ያለፈው ኢትዮጵያውያን የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሰራዊት አስክሬን ዛሬ ጠዋት ወደ አዲስ አበባ መሸኘቱ ተገለጸ፡፡ የሱዳንና በደቡብ ሱዳን ተወካዮች ለተጎጂ ቤተሰቦች የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል፡፡ ሂሊኮፍተሯ ትናንት የተከሰከሰችው 23 የሠላም አስከባሪ አባላትን አሳፍራ በአካባቢው ቅኝት እያደረገች ሳለ መሆኑና ምክንያቱ እስካሁን አለመታወቁን ሲጂቲኤን ዘግቧል። በአደጋው የአራት ሰላም አስከባሪዎች ህይዎት አልፏል አስሩ ደግሞ ተጎድተዋል። ተጎጂዎች ለሰለም አስከባሪዎች አገልግሎት ወደ ሚሰጠው ሆስፒታል ተወስደው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑንም ዘገባው አስታውቋል። ኢትዮጵያውያኑ የሠላም አስከባሪ አባላት 8 በተባለች ሄሊኮፕተር ካዱግሊ ከተባለ ሥፍራ ወደ አብየ ግዛት ለመደበኛ ቅኝት ተሰማርተው እያሉ ነው አደጋው እንደደረሰ የተዘገበው። አደጋው የደረሰው በተባበሩት መንግሥታት የአብየ ግዛት ሰላም አስከባሪ ጊዚያዊ መጠለያ ውስጥ ነው። በአብየ ግዛት የተመድ ሰላም ማስከበር የተልዕኮና ግዳጅ ተጠባባቂ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ገብረ አድሃና ወልደእዝጉ የአደጋው ምክንያት እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል።ምንጭ ተመድ ### Response:
### Text: ከንፈር በመምጠጥ ለውጥ አይመጣም አቶ እንድግዳ ማንደፍሮ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እጅግ በርካታ ሰዎች እገዛ ያስፈልጋቸዋል።በትግራይ ክልል ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ፣ በደቡብ ክልል በኮንሶ፣ አሌና ደራሼ አሁንም ከፍተኛ እርዳት የሚፈልግ ሰው ቁጥር አለ።እየተደረገ ያለው ድጋፍ ከእርዳታ ፈላጊው ቁጥር ጋር ሲነፃፀር ገና የሚቀረው በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ እየቀረበ ይገኛል።ማህበረሰቡ የቻለውን ያህል ድጋፍ ማድረግ አለበት።ምግብ ፣ ለህፃናት የአልሚ ምግብ፣ ለአራስ እና አጥቢ እናቶች የምግብ አቅርቦት ያስፈልጋል። በተጨማሪ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች በእጅጉ ያስፈልጋሉ።ቲክቫህ ያናጋገራቸው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ምክትል ዋና ፀሃፊ አቶ እንግዳ ማንደፍሮ ከንፈር በመምጠጥ ለውጥ አይመጣም፣ የተለያዩ ድርጅቶች የሚያወጧቸውን ሪፖርቶች አይቶ ማለፍ ብቻ ሳይሆን ቀረብ ብሎ የተቸገሩትን ማገዝ ያስፈልጋል ብለዋል።ሰሞኑን ቀይ መስቀል በዓዲግራት ፣ አክሱም ፣ ሽረ መስመር የተለያዩ ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ማህበሩ ከመጀመሪያውም አንስቶ ዳጋፍ ለሚፈልጉ ድጋፍ እያደረገ ቢገኝም ያለው አቅርቦት ከድጋፍ ፈላጊው ጋር ሲናፃፀር እጅግ በጣም የሚቀረው ነው።ቀጣዩን ያንብቡ 0122 ### Response:
### Text: ከመርሳ፣ ከወልዲያ እና ከውርጌሳ አካባቢ በርካታ ሰው በስፋት እየመጣ ነው እሱን እየለየን ወደ ማረፊያ ቦታ እየገቡ ነው አቶ አበበ ገመስቀል የደሴ ከንቲባእየተካሄደ የሚገኘውን ጦርነት በመሸሽ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከሰሜን ወሎ ወደ ደሴ ከተማ መግባታቸውን የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ አበበ ገመስቀል ተናገሩ።አቶ አበበ ይህንን ያሳወቁት ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ ነው።ቀደም ብሎ ከ4 አስከ 5 ሺ የሚሆኑ ሰዎች ከሰሜን ወሎ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ ደሴ ከተማ ገብተው ነበር ያሉት አቶ አበበ ከትናንት ጀምሮ ግን በርካታ ተፈናቃዮች ወደ ከተማዋ እየገቡ መሆኑን አስረድተዋል።አቶ አበበ ከመርሳ፣ ከወልዲያ እና ከውርጌሳ አካባቢ በርካታ ሰው በስፋት እየመጣ ነው እሱን እየለየን ወደ ማረፊያ ቦታ እየገቡ ነው። ትክክለኛውን ቁጥር ለጊዜ ባላውቀውም ከ10 አስከ 15ሺህ የሚገመት ሕዝብ እየገባ ነው ያለው ሲሉ ለዜና ማሰራጫው ተናግረዋል።በርካታ ቁጥር ያለው ሕዝብ ወደ ደሴ እየገባ በመሆኑ በሕዝቡ ጥያቄ መሠረት የሰዓት እላፊ መታወጁን አሳውቀዋል።የደሴ ከተማ ነዋሪዎች የህወሓት ታጣቂዎች በአማራ ክልል በተለይ የሰሜን ወሎ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ባለፉት ሳምንታት የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ ነዋሪዎች ለደኅንነታቸው በመስጋት ወደ ደሴ ከተማ እየገቡ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ### Response:
### Text: ወንጀል ነክ መረጃ️ከባድ የውንብድና ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ። ተከሳሽ እስጢፋኖስመለሰ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 010203 ክልል ልዩ ቦታው መርካቶ ለይላ ህንፃ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ግንቦት 21 ቀን 2008 ዓም ከቀኑ 6፡30 ሲሆን በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀፅ 6711ለ ላይ የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ተከሳሽ የማይገባውን ብልፅግና ለማግኘት በማሰብ ካልተያዘው ግብራበሩ ጋር በመሆን የግል ተበዳይፋሲል ማሞ የተባለውን ግለሰብ ጋላክሲ ኖት 3 የዋጋ ግምቱ ስድስት ሺህ አምስት መቶ ብር የሆነውን ሞባይል ቀምቶ ሲሮጥ የግል ተበዳይ ለመያዝ በሚከተልበት ጊዜ ያልተያዘው ግብረአበሩ ለማስቆም በገጀራ የቀኝ እጅ አውራ እጣቱን የመታውና ጉዳት ያደረሰበት በመሆኑ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ የውንብድና ወንጀል በዐቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል።ዐቃቤ ህግ የተከሳሽን ጥፋተኝነት ለፍርድ ቤቱ ያስረዳልኛል ያላቸውን የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች በማቅረቡ እንዲሁም ተከሳሽ የተመሰረተበትን ክስ ማስተባበል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽን ጥፋተኛ ነህ ብሎታል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 7ኛ ወንጀል ችሎትም ህዳር 05 ቀን 2011 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሽ በ6 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።ምንጭ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ### Response:
### Text: አንጋፋው የኢትዮጵያ አርቲስት ክቡር ዶር አሊ ቢራ በህይወት አለ።በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ አንጋፋው የሀገራችን አርቲስት ክቡር ዶክተር አሊ ቢራ አረፈ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።ክቡር ዶር አርቲስት አሊ ቢራ ባጋጠመው የጤና እክል የተነሳ በአዳማ ጄነራል ሆስፒታል ለላፉት ቀናት የሕክምናክትትል እየተደረገለት ይገኛል።የ75 ዓመቱ አርቲስት አሊ ቢራ ከዚህ ቀደምም የጤና እክል አጋጥሞት በአዲስ አበባ እና አዳማ ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች የውስጥ ደዌ ህክምና ተደርጎለት ነበር።ከዚህ ቀደም ህክምና ላይ እያለ ህይወቱ እንዳለፈ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሀሰተኛ መረጃዎች ተሰራጭተው የነበረ ሲሆን በዚህ ሀሰተኛ መረጃ ቤተሰቦቹ እጅግ መጎድታቸው እና ማዘናቸውን መግለፃቸው ይታወሳል።ሳናረጋግጥ የምናወራው ወሬ ምን ያህል የሰዎችን ህይወት እንደሚበጠብጥ እናውቀው ይሆን 0 ሁሉ ነገር ስርዓት አለው የሰውን ሀዘን ለማርዳት ይሄን ያህል መቸኮል ምንድነው ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ወዳጅ ይደነግጣል አይባልም በችኮላ እና መረጃ አደረስኩ ለማለትና ለዩትዩብ ገንዘብ መሰብሰቢያ ሲባል ያልተረጋገጠ መረጃ ማሰራጨት ፍፁም ስርዓት የጎደለው ተግባር ነው። ውድቤተሰቦቻችን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የምትመለከቱትን ሀሰተኛ መረጃ ከማጋራት ተቆጠቡ። ### Response:
### Text: በትናንትናው ዕለት በአዲስአበባ ዙሪያ በቡራዩ፣ አሸዋ ሜዳ፣ ከታ እና ፊሊ ዶሮ አካባቢ በንፁሀን ዜጎች ላይ በተፈጸመውን ግድያ ብዙ ወገኖቻችን ተፈናቅለው በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ይገኛሉ። ፊሊጶስ ሚኪሊላንድ ቃሌ ብስራት ጉለሌ ፋና አወሊያ ፊትአውራሪ መድሀኒያለም ትቤትእንዲሁም ሌሎችበነዚህ ትምህርት ቤቶች የተጠለሉ በብዙሺህ የሚጠጉ ዜጎቻችን አስቸኳይ የምግብ የህጻናት ምግቦች እና ዳይፐር እና የአልባሳት እርዳታ ያስፈልጋቸዋል በተጨማሪም ያረፉት በትምህትቤት ክፍል ውስጥ በመሆኑ ለመተኛት ቅዝቃዜውን የማይችሉ በተለይ ህፃናት እና እናቶቻችን ስላሉ ሁላችን በቻልነው አቅም በመርዳት ለወገኖቻችን አለን እንበላቸው።ሙስተቅበል ልማት እና መረዳጃ ኢኒስቲትዩት ከናንተ ጋር በመሆን ለወገኖቻችን የመቆም ሃላፊነታችንን እንድንወጣ ጥሪ እናስተላልፋለን።አልባሳት እና ቁሳቁስ ለማሰባሰብ የሚከተሉትን አድራሻዎች እንጠቀም ፒያሳ 0911486333 መርካቶ 0912606168 ሜክሲኮ 0944069391 መድሃኒያለም 0912745050 ኮልፌ 0910653898 ጦርሃይሎችቤተል 0920656215 ቦሌ 0911160899 እንዲሁም በሌላ አካባቢ ያላቹ በማንኛውም ስልክ በመደወል ያላችሁበት ድረስ እንመጣለንለተጨማሪ መረጃዎች 0913528484 0911214719 0911486333 ኑ ሰብዐዊነትን ህያው እናድርግ ለወገን ደራሽ ወገን ነውሙስተቅበል የልማት እና መረዳጃ ኢኒስቲትዩት ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና️በጅማ ከተማ በተከሰተ የአፈር መንሸራተት የ3 ሰዎችን ህይወት መለፉን ፖሊስ አስታወቀ።የጅማ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የኮሙዩኒኬሽን ዲቪዚዮን ኃላፊ ኢንስፔክተር ገዛኸኝ አውግቻው እንደገለጹት አደጋው የደረሰው አንድ ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ትናንት ቀን አስር ሰዓት አካባቢ በቦቼ ቦሬ ቀበሌ ቺሻየር በተባለው ሰፈር የደፋው አፈር መኖሪያ ቤት ላይ በመደርመሱ ነው፡፡አፈር ተደርምሶ የመኖሪያ ቤት በመጫን ባስከተለው አደጋ የ3 ሰዎችን ህይወት መጥፋቱ የተገለጸ ሲሆን ከሟቾቹ መካከል የአንድ ቀን አራስ ከነልጇ እንደሚገኙበትም ገልጸዋል።መኖሪያ ቤት አፈሩ ከተደፋበት ቦታ በቅርበት ዝቅተኛ ቦታ ላይ የነበረ በመሆኑና ለአደጋው መጋለጡን አመልክተዋል፡፡የተደፋው አፈር ተደርምሶ ቤቱ ላይ አርፎ ባደረሰው አደጋም ከነልጇ ህይወቷ ያለፈው አራስ የ22 ዓመት ዕድሜ የነበራት መሆኑን ኢንስፔክተር ገዛኸኝ ተናግረዋል።የሟቿ ባለቤትም የአካልና የስነልቦና ጉዳት ደርሶበት በጅማ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት የሚገኝ ሲሆን ሶስተኛውም ሟችም ህጻን ልጅ መሆኑ ታውቋል።በአደጋው ቤቱ ከጥቅም ውጭ መሆኑን የገለጹት ኢንፔክተር አውግቸው አፈሩን የደፋው ሲኖትራኩ አሽከርካሪ ለጊዜው ቢሰወርም ፖለስ ክትትል እያደረገበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ምንጭ ኢዜአ ### Response:
### Text: በኢትዮጵያ የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ 3 መተግበሪያዎች በዚህ ሳምንት ይፋ ሆነዋል።መተግበሪያዎቹ ይፋ የሆኑት በ ዚ ትራክ የትራንስፖርት አገልግሎት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኀበር ነው።ዚ ትራክ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት በሞባይል ስልክና በኮምፒውተር ላይ ተጭነው የሚሰሩ ሶስት መተግበሪያዎችን ሰርቶ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል።መተግበሪያው በሀገራችን ውስጥ ያለውን የሎጀስቲክ አሰራር የሚያሻሽሉና የሚያቀሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጅን በመጠቀም ምርታማነትን የሚጨምሩ፣ የሃገርን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው ብሏል። በኢንፎርሜሽንና መረብ ደህንነት አስተዳደር እና ኢንኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እውቅና እንዳለውም ተገልጾልናል።መተግበሪያዎቹ በጭነት ትራንስፖርት ሥራ ለተሰማሩ አስተላላፊዎች አሽከርካሪዎች ደንበኞች አስጫኞች በቀላሉ እና በግልጽ የሚግባቡበት ሲሆን በቅንጅት እየተናበቡ የጭነት አገልግሎት ሰጪውንና ፈላጊውን አገናኝተው የተጫነው እቃ የት እንደደረሰ፣ መቼ በአስጫኙ እጅ እንደሚገባ፣ በግልፅ ለከፋዩም ሆነ ለአገልግሎት ሰጪው ተመኑ ስንት እንደሆነ ታውቆ ጭነቱ በአስተማማኝ ይዞታና በቅልጥፍና ወደፈለጉበት ቦታ የሚደርስበት ዘመናዊ አሰራር የሚከተል መሆኑ ድርጅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ### Response:
### Text: የመንግስት ኮሚኒኬሽን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ዛሬ 74 ዕርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ከአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በአባአላ መንገድ በኩል ወደ ትግራይ ክልል መላካቸውን አስታውቋል።በ3ኛ ዙር ወደ ትግራይ ክልል ከተላኩት ተሽከርካሪዎች ውስጥ 6ቱ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ናቸው ብሏል።የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው መግለጫ በትግራይ ክልል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደርሳቸው ለማድረግ የገባውን ቃል በማክበር ምቹ የሰብአዊ ዕርዳታ ማጓጓዣ ሁኔታን ለመፍጠር እየሠራሁ ነው ብሏል።ከዓለም የምግብ ፕሮግራም እና ሌሎችም አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች ድጋፍ እንዲደርስ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።በዚሁ መግለጫው በችግር ላይ ያሉ ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደርሳቸው ህወሓት አሁንም ከያዛቸው የአፋር እና አማራ ክልል አካባቢዎች እንዲወጣ ምቹ የእርዳታ ማስተላለፊያ መስመርን መዘርጋት እንዲቻል እንዲሁም ቡድኑ ከሚነዛቸው የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎች እንዲቆጠብ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና ሊያደርግ ይገባል ሲል ጥሪ አቅርቧል።በተጨማሪ እስካሁን ድረስ ያልተመለሱ 1 ሺህ 25 ተሽከርካሪዎች በፍጥነት እንዲመለሱ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል። ### Response:
### Text: ለሁሉም አዲስ ወደ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የመጀመርያ ዓመት ተማሪዎች ከሁሉም በማስቀደም ወደ ዩኒቨርሲቲያችን ስለተመደባችሁ እንኳን ደስያላችሁ። ዓዲግራት ውብና ተወዳጅ ከተማ ስትሆን ከኣዲስ ኣበባ በስተሰሜን በኩል ወደ 900ኪሜ ያህል ርቃ የምትገኝ ናት። ከመቐለ 120ኪሜ በስተሰሜን በኩል ተግኛለች።በኣውሮፕላን እስከ መቐለ ለምትምጡ እስከ መነሃርያ ብላችሁ ታክሲ በመያዝ ከመነሃርያ ወደ ዓዲግራት በህዝብ ማመላለሻ በ4050 ብር ኣከባቢ ወደ ዓዲግራት መነሃረያ ወይም ወደ ዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በ200ሰዓት ኣከባቢ ትደርሳላችሁ። ዓዲግራት ለኑሮ ብእጅጉ ተስማሚ የሆነ የኣየር ፀባይ ያላት ውብ ከተማ ስትሆን ዩኒቨርሲቲያችን በከተማዋ በስተሰሜንና ደቡብ በኩል በሁለት ግቢዎች ይገኛል። 29 302010 8 የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 29 እና 30 2010ዓም መሆኑ ኣውቃችሁ ብርድልብስ ኣንሶላ፡ ከተቻለ የስፖርት ቱታ 8 ጉርድፎቶ ግራፎች፡ የመማርያ እቃዎች እንደ ደብተር፡ እስክርቢቶ ወዘተ ይዛችሁ እንድትመጡ በኣክብሮት እንጠይቃለን። ተማሪ በተማሪ በተማሪ የሚባል ዝውውር የሌለ መሆኑ ኣውቃችሁ ግዜኣችሁ ኣንዳንዴም ገንዘባችሁ እንዳታጠፉ ከኣደራ ጭምር እናሳስባለን። መልካም ጉዞ ወደ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ይሆንላችሁ ዘንድ ልባዊ ምኞታችን እንገልፅላቸዋለን። 242010ምንጭ ### Response:
### Text: ሮሜሎ ሉካኩ ከትላንት ምሽት የዘረኝነት ጥቃት በኋላ ያስተላለፈው መልዕክት ባሳለፍነው ወር በርካታ ተጫዋቾች የዘረኝነት ጥቃት ደርሶባቸዋል። እኔም በትላንትናው ዕለት የጥቃቱ ገፈጥ ቀማሽ ሆኛለው። እግር ኳስ ሁሉም የሰው ዘር በእኩል የሚዝናናበት ጨዋታ ነው አንዱን ከሌላው ማግለል የምንወደውን ጨዋታ ዝቅ ያደርገዋል። በሁሉም ሀገራት የሚገኙ የእግርኳስ ፌዴሬሽኖች ለእንደዚህ አይነት ማግለል ጠንከር ያለ እርምጃ ይወስዳሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለው። የማህበራዊ ትስስር አውታሮች ኢንስታግራም ትዊተር ፌስቡክ እና ሌሎችም ከእግር ኳስ ክለቦች ጋር እጅ እና ጓንት ሆነው መስራት ይጠበቅባቸዋል ምክንያቱም አብዛኛው የሚለጠፉ መልእክቶች ስር ቀለምን መሰረት ያደረገ ጥቃት ስለማይጠፋ ነው። ክቡራት እና ክቡራን አሁን 2019 ላይ ነው የምንገኘው በዚህ የሰለጠነ ወቅት ላይ ወደፊት መሄድ ሲገባን የኋልዮሽ ጉዞውን ተያይዘነዋል ስለዚህ እኛ ኳስ ተጫዋቾች ህብረታችንን አጠንክረን የምንወደውን እግር ኳስ ንፁህ ለማድረግ አንድ አቋም ላይ መድረስ አለብን ሮሜሎ ሉካኩ ክለቡ ኢንተርሚላንን አሸናፊ ያደረግችዋን ግብ ካስቆጠረ በኋላ በ ካግላሪ ደጋፊዋች የዘረኝነት ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ያስተላለፈው መልዕክት።ቲኪቫህ ኢትዮጵያ እና ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ስፖርት ዘረኝነትን ያወግዛል። ### Response:
### Text: ሲአይኤ መፈንቅለ መንግሥት አሲሮብኝ ነበር የኤርትራ መንግስትየኤርትራ መንግሥት ትላንት አርብ ባወጣው ያልተለመደ መግለጫ ሲአይኤን በመፈንቅለ መንግሥት ሽረባ ይከሳል። የእስራኤል የስለለ መረብ ሞሳድንም ስም በማጥፋት ተባብሯል ይላል።የኤርትራ መንግሥት ይህን ስኢረ መንግሥት ተሸርቦብኝ ነበር የሚለው በፈረንጆች 2011 ላይ ነው። ይህንኑ የተመለከተ ሁነኛ ምሥጢራዊ መረጃ እጄ ገብቷል ብሏል።ምስጢራዊው የመፈንቅለ መንግሥት ሴራው በኤርትራ ውስጥ ልክ እንደ አረቡ ጸደይ ዓይነት ሕዝባዊ ተቃውሞና አመጽ የማስነሳት ጥንስስ ነበረበትም ብሏል።ይህ በትግርኛ ቋንቋ ትላንት አርብ የተሰራጨው የኤርትራ መንግሥት መግለጫ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራውን ለመጎንጎን በኬንያ መዲና ናይሮቢ ተሰብስበው ነበር ያላቸውን ተቋማትና ግለሰቦች በስም ሳይቀር ይዘረዝራል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን ዩኤንኤችሲአር ኤርትራዊያንን በገፍ እንዲሰደዱ የማሳለጥ ሥራ እንዲሰራ በሲአይኤ ይታዘዝ ነበር ይላል።ሴረኞቹ የኤርትራ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አባላትም አገራቸውን ጥለው እንዲኮበልሉ ያባብሏቸው ነበር ሲልም ይከሳል። በ2009 በኬንያ ተሳትፎ ያደረገው የኤርትራ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከፊል አባላት ወደ አገር ቤት ለመመለስ አሻፈረኝ ማለታቸው ይታወሳል። 11022 ### Response:
### Text: ኢራን የአውሮፕላን አደጋውን በቪድዮ የቀረፀውን ሰው በቁጥጥር አውላለችኢራን የአውሮፕላን አደጋውን በምስል የቀረጸውን ሰው በቁጥጥር ስር አውላለች፡፡ አውሮፕላኑ በሚሳኤል ተመቶ ሲወድቅ በምስል ያስቀረውን ሰው በቁጥጥር ስር ማዋሏን ነው ኢራን ያስታወቀችው፡፡ ግለሰቡ ከብሄራዊ ደህንነት ጋር በተያያዘ ክስ ይመሰረትበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡የበረራ ቁጥሩ 752 የሆነው ይህ አውሮፕላን ባለፈው ሳምንት ረቡእ እለት ነበር ከቴህራን ከተነሳ በኋላ በሚሳኤል ተመቶ የተከሰከሰው፡፡ ኢራን ድርጊቱ በስህተት የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ተሳትፈዋል ያለቻቸውን ሰዎች በቁጥጥር ስር እያዋለች መሆኑን አስታውቃለች፡፡ምርመራው በልዩ ፍርድ ቤት እንደሚታይም ፕሬዘዳንት ሃሰን ሩሃኒ ተናግረዋል፡፡ ይህ መደበኛና የተለመደ አይነት ጉዳይ አይደለም መላው አለም ይህን ችሎት ይመለከተዋል ብለዋል፡፡በተፈጠረው አሳዛኝ ክስተት ተጠያቂ የሚሆነው አንድ ግለሰብ ብቻ እንደማይሆንም ተናግረዋል፡፡ ኢራን አውሮፕላኑ በሚሳኤል መመታቱን ክዳ የነበረ ቢሆንም በኋለ ግን በአየር መቃወሚያ ሚሳኤል ተመትቶ መውደቁን አምናለች፡፡ይህን የሚያሳየው ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ከተሰራጨ በኋላ ተንታኞች አውሮፕላኑ በሚሳኤል መመታቱን በእርግጠኝነት እንዲናገሩ አድርጓቸዋል እንደ ቢቢሲ ዘገባ፡፡ 1078 ### Response:
### Text: በትግራይ ክልል ለሚገኙ ተማሪዎች 28 ሚሊዮን ማስክ ይከፋፈላል ትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያየትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ስርጭትን በተመለከተ ክልሎች ለተማሪዎቻቸው ተረክበው እንዲያሰራጩ የሚገልጽ እና ድልድሉንም አስመልክቶ የጊዜ እና የመጠን ዝርዝር ያለው ደብዳቤ ለክልል ትምህርት ቢሮዎች ጽፏል፡፡ በዚህ ደብዳቤ ውስጥ የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ አልተካተተም፡፡ ይህም በበርካቶች ዘንድ ጥያቄ ፈጥሯል፡፡ጉዳዩን በተመለከተ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጠይቀን ተከታዩ መረጃ ተሰጥቶናል የተደረገው ድልድል የትግራይ ክልል ተማሪዎችን ጭምር የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ እንዲያገኙ ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡ በደብዳቤው ላይ ማካተት ያልተቻለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት በቅርቡ ባሳለፈው ውሳኔ ምክንያት ነው፡፡ አሁን ላይ በመላ ሀገሪቱ ላሉ 26 ሚሊዮን ተማሪዎች የማስክ አቅርቦት እንዲሟላ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ለትግራይ ክልል ለሚገኙ ተማሪዎችም ይህንን ሥርጭት ለማድረስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከወረዳዎች እና ከዞኖች ጋር ግንኙነት ጀምሯል፡፡ ሥርጭቱም በዚያው በኩል የሚካሄድ ይሆናል፡፡ አጠቃላይ ወደ 50 ሚሊዮን ማስክ በዝግጅት ላይ ነው፡፡ ከዚህም ውስጥ 28 ሚሊዮን የሚሆነው በትግራይ ክልል ለሚገኙ ተማሪዎች የሚከፋፈል ይሆናል፡፡ ### Response:
### Text: ትምህርት ቤቶች ዳግም ሊዘጉ የሚችሉበት እድል አለ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮበትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መንገዶች በአግባቡ ተግባራዊ ባለመደረጋቸው ትምህርት ቤቶች ዳግም ሊዘጉ የሚችሉበት እድል መኖሩን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።ትምህርት ቢሮው ይህን ያሳወቀው በባህር ዳር ከተማ እንድናገለግሎ ማስክዎን ያድርጉ የሚል ንቅናቄ በተጀመረበት ወቅት ነው።በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተዘግተው የነበሩ ትምህርት ቤቶች ተገቢው ጥንቃቄ እየተደረገ ትምህርት እንዲቀጠሎ ተደርጎ መከፈታቸው ይታወሳል።ምንም እንኳን ትምህርት ቤቶች ቢከፈቱም በኮሮና ቫይረስ መከላከያ ላይ ያለው አተገባበር በታሰበው መልኩ እየሄደ አይደለም ተብሏል።ተማሪዎች ትምህርት ቤት ዳግም የተከፈተ ሰሞን ጥሩ ጥንቃቄ ያደረጉ የነበር ሲሆን አሁን ላይ ትኩረት እያጡ መከላከያውም እየተረሳ መሆኑ ተገልጿል።የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላው አበበ አሁን እየታየ ያለው መዘናጋት እና ግዴለሽነቱ ካልቆመ ትምህርት ቤቶች ተመልሰው ሊዘጉ እንደሚችሉ አሳስበዋል።ምክትል ቢሮ ኃላፊው አክለው በክልሉ ውስጥ ያሉ ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያን ተግባራዊ በማድረግ ሊመጣ እና ሊያጋጥም ከሚችለው አደጋ እራስን መጠበቅ እንደሚገባ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: ከኢትዮጵያ ያመለጠው ኤርትራዊ ሰው አዘዋዋሪ ኪዳኔ ዘካሪያስ ሀብተማርያም በኔዘርላንድስ በጥብቅ ከሚፈለጉ ዝርዝር ውስጥ ተካተተ።የኔዘርላንድስ ዐቃቤ ሕግ ኤርትራዊውን በሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪነት የሚፈለገውን ኪዳኔ ዘካርያስ ሀብተማርያምን በሕግ በጥብቅ ከሚፈለጉ ሰዎች ዝርዝር ውስጥ አካቶታል።ኪዳኔ ዘካርያስ ሀብተማርያም ከሚቀርቡበት በርካታ ክሶች መካከል ግድያ፣ ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና በሕገ ወጥ መንገድ የተገኘ ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ መጠቀም የሚሉት ይገኙበታል።የኔዘርላንድስ ዐቃቤ ሕግ ኤርትራዊው ተይዞ በወንጀል እንዲጠየቅ በሚል በከፍተኛ ደረጃ ከሚፈለጉ ሰዎች ዝርዝር ውስጥ እንዳካተተው ተዘግቧል።ኪዳኔ በአዲስ አበባ ለአንድ ዓመት ገደማ የሁለት ስደተኞች ግድያን ጨምሮ በስምንት ሰዎች ዝውውር ተከሶ የፍርድ ሂደቱን እየተከታተለ ሳለ ነው ከእስር ያመለጠው።በወቅቱ መጸዳጃ ቤት ውስጥ ልብስ ቀይሮ ከፖሊስ እጅ እንዳመለጠ ተዘግቧል።በፍርድ ቤት ቀጠሮ ዕለት ከፍርድ ቤት ማምለጡ በርካቶችን ያነጋገረ እና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ለፍርድ እንዲቀርብ ንቅናቄ የሚያደርጉ የመብት ተሟጋቾችን ያስቆጣ ነበር።ኪዳኔ ከእስር ቢያመልጥም ፍርድ ቤቱ በሌለበት የእድሜ ልክ እስራት ፈርዶበታል። ኪዳኔ አሁን የት እንዳለ በትክክል አይታወቅም።ያንብቡ 10202 ### Response:
### Text: ወላጆች ልጆቻቸው እንዲመለሱ ጠይቀዋልልጆቻቸውን ለትምህርት ወደቻይና የላኩ ወላጆች መንግስት ወደ አገራቸው እንዲመልሳቸው ጠይቀዋል። በቻይና በተለይም በዉሃን ግዛት ከ300 በላይ ኢትዮጵያዉያን ተማሪዎች የሚገኙ ሲሆን መንግስት እነዚህን ተማሪዎቸ ወደ አገር ያስመልስልን ሲሉ ወላጆቻቸዉ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድምፃቸውን አሰምተዋል፡፡የተማሪ ወላጆችበጭንቀት ዉስጥ ነን መንግስት ልጆቻችንን ይመልስልን በሰው አገር በረሃብ እና በበሽታ ሊያልቁብን ነው ሲሉ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተገኝተው በአካል ጠይቀዋል።በቻይናዋ ቾንቺ ግዛት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጀነራል ፅቤት ተጠባባቂ ቆንስል ጀነራል አቶ አንተነህ ታሪኩተማሪዎቹ እያጋጠሟቸዉ ያሉትን ችግሮች መግለጫ አዉጥተን ለኢትዮጵያ መንግስት አቅርበናል። ተማሪዎቹ ምላሽ እንዲያገኙ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሰራ ነዉተማሪዎቹ የምግብ እና ሌሎች መሰራታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ተቸግረዋል ችግሩ በስፋት የሚስተዋለዉ በሁቺያንግ ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ዉስጥ ነዉ። ለዚህም 3 ሱፐርማርኬቶች ለተማሪዎች ከፍት እንዲሆኑ ተደርገዋል።መንግስት ኢትዮጵያዊያኑን የመመለስ እቅድ አለውተማሪዎቹ ባሉበት ሆነው ከችግር ነጻ እንዲሆኑ ከቻይና መንግስት ጋር ውይይት እያደረግን ነው ፣ ከተማሪዎቹ ተወካዮች ጋርም እየተመካከርን ነው 1078 ### Response:
### Text: ነሃሴ 182012 ዓም የኢትዮጵያ የኮቪድ19 መረጃዎች 2 ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 601 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 78 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰድ ህይወት አልፏል።በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 22 ከሀዋሳ ከተማ 16 ከወንዶ ገነት ወረዳ 8 ከይርጋለም ከተማ 6 ከአለታ ጩኮ ከተማ ይገኙበታል።አጠቃላይ በሲዳማ 1206 በቫይረሱ የተያዙ 14 ሞት 328 ያገገሙ በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 849 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 26 ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።አጠቃላይ በሐረሪ 874 በቫይረሱ የተያዙ 17 ሞት 274 ያገገሙ በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 1623 የላብራቶሪ ምርመራ 59 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። የሶስት ሰዎች ህይወት አልፏል 1 ከአርባ ምንጭ፣ 2 ከጌዴኦ ዞንበቫይረሱ የተያዙት ከወላይታ 22 14ቱ ከዳሞት ወይዴ፣ 4 ከሶዶ፣ 2 ኪንዶ ኮይሻ፣ 1 ኦቢቻና 1 ቦሎሶ ሶሬ፣ ከጋሞ 12 4 ከአርባምንጭ፣ 5 ከጨንቻ፣ 1 ከገረሴና 1 ከቁጫ፣ ከደኦሞ 4 4ቱም ከሐመር፣ ከጉራጌ 3 2 ከእነሞር እና 1 ከቀቤና ከጌድኦ 3 1 ከዲላና 2 ገገደብ፣ ከዳውሮ 3 3ቱም ከተርጫ፣ ከሐዲያ 3 2ቱ ከሚሻና 1 ከአንሌሞ፣ ከስልጤ 2 1 ከሚቶና 1 ከሳንኩራ፣ ከምዕራብ ኦሞ 3 3ቱም ከጋቺት ወረዳ፣ ከምባታ ጠምባሮ 1 ከሺንሺቾ፣ ከሸካ 1 ማሻ ከተማ እና ከደራሼ ልወረዳ 2 ናቸው፡፡ ### Response:
### Text: ዙምባዌ️በዚምባቡዌ የተቀሰቀሰውን አለመረጋጋት ለመቆጣጠር የተሰማሩ የጸጥታ ኃይሎች ቤት ለቤት በሚያደርጉት አሰሳ ሴቶችን አስገድደይደፍራሉ ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ወነጀሉ። መንግስት እየወሰደ ያለው ኃይል የተቀላቀለበት እርምጃ መቀጠሉ ተነግሯል።ቁጥራቸው በርከት ያሉ ሴቶች በጸጥታ ኃይሎች አባላት እንደሚደፈሩ የሚያመለክቱ የሚረብሹ መረጃዎችን ተቀብለናል ሲሉ የዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ሂዩማን ራይትስ ዎች የደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ዴዋ ማሂንጋ ለአሶሴትድ ፕሬስ ተናግረዋል። ድብደባ፣ ማስፈራራት እና ሌሎችም ጥቃቶች ከምንጋጋዋ መመለስ በኋላም ቀጥለዋል ብለዋል። የዚምባቡዌ ፕሬዝዳንት ኤመርሰንምንጋጋዋ በነዳጅ ዋጋ መናር ምክንያት በሀገራቸው የተቀሰቀሰውን ብጥብጥ ለማረጋጋት በውጭ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉብኝታቸው አቋርጠው ባለፈው ሰኞ ወደ መዲናይቱ ሃራሬ መመለሳቸው ይታወሳል። ፕሬዝዳንቱ በሀገሪቱ ያለው ሁከት ተቀባይነት እንደሌለው ቢናገሩም ዚምባቡዌ አሁንም መረጋጋት እንደራቃት እና ጥቃቶች መቀጠላቸውን የሀገሪቱ ዜጎች ይናገራሉ።ባለፈው ሳምንት በዚምባቡዌ በተቀሰቀሰው ግጭት ቢያንስ 12 ሰዎች ሲገደሉ 300 ሰዎች መቁሰላቸውን የመብት ተሟጋቾች እና የህክምና ባለሙያዎች አስታውቀዋል።ምንጭ የጀርመን ድምፅ ራድዮ ### Response:
### Text: ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት እስረኞች አመለጡ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዞን አንድ በነፍስ ግድያ ጥፈተኛ ተብለው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበሩት 2 ታራሚዎች አሸናፊ መለሰ ሳሙኤል መካ ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ ም ከረፋዱ 3 እስከ 4 ባለው ሰአት ውስጥ ከማረሚያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ያመለጡ ሲሆን ኤፍሬም ገ ጊዩርጊስ የተባለ ሌላ እስረኛ ደግሞ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ከመኪና ላይ ዘሎ ማምለጡን ተሰማ፡፡ ማረሚያ ቤቱ የሁለቱ የታራሚዎቹን ማምለጥ ማታ በቆጠራ ሰአት እንዳወቀ ዋዜማ ሬድዮ ምንጮቹ እንደገለፁለት ተናግሯል፡፡ ይህን ተከትሎ ማረሚያ ቤቱ በእስረኞች ላይ ቁጥጥሩን ማጥበቁን ተሰምቷል። እንደሚያመልጡ ታውቁ ነበር ፣ ያያችሁት ነገር አለ በሚል ታራሚዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ እየደረሰ እንደሆነ የታራሚ ቤተሰቦች ተናግረዋል። እስረኞች የጣት ቀለበትና የአንገት ሀብልም እንዲያወልቁ መደረጋቸው አግባብ አይደለም ይላሉ።የእስረኞቹን እንዴት አንዳመለጡ እና አሁንስ በቁጥጥር ስር ውለዋል ወይ ብለን ተጨማሪ ማብራሪያ ለመጠየቅ ወደ ማረሚያ ቤቶች የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ገረመው አያሌው ስልክ የደወልንላቸው ሲሆን ከጠየቅናቸው በኃላ የማይመች ቦታ ነኝ መልሼ ልደውል በማለት የእጅ ስልካቸውን ዘግተውታል ፣ በተደጋጋሚ ብንደውልም ሊሰራልን አልቻለም፡፡ምንጭ ዋዜማ ራዲዮ ### Response:
### Text: የኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ምላሽበጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረትየሙዚቃ መሳርያ ያለበት የዩኒቨርሲቲ ምርቃት ፕሮግራም እንዲሁም የእነ እስክንድር ፕሮግራም አጠገብ ለአጠገብ ባሉ የአዳራሽ ክፍሎች ተገጣጥሞብን ነበር። የዩኒቨርሲቲው ፕሮግራም ቀደም ብሎ የተያዘ የነበረ ሲሆን ይሄኛው ግን በሁዋላ ላይ የተያዘ ነበር ፣ እርግጥ ሁለቱንም አንድ ላይ መቀበል አልነበረብንም። ትናንት ማታ ደውለን ሌላ ቀን በፈለጋችሁበት ቀን አድርጉት፣ አለበለዛ የሙዚቃ መሳርያ ያለበት ፕሮግራም አጠገባችሁ ያለ አዳራሽ ውስጥ ስላለ ትረበሻላችሁ አልን። እነርሱ ግን አልተስማሙም። አሁንም በፈለጉበት ሌላ ቀን መጥተው ፕሮግራማቸውን ማካሄድ ይችላሉ። ፖሊስ ግን ጫናም አላደረገብንም። አቶ ወገኔ ማቴዎስ የኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ስራ አስኪያጅሂልተን ሆቴልም፣ ራስ ሆቴልም፣ ኢትዮጵያ ሆቴልም ሲሉ የነበረው እኛ አልከለከልንም ነበር። አሁን ይሄ ለአራተኛ ግዜ መደገሙ ነው። ሆቴሎቹ ማለት ያለባቸውን ብለዋል። ከዚህ ውጪም አልጠበቅንም። ለእኛ ግን በውስጥ የሚነግሩን ሌላ ነገር ነው፣ ይሄ ከእኛ አቅም ውጪ ነው ይሉናል። ብዙ ግዜ ገንዘብ ከፍለን ከዛ ስለ ስብሰባችን በሚድያ ስናሳውቅ ነው ይሄ ክልከላ እየመጣ ያለው። ምክንያቱ ይሄ ከሆነ ገንዘብ ለምን ተቀበሉን ብዙ ጥያቄዎች ሊነሱ ይችላሉ። ### Response:
### Text: ማስረጃ ካገኘን ነገ ጥዋት እናነሳለን ዶር ዐቢይ አህመድጠቅላይ ሚኒስትር ዶር ዐቢይ አህመድ ካቢኔያቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበው አፀድቀዋል።እጩዎች ሹመታቸው ከመፅደቁ በፊት በምክር ቤቱ አባላት አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ቀርበው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።አንድ አስተያየት የሰጡ የምክር ቤት አባል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡት እጩዎች 95 በመቶ አስደሳች መሆኑን ገልፀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሚኒስትሮቹን ሲመርጡ ካነሷቸው ነጥቦች ሌብነትን የማስቀረት ጉዳይ አንዱ መሆኑ በዋነኝነት አንስተው ጉዳዩ አሳሳቢ ነው ብለዋል። አንዳንድ ሾልከው የገቡ ሚኒስትሮች አሉ የሚል ስጋት አለኝ ያሉ ሲሆን ለዚህም መረጃው አለኝ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈለጉ ጊዜ ተጨባጭ መረጃዎችን ሌላ ጊዜ ልሰጣቸው እችላለሁ ሲሉ ተደምጠዋል።ጠሚ ዶር ዐቢይ በዚህ የምክር ቤቱ አባል ሃሳብ ላይ አስተያየት የሰጡ ሲሆን ማስረጃ ካገኘን ነገ ጥዋት እናነሳለን የሚከለክለን ነገር የለም ከነገ ወዲያም ካገኘን እናነሳለን፣ ዋናው አሁን ባለን እይታ በተቻለ መጠን የተሻለ ስራ የሚሰሩ ሰዎችን ለማቅረብ ሞክረናል ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ 100 ፐርሰት ፕርፌክት የሆነ ነገር መጠበቅ እንደማይገባ እና ያሉ ችግሮችም ካሉ በሂደት በመደጋገፍ ማስተካከል እንደሚቻልም ለምክር ቤቱ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: እኛ ለጎንደር ከተማ እና ለህዝቡ ክብር አለን 0 አቶ ኢሳያስ ጅራየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዛሬው ዕለት የምርጫ የጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስብሰባ አዳራሽ በማካሄድ ላይ ይገኛል ።ምርጫው ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ለምን ተቀየረ ይሄ አስተዳደራዊ ጉዳይ ነው ያሉት የወቅቱ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ጣልቃ ገብነቶች እና ሂደቶችን ስላየን ቦታውን ቀይረናል ፣ ውሳኔውን አስተላልፈን ለስራ አስፈፃሚ አቀረብን ሂደቱን ጠብቀን ነው ያደረግነው ብለዋል ። ሂደቱ የነበረው ይህ ነው ፣ ራስን መፈተሽ አስፈላጊ ነው ፣ ይሄንን ጉባኤ በዚህ መልኩ ነው ማስኬድ ያለብህ ብሎ የመንግስት አካል ትዕዛዝ መስጠት አይችልም።ቦታ ተቀየረ ተብሎ ጥቃቅን ጉዳይ አንስቶ አጀንዳ ማድረግ አግባብ አይደለም ፣ ደግሞም ቦታ ስንሰጥ የሰጠነው ለክልሉ ሳይሆን ለከተማው ነው።እኛ ለጎንደር ከተማ ለህዝቡ ክብር አለን ፣ የጦርነት ወላፈን ከነካቸው ቦታዎች አንዱ ነው ሁለት ወር ለኢኮኖሚውም እገዛ ውድድር ሁሉ አድርገን የቆየነው እንጂ የሁለት ቀን ከለከሉ መባል የለብንም በማለት አቶ ኢሳያስ ጅራ ተናግረዋል።በዛሬው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከፊፋ እና ካፍ ተወክለው የመጡ ታዛቢዎችን ጨምሮ ከፍተኛ የስፖርቱ ባለስልጣናት ታድመዋል ።ቲክቫህ ስፖርት 0 0000 ### Response:
### Text: በሀገራችን የስኳር እጥረት እንዳለ የሚታወቅ ነው። ኢቢሲ ዛሬ ስኳር ማብዛት ለካንሰር ያጋልጣል ብሎ በፌስቡክ በለጠፈው የጥናት ውጤት ኢትዮጵያዊያን አዝናኝ አስተያየቶችን ሲሰጡ ውለዋል እኔም ለእናተ ጥቂቱን መረጥኩላችሁ ኧረ በቃ ይቅርብና ውጪ ይሸጥና አለምን በካንሰር ጨርሱት እኛ ጤና እንሁን።እንኳን ጠፋ ስኳር የታባቱ ድሮም ያለምክንያት አልጣፈጠም። ወዴት ወዴት ነው ነገሩ ምነው የመብራቱን ጥናት ረሳችሁትሳ መብራት አዘውትሮ ማብራት ለትራኮማ ያጋልጣል ይላሉ አንዳንድ ጥናቶች ሃሃሃሃ ድሮም ሙጀሌ የሚፈነዳው ሲያብጥ ነው አለች አያቴ መንግስታችን የህዝቦቹን ጤንነት ከካንሰር ለመጠበቅ ሲል በቅርቡ 40ሺህ ኩንታል ስኳር ላይ የወሰደውን እርምጃ ከልብ እናደንቃለን እድሜ ለፀሐዩ መንግስታችን አርቆ አሳቢ ስለሆነ ይኸው ስኳር ካዬን 3 ወር ሞልቶናል ደግሞ መናፈቃችንን አውቀሽበሽታ ነው አይጠቅማችሁምአውቀን ነው ያጠፋነው አልሽን እናመሰግናለን። እናንተ ባትኖሩ ማን ይመክረን ነበር ስኳር ሲጠፋ በዚህ መልኩ ህዝብ ስኳር እንኳን ቀረብኝ እንዲል መስራት ጀመራችሁ። ነገ ደግሞ ፋብሪካዎቹ የተሳካላቸው እለት ስለ ስኳር ጥቅም የሚዘግብ አዲስ ጥናት እንደማታጡ ተስፋ አደርጋለሁ።ምንም እንኳን በስኳር መጥፋት የተማረራችሁ ብዙ ብትሆኑም አስተያየቶቹ እንዴት ናቸው ### Response:
### Text: ተመራቂ ተማሪዎች ለሀገር በመስራት ብድሯን መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 9 ሺህ 637 ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ንግግር አድርገዋል፡፡በንግግራቸውም ወላጆች ማየት የሚፈልጉት የተመራቂ ተማሪዎችን ስኬት ነው ያሉ ሲሆን ተመራቂ ተማሪዎችም ወላጆቸውን ማስታወስ ይገባቸዋል ብለዋል።እንዲሁም ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምሮ ያሉ መምህራኖቻቸውን ሊያስታውሱ እንደሚገባ እና እነሱን ሊያስደስቱ የሚችሉ ተግባራትን እንዲፈፅሙ አሳስበዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመራቂ ተማሪዎች በማንኛውም ጉዳች ሊደራደሩ ይገባል ያሉት ሲሆን በኢትዮጵያና በኢትዮጵያውያን ጉዳይ ግን ድርድር አያስፈልግም ብለዋል።ለተመራቂ ተማሪዎች መልካም ምኞታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዩኒቨርስቲዎች የምርምር፣ የተለያዩ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባቸው እና ጥልቅ ትንተና የሚካሄድባቸው ናቸው ሲሉ ገልፀዋል።ተመራቂዎችም የአገልግሎት መርሆችን፣ መስጠት፣ ፍቅር እና በህይወት ዘመን ለመማር ዝግጁ መሆንን ሊከተሉ ይገባል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 9 ሺህ 637 ተማሪዎችን ባስመረቀበት ወቅት ለአቶ ተወልደ ገብረማርያም እና ሀጂ ሙፍቲ ሼክ ዑመር እድሪስ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል። ### Response:
### Text: ዶር አብይ ግብፅን አስጠንቅቀዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ባሰሙት ንግግር የ«ታላቁ ህዳሴ ግድብ»ን በተመለከተ ግብጽን አስጠነቀቁ። ግድቡ የማንንም ጥቅም ለመንካት ሳይኾን ኢትዮጵያ የሚገባትን ጥቅም ለማግኘት የሚከወን መኾኑን አስገንዝበዋል። በግብጽ በኩል ግድቡን በተመለከተ ቀደም ሲል ስለተሰጠው ማስጠንቀቂያ ሲናገሩም አስፈላጊ ከኾነ ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶቿን ለጦርነት ማሰለፍ እንደምትችል አሳስበዋል።«አንድ አራተኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ደሃ እና ወጣት ነው። ስለዚህ አፍሪቃ ጋርም እንዋጋ ከተባለ ብዙ ሚሊዮን ማሰለፍ ይቻላል ማለት ነው። ውጊያ መፍትኄ አይደለም እንጂ በውጊያ፣ በጥፋት ብዙ ጥቅም የለውም። ግብጽንም አይጠቅምም እኛንም አይጠቅምም ሱዳንንም አይጠቅምም። አንዳንዱ ሚሳይል መተኮስ የሚችል ከኾነ አንዳንዱ ደግሞ ቦንብ ታጥቆ ለኢትዮጵያ ከኾነ፣ ለባንዲራ ከኾነ ለምን ያ አልኾነም ካይሮ ላይ ያፈነዳል ማለት ነው። በማፈንዳት በጦርነት ሰላም፣ ጥቅም አይገኝም። እንደዚህ አይነት ሐሳብ ጥሩ አይደለም። ጥሩ ቁጭ ብሎ መነጋገር ነው። ጥሩ ጉዳት እንዳያመጣ መወያየት ነው። ያ እንደተጠበቀ ኾኖ ግን ምንም ኃይል ኢትዮጵያን ግድብ ከመገደብ ሊያስቆማት አይችልም።»ምንጭ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ፋይል ### Response:
### Text: ችሎት ብርጋዴርጄነረልተፈራማሞ የአብክመ ጠቅላይ ፍቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2014 ዓም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል።በዚህም የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ መርማሪ ፖሊስ ምርመራየን ጨርሸ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቢ ህግ ለመላክ በዝግጅት ላይ ነኝ ያለ ሲሆን የክልል ዐቃቤ ህግ በችሎት ቀርቦ አዎ ምርመራው አልቋል የክስ መመስረቻ ጊዜ 15 ቀናት ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው ምርመራ ካለቀ ደንበኛችን የተከሰሱበት ጉዳይ ዋስትና የሚያስከለክል ባለመሆኑ እና ተጠርጣሪው ደንበኛችን ታዋቂ ሠው በመሆናቸው ሊጠፉ ስለማይችሉ የደንበኛችን የዋስትና መብት ይከበርላቸው ሲሉ ተከራክረዋል። ፍርድ ቤቱም ሲሰጥ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ምርመራው ያለቀ በመሆኑ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ ዘግቷል። በመቀጠል የተጠርጣሪ ጠበቆች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ዐቃቤ ህግ አስተያየት እንዲሰጥበት አድርጓል። ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሰሱበት ጉዳይ የሽብር ወንጀል ስለሆነ በተጨማሪም ከሚዲያ ጋር በተያያዙ ሌሎች ተጨማሪ ክሶች ሊቀርቡ ስለሚችሉ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም ሲል ተከራክሯል።ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ የተጠርጣሪ የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ ለሰኔ 32014 ዓም ቀጠሮ ሰጥቷል።መረጃው የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው። ### Response:
### Text: የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠሚ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በጣና ፎረም የተናገሩት ያለፈው ታሪካችን ሊያስተምረን ይገባል ስለችግሮቻችን ማንንም አንወቅስም መውቀስ ካለብን ራሳችንን ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ በአክሱም ዘመን የነበረንን ስልጣኔ ተመልከቱ በግብጽ የነበረንን የቀደመ ስልጣኔ አስቡ ችግራችን የነበረንን ጥንታዊ ስልጣኔ እና ታሪክ በተገቢው መንገድ ለልጆቻችን አለማስተማራችን ነበር። አሁን ግን ለልጆቻችን ከማስተማራችን በፊት ስለራሳችን የተሳሳተውን እይታችን ማረም ይገባናል።አዎ ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት አሜሪካ ለሀገሬ ኢትዮጵያ በመቶ ሚሊየኖች የሚቆጠር ዶላር አውጥታ ምግብ እረድታ ይሆናል ነገር ግን አሜሪካ የረዳችን ከችግራችን በምንወጣበት መንገድ አልነበረም። ግብርናችን እንዲሻሻል፣ ቴክኖሎጂ እንድንጠቀም እና የተሻሻለ አሰራርን እንድንተገብር ተደጋጋሚ ድጋፍ የጠየቅናት አሜሪካ በፖሊሲ ሰበብ ፈቃደኛ አልነበረችም።ኢትዮጵያዊቷ ንግስት ሳባ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ተሻግራ እንደ ሀገር ንጉስ ሰለሞንን ስትጎበኝ አሜሪካ እንደ አህጉርም እንደ ሀገርም አትታወቅም ነበር።ከኋላ እየመጡ ለሚቀድሙን ሁሉ እርግጥ ነው ኅላፊነቱን መውሰድ ያለብን ራሳችን ነን።የጣና ፎረም መንፈስም ችግርን በግልፅ ተናግሮ በጋራ እና በትብብር መፍትሔ መፈለግ ነው። ### Response:
### Text: መምህራኑ ወደ ተቋማቸው እንዲመለሱ ጥሪ ተደረገ።በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት ተመድበው የነበሩ የኣክሱም እንዲሁም የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መምህራን ወደ ተቋማቸው እንዲመለሱ ጥሪ ተደርጓል።አክሱም ዩኒቨርሲቲ ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት ለመጀመር የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን ሐምሌ 202015 ዓም ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።በመሆኑም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት ተመድበው የነበሩ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ መምህራን የአገልግሎት ጊዜና የተከፈላቸውን ደመወዝ የሚገልጽ ክሊራንስ በመያዝ ከነሐሴ 102015 ዓም በፊት ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በመመለስ ሪፖርት እንዲያደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።በተመሳሳይ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መምህራን ወደ ተቋማቸእ እንዲመለሱ ጥሪ ተደርጓል።ዩኒቨርሲቲው ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት ለመጀመር የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን ሐምሌ 202015 ዓም ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።ትምህርት ሚኒስቴርም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት ተመድበው የነበሩ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መምህራን የአገልግሎት ጊዜና የተከፈላቸውን ደመወዝ የሚገልጽ ክሊራንስ በመያዝ ከነሐሴ 052015 ዓም በፊት ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በመመለስ ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ### Response:
### Text: ከአዲስ ቸኮል️አሁን መረጋጋት ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡ ቁጣን የሚቀሰቅሱና ወደጎዳና መውጣትን የሚያበረታቱ ፅሑፎች ጉዳት እንጂ ጠቀሜታ የላቸውም፡፡ በተፈፀመው ግድያ ዙሪያ የየራሳችን ትንታኔዎች ይኖሩናል፡ የምዝበራ ሚስጥር እንዳያወጣ ነው የጠሚ አብይ ጉዞን ለማደብዘዝ ነው በኢንጂንሩ ቦታ ሌላ ሰው ለማስቀመጥ ተፈልጎ ነው እርስ በርስ በጥርጣሬ እንድንተያይና ወደግጭት እንድንገባ ነው ኦሮማራን ለማፍረስ ነው የግብፅ ሴራ ነው፣ ብዙ መላምቶች አሉ፡፡ አንድና ከዚያ በላይ ለልባችን የቀረቡ ግምቶች ይኖራሉ፡፡ ግን ስሜት ከመንገድ ያወጣናል እንጂ አይጠቅመንም፡፡ ባለፈው አንድ ወር በተለያዩ የሐገሪቱ አካባቢዎች ከደረሱ ጉዳቶች መካከል አብዛኞቹ ወጣቶችን በስሜት በሚቀሰቅሱ ፕሮፓጋንዳዎች የተፈጠሩ ናቸው፡፡ አሁን እሱ መደገም የለበትም ለሌላ ሳይሆን ምንም ጠብ የሚል ጥቅም ስለማናገኝበት፣ ይልቁንም አላስፈላጊ ጥፋት ውስጥ ልንገባ ስለምንችልበት፡፡ ነገር ግን ቀጣይ አቅጣጫንን ምን መሆን አለበት በሚለው ላይ ተረጋግተን እናስብ መድረኮችን ወይ ሌሎች አጋጣሚዎችን ፈጥረን ስለነጋችን እንምከር፡፡ እየተገደልን መቀጠል የለብንም የሚለው የሁሉም አቋም ነው፡፡ ግን እንደምናወራው ቀላል መፍትሔ የለውም፡፡ ረጋ ብለን ተጨንቀን ማሰብ ያለብን ሰዓት ላይ ነን፡፡ ### Response:
### Text: በጄዳ የሹሜሲ ዲፖርቴሽን ማዕከል ከገቡ በኃላ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ ህይወታቸው ያለፈ የኢትዮጵያ ዜጎችን የሚያውቃቸው ቤተሰብ ፣ ዘመድ እና ጎደኞች ሪፖርት እንዲያደርጉ ተጠየቀ።ከዚህ በታች የሟቾች ስም አስክሬናቸው የሚገኝበት ሆስፒታል የተገለፀ ሲሆን የምታውቋቸው ሰዎች በቢሮ ቁጥር 13 ቀርባችሁ ሪፖርት እንዲያደርጉ በጄዳ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅቤት አሳውቋል። ሂክመት መሀመድ የአስክሬን መገኛ ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል ከዲጃ ማህመድ የአስክሬን መገኛሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል ሮዳስ ሙሉ የአስክሬን መገኛ ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል ጀማል ከማል የአስክሬን መገኛ ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል ቢንያም ምሩፅ ሃጎስ የአስክሬን መገኛ ሰግር ሆስፒታል የኢንዲያ ተማም ህፃን ልጅ የአስክሬን መገኛ ሰግር ሆስፒታል መሃሪ ኃይሌ የአስክሬን መገኛ ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል ሱልጣን ሙሀመድ የአስክሬን መገኛ ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል በህታ ነጋሲ አፈወርቂ የአስክሬን መገኛ ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል ሰለሞን ሀዱሽ ተካ የአስክሬን መገኛ ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታልበዚሁ አጋጣሚ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን የመመለስ ስራ ዳግም የተጀመረ መሆኑ ቢታወቅም አሁንም ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ያሉ ዜጎች በርካታ በመሆናቸው ልዩ ትኩረት ሊደረግ ይገባል። ### Response:
### Text: የአፍሪካ ህብረት የጸጥታው ምክር ቤት በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በህብረቱ ልዩ መልዕክተኛ ኦባሳንጆ ገለጻ እንደተደረገለት አል ዐይን በድረገፁ አስነብቧል።ህብረቱ ዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓም አስቸኳይ ዝግ ስብሰባ አካሂዷል፡፡ ስብሰባው በበይነ መረብ የተካሄደ እንደነበር ተገልጿል።በስብሰባው ላይ የህብረቱ የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዲዎዬ፣ የህብረቱ የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት0ኦሊሴገን ኦባሳንጆ፣ በአፍሪካ ህብረት የግብጽ ቋሚ ተወካይ መሃመድ ጋድ እና በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ ተሳትፈዋል፡፡ስብሰባው የተካሄደው በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ለመምክርና የአፍሪካ ህብረት የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴገን ኦባሳንጆን ገለጻ ለማድመጥ ነበር፡፡በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ በተሳተፉበት በዚህ ስብሰባ ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ከመከረና የኦባሳንጆን ገለጻ ካደመጠ በኋላ ያለው ወይም ያስቀመጠው ቀጣይ አቅጣጫ እንዳለ የታወቀ ነገር የለም፡፡ነገር ግን ም ቤቱ የተሰበሰበበትን ጉዳይ የተመለከተ መግለጫን እንደሚያወጣ መረጃ እንዳለው አል ዓይን ዘግቧል። ### Response:
### Text: የ2014 ዓም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ድረስ በሁለት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።ለዚህም ተማሪዎች እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ረዲ ሽፋ ለኦቢኤን በሰጡት ቃል በአጠቃላይ በሁለት ዙር በሚሰጠው ፈተና ከ984000 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።ፈተናውን ከሚወስዱት ውስጥ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር 622739 መሆኑን አመልክተዋል።የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብዛት ያላቸው በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 3 2015 አስቀድሞ ፈተናው እንደሚሰጣቸው አቶ ረዲ ተናግረዋል።የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር ደግሞ 361279 ሲሆን በሁለተኛው ዙር ከጥቅምት 8 እስከ 112015 ፈተናውን እንደሚወስዱ አስረድተዋል።ከዚህ ቀደም የነበሩ የፈተና ችግሮችን ለመፍታት ፈተናው በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል ፈታኞቹ ደግሞ የዩኒቨርሲቲ መምህራን መሆናቸውን አሳውቀዋል።በተጨማሪም ፈተናው ከዚህ ቀደም ከነበረው ከ4 ኮድ ከፍ ማለቱን ገልፀዋል።ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ሲሆን ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ### Response:
### Text: መከላከያሰራዊት የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጽንፈኛ ሀይሎችንና ህገወጦችን በመታገል የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት እንደሚያረጋግጥ አስታወቀ፡፡ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታና በሰራዊቱ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄደዋል፡፡ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በሰራዊቱ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ አተኩሮ የተካሄደውን ውይይት ያስጀመሩት የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አደም መሀመድ ናቸው፡፡ ከፍተኛ አመራሮቹ በቅርቡ በተቋሙና በአማራ ክልል አመራሮች ላይ የደረሰው አደጋ ታላቅ ቁጭት መፍጠሩን በመግለጽ በቀጣይ ድርጊቱ እንዳይደገም እንደሚሰሩ በውይይቱ ማጠቃለያ ባወጡት ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ አረጋግጠዋል፡፡የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱና ለህዝቦች ሰላም መስዕዋትነት እየከፈለ የመጣ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው በቀጣይም የተለያዮ ጽንፈኛ ሀይሎችንና ህገወጦችን በመታገል የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት እንደሚያረጋግጥ አስታውቋል፡፡ ሰራዊቱ ከምንጊዜም በላይ ህገመንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት ለመወጣት በሚያስችለው ቁመና ላይ እንደሚገኝና የተሰውት ጓዶች ህልፈት አባላቱን ለበለጠ ጀግንነትና መስዋዕትነት የሚያነሳሳ እንጂ የሚያዳክም እንዳልሆነ ገልጿል፡፡ምንጭ የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዳይሬክቶሬት ### Response:
### Text: 0 በትግራይ የሰብዓዊ ረድዔት ሠራተኞች ችግር ላይ ያሉ ማህበረሰቦችን ለመድረስ በሚያደርጉት እንቅስቃሴዎች ላይ የሚገጥማቸው መሰናክል ተባብሷል ሲል የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ አሳስቧል።አጣዳፊ የምግብ እርዳታ ከሚያስፈልገው 52 ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ ከመጋቢት ወር መጨረሻ ወዲህ ለመድረስ የተቻለው 18 ሚሊዮኑን ብቻ ነው ብሏል።በክልሉ አሁን ካለው የከፋ የተመጣጠነ ምግብ ዕጥረት እንዳይከሰት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ያስታወቀው ኦቻ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ እስከዚህ የአውሮፓ 2021 ማብቂያ ድረስ በቂ እርዳታ ለማቅረብ 853 ሚሊዮን ዶላር እስከፊታችን ሃምሌ መጨረሻ ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል።በሌላ መረጃ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ተራድዖ ድርጅት ወይም አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር የትግራይ ግጭት እጅግ የከበደ ረሃብ እያስከተለ እንደሆነ እና ከ5 ሚሊዮን የሚበልጥ ህዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑን አሳስበዋል።ሳምንታ ፓዎር የቅድመ ማስጠንቀቂያ ቅኝታችን አጣዳፊ የምግብ ችግር መኖሩን ይጠቁማል ያሉ ሲሆን ችግሩ እጅግ አስከፊው ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል።የኢትዮጲያ መንግሥት ግጭቱን ለማቆም እንዲሁም የሰብዓዊ ረድዔት ሠራተኞች የተቸገረውን ህዝብ ለመድረስ እንዲችሉ አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ አለበት ሲሉ ገልፀዋል። ### Response:
### Text: በናይጄሪያ አንድ የ40 ዓመት ጎልማሳ በዝንጀሮ ፈንጣጣ መሞቱን የሀገሪቱ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል ትላንት ምሽት አስታውቋል።ይህ ሞት በዚህ ዓመት በሀገሪቱ ከተመዘገበው አጠቃላይ 21 ኬዝ ቫይረሱ ከተገኘባቸው 21 ሰዎች መካከል ነው። በናይጄሪያ ከሚገኙት 36 ግዛቶች ዘጠኙ የዝንጀሮ ፈንጣጣ ተመዝግቦባቸዋል።በሌላ በኩል በኮንጎ በ2022 9 ሰዎች በበሽታው መሞታቸው ሪፖርት መደረጉን ዋሽንግተን ፖስት አስነብቧል።ከግንቦት መጀመሪያ ጀምሮ ከ200 በላይ የተጠረጠሩ ኬዞች እና በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች በአብዛኛው በአውሮፓ ውስጥ ተገኝተዋል።የዓለም ጤና ድርጅት እስካሁን በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች መያዙ የታወቀው የዝንጀሮ ፈንጣጣ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብሎ እንደማይጠብቅ ትላንት መግለፁ ይታወሳል።ምንም እንኳን ድርጅቱ ይህን ይበል እንጂ በሽታው እንዴት እንደሚስፋፋ ሆነ ከበርካታ ዓመታት በፊት የፈንጣጣ መከላከያ ክትባት ዘመቻ መቋረጡ ያስከተለው አንድምታ ይኖር እንደሆን ጨምሮ ብዙ የማይታወቁ ነገሮች መኖራቸውን ገልጿል።ድርጅቱ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወይም በአየር በትንፋሽ ይተላለፍ እንደሆን በተጨማሪ የህመም ምልክት የሌላቸው ሰዎች በሽታውን ያስተላልፋሉ ወይ የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ጥያቄዎችን ይዞ እየመረመረ ነው። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሰራተኛ ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን ገለፀ።ጉባኤው ትናንትና እና ዛሬ ነው የተካሄደው።ትላንህ ጉባኤው በማህበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኪያ ለማ፣ በአየርመንገዱ የሰዉ ሀብት ም ፕሬዚዳንት ወሮ ዘነበወርቅ ገጻድቅ የመክፈቻ ንግግር የተጀመረ ሲሆን የማህበሩ የስራና የኦዲት ሪፓርቶች፣ የማህበሩ የ20222023 በጀትና እቅድ ውይይትና ማጽደቅ እንደተደረገባቸው ተገልጿል።የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ በዛሬው ውሎ ከድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውና ከፍተኛ የማኔጅሜንት አባላት ጋር ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከሰራተኞች በተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ምላሽ ተሰቶባቸዋል።ጠቅላላ ጉባኤው ለተለያዩ የሰራተኛ ተወካዮች ፣ የተመሰገኑ የስራ መሪዎችን የምስጋና የምስክር ወረቀት የሰጠ ሲሆን የአየርመንገዱ ሰራተኞች የማህበሩን ፕሬዝዳንት ኢር ተሊላ ዴሬሳን በማህበሩ ላስመዘገቡት ለውጥ ከፍተኛ ሽልማት እንዲሁም የአየር መንገዱን ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው የተለያዩ ስጦታዎችን አበርክቷል።በሌላ በኩል ጉባኤው ታግዷል ፣ አልተካሄደም በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩት መረጃዎች ውሸትና አሉባልታ ናቸው ያለው ማህበሩ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ ነው የተጠናቀቀው ሲል ገልጿል። ### Response:
### Text: የሁሉንም የክልል ልዩ ኃይሎችን እንደገና የማደራጀው ለዘላቂ የሀገር ጥቅም እና ድህንነት ነው ፌዴራል መንግሥትየፌዴራሉ መንግሥት በሁሉም ክልል ያለውን የልዩ ኃይል አደረጃጀት እንደገና የማደራጀቱ ስራ0 ለዘላቂ የሀገር ጥቅም እና ድህንነት ሲባል የሚደረግ ነው ብሏል።መንግሥት የዚህ ተግባር ዓላማ ትጥቅ ማስፈታት አይደለም ያለ ሲሆን ስራውን ከሁሉም የክልል መዋቅር ጋር በመወያየት እና በመግባባት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።ለዘላቂ የሀገር ጥቅም እና ድህንነት ሲባል የሚሰራው ስራ በጥንቃቄ እንደሚመራው ፌዴራል መንግሥት ህዝቡ እንዲያውቀው ብሏል።ከዚህ ቀደም የክልል ልዩ ኃይሎች በሀገሪቱ ወዳሉት ሌሎች መዋቅሮች እንዲገቡ ህዝብም ጭምር ሲጠይቅ ነበር ያለው የፌደራል መንግሥት በዚህ መሰረት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንደጀመረ አመልክቷል።በልዩ ኃይል ውስጥ ያሉ አባላት እንደምርጫቸው እንደ ፍላጎታቸው በሀገር መከላከያ ሰራዊት በፌዴራል ፖሊስ በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ። ወደነዚህ የፀጥታ መዋቅሮች የሚቀላቀሉት ትጥቃቸውን እንደያዙ ነው ተብሏል።በዚህ ውስጥ መካተት የማይፈልጉ የልዩ ኃይል አባላት መብታቸው እንደሚጠበቅ እና ወደ መደበኛ ሲቪል ህይወት እንደሚገቡ መንግሥት የማቋቋም ስራ እና ድጋፍም እንደሚያደርግ የፌዴራል መንግሥት አሳውቋል። ### Response:
### Text: ዛሬም ድረስ አሸናፊም ሆነ ሰላማዊ የሆነ መፍትሄ ያልተገኘለት የጎረቤት ሀገር ሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት አራት ወራት ሊያስቆጥር ተቃርቧል። በዚህ ጦርነት ምክንያት ከ24 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ይህ ማለት ከሀገሪቱ አጠቃላይ ዜጎች ውስጥ ግማሹ ያህሉ የምግብ እና ሌሎች ዕርዳታ እንዲፈልጉ አድርጓቸዋል።ነገር ግን በአሰቃቂው ጦርነት እና የገንዘብ ድጋፍ እጦት ምክንያት 25 ሚሊዮን ዜጎች ብቻ ናቸው ድጋፍ ያገኙት ተብሏል።እንደ ተመድ መረጃ ድጋፍ ከሚፈልጉ ዜጎች 14 ሚሊዮኑ ህፃናት ናቸው።በአጠቃላይ እስካሁን በጦርነቱ ከ3000 የሚልቁ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ከ6000 በላይ ተጎድተዋል ሚሊዮኖችም ሀገራቸውን ጥለው ተሰደዋል የሀገሪቱ ኢኮኖሚም ክፉኛ ተጎድቷል፣ የዜጎች ደህንነትም ጠፍቷል።ተመድ በጦርነቱ ምክንያት በሱዳን ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ ጥረት ቢያደርግም ከአጠቃላይ ድጋፍ ፈላጊው መድረስ የቻለው ለ25 ሚሊዮኑ ብቻ ነው አሁን ላይ ሱዳን እጅግ አደገኛ ከሚባሉ ቦታዎች መካከልም መድቧታል።በሱዳን ጦር መሪ ጄነራል አልቡርሃን እና በፈጥኖ ደራሽ በሚባለው ኃይል መሪ ጄነራል መሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ ወይም ሄምቲ መካከል ጦርነት የተቀሰቀሰው ሚያዝያ 7 2015 ዓም ነበር ዛሬም ድረስ አንዱ አሸናፊ ሳይሆን የሰላም መፍትሄም ሳይገኝ ሀገሪቱ የከፋ ውድቀት ውስጥ እንደገባች ቀጥላለች። ### Response:
### Text: ሰበር ዜና️ዓለማቀፉ ጣናን መልሶ ማቋቋም ማህበር ሲያካሂድ የነበረውን ጥናት በማጠናቀቅ ሁለት ከፍተኛ አረም ማጨድ የሚያስችሉ ማሽኖች ከነሙሉ መለዋወጫቸው ግዥ ፈጽሟል።359 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወይም 10 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው እነዚህ ሁለት 9 905 የተባሉ ከፍተኛ የአረም ማጨጃ ማሽኖች እያንዳንዳቸው 75 የፈረስ ጉልበት አላቸው፡፡በአንዴ 262 ሜትሪክ ኪዩብ አረም ማጨድ የሚያስችሉ ናቸው። ይህም ከዚህ በፊት ከተገዛው ማሽን ጋር ሲነጻጸር በአምስት እጥፍ አረም የመሸከም አቅም ያለው ነው።ለዚህ ግዥ የሚሆነውም ገንዘብብ የተሰባሰበው በዲሲ ዳላስ ቺካጎና ለንደን ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እንደተሰበሰበ ነው ማህበሩ ለአማራብዙኃን መገናኛ ድርጅት ያስታወቀው።በተጨማሪም ዋሺንግተን ዲሲ የምትገኘው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ደብረገነት መድሃኒያለም ቤተክርስቲያን 70 ሺህ ዶላር ለዚሁ ተግባር ማበርከቷን ማህበሩ አስታውቋል።ጣናን ከእንቦጭ ለመታደግ ገንዘባችሁን ጉልበታችሁን ጊዜያችሁንና ዕውቀታችሁን ለጣና ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ ምስጋናችን ከፍ ያለነው ሲል አሳውቋል።ዓለማቀፉ ጣናን መልሶ ማቋቋም ማህበር ግብረሰናይ ድርጅት ከዚህ ቀደም የእንቦጭ ማጨጃ ማሽን ገዝቶ ወደ ሀገር ቤት ልኮ አሁን ላይ ስራ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ምንጭ አብመድ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ብሔራ ቡድን ከፊታችን ላለበት የ 2021 የአፍሪካ ዋንጫ የማጣርያ የምድቡ ሁለት ከባድ ጨዋታዎች ከነገ ጀምሮ ልምምዳቸውን በመቀሌ የሚያካሂዱ ይሆናል ፡፡ በዚህም መሰረት በኢንስትራከተር አብርሀም መብርሀቱ የሚሰለጥኑት ዋልያዎቹ ፕሮግራማቸው የሚከተለውን ይመስላል ፡፡ጥቅምት 24 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአዲስ አበባ በመነሳት ወደ መቀሌ በማቅናት በዚሁ ዕለት ልምምዳቸውን ማምሻውን የሚያደርጉ ይሆናል ፡፡ህዳር 1 ልምምዳቸውን በማድረግ ከቆዩ በኋላ ዋልያዎቹ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ የሚመለሱ ይሆናል ፡፡ህዳር 2 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዕለተ ማክሰኞ የመጀመሪያ ተጋጣሚው ወደ ሆነው ማዳጋስካር አንታናናሪቮ የሚጓዝ ይሆናል ፡፡ህዳር 6 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ የ 2021 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታውን ከሜዳው ውጪ ከማዳጋስጋር ጋር የሚያደርግ ይሆናል ፡፡ ህዳር 7 ዋልያዎቹ የመክፈቻ ጨዋታቸውን ባደረጉ ማግስት በዕለተ እሁድ ወደ አዲስ አበባ የሚመለሱ ይሆናል ፡፡ህዳር 8 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምድቡን ሁለተኛውን ወሳኝ ጨዋታ ለማድረግ ወደ መቀሌ ለዝግጅት በረራውን ያደርጋል ፡፡ህዳር 9 ዋልያዎቹ የምእራብ አፍሪካዋን ከባዷን ኮትዲቯር የምድቡ ሁለተኛ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል ፡፡ ### Response:
### Text: ችሎት የዙና ትሬዲንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን ጌታሰው በ14 ዓመት ፅኑ እስራት እና በ300 ሺህ ብር ተቀጡ። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት በዛሬው ዕለት የዙና ትሬዲንግ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዘሪሁን ጌታሰውን ጉዳይ ተመልክቷል። አቶ ዘሪሁን ከ109 ግለሰቦች ሲኖትራክ ተሽከርካሪ አስመጣለሁ በማለት በአጠቃላይ ከ73 ሚሊየን ብር በላይ በማጭበርበር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል።የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በዙና ትሬዲንግ ስራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን ጌታ ሰው ላይ 122 ክሶችን መመስረቱም ይታወሳል።በዚህም ከ109 ግለሰቦች ከ 2ሚሊየን 600 ሺህ እስከ 314 ሺህ ብር መኪና አስመጣለው በማለት ባጠቃላይ ከ73 ሚሊየን ብር በላይ ተቀብሎ መሰወሩ በክሱ ተመላክቶ ነበር። በክሱ መሰረትም አቃቤ ህግ አለኝ ያለውን የሰነድ ማስረጃ እና የግል ተበዳዮችን ምስክርነት አቅርቦ አሰምቷል።ተከሳሽ የመከላከያ ምስክር ያቀረቡ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት 13 ክሶችን ውድቅ በማድረግ ተከሳሹን በ109 ክሶች ጥፋተኛ ብሏቸዋል።በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ የዙና ትሬዲንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን ጌታሰው በ14 ዓመት ፅኑ እስራትና በ300 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ ወስኗል። ### Response:
### Text: እስከ ሀምሌ 2013 ዓም ከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ መረጃ መሰረት ካሉት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ዩኒቨርሲቲ፣ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ ኮሌጅ እና ኢንስቲትዩት የሚል የደረጃ ስያሜ ያላቸው የሚከተሉት ናቸው።ዩኒቨርሲቲ የሚል የደረጃ ስያሜ ያላቸው እስካሁን 5 ሲሆኑ እነርሱም፡1 ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ2 ቅድስተማርያም ዩኒቨርሲቲ3 ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ4 ሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ እና5 አድማስ ዩኒቨርሲቲ ናቸው፡፡ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ስያሜ ያላቸው የግል ተቋማት እስካሁን 5 ሲሆኑ እነዚህም 1 አልፋ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ2 ኒው ጀነሬሽን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ3 ሸባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ4 ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ5 ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ናቸው፡፡ የተቀሩት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኮሌጅ ወይም ኢንስቲትዩት የሚል የደረጃ ስያሜ ያላቸው ናቸው፡፡ከላይ ከተጠቀሰው ውጪ ከደረጃ ስያሜ ውጪ ባልተፈቀደ የደረጃ ስያሜ በሚዲያ ማስታወቂያ ማሰራት፣ በተለያዩ ሰነዶች እና ባነሮች ላይ መጠቀም ማዕተም ማሰራት ወዘተ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ኤጀንሲው አሳውቋል።ባልተፈቀደ የደረጃ ስያሜ የተሰጠ የትምህርት ማስረጃ ካለም ተቀባይነት አይኖረውም ተብሏል፡፡የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የደረጃ ስያሜ መመሪያ ማክበርን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ ከላይ ተያይዟል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ መንግስትና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ስምምነት የጋራ መግለጫ️በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ዶር ለማ መገርሳ የሚመራውና የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶር ወርቅነህ ገበየሁ የሚገኙበት የልዑካን ቡድን፣ በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር ኣቶ ዳውድ ኢብሳ ከሚመራውና ኣቶ ኢብሳ ነገዎ፣ ኣቶ ኣቶምሳ ኩምሳ፣ ኣቶ ቶሌራ ኣደባና ኣቶ ገመቹ ኣያና የሚገኙበት የልዑካን ቡድን ነሃሴ 7 ቀን 2018 በኣስመራ ኤርትራ በመገናኘት ወንድማዊ መንፈስ በተንጸባረቀበትና በሙሉ መተማመን በተካሄደ የእርቅ ውይይት ከዚህ በታች ያሉ ስምምነቶችና መግባባቶች ላይ ተደርሷል።ሁለቱም ቡድን ስለኦሮሞና ኦሮሚያ እንዲሁም ኢትዮጵያን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ በውይይት ኣብረው ለመስራት ተስማምተዋል።ለረዥም ዓመታት በኦነግና በኢትዮጵያ መንግስት መካከል የነበረው ጦርነት ተገትቶ፡ ካሁን በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረው ሁኔታ ኦነግ በሃገር ውስጥ በግልጽ ሊሰራ የሚያስችለው መሆኑ ከግንዛቤ ገብቶ፡ ትግሉን በሰላማዊ መንገድ እንዲቀጥል ከስምምነት ተደርሷል።በመጨረሻም ከስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች ስራ ላይ እያዋሉ ምርመራና ጊዜ የሚጠይቁትን ቀስ በቀስ ለመጨረስ በቀጣይነት ከፍጻሜ የሚያደርስ ኮሚቴ በኣስቸኳይ እንዲቋቋም ተስማምተዋል።ነሀሴ 72018 አስመራ ### Response:
### Text: የኤሌክትሪክ ኃይል በፈረቃ መከፋፈሉ ከዛሬ ጀምሮ መቆሙ ተገለጸ። የኃይል ማመንጫ ግድቦች በቂ ውኃ ባለመያዛቸው ምክንያት የኤሌክትሪክ ኃይል በፈረቃ ማከፋፈል የተጀመረው ባለፈው ግንቦት 9 ቀን 2011 ዓም ነበር። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ «ምንም እንኳን ሁሉም ግድቦች የሚጠበቀውን ያህል ውኃ የያዙ ባይሆንም በክረምቱ እንደሚሞሉ ታሳቢ በማድረግ ከዛሬ ጀምሮ ፈረቃው እንዲቀር ተደርጓል» ብሏል። የፈረቃ አቅርቦቱ መቆሙን የገለጸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል «የኢንደስትሪ ተጠቃሚዎችም የፈረቃ ማሻሻያው ተጠቃሚ ይሆናሉ» ብሏል። ይሁንና ከፍተኛ ኃይል የሚሹ ኢንዱስትሪዎች ተጠቃሚ በሚበዛበት ሰዓት በግማሽ አቅማቸው ለመሥራት እንደሚገደዱ መግለጫው ይጠቁማል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ እንደሚጠቁመው የአገሪቱ ግድቦች «የሚጠበቀውን ያህል ውኃ የያዙ ባይሆንም በክረምቱ እንደሚሞሉ» ታሳቢ ተደርጓል። ከፍተኛ የውኃ እጥረት ከገጠማቸው ግድቦች መካከል በኦሞ ወንዝ ላይ የተገነባው የጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ ይገኝበታል። ግድቡ ካለፈው ዓመት አኳያ «አሁንም አነስተኛ ቢሆንም የበርካታ ዓመታት አማካይ የውኃ መጠን ጋር የሚቀራረብ በመሆኑ ፈረቃው እንዲቀር» መወሰኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል። ቀን ሃምሌ 12011 ዓም ### Response:
### Text: ላልይበላ ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከ45 ሽህ በላይ የውጭ ሃገር ዜጎች ላልይበላን መጎብኘታቸውን የላልይበላ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽቤት አስታወቀ፡፡ የቅዱስ ላልይበላንና በዙሪው ያሉ ድንቅ ቅርሶችን 45144 ጎብኝዎች መጎብኘታቸውን ከጽፈት ቤቱ የተገኘው መረጋጃ ያመለክታል፡፡ ጽቤቱ እንዳመለከተው በየዓመቱ የጎብኝዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ያስታወቀ ሲሆን የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜም ለማራዘም እየተሰራ መሆኑን አመልክቷል፡፡ ለዚህም ደግሞ የሆቴሎችን አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ለማሳደግ በተሰራው ስራ 5 ሆቴሎች በኮኮብ ደረጃ እንዲመደቡ የጎደላቸውን በሱፐርቪዥን ቡድን በተሰጠው ግበረ መልስ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ መቻሉንም አስታውቋል፡፡በተያያዘ መረጃባሳለፍነው 2011 በጀት ዓመት የላልይበላ ውቅር አብያተ ክርስቲናትና በዙሪው የሚገኑ ታሪካዊ ቦታዎችን ይጎበኛሉ ተብለው በእቅድ ከተያዘው 483167 የሃገር ውስጥ ጎብኝዎች ውስጥ 211909 የሃገር ውስጥ ጎብኝዎች መጎብኘታቸውን ከላልይበላ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ መረጃው እንደሚመለክተው በየአመቱ የጎብኝዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን አስታውቋል፡፡ በበዓላትና በሌሎችም ቀናት ቅርሶችን የሚጎበኙ ዜጎችም መጨመራቸው ነው ከጽቤቱ የተገኘው መረጃ የሚያመለክተው፡፡ ### Response:
### Text: የሱዳንን አብዮት የመሩት ሴቶች ናቸው የአፍሪካ ህብረት ልዑክየሱዳን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ የመረጧቸውን የካቢኔ አባላት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡እጩዎቹን ለማጥናት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጨማሪ ጊዜ መስጠት በማስፈለጉ እነርሱን ይፋ የማድረጊያው ጊዜ ዘግይቷል ነው የተባለው፡፡ በሱዳን ወታደራዊ እና ተቃዋሚ ቡድኖች በተፈረመው የአገሪቱ ህገመንግስት ማሻሻያ አዋጅ መሠረት 40 ከመቶ የሚሆነው የሚኒስትሮች እና የመንግስት የስራ ቦታዎች በሴቶች አንደሚያዙ ነው የተገለፀው፡፡የአፍሪካ ህብረት የሴቶች የሰላምና ደህንነት ልዩ መልዕክተኛ ቢኒታዲዩፕ በካርቱም የሚገኙ ሲሆን መንግስት 40 ከመቶ የሚሆኑ ሴቶችን በካቢኔው በሚያካትትበት አግባብ ላይ ከሱዳን ሴት ፖለቲከኞች ጋር ተወያይተዋል፡፡ አብዮቱን የመሩት ሴቶች ናቸው ሲሉ መልዕክተኛዋ ለቢቢሲ ኒውስዴይ ተናግረዋል፡፡ ሴቶቹ ትናንት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መገናኘታቸውን የገለፁት መዝ ዲዩፕ ጠቅላይ ሚኒስትሩም የተቻላቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡ እሷ አጋር መሆኗን አረጋግጠዋል ስለ ሥርዓተጾታ እኩልነት እና ሴቶችን ስለማብቃት ያውቃሉ ከወታደራዊው ኃይል ጋር ለመደራደር የሚያስችል ኃይልም ያላቸው ይመስለናል ብለዋል መዝ ዲዩፕ፡፡ምንጭ᎓ ቢቢሲ ### Response:
### Text: የ10ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አልተደረገም የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲም መቼ ይፋ እንደሚደረግ አላሳወቅም ። በተመሳሳይ ስለዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ የሚዋራው ሀሰት ነው። መቁረጫ ነጥብ ይፋ አልተደረገም። ውድ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በተለያዩ ሀሰተኛ ገፆች እንዳትታለሉ ተማሪዎች እና ወላጆች አጠቃላይ ስለፈተናችሁና ውጤታችሁ ትክክለኛ መረጃን ልታገኙ የምትችሉት በዚህ መንገድ ብቻ ነው 1 ይህ ትክክለኛው የኤጀንሲው የፌስቡክ ገፅ ነው። አዲስ መረጃ ካለ በዚህ በኩል ይገልጻሉ።2 ይህ የኤጀንሲው ድረገፅ ነው። አዲስ መረጃ ካለ በዚህ በኩል ይገልጻሉ።3 በተለያዩ የመንግስትና የግል የቴሌቪዥንና ሬድዮ ጣቢያዎች በኤጀንሲው በኩል የሚሰጠውን መረጃ ብቻ ተከታተሉ።4 ህጋዊ በሆኑና በቴሌቪዥንና በሬድዮ ጣቢያዎች ቁጥጥር ስር ባሉ ህጋዊ️የፌስቡክ ገፆች ላይ ስለውጤታችሁ የሚወጣ መረጃ ካለ ተመልከቱ አረጋግጡ።ከዚህ ውጪ በትኛውም አይነት መንገድ የሚሰራጩ መረጃዎች እንዳታምኑ ። በሚሰራጩ ሀሰት ወሬዎችም እንዳትጨነቁ ። የምታዩትን ነገር ሁሉ ሼር እንዳታደርጉ በቅድሚያ አረጋግጡ ኤጀንሲው ምንም አይነት የቴሌግራም ቻናል የለውም ሁሉም በኤጀንሲው ስምና በትምህርት ሚኒስቴር ስም የተከፈቱት ቻናሎች ህጋዊ እውቅና የሌላቸው ናቸው። ### Response:
### Text: ሲዳማ ክልልና ደቡብ ክልል ንብረት ቆጠራሲዳማ ክልል ንብረት አለኝ የሚለውና ቆጠራ የሚደረገው በሃዋሳ ከተማ ውስጥ ያለውን በተመለከተ ነው ወይስ በሌሎች የደቡብ ክልል ስር በሚገኙ አካባቢዎችም ጭምር ያለውን ነውየአዲሱ ሲዳማ ክልል አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት ፅቤት ኃላፊ አቶ ገነነ አበራ ለበገር ኤፍ ኤም የሰጡት ምላሽ56ቱም ብሄር ብሄረሰቦች አንድ ላይ በነበሩበት ጊዜ ያፈሩት ንብረት አለ። ከፌደራልም ከፌደሬሽን ምክር ቤትም በሚደጎሙ ድጎማዎች የጋራ ሃብት ናቸው ተብለው ከተቋም ጀምሮ ብዙ አይነት ንብረቶች አሉ። በአይነት ንብረት አለ፣ በገንዘብ አለ፣ በንብረት ደረጃ ንብረትነቱ ለክልል የነበረው እነኛ በሙሉ ሲዳማ እኔ ክልል ሆኜ እወጣለሁ ብሎ ከ56ቱ ሲወጣ የራሱን ድርሻ ይዞ ነው የሚወጣው ባዶ እጁን አይወጣም። ንብረት ያለው በሀዋሳ ከተማ ውስጥ ብቻ አይደለም። በተለያዩ አካባቢዎች ንብረት አለው ክልሉ በራሱ። ስለዚህ በክልል ደረጃ በክልል ደረጃ የነበሩ ተቋማት ውስጥ ያሉት ንብረቶች ምክንያቱም ክልል እስከሆነ ድረስ ደቡብ ክልል ሁሉንም ነው የሚይዘው ሲዳማንም አቅፎ ነበረ የነበረው። ንብረትነቱ የክልል የሆነ ንብረት ሁሉ ሲዳማ ይመለከተዋል። ስለዚህ ንብረትነቱ ለክልል የሆነው በሙሉ ምዝገባ ይደረግና ፐርሰንት ወጥቶ የሚደርሰው ድርሻ ይዞ ይወጣል። 1021 ### Response:
### Text: የእንግሊዙ ኩባንያ ከፊ ጎልድ በቱሉ ካፒ አካባቢ የተገኘውን የወርቅ ማዕድን ለማውጣት፣ ወደ ሙሉ የፕሮጀክት ልማት እንዲገባ የተሰጠው የጊዜ ገደብ እንዲራዘምለት ያቀረበውን ጥያቄ የማዕድን ሚኒስቴር ውድቅ ማድረጉን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።0የእንግሊዝ ኩባንያ የቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን ልማትን በፀደቀው ዕቅድ መሠረት ማከናወን ባለመቻሉ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያና የጊዜ ገደቦች እየተሰጠው ለበርካታ ዓመታት የቀጠለ ሲሆን፣ በሰኔ ወር 2013 ዓም የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ነበር።0ነገር ግን ኩባንያው የፕሮጀክት ልማቱን ለመጀመር የሚያስፈልገውን ፋይናንስ በማግኘቱ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ተሻሽሎ እኤአ እስከ ኦክቶበር 2021 መጨረሻ ቀን ድረስ ልማቱን እንዲጀምር አዲስ የጊዜ ገደብ ተቆርጦለት ነበር።0ይሁን እንጂ ኩባንያው በመስከረም ወር 2014 ለማዕድን ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ ፕሮጀክቱ በሚገኝበት ቱሉ ካፒ አካባቢ የፀጥታ ችግር መኖሩን ጠቅሶ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የወርቅ ማዕድን ልማቱን መጀመር እንደማይችል አስታውቆ፣ የጊዜ ማራዘሚያ ጠይቆ ነበር።የማዕድን ሚኒስቴር በበኩሉ ጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓም በኢትዮጵያ ለተቋቋመው እህት ኩባንያ በጻፈው ደብዳቤ የተጠየቀውን የጊዜ ማራዘሚያ ከነምክንያቱ በመጥቀስ ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል።ያንብቡ 1017 ### Response:
### Text: ዛሬ በኡጋንዳ በደረሱ 2 የሽብር አደጋዎች 3 ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆሰሉ፡፡ካምፓላ ሁለት ቦታዎች በደረሱ የአጥፍቶ ጠፊዎች የሽብር ጥቃት ይ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ፖሊስ አስታቋል፡፡በአደጋው ከቆሰሉት 33 ሰዎች ውስጥ አምስቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል፡፡ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል፡፡በካምፓላ ሁለት የገበያ ማዕከላት ላይ ደረሰ የተባለው ይህ የዛሬ ረፋድ የሽብር ጥቃት በአገሪቱ ፓርላማ መግቢያ አካባቢ ነው የተፈጸመው፡፡የአገሪቱ ፖሊስ በበኩሉ አደጋው በሁለት የአገር ውስጥ የሽብር ቡድን አባላት አማካኝነት በተመሳሳይ ሰዓት በተለያዩ ቦታዎች ፍንዳታው መድረሱን ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት አስታውቋል፡፡ይሁንና እስካሁን በሽብር ድርጊቱ ዙሪያ ሃላፊነት የወሰደ አካል እንደሌለ የተገለጸ ሲሆን የአገሪቱ ፖሊስ ድርጊቱን እየመረመርኩ ነው ብሏል፡፡ከ1 ወር በፊት በካምፓላ ከተማ ባለ አንድ ሬስቶራንት ውስጥ በደረሰ ተመሳሳይ የሽብር አደጋ ሁለት ሰዎች የሞቱ ሲሆን ሀላፊነቱን አይኤስ አይ ኤስ ለድርጊቱ ሃላፊነት ወስዶ ነበር፡፡በዚሁ ዓመት መስከረም ወር መጨረሻ ቀናት ላይ አንድ አጥፍቶ ጠፊ የሽብር ቡድን በፈጸመው ጥቃት እራሱን ገድሎ በርካቶችን ማቁሰሉ አይነጋም ### Response:
### Text: የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የቀጠለ ሲሆን በግንቦት 232014 ዓም ውሎ የደቡብ ክልል ፕሬዝደንት እና ሌሎች የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በምልዓተ ጉባኤው ተገኝተው ነበር።የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቤተክርስቲያን ላይ በየጊዜው እየደረሱ ባሉ ችግሮች ዙሪያ ውይይት ለማድረግ ነው ከደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝደንት አቶ ርስቱ ይርዳው ከሌሎች የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደረገው።ምልዓተ ጉባኤ በሃይማኖታቸው ምክንያት ስለተገደሉ፣ ስለተቃጠሉ አብያተ ክርስቲያናትና ከማምለኪያ ቦታዎች ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን በደብዳቤ ንባብ እንዲሁም በክልሉ በሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳት አማካይነት የቃል ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን አፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙም ተጠይቋል። የክልሉ ፕሬዝደንት የተፈጠሩትን ችግሮች ለመፍታት አስተዳደሩ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶችን ገልጸው በየደረጃው ለመፍታት እንደሚሠሩ ገልፀዋል።ምልዓተ ጉባኤው በክልሉ በሚገኙ አንዳንድ ቦታዎች ምላሽ የተሰጠባቸው ጉዳዮችን አንስቶ የክልሉ ፕሬዝደንት በምልዓተ ጉባኤው ተገኝተው ላደረጉት ውይይትና ለሰጡት ምላሽ ምስጋና አቅርቧል። መረጃውን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ዩሴፍን ዋቢ አድርጎ ያሰራጨው የኢኦተቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት ነው። ### Response:
### Text: በዳሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ በመሙላቱ ከመደበኛ ፍሰቱ ወጥቶ ሞልቶ በመፍሰሱ ዜጎቻችን እየተጎዱ ነው።እንደ ዳሰነች ወረዳ አስተዳደር መረጃ በ34 ቀበሌያትና በ7 ደሴቶች የሚኖሩ 79828 ቤተሰብ አባላት በወንዙ ሙላት የተጎዱ ተጎድተዋል። በወረዳው ካሉ 40 ቀበሌያቶች 34ቱ ቀበሌያት0 በውሃ የመዋጥና የመከበብ አደጋ ያጋጠማቸው ሲሆን ከዚህ ውስጥ 27ቱ ቀበሌያት ሙሉ በሙሉ በውሃ ሙላት ተውጠዋል 7ቱ ቀበሌያት ደግሞ በቀጣይ ስጋት ውስጥ ናቸው። በኦሞ ወንዝ ሙላት ሳቢያ 143575 ሄር በመስኖ የተዘራ ሰብልና 123000 ሄር የእንስሳት የግጦሽ መሬት ሙሉ በሙሉ በውሃ ተሸፍኗል። በደሴቶች ውስጥ የነበሩና በውሃ ሙላት የተከበቡ እንስሳት ብዛት 2993135 ሲሆን ከዚህ ውስጥ አስካሁን ከውኃ ሙላት የወጡ 889454 እንስሶች ናቸው። በውሃ መጥለቅለቁ 8 የሰው ጤና ኬላዎች፣ 1 ጤና ጣቢያ፣ 6 ትምህርት ቤቶች፣ 6 የእንስሳት ጤና ኬላ፣ 5 የአርብቶ አደር ማሰልጠኛ ጣቢያ ፣ 4 የመኖ ቤል እስቶር እና በ14 ቀበሌያት በስራ እድል ፈጠራ በማህበራት ተደራጅተው ከተለያዩ አበዳሪ ተቋማት ተበድረው ወደ ስራ የገቡ እና በፕሮጀክት የታቀፉ 32 ማህበራትና 15 ሼዶች ሙሉ ለሙሉ በውሃ ሙላት ተውጠዋል ስራም አቁመዋል።በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመተባበርና በመቀናጀት አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል። ### Response:
### Text: ትላንት እንዲሁም ዛሬ በሀረር፣ አቦምሳና ድሬዳዋ ከተሞች ከበዓለ ጥምቀቱ ጋር ተያይዞ የተስተዋሉ አለመረጋቶችን በሚመለከት ለእናተ ለውድ ቤተሰቦቻችን መረጃዎችን ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ለማቅረብ መረጃዎችን ስናስስ ነበር። የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ሀረርና አቦምሳ የሰጧቸውን እንዲሁም ከተለያዩ ሚዲያዎች የተገኙትን መረጃዎች በዚህ ገብታቹ ተመልከቷቸው 0120 መንግስት ግን እየታየ ያለውን አደገኛ አዝማሚያ እና ሀገር የሚያሳጣ ድርጊት ትኩረት ሰጥቶ መፍትሄ መፈልግ አለበት። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በሀገሪቱ ውስጥ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የአለመግባባት መንስኤ ሲሆኑ እየተመለከትን ነው። ስርዓት አልበኝነት፣ የህግ የበላይነት መሸርሸር፣ የዜጎች እንግልት፣ የንብረት ውድመት፣ የሰዎች ጉዳት በተደጋጋሚ እየታዩ እንደሆነ ግልፅ ነው። መንግስት የህግ የበላይነትን በሀገሪቱ ወስጥ ማረጋገጥ ካልቻለ ሀገሪቱ ካለችበት የገደል አፋፍ ወደ ገደሉ ውስጥ መውደቋ አይቀርም። የህዝብን ስሜት ወዲያው የሚቀሰቅሱ በተለይ በተለይ ሃማኖታዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰራጩ መረጃዎች እጅግ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ካልተደረገባቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ሀገር አልባዎች ሊያደርገን ስለሚችል መጠንቀቅ አይከፋልም።ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ### Response:
### Text: መንግስት ለተጎጂዎች ተገቢውን ድጋፍ ያደርጋል አቶ ኦርዲን በድሪ የሀረሪ ክልል ርዕሰመስተዳደርከጥምቀት በዓል አከባበር ጥር 10 እና ጥር 11 ጋር ተያይዞ በሀረር ከተማ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ለደረሰው ጉዳት መንግስት አፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስድ የሀረሪ ክልል ርዕሰመስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ አስታወቁ።ርዕሰመስተዳድሩ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ለበዓሉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አስፈላጊው ዝግጅት ቢደረግም ግጭት የመፍጠር ተልዕኮን ባነገቡ አካላት በተፈጸመ ተግባር በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል ብለዋል። በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን የገለጹት ርዕሰመስተዳደሩ፣ መንግስት ለተጎጂዎች ተገቢውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም አሳውቀዋል።በቀጣይም በድርጊቱ የተሳተፉ፣ በተለያየ መንገድ ሲመሩና ሲደግፉ የነበሩ አካላትን የክልሉ የፀጥታና ፍትህ አካላት በአፋጣኝ አጣርተው ለፍርድ በማቅረብ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ገልፀዋል።ሕብረተሰቡ ላሳየው ትዕግስት እና ከጸጥታ አካላት ላደረገው ትብብር በራሳቸው እና በሀረሪ ክልል መንግስት ስም ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ኦርዲን በድሪ በቀጣይም ከመንግስት ጎን በመቆም አጥፊዎችን ለህግ ለማቅረብ ትብብሩን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ### Response:
### Text: የህዳሴውን ግድብ ፕሮጀክት ለማደናቀፍ ማሰብ ኢትዮጵያውያን በሃገራቸው ጉዳይ እንደማይደራደሩ በቅጡ ካለመረዳት የሚመነጭ ስሕተት ነው ሌጄኔራል አስራት ዴኔሮንየኢትዮጵያ ጦር ከፍተኛ መኮንኖች ሀገራችን ኢትዮጵያ እየገነባች ያለውን ግዙፉን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ጎብኝተዋል።በግንባታው ስፍራ ተገኝተው ጉብኝት ያደረጉት የምድር ሃይል ዋና አዛዥ ሌጄኔራል አስራት ዴኔሮን ጨምሮ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ናቸው።ከኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ አባላት በተጨማሪ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከፍተኛ የመግስት የሰራ ሃላፊዎች የጉብኝቱ ተካፋይ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ፣ ለፕሮጀክቱ መሳካት እየተከናወነ ያለውን እረፍት አልባ የሰራዊቱ የግዳጅ አፈፃፀም አድንቀዋል። ምስጋናም አቅርበዋል።ሌጄኔራል አስራት ዴኔሮን በጉብኝቱ ወቅት ባሰሙት ንግግር የህዳሴውን ግድብ ፕሮጀክት ለማደናቀፍ ማሰብ ኢትዮጵያውያን በሃገራቸው ጉዳይ እንደማይደራደሩ በቅጡ ካለመረዳት የሚመነጭ ስሕተት ነው ብለውታል።አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስተጓጎል የሚቀሳቀሱ የውክልና ጦር አስፈፃሚዎች ከወስጥም ሆነ ከውጭ የሚቀሳቀሱ ቅጥረኛ ሃይሎች ምንም አይሳካላቸውም ሲሉ ተናግረዋል። ### Response:
### Text: ነዳጅ ለነዳጅ የሚደረግ ድጎማን ከሐምሌ 2014 ዓም ቀስ በቀስ ለማንሳት በዝግጅት ላይ ያለው መንግሥት፣ ከስሌቱ በታች በአነስተኛ ዋጋ ከነዳጅ እየተሰበሰበ ያለው የኤክሳይስ ታክስና የቫት ገቢ ለታለመ የነዳጅ ድጎማ ሊያውል መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።ይሁንና መንግሥት በአነስተኛ መጠን የሚሰበስበውን የኤክሳይስ ታክስና ቫት ገቢ በሕጉ መሠረት ሙሉ ለሙሉ እንዲሰበሰብ ዕቅድ አለው ተብሏል። ይህም የነዳጅን ዋጋ ይበልጥ ያንረዋል የሚል ሥጋት በመፍጠሩ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሠራሩ እንዲቀጥል የውሳኔ ሐሳብ ማቅረቡ ተሰንቷል።ከነዳጅ የሚሰበሰበው ይህ ኤክሳይስ ታክስና ቫት ከሰኔ 2 ቀን 2002 ዓም በተላለፈ ውሳኔ፣ እንደ ሕጉ የኤክሳይስ 30 በመቶና የቫት 15 በመቶ አይደለም፡፡ በጊዜው ነዳጅ ያሳየው ከፍተኛ ጭማሪ ተከትሎ መንግሥት 30 እና 15 በመቶ በመሰብሰብ ፋንታ፣ የነዳጅ ዋጋ ሲተመን እያንዳንዱ ሊትር ናፍጣ ላይ ሁለት ብር ከ98 ሳንቲም፣ በቤንዚን ላይም እንዲሁ ከሦስት ብር ያነሰ ጭማሪ እንዲደረግ ተወስኖ እስካሁን ቀጥሏል፡፡መንግስት ከዚህ ግብር የሚሰበሰበው ገቢ ከሐምሌ ወር አንስቶ ነዳጅ ላይ ለሚደረገው የታለመ ድጎማ እንዲውል መወሰኑን፣ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን አንድ የመንግሥት ኃላፊን ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።ያንብቡ 0619 ### Response:
### Text: 10 572 ሰዎች ደሴት ላይ ገና በውሃ ተከበው አልወጡም የዳሰነች ወረዳ አስተዳደርበዳሰነች ወረዳ ተከሰተ የተባለው የጎርፍ አደጋ በምን ሁኔታ እንደሚገኝ ፣ በአደጋው የሰውና የእንስሳት ሕይወት እንዳለፈና እንዳላለፈ፣ በንብረት ላይ0 ምን ያህል ውድመት እንደደረሰ0 ወረዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥቷል።የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ማልኮ እንደገለጹት ከሆነ፣ 10572 ሰዎች ደሴት ላይ ገና በውሃ ተከበው አልወጡም። እንዲሁም በጎርፍ አደጋው 45 ቢሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል።69256 ቤተሰቦች ከወንዙ እንደወጡ ያስረዱት ያሉት አስተዳዳሪው፣ 79828 ሰዎች በአጠቃላይ በጎርፉ ጉዳት የደረሰባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።አስተዳዳሪው አክለውም፣ እንስሳት የዳልጋ ከብት፣ በግና ፍየልን ጨምሮ 889454 ከወንዙ እንደወጡ ገልጸው፣ በጎረፍ አደጋ የሞተ የለም። እንስሳት ላይም ሞት የለም። ተቋማትና የአርብቶ አደር ቤቶች በጎርፍ እንደተያዙ ይገኛሉ ብለዋል። መፍትሄው ምን እንደሆነ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽም፣ መንግሥት ማህበረሰቡን ወንዝ ወደማይደረስበት ማስፈረና ትልልቅ የመስኖ አውታር በማቋቋም ወደልማት ፊታቸውን እንድያዞሩ ማድረግ፣ አስፈላጊው መሰረተ ልማት በሰፈሩበት ቦታ ማሟላት አለበት ብለዋል።ዘገባው በአአ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው። ### Response:
### Text: ብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ፅጌ️የአማራ መስተዳድር የልዩ ጥበቃ ፖሊስ አዛዥ መኖሪያ ቤት ዉስጥ ትናንት የተያዘዉ የሽጉጥ «ክምር» በየሥፍራዉ ሊከፋፈል እና ሊሰራጭ የተቃደ እንደነበር የመስተዳድሩ የሠላም እና ደሕንነት ቢሮ አስታወቀ። ባሕርዳር በሚገኘዉ የመስተዳድሩ የልዩ ጥበቃ አዛዥ በነበሩት በኮምንደር ዉበቱ ሺፈራዉ መኖሪያ ቤት፣ በሰባት ጆንያዎች ተቋጥሮ የተገኙት ሽጉጦች ብዛት 498 ነዉ። የአማራ መስተዳድር የሠላም እና የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ብርጌድየር ጄኔራል አሳምነዉፅጌ ዛሬ ለ እንደነገሩት ሽጉጦቹ በሙሉ አዳዲስ እና ቱርክ ሠራሽ ናቸዉ።ሽጉጦቹ የተያዙት ጉዳዩን በቅርብ በሚያዉቁ ወገኖች ጥቆማ እና ትብብር ነዉ። ጄኔራል አሳምነዉ አክለዉ እንዳሉት ሽጉጦቹ የተያዘባቸዉ ኮማንደር ዉበቱ በቁጥርጥር ስር የዋሉ ሲሆን «አባሪ ተባባሪ» ተብለዉ የሚጠረጠሩ ወገኖችን ለመያዝ ክትትሉ ቀጥሏል። ጄኔራል አስምነዉ «ባንድ እና በሁለት ሰዉ ይሠራል ብለን እንገምትም» ብለዋል።አንድ የክልሉ ፀጥታ ኃይል ከፍተኛ ባለሥልጣን ይሕን ያክል ጦር መሣሪያ ደብቀዉ መገኘታቸዉን፣ ጄኔራል አሳምነዉ «አሳዛኝ እና አሳፋሪ» ብለዉታል። ሽጉጦቹ ሊከፋፈልላቸዉ ነበር የተባሉት ወገኞችም ሆነ የተላከበት ስፍራና የላኪዉ ማንነትም እስካሁን በይፋ አልተነገረም።ምንጭ አማርኛው አገልግሎት ### Response:
### Text: የፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም መታሰቢያ እና ዓመታዊ ኮንፈረንስ መስከረም 22 ቀን 2015 ዓም ሊካሄድ ነው።የፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ፋውንዴሽን በላከልን መልዕክት መስከረም 22 ቀን 205፣ ከ7፡30 አንስቶ ለግማሽ ቀን በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ እሸቱ ጮሌ አዳራሽ በርካታ እንግዶች በተገኙበት ታላቅ ጉባዔ ይካሄዳል ብሏል። የተመራማሪ፣ መምህር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ደራሲ፣ የሰላማዊ ትግል አቀንቃኝ እና የፍትሕ ተቆርቋሪ በሆኑት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ስም የተመሰረተው ፋውንዴሽን በሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ተመዝግቦ በሕጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ሲል ፋውንዴሽኑ አስታውሷል። የድርጅቱ ዋና ዓላማ ከችግርና ድህነት የተላቀቀች፣ ሰላም የሰፈነባት፣ ሰብዓዊ መብትና የሕግ የበላይነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው ብሏል።ፋውንዴሽኑ ዓላማውን ለማሳካት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ በሰብዓዊ መብትና ማሕበራዊ ፍትሕ፣ አገራችን ከድህነትና ችጋር ልትላቀቅ ስለምትችልበት መንገዶች፣ ቅራኔን በሰላማዊ መንገድ ስለመፍታት፣ በመስኩ ሰፊ የሆነን ልምድ እና እውቀት ባካባቱ ሰዎች ጥናታዊ ወረቀት በማቅረብ ሰፋ ያለን ውይይት በዓመታዊው ጉባኤ ማካሄድ ዋነኛው ነው ሲል ገልጿል። ### Response:
### Text: ላይቤሪያ️ላይቤሪያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በነጻ እንዲማሩ ወሰነችየላይቤሪያው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ በሀገሪቱ በየትኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ተማሪዎች ከከፍያ ነጻ ሆነው እንዲማሩ አወጁ፡፡የቀድሞው የእግር ኳስ ኮከብ እና የአሁኑ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ ላይቬርያውያን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከክፍያ ነጻ ሆነው እንዲማሩ አውጇል፡፡ፕሬዝዳንት ዊሃ ይህን አዋጅ ያሳወቁት ሰሞኑን በላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ ባደረጉበት ጉብኝት ነው፡፡ ማንኛውም የሀገሪቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከዚህ በኋላ ወጪው በሀገሪቱ እንዲሸፈን ለተሰበሰበው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና ተማሪዎች አስታውቀዋል፡፡ፕሬዝዳንቱ ይህን ያደረጉትም የተማሪዎች ወጪ በመንግስት በኩል መሸፈን አለበት በማለት ለአፍሪካም ፈር ቀዳጅ መሪነታቸውን አሳይተዋል ነው የተባለው፡፡ላይቤሪያውያን ተማሪዎች ለአንድ ክሬዲት 4 የአሜሪካን ዶላር ክፍያ ይጠየቁ ነበር፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የክፍያው መጨመርም በተማሪዎች ዘንድ ተቃውሞን አስከትሏል፡፡ፕሬዝዳንቱ ባልተጠበቀ መልኩ ማወጃቸው በሀገሪቱ ተማሪዎች አግራሞትን ፈጥሯል፡፡ላይቬሪያ 9 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች አሏት።ጆርጅ ዊሃ 23ኛ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው ባለፈው ዓመት መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ምንጭ፡አፍሪካን ስታንድአብመድ ### Response:
### Text: ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት ግንባታ ተጀመረከ29 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቀው የአዲስ አበባ የወንዞችና ወንዝ ዳርቻዎች ልማት ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት የመጀመሪያው ዙር ግንባታ ተጀመረ። የካቲት 14 ቀን 2011 ዓም በይፋ የተጀመረው የመጀመሪያው ክፍል ፕሮጀክት ከዚህ በፊት የሸራተን ማስፋፊያ በሚል የሚታወቀው ቦታ ላይ ያለው ሲሆን ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደ ስራ መገባቱን ለማወቅ ተችሏል።ይህ በቻይናው የኮንስትራክሽን ኩባንያ አማካኝነት ስራው የተጀመረው ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት ሶስት ስክዌር ኪሎ ሜትር አካባቢን ስፋትን የሚሸፍን ሲሆን ወንዝ ዳርና አካባቢውን እንደሚያካትት ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።በአካባቢው ላይ በመገኘት ለመረዳት እንደተሞከረው የግንባታ ስራው ወደ መሬት ወርዶ የተጀመረ ከመሆኑም በላይ ለግንባታው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ከውጭ አገር በመግባት ላይ ሲሆኑ ግንባታው በሚከናወንባቸው አካባቢዎች የፅዳት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።አትላስ ሆቴል አካባቢ ወደ ሚገኘው የኩባንያው ፅህፈት ቤት በመሄድ ለመመልከት እንደተቻለው ፕሮጀክቱን የተመለከቱ ስራዎችን የሚሰሩ ቻይናውያን ባለሙያዎች በከፍተኛ ደረጃ ስራዎቻቸውን እያከናወኑ ሲሆን ስራው እስከ ሚያዝያ ወር መጨረሻ ድረስም እንደሚጠናቀቅ የፕሮጀክቱ መሃንዲሶች ገልፀዋል። ### Response:
### Text: ቆይታ አቶ ሀይለ ሰመሀት መርሀ ጥበብቲኪቫህ ስፖርት ከአዲስ አበባ ከተማ የሴቶች እግር ኳስ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሀይለ ሰመሀት መርሀ ጥበብ ጋር ከደቂቃዎች በፊት በስልክ ለማውራት ችለናል።በደሞዝ ጉዳይ ለተነሱት ሀሳቦች ተጫዋቾች ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው ሲናገሩ እንደ ምክንያትነት የቀረበው ደግሞ ቡድኑ በባለፈው የውድድር አመት ከ 4 ሚልዮን ብር በላይ ያልተከፈሉ የሆቴል የትራንስፖርት መሰል ወጪዎች ስለነበሩበት እና የራሱ የሆነ የፋይናንስ ክፍል አለመኖሩ ለችግሩ መንስዔ መሆኑን ገልፀውልናል።ነገር ግን በአሁን ሰአት ይህ ችግር መቀረፉን እና በጀት ተፈቅዶ ያለፈው ወር ደሞዝ መውጣቱን ሲያሳውቁ ከዚህ ቀደም በክረምቱ ከክለቡ የተቀነሱ ተጫዋቾች እንኳ ክፍያ እንደሚፈፀምላቸው አሳውቀውናል። ደሞዝን በተመለከተ እየተነሱ ላሉት ጥያቄዎች አዎ የሚከፈላቸው 5000 ብር ነው ይህም የሆነው የቡድኑ የመክፈል አቅም ይህ ስለሆነ ነው።በዛሬው እለትም ከሰአታት በሃላ ከቡድኑ ተጫዋቾች ጋር ስብሰባ እንደሚያደረጉ ሲገልፁ ቡድኑ ገብቶበት ከነበረው የ 4 ሚልዮን ብር እዳ ከፍለን ቡድኑን ነፃ በማውጣት ለውድድር ማብቃት መቻላቸውን አሳውቀዋል። እንደ ችግር ግን የተፈጠሩት ነገር የሚመለከተው የክለቡን ስራ አስኪያጅ እና ፕሬዝዳንት መሆኑን አብረው ገልፀውልናል።ምንጭ በ 8068 ### Response:
### Text: ለ5ኛ ጊዜ የጅቡቲን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ 98 የመራጮች ድምፅ በማግኘት እንዳሸነፋ የተነገረላቸው ኢስማኤል ኦመር ጌሌህ በዓለ ሲመታቸው ተከናውኗል።በበዓለ ሲመታቸው ላይ የኢትዮጵያ ጠሚ ዶር አብይ አህመድ፣ የኬንያው ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የሱማሊያ ጠሚ ሙሀመድ ሁሴን ሮቤሌን ጭምሮ ሎሎችም ተገኝነት ነበር።በሌላ መረጃ ለፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኡመር ጌሌህ በዓለ ሲመት ጅቡቲ ሄደው የነበሩት ጠሚ ዶር አብይ አህመድ ወደኢትዮጵያ ተመልሰው በአፋር ክልል የሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ከፍተዋል።ጠሚስትሩ ፓርኩን በመረቁበት ወቅት ባደረጉት ንግግር አሁን ባለው ፕሮፖጋንዳ እና የሚዲያ ዘመቻ ሳንበረከክ የጀመርናቸውን ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ የኢትዮጵያን ከፍታ እውን በማድረግ ለዓለም እናሳየለን ሲሉ ተደምጠዋል።የሠመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ በታቀደው እና ለሌሎችም ሞዴል በሚሆን መንገድ እንደተከናወነ ገልፀዋል።ይህም ኢትዮጵያውያን ከተባበርን የምንፈልገውን መስራት እንደምንችል ማሳያ ነው ብለዋል፡፡በቀጣይም የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና ብልጽግና ማንም አያስቆመውም ያሉ ሲሆን አንዳንድ ሀገራት በሀገሪቱ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት ይሞክራሉ ነገር ግን ይህ ታሪክን አለማወቅ ነው ሲሉ መደመጣቸውን ከብሄራዊ ቴሌቪዥን የተገኘው መረጃ ያሳያል። ### Response:
### Text: ተፎካካሪ ፓርቲዎችግንቦት 2011 ዓም107 ፓርቲዎችነሀሴ 2011 ዓም137 ፖርቲዎች አቶ ኤፍሬም ማዲቦ በኢትዮጵያ ሰዎች በፓርቲ ውስጥ መደራጀትን የሚያገናኙት ከኢኮኖሚ ጥቅም መኖሩ ነው ቁጥሩን ያበዛው፣ በቅርቡ እንኳ ከምርጫ ቦርድ ጋር የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ድርድር ላይ የውሎ አበል ስጡን ብለው መንግስትን የጠየቁ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው ምን ያህል ለጥቅም የቆሙ እንደሆነ አንዱ ማሳያ ነው፣ የፖለቲካ ፓርቲ በየትኛውም አገር ውስጥ ሲመሰረት በህዝብ ድጋፍና በአባላት መዋጮ ድጋፍ እንጂ በመንግስት አይደለም። በተቃራኒው በኢትዮጵያ ውስጥ ግን መንግስት ሲሸፍንላቸው መቆየቱ፣ እያንዳንዱ ብሄር የእኔን ጥቅም የሚያስጠብቀው በብሄር የተደራጀው ነው በሚል ሁሉም በየዘውጉ እንዲደራጅ ምክንያት መሆኑ 100 ፓርቲ በመጪው ምርጫ ቢወዳደሩ ፓርቲዎች በመከፋፈላቸውና ድምጻቸው በመበታተኑ ምክንያት ብቻ ኢህአዴግ ተመልሶ ስልጣን ላይ እንዲመጣ ሊያደርግ ይችላል፣ ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ባላት አገር ከ10 ሺ በላይ ፊርማ ማሰባሰብ በጣም አነስተኛ ቁጥር ነው። ይህን የተቃወመ ሁሉ አለ። እኛም አገር ፓርቲ የቤተሰብ ፓርቲ ማለትም አባት ፕሬዚዳንት እናት ገንዘብ ያዥ፣ ወንድም የህዝብ ግኙነት ሀላፊ የሆነበት ፓርቲ ይዘን የትም አንደርስም። አዲስዘመን ተጨማሪ ያንብቡ 0812 ### Response:
### Text: የገዋኔው ጥቃትበትግራይ ዋልታ ፖሊስ እግር ኳስ ቡድንየትግራይ ክልል ፀጥታ እና አስተዳደር ጽህፈት ቤት የኮምኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሀፍታይመለስ ጥቃቱ በዛሬው ዕለት ጠዋት 3 ሰዓት ተኩል ገደማ ላይ መፈፀሙን ተናግረዋል።በጥቃቱ ከቆሰሉ ስድስት ሰዎች መካከል የአንዱ ሕይወት ማለፉንም ተገልጿል። አቶ ሀፍታይ መለስ ስለጥቃቱ ይህ ብለዋል«የትግራይ ፖሊስ እግር ኳስ ቡድን ከጨዋታ እየተመለሰ መንገድ ላይ ማንነታቸው እስካሁን ድረስ ማንነታቸው በግልፅ ማን እንደሆኑ ያላወቅናቸው ታጣቂዎች ጥቃት አድርሰዋል። በደረሰው ጥቃት ወደ ስድስት የቡድኑ አባላት ቆስለዋል። ከቆሰሉት ሁለቱ ከበድ ያለ ጉዳት ደርሶባቸው ነበር። አንደኛው ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል። በጣም የሚያሳዝን እና እጅግ የሚያስቆጭ አደጋ ነው» እንዲሁምየትግራይ ክልል የጸጥታ እና አስተዳደር ጽህፈት ቤት ጥቃቱን በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለው አረመኒያዊ ድርጊት ነው ሲል አውግዞታል ። የጥቃቱ ፈፃሚዎች ማንነት እንደማይታወቅ የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ማንም ሽፍታ እየተነሳ በአውላላ ሜዳ ላይ ዜጎችን ለአደጋ እንዲያጋልጥ እያደረገው ያለው የፌዴራል እና የክልል መንግስታት የዜጎችን በነፃ የመንቀሳቀስ መብት ላይ ብቁ ስራ መስራት በሚችሉበት ቁመና ላይ አለመገኘታቸው ነው ሲል ወቅሷል ። የጀርመን ራድዮ ### Response:
### Text: የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ክሳቸው ስለተቋረጠላቸው የህወሓት አመራሮች ምን አሉ የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት የሆኑት ዶር ይልቃል ከፍያለ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተው ነበር።በዚህ መግለጫ ወቅት ክሳቸው ስለተቋረጠ የህወሓት አመራሮችም አንስተው ተናግረዋል።ዶር ይልቃል አመራሮቹ የአማራን ህዝብ ጠላት አድርገው በመሳል ባለፉት በርካታ አመታት በህይወት፣ በንብረትና በስነ ልቦናው ላይ በደል እንዲደርስበት በማድረጋቸው ህዝቡ በአመራሮቹ መፈታት ላይ ቅሬታ ቢይዝ እውነት አለው ብለዋል።የአማራ ህዝብ በተከታታይ ሲደርስበት የነበረው በደል በእነዚህ ሰዎች ጠንሳሽነት እንደነበር ለአፍታም አንዘነጋም ሲሉም ገልፀዋል።ነገር ግን አሁን ማየት ያለብን እና ጠቃሚ የሚሆነው የሰዎቹ መፈታት አለመፈታትን ሳይሆን ሊከፋፍሉንና ሊያዳክሙን የሚችሉ ሀሳቦችን ወደ ጎን በማቆየት በዋና ዓላማችንና መርሃችን ላይ አተኩረን አንድነታችንን መጠበቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል።ዶር ይልቃል የእነስብሃት ነጋ መፈታት አለመፈታት ላይ አተኩረን ከተለያየን እንዳከማለን ለሌላ ጥቃት እንጋለጣለን ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ለእኛ እንደ አማራ ክልል የሚጠቅመው መርሃችን ላይ ትኩረት በማድረግ አንድነትን በማጠናከር ሊመጣ ከሚችል ዳግም ወረራ ራሳችንን መጠበቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ኤፍቢሲ ### Response:
### Text: ነጻነት ጉደታ የቫሌንሺያውን ግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ክብረወሰን በማስመዘገብ አሸነፈች ትላንት በተካሄደው የቫሌንሺያው ግማሽ ማራቶን የአለም ሻምፕዮና ውድድር ነጻነት ጉደታ የርቀቱን አዲስ ክብረ ወሰን በማስመዝገብ አሸናፊ ሆናለች፡ ከዚህ በፊት የርቀቱ ክብረወሰን ተይዞ የነበረው በኬኒያዊቷ ጀትሲሊን ጄፕኮሰጌይ የነበረ ሲሆን ነጻነት ጉዲና ይህን ድል መቀዳጀቷ ያልተጠበቀ ነው ተብሏል፡፡ ነጻነት ውድድሩን ለማጠናቀቅ 10611 ሰዓት የፈጀባት ሲሆን የርቀቱንምሰዓት በ14 ሰኮንዶች በማሻሻል አዲስ ክብረወሰን በማስመዝገብ አዲስ ታሪ አጽፋለች፡፡ ሌሎቹ ኢትዮጵያዊያን ዘነበ ይመር 5ኛ መሰረት በለጠ 6ኛ እና በቀለች ጉደታ 8ኛ ዝናሽ መኮንን 11ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡በወንዶቹ ምድብ ደግሞ ኬንያዊው ጂኦፈሪ ኪፕሳንገ ካምዎሮር ቀዳሚ ሆኖ ሲገባ ባህሬናዊው አብርሃም ናይቢ ቼሮበን እና ኤርትራዊው አሮን ክፍሌ 2ኛ እና 3ኛ ወጥተዋል፡፡ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት የነበረው ይመር ሞላ 4ኛ ጌታነህ ሞላ እና በተስፋ ጌታሁን ደግሞ 5ኛ እና 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውድድሩን በ3 ወርቅ በበላይነት ስታጠናቅቅ ኬንያ ኬንያ በአንድ ወርቅ ሶስት ብር እና አንድ ነሃስ 2ኛ እንዲሁ ኤርትራ በእንድ ብርና 2 ነሃስ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡ ምንጭ ### Response:
### Text: አቶ ልደቱ አያሌው ፍርድ ቤት ቀረቡአቶ ልደቱ አያሌው በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡ፖሊስ በሰኔ 23 ቀን 2012 በቢሾፍቱ ከተማ ለወጣቶች ገንዘብ በመስጠት ለብጥብጥና አመፅ በማነሳሳት በሚል ወንጀል እንደጠረጠራቸው አስታውቋል።ባለፈው አርብ አራት ሰዓት ላይ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸውና በዚህም ወቅት ሁለት ሽጉጦች ማግኘቱን አስታውቋል።የሰው እና የሰነድ ማስረጃ ለማቅረብም የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜንም የኦሮሚያ መርማሪ ፖሊስ ጠይቋል።አቶ ልደቱ በበኩላቸው ቋሚ አድራሻቸው አአ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፣ መታወቂያቸውም በዚያው መሆኑን በማንሳት በፌደራል ፍርድ ቤት ነው መቅረብ ያለብኝ በሚል መቃወሚያ አንስተዋል።በተጨማሪ በዋስ እንዲፈቱ የጠየቁ ሲሆን የዛሬ ዓመት የልብ ቀዶ ጥገና ወዳደረጉበት ሀገር ዛሬ 4 ሰዓት ላይ ለመጓዝ የተዘጋጁ መሆናቸውንና ትኬት ያላቸው ቢሆንም አሁን ታስረው እንደሚገኙና የአስም በሽተኛ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልፀዋል። የእስር አያያዙም ለኮሮና ቫይረስ ኮቪድ19 እንዳያጋልጠኝ ያሰጋኛል በማለት ይህ ታሳቢ ተደርጎ በዋስ ይፍታኝ ብለዋል።መርማሪ ፖሊስ0የእስር አያያዛቸው ምቹ እና ጥንቃቄ ያለው መሆኑን እና ከእስር ቢፈቱ ማስረጃ እንደሚሸሽበት በማሳወቅ ዋስትናውን ተቃውማል 0727 ### Response:
### Text: ባህርዳር ጎንደር ባህር ዳር ከተማ ከትላንት ለሊት ጀምሮ ዝምታ ሰፍኖባት እንደምትገኝና ዛሬ የሟቾች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም እንደነበር ነዋሪዎቿ ተናግሩ።ባለፉት ቀናት በከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ስትናጥ የነበረችው ባህር ዳር ከተማ ከለሊት ጀምሮ ፀጥ ብላ መዋሏን ነዋሪዎች መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።በሌላ በኩል ዛሬ በባህር ዳር በግጭቱ የሞቱ ሰዎች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም መዋሉን ነዋሪዎቹ አመልክተዋል።ትላንት በቀበሌ 13 ፣ 14 እና 16 በነበረ ውጊያ በርካታ ሰዎች መሞታቸው እና መጎዳታቸው ተነግሯል። እነዚሁ ሟቾች ስርዓተ ቀብራቸው ዛሬ በተለያዩ ስፍራዎች ሲፈፀም ውሏል።ነዋሪዎቹ በጦርነቱ ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈው አብዛኞቹ ከጦርነቱ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰዎች መሆናቸውን ገልጽዋል።የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ያነጋገራቸው ሁለት ዶክተሮች በውጊያው ሰላማዊ ሰዎች ስለመገደላቸው ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ የባህር ዳር ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ሬድዮ በሰጡት ቃል ከከተማው ማረሚያ ቤት 2 ሺህ የሚጠጉ ታራሚዎች ሲወጡ መመልከታቸውን ጠቁመዋል።በጎንደር ዳግሞ ዛሬ ከሰሞኑን የተሻለ መረጋጋት እንዳለ ነዋሪዎች ገልጸዋል። የመንግሥት ጦር በከተማው ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን የተደረደሩ ድንጋዮችን ሲያነሱ መዋላቸውን ነዋሪዎች ጠቁመዋል። ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና️ከሆሮ ጉዱሩ ዞን ሻምቡ ከተማ ወደ ነቀምቴ ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ በደረሰ የመገልበጥ አደጋ በሰዎች ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።45 ሰዎች የመጫን አቅም የነበረው ህዝብ ማመላለሻ አውቶብሱ መጫን ከነረበት አቅም በላይ ሰዎችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ እያለ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር አደጋው አንዳጋጠመው የሆሮ ጉዱሩ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ ደሳለኝ ተፈራ እንደተናገሩት የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ባሳለፍነው ቅዳሜ ነው ባኮ እና ሀረቶ በሚባሉ አካባቢዎች መካከል ላይ በሚገኝ ለገ ጂማ ስፍራ የተገለጠበው።በህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ላይ በደረሰው አደጋም የ17 ሰዎች ህይወት ማለፉን ሀላፊው አስታውቀዋል።በትራፊክ አደጋውም የበህዝብ ማመላለሻው አሽከርካሪ እና ረዳትን ጨምሮ ከተሽከርካሪው ውጨ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ የነበሩ ሰዎች ህይወት ማለፉንም አስታውቀዋል።በአደጋው ህይወታቸው ካለፈ ሰዎች በተጨማሪ በተሽከርካሪው ላይ ተሳፍረው የነበሩ በርካታ ሰዎች ላይ ከቀላል አስከ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱንም ገልፀዋል።እንደ አቶ ደሳለኝ ደለፃ የመገልበጥ አደጋ ያጋጠመው ተሽከርካሪ ለረጀም ዓመት አገልግሎት የሰጠ እና ያረጀ ነው።0ምንጭ ### Response:
### Text: በቡለን ወረዳ በተፈፀመ ጥቃት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን እንዲሁም በሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የቤኒሻነጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን ወረዳ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አሳውቀል።የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆኑ የጤና ባለሞያዎች እንደተናገሩት በሚሰሩበት የጤና ተቋም ጉዳት ደርሶባቸው የመጡ የፀጥታ ኃይል አባላት ስምንት 8 የሚደርሱ እና በርካታ ነዋሪዎች አሉ።ከነዋሪዎች መካከል ህይወታቸው ያለፈ አጠቃላይ ቁጥራቸው እስካሁን ባይታወቅም የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን እንዳረጋገጡ ተናግረዋል እንዲሁም የሁለት 2 የፀጥታ ኃይሎች ህይወት ማለፉን እንደሰሙ መረጃውን አካፍለዋል።በዛሬው ዕለት አካባቢው ሙሉ በሙሉ እንዳልተረጋጋ ያሳወቁት አባላቶቻችን ተጨማሪ ህክምና እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ታካሚዎችን ወደ ባህር ዳርና ፓዊ ለመላክ መኪና እየተጠበቀ እንደሆነ አሳውቀዋል።የቤንሻንጉል ጉሙዝ ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር ነጋ ጃራ ትላንት በወንበራና ቡለን ወረዳዎች ድጋሚ ግጭት መቀስቀሱን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።ኃላፊው ጸረ ሰላም ያሏቸው አካላት ወንበራ ወረዳ መልካን በሚባለው ቀበሌ ውስጥ ገብተው ሰዎችን አፍነው ገንዘብ ሲቀነበሉ እንደነበርና በዚህም ሰላሳ 30 የአካባቢውን ነሪዎች አፍነው ገንዘብ በመቀበል መልቀቃቸውን አረጋግጠዋል። ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጨት በይፋ ሲያስጀምሩ ባሰሙት ንግግር ኢትዮጵያ ማንንም የመጉዳት ፍላጎት የላትም ፍላጎቷም ኤሌክትሪክ አይተው የማያውቁ ዜጎቿን የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአንድነታችን፣ የመነሳታችን፣ የማደጋችን እና የአይበገሬነታችን ምልክት ነው ሲሉም ተናግረዋል።ግድቡ ለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን ከጨለማ እና ከድህነት መውጫ ድልድይ ሆኖ በማገልገል ረገድ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ እንደሆነም ገልጸዋል።ግድቡ ኃይል የማመንጨት ስራውን መጀመር ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለታችኛው ተፋሰስ አገራትም ጭምር ታላቅ የምሥራች ነው ብለዋል። ግድቡ የሚያመነጨውን ኃይል ከጎረቤት አገራት ባለፈ አፍሪካን ለማስተሳሰር ጉልህ ሚና እንዳለውም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ከፍተኛ የውሃ ሃብት ያላት አገር እንደመሆኗ መጠን በርካታ ግድቦችን በመገንባት ሃይል የማምረት እና የመሸጥ እምቅ አቅም አላት ያሉት ጠሚ ዶር ዐቢይ አህመድ የበለጸጉ አገራት አሁን ያለውን የውሃ ፖለቲካ መልክ በመቀየር በመስኩ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው በዚህም በርካታ አገራትን ተጠቃሚ ማድረግ ይቻላል ብለዋል፡፡ ### Response:
### Text: ብሄራዊመታወቂያ ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ዲጂታል መታወቂን ግዴታ ማድረግ እንደሚችሉ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል።በኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የተዘጋጀው የዲጂታል መታወቂያ ረቂቅ አዋጅ፣ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ደንበኞቻቸው አገልግሎት ለማግኘት ሲመጡ ዲጂታል መታወቂያ መያዝን ማስገደድ እንዲችሉ ፈቀደ፡፡ረቂቅ አዋጁ በፍርድ0ቤት0ትዕዛዝ0የዲጂታል0መታወቂያ0ልዩ0ቁጥር0ሊቆለፍ0ወይም0ከሥራ0ውጪ0ሊደረግ እንደሚችል የሚደነግግ ሲሆን፣ ይህም አገልግሎት ለማግኘት ዲጂታል መታወቂያን መያዝ ግዴታ በሚሆንበት ጊዜ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቁጥሩ የታገደ ነዋሪ አገልግሎት እንዳያገኝ ሊያደርገው ይችላል፡፡ከዚህ ቀደም ብሔራዊ መታወቂያ በመባል ሲጠራ የነበረውና ስያሜው ዲጂታል መታወቂያ በሚል የተቀየረው ማንነትን መለያ ልዩ ቁጥር የመስጠት ሥርዓትን የሚመራ ረቂቅ አዋጅ በዓቃቤ ሕግ አስተያየት ተሰጥቶበት ወደ ሚኒስቴሮች ምክር ቤት ለመላክ በዝግጅት ላይ ነው፡፡ረቂቅ አዋጁ0ከወንጀል ጋር የተያያዙ ሥጋቶችን በመቀነስ አገራዊ ደኅንነትን ለማረጋገጥ ጠንካራና አስተማማኝ፣ ተደራሽና ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ የኢትዮጵያ ዲጂታል የመታወቂያ መለያ ሥርዓትን መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን እንደሚጠቅስ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።ያንብቡ 0515 ሪፖርተር ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕገወጥ እንደሆነ ገልጻ እንዲቆም ያሳሰበችው የትግራይ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ተፈፀመ። የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ከፍተኛ ቤተ ክህነት ዛሬ ሃምሌ 15 2015 ዓም0 በአክሱም ከተማ የኤጲስ ቆጶሳት በአለ ሲመት አከናውኗል።በዚህም 1 ንቡረ ዕድ መሓሪ አቡነ ሊባኖስ2 ቆሞስ አባ ዘሥላሴ አቡነ ናትናኤል3 ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ አቡነ ኣረጋዊ4 ቆሞስ አባ ኃሚካኤል አቡነ ዮሐንስ5 ቆሞስ አባ ጽጌገነት አቡነ ኣትናቴዎስ6 አባ ኤልያስ አቡነ ዕንባቆም ተብለው ተሰይመዋል።ከጥቂት ቀናት በፊት በትግራይ ያሉ ብፁኣን አባቶች በትግራይ እና በውጭ ሀገር የሚያገለግሉ 10 ኤጲስ ቆጲሳትን መምረጣቸው አይዘነጋም።የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሹመት እንቅስቃሴው ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ የሆነና ሕገወጥ ተግባር በመሆኑ እንዲቆም አሳስባ ነበር።በትግራይ ባሉ የአህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና ሊቃውንት እየተከተሉት ያለው አካሄድ ላለው ችግር መፍትሔ የማይሆን እንደሆነ በመግለፅ የፌዴራሉ እና ክልሉ መንግስት ሕገወጡ ን ሹመት በማስቆምና ሰላማዊ የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት የበኩላቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርባ ነበር።ፎቶ ቴሌቪዥን ትግራይ ድምፂ ወያነ ### Response:
### Text: አሳዛኝ ዜና በወላይታ ዞን በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አንድ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ አዉቶብስ ተገልብጦ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ20 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት መድርሱን የወረዳው ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።በጽህፈት ቤቱ የትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ ሳጂን አዳነ አሰፋ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሱ በወረዳው ዋሙራ በሚትባል የገጠር ቀበሌ አካባቢ ተገልብጦ ወንዝ ውስጥ በመግባቱ ነው።የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 4147 ደህ የሆነው ይህ አውቶብስ ከአረካ ወደ ማዞሪያ 29 መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ ከሟቾቹ በተጨማሪ ሶስቱ ከባድ የመቁሰል አደጋ ሲደርስባቸው አሽከርካሪውን ጨምሮ ሌሎች 17ቱ ደግሞ ቀላል የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው ገልጸዋል።ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በደረሰው በዚህ አደጋ የቆሰሉ መንገደኞች በዱቦ ማሪያም ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸዉ መሆኑን ገልጸው የሟቾቹ አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው መሰጠቱን ተናግረዋል።የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝ የገለጹት ሳጅን አዳነ አካባቢው ቁልቁለታማ በመሆኑ አሽከርካሪዎች የመንገድ አጠቃቀም ስርዓትን አክብረው በጥንቃቄ ሊጓዙ እንደሚገባ አሳስበዋል።ምንጭ ኢዜአፎቶ መአዛ ### Response:
### Text: የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች ምልመላ ያወጣው ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ህዳር 2012 ዓም ለሚያካሂው የሲዳማ የክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ 6000 የሚሆኑ የህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎችን በበጎ ፍቃደኝነነት ለአንድ ወር ማሰራት ይፈልጋል፡፡ስለሆነም ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን ና ኮፒ በመያዝ ንፋስ ስልክ ቡና ቦርድ ፊትለፊት በሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ማእከል በአካል በመገኘት ከመስከረም 24 ቀን 2012 ጀምሮ በስራ ሰአት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡ አመልካቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች የማንኛውም የፓለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነያልሆነች በትምህርት ዝግጅታቸው በማንኛውም የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላት ያለው እድሜ ከ20 45 አመት የሆነችየሆነ በገጠር ቀበሌዎች ተንቀሳቅሰው መስራት የሚችሉ የስራ ልምድ አይጠይቅም ሆኖም በምርጫ አፈጻጸም ዙሪያ ወይም በተለያየ ማህበራዊ አገልግሎቶች የተሳተፉ አመልካቶች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ቦርዱ በስራ የሚያሳልፉትን ጊዜ አበል የሚከፍል ሲሆን በተጨማሪም በህዝበ ውሳኔው ላይ በበጎ ፈቃደኝነት ለተሳተፉ አስጻሚዎች የተሳትፎና የእውቅና ምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ### Response:
### Text: ተማሪዎች የእርስ በእርስ የዩኒቨርሲቲ ቅያሬ ሙከራ አይቻልም ወሮ አመለወርቅ ሕዝቅኤልየኢትዮጵያ ቴሌቪዥንአዲስ የተመደቡ ተማሪዎች በግል የሚያደርጉት የእርስ በእርስ የዩኒቨርሲቲ ቅያሬ ሙከራ ህገወጥ እንደሆነ እና እንደማይቻል የኢፌዴሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ በግል ለመቀያየር እየተቀመጡ ያሉ መልዕክቶች ተገቢ ያልሆኑ እና ህጋዊ አለመሆናቸውን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።ዘንድሮ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ከ147 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመቀበል የተዘጋጁ ሲሆን የተማሪዎች ምደባም ይህን የመቀበል አቅም መሰረት በማድረግ እንደተካሄደ ወሮ አመለወርቅ ሕዝቅኤል ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።ወሮ አመለወርቅ አክለው ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመሄድ የማያስችል ምክንያት ያላቸው ተማሪዎች ማስረጃቸውን በማቅረብ ውሳኔ እያገኙ ነው ይህ አሰራር ከዚህ በፊትም እየተሰራበት ነበር ብለዋል።በተለይ ከህመም ጋር በተያያዘ ችግር ያለባቸው ተማሪዎች በሀኪሞች ቦርድ የተረጋገጠ ማስረጃ ካቀረቡ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል ሲሉ ገልፀዋል። ከዚህ ውጭ ሚኒስቴሩ አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአመዳደብ ላይ ያላቸውን ቅሬታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ ይሰጣል ብለዋል። ### Response:
### Text: ዘራፊዎቹ ተይዘዋል በአዲስ አበባ የአቢሲኒያ ባንክ ቴሌ መድሃኒዓለም ቅርንጫፍን ለመዝረፍ የሞከሩ ግለሰቦች ተያዙ፡፡ትናንት ምሽት አስራ ሁለት ሰዓት ተኩል ገደማ በተለምዶ ቦሌ መድሃኒዓም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ የአቢሲኒያ ባንክ ቅርንጫፍ ላይ የዘረፋ ሙከራ ያደረጉ ግለሰቦች መያዛቸው ተነግሯል፡፡እነዚህ የተደራጁ ዘራፊዎች መኪና ይዘው ያደረጉት የዘረፋ ሙከራ በባንኩ ሠራተኛ እና ፖሊስ ብርቱ ጥረት ከሽፏል ተብሏል፡፡የአቢሲኒያ ባንክ የማርኬቲንግ ኮሙኒኬሽን እና ኦፕሬሽን ስራ አስኪያጅ አቶ አስቻለው ታምሩ ዛሬ ለሸገር ራድዮ እንደተናገሩት፣ በሙከራው በሠው ህይወትም ሆነ በባንኩ ላይ የደረሰ ጉዳት የለም፡፡ምንም አይነት ገንዘብ ከቅርንጫፉ እንዳልተዘረፈም አቶ አስቻለው ነግረውናል፡፡ሙከራውን ካደረጉ የተደራጁ ዘራፊዎች የተወሰኑት በዚያው ዕለት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ብለዋል፡፡የተወሰኑት ደግሞ ዛሬ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተናግረዋል፡፡ጉዳዩ በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተካሄደ እንደሚገኝም ተሠምቷል፡፡ከምርመራ ውጤቱ በኋላ ሌሎች ተጨማሪ ግለሰቦች ከሙከራው በስተ ጀርባ መኖር አለመኖራቸው ይታወቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡ባንኩም ምርመራው እንዳበቃ ስለ ጉዳዩ ለህዝቡ ስለ ሁኔታው ያሳውቃል ብለዋል፡፡ምንጭ ሸገር ራድዮ ### Response:
### Text: አብዱል ጃባርበደቡባዊ ተገደሉ️በአፍጋኒስታን የምርጫ እጩ ተወዳዳሪ ከታሊባን በተሰነዘረው ጥቃት ተገደሉ።እጩ ተወዳዳሪ አብዱልጃባርበደቡባዊ አፍጋኒስታን የሄልማንድ ግዛት በፈነዳው ቦንብ ጥቃት ነው ከሌሎች አራት ሰዎች ጋር የተገደሉት፡፡አብዱል ጃባር ቅዳሜ ለሚካሄደው የምክርቤት ምርጫ ዝግጅት በማድረግ ላይ እያሉ በላሽካርጋህ ከተማ ተገድለው መገኘታቸውን የሄልማንድ አስተዳዳሪ አስታውቀዋል፡፡የሄልማንድ አስተዳዳሪ ቃል አቀባይ ኦማር ዝዋክ ከሟቾቹ በተጨማሪ ሰባት ሰዎች በጥቃቱ ጉዳት እንደደረሰባቸው የገለፁ ሲሆን ጥቃቱን የፈፀመው ምርጫው እንዳይካሄድ ጥረት በማድግ ላይ የሚገኘው የታሊባን ታጣቂ ቡዱን ሳይፈጽመው እንዳልቀረ ተጠቅሷል፡፡የታሊባን ታጣቂ ቡዱን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ ተማሪዎች እና አስተማሪዎች ቅዳሜ በሚካሄደው ምርጫ እንዳይሳተፉ ያስጠነቀቀ ሲሆን በትምህርት ቤቶች የምርጫ ማእከላት እንዳይኖሩም አስጠንቅቆ ነበር፡፡ከምርጫው ጋር ተያይዞ ባለፉት ሁለት ወራት አብዱል ጃባርን ጨምሮ 10 የምርጫ እጩዎች የተገደሉ ሲሆን ሁለት እጮዎች ተሰውረዋል ተሰውረዋል፡፡249 የምክርቤት አባላት የሚመረጡበት የአገሪቱ ምርጫ ለሶስት ዓመታት የዘገየ ሲሆን የፊታችን በያዘነው ወር ኦክቶበር 30 ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ምንጭ ### Response:
### Text: የጥላቻ ንግግርየፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭትን ለመከላከል ያረቀቀዉ አዋጅ «በተለይ በማኅበረሰቡና በሕዝቡ መካከል እኩልነት እንዲሰፍን» ለማጎልበት የወጣ ነው አለ። የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ «በጥንቃቄ ከሕገመንግሥቱም አጠቃላይ ከዜጎች መሠረታዊ መብቶች ጋር በማይጋጭ መልኩ አዋጁን ለማዘጋጀት ጥረት» መደረጉን ተናግረዋል። ረቂቁ በውይይት ላይ እንዳለ የገለጡት ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ «በሕጉ ውስጥ የወንጀል ድንጋጌዎች» መካተታቸውን ተናግረዋል። «ማንነታቸውን ደብቀው በተለያየ መልኩ በተለይ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የዜጎችን የብሔሮችን እና የሌሎች በሕገመንግሥቱ እና በሌሎች ሕግጋት የተረጋገጡ መብቶችን የሚጥሱና ከዚህ በተቃራኒ የሚንቀሳቀሱ» አካላት ሕግ ማክበር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። እነዚህ አካላት ግለሰቦች ቡድኖች የፖለቲካ አካላት የመንግሥት ተሹዋሚዎች እንዲኹም የመንግሥት አለያም የግል መገናኛ ዘዴዎች ሊኾኑ እንደሚችሉ ገልጠዋል። «ይኽን ሕግ አክብረው መንቀሳቀስ» እንዳለባቸውም አሳስበዋል። «ከዚያ ባለፈ ግን የሕግ የበላይነቱን ለማስከበር በሕጉ ውስጥ በተቀመጠው የወንጀል ድንጋጌ መንግሥት አስፈላጊውን ርምጃ የሚወስድ መኾኑ ነው» ብለዋል። ### Response:
### Text: የጎርፍ እና የእሳት አደጋዎች በአዲስአበባ በአዲስ አበባ ከተማ ቅዳሜና እሁድ ሁለት የእሳት እንዲሁም ሶስት የጎርፍ አደጋዎች እንደተከሰቱ የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ በአደጋዎቹ ሳብያም የሰው ሂወት አለመጥፋቱን የኮሚሽኑ የህዝብ ግኑኝነት ባለሙያው አቶ ሲለሺ ተስፋዬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ራድዮ ገልጸዋል፡፡የእሳት አደጋዎቹ የደረሱት በአዲስ ከታማ ክፍለ ከተማ መርካቶ በርበሬ በረንዳ ላይ በሚገኙ የንግድ ሱቆች ላይ ሲሆን በአደጋው ሳቢያም አንድ ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ወድቧል ተብሏል። ኮሚሽኑ ሀያ ሚሊየን የሚጠጋ ንብረት ከውድመት ታዲጌያለሁ ብሏል።ሁለተኛው የእሳት አደጋ የደረሰው በኮሊፌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ልዩ ስሙ አለም ባንክ አካባቢ በሚገኙ የንግድ ሱቆች ላይ ሲሆን በአደጋው 850 ሺ ብር የሚጠጋ ንብረት እንደጠፋና ስምንት ሚሊየን የሚገመት ንብረት ደግሞ ማዳን ተችላል፡፡የጎርፍ አደጋዎቹ የደረሱት ደግሞ ሁለቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ ሲሆን አንደኛው በወረዳ አምስት ሶር አምባ ሆቴል አካባቢ ሲሆን ሌላኛው የጎርፍ አደጋ ደግሞ በወረዳ ሁለት ጣሊያን ሰፈር አካባቢ በመኖርያ ቤት የደረሰ የጎርፍ አደጋ ነው። በሁለቱም የጎርፍ አደጋዎች በግምት ሁለት መቶ ሺ ብር የሚገመት ንብረት መጥፋቱ ተገልጿል፡፡ ኢትዮኤፍኤም ### Response:
### Text: ቲክቫህ ቤተሰቦች ቄለም ወለጋከደቂቃዎች በፊት በቄለም ወለጋ አንፊሎሙጊ ከተማ ቤተሰቦቻቸው የሚኖሩ የዩዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሆኑ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በስልክ ለማግኘት ችለናል። ተማሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ በወለጋ የሰው ህይወት እየጠፋ ነው መንግስት ግልፅ መረጃ ለህዝብ እየሰጠ አይደለም የኢተርኔት እና ስልክ መቋረጥ ከቤተሰቦቻቸው እንዲርቁ እንዳደረጋቸውም ተናግረዋል። በሙጊ ከተማ በያዝነው ሳምንት የሰዎች ህወይት አልፏል የንግድ እንቅስቃሴ፣ ትምህርትም ቆማል፣ በከተማይቱ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የተኩስ ድምፅ በየጊዜው ይሰማል፣ ከባድ መሳሪያዎችም ሲተኮሱ ይሰማል፣ ወጣቶች በነፃነት መንቀሳቀስ አልቻሉም በርካታ ወጣቶች ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል እንግልት እየደረሰባቸው ይገኛል በምሽት 100 በኃላ መንቀሳቀስ አይታሰብም ብለውናል።በተጨማሪ የሀገሪቱ ሚዳያዎች ዝምታን መምረጣቸው፣ በማህበራዊ ሚዲያም ለወለጋ ህዝብ ድምፅ መነፈጉ እጅግ እንዳሳዘናቸው ተማሪዎች አስረድተዋል። ወላጆቻችን በችግር ላይ ናቸው እየሆነ ያለውም ጉዳይ መንግስት ግልፅ ማብራሪያ ይስጥ፣ መንግስት በሚወስደው እርምጃ ንፁሃን ዜጎች እንግልት ውስጥ ሊገቡ አይገባም ጋዜጠኞችና ሚዳያዎች ገለልተኛ ሆነው የህዝቡን ድምፅ ማሰማት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ### Response:
### Text: አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች አርጀንቲና ግዙፉን የኢግዚቢሽን ማዕከል ወደ ኮቪድ19 የህክምና ማዕከል ቀይራለች። እስከ 2ሺህ 5መቶ የሚጠጉ የኮቪድ 19 ታማሚዎችን ለማከም እንዲውልና ማዕከሉ በሆስፒታሎች የሚኖረውን ጫና ለማገዝ እንደሚረዳ ተገልጿል በዩናይትድ ኪንግደም ባለፉት 24 ሰዓት 888 ሰዎች ሞተዋል። ቁጥሩ ባለፉት 7 ቀናት ከተመዘገበው ከፍተኛው ነው። በሌላ በኩል 5526 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቅላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 114217 ደርሷል። በጃፓን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 10000 ደርሷል። በአውሮፓ ብቻ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1000000 ደርሷል። ደቡብ ኮሪያ ባለፉት 24 ሰዓት 18 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ሪፖርት አድርጋለች። ዘጠኙ ከውጭ የገቡ ናቸው። በደቡብ ኮሪያ ከ በኃላ የተመዘገበ ዝቅተኛው ኬዝ ነው። በቻይና 27 ተጨማሪ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። አስራ ሰባቱ 17 ከውጭ ሀገር የገቡ ናቸው። በጣልያን በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እንዲሁም የሟቾች ቁጥር መቀነስ አሳይቷል። ባለፉት 24 ሰዓት 482 ሰዎች ሲሞቱ 3491 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት 585 ሞተዋል። ጅስቲን ትሩዶ የካናዳ እና የአሜሪካ ድንበር ተዘግቶ እንደሚቆይ ተናግረዋል። ድንበሩ ተዘግቶ እንዲቆይ ሁለቱም ሀገራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውም ተሰምቷል። ### Response:
### Text: የግድቡ ግንባታ ውሃ ይቀንስብኛል የሚለው የግብጽ ጩኸት የማጭበርበሪያና የተለመደ የሃሰት ክስ ነው አቶ ዘሪሁን አበበ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዲፕሎማት፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ኮሚቴ አባል አቶ ዘሪሁን አበበ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ውሃ ይቀንስብኛል የሚለው የግብጽ ጩኸት የማጭበርበሪያና የተለመደ የሃሰት ክስ ነው ሲሉ ገለፁ።አቶ ዘሪሁን ይህን ያሉት ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ነው።የግብፅ ጩኸት አጠቃላይ ዓላማ ኢትዮጵያ ለምን የዓባይን ውሃ ትጠቀማለች ከሚል ምቀኝነት የመነጨ ነው ያሉት አቶ ዘሪሁን፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሃይል ማመንጪያ ግድብ ነው ውሃ ይይዛል፣ ተርባይኖቹን ይመታል ኤሌክትሪክ አመንጭቶ የፍሰቱ ሂደቱን ይቀጥላል ብለዋል። የግብጽ አካሄድ በአጠቃላይ የአባይ ውሃ ለእኛ ይገባል ከሚል የስግብግብነት መንፈስ የመነጨ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም ሲሉም አክለዋል።የዓባይን ውሃ የሚጋሩት 11 አገራት ናቸው ውሃው ለአገራቱ የሚበቃ በመሆኑ በትብብር እና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል።ግብጽ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ውሃ እጥረት ያጋጥመኛል የሚለው ስሞታ ፈጽሞ ሃሰት ነው። ግብጽ በከፍተኛ ደረጃ ውሃ ከሚያባክኑ አገራት መካከል የምትመደብ ነችም ብለዋል።ያንብቡ 05172 ### Response: