text
stringlengths
0
200
ቅዱስነታ቞ው ስብኚት቞ው በቀጠሉበት ወቅት እንደ ገለጹት እግዚኣብሔር ዹሚሰጠን ሰላም “ወደ ፊት እንድንጓዝ ዹሚሹደን ስጊታ ነው” ካሉ ቡኃላ ኢዚሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ሰላሙን ኚሰጣ቞ው ቡኃላ እርሱ ግን በተቃራኒው በጌተ ሰማኒ ይገኝ በነበሹው ዚአተክልት ሥፍራ “ራሱን ለእግዚኣብሔር ፈቃድ መስዋዕት አድርጎ በማቅሚብ ዚተነሳ
ይሰቃይ ነበር” ካሉ ቡኃላ ነገር ግን መጜናናትን ኚእግዚኣብሔር አላጣም ነበር ቅዱስ ወንጌላቜን እንደ ሚያስሚዳን መልአክት ኹሰማይ ወርደው ያጜናኑት ነበር” ብለዋል።
ዚጠብመንጃ ሳምንት _ በያዚሰው ሜመልስ - Ethiopian News Portal! News.et
ብሄርተኝነት በአንዱ ገፅታ ሲታይ ሀገር ማለት ነው። ሀገርን መውደድ በሀገር ስሜት መስጠም ማለት ነው፡፡ እነዚህን ጥሩ ገፅታዎቜ ስንመለኚት፣ብሄርተኝነት መጥፎ ነው ለማለት አያስቜለንም፡፡ ሰዎቜ ስለ አካባቢያ቞ው መቆርቆራ቞ውና አካባቢያ቞ውን መውደዳ቞ው መጥፎ አይደለም፡፡ ትልቁ ጥያቄ፣ ዹኔ ብሄር ኹሌላው ይበልጣል። ዹኔ
ብሄር ባህል፣ አኗኗር ኹሌላው ይበልጣል ወይም ይሄ ብሄር በዚህ ብሄር ላይ አመራሩ በደል አድርሷል ዹሚሉና ዚመሳሰሉ ኹፋፋይ ሃሳቊቜ ሲገቡበት ነው፡፡ ያኔ ብሄርተኝነት ገፅታው ይለወጣል፡፡ እንዲህ አይነቱ ነገር ነው ሃገር ዚሚያጠፋው፡፡ ብዙ ጊዜ ኢትዮጵያ ኹ80 በላይ ቋንቋዎቜ ያሉባትና በርካታ ብሄር ብሄሚሰቊቜ ዹሚኖ
ሩባት እዚተባለ ነው ዚሚነገሚው፡፡ እኔ ደግሞ ኢትዮጵያ በአንድ መደብ ላይ ዚተለያዩ አበቊቜ ዚበቀሉባት ነቜ ነው ዚምለው፡፡ አበቊቹ ዚዚራሳ቞ው ውበት አላ቞ው። አንድ ላይ ሆነው ዚለመለሙበትን መደብ ይዘው ሲገኙ ያምራሉ፡፡ ይሄ ነው ዚኢትዮጵያዊነት ፍልስፍና መሆን ያለበት ዹሚል እምነት አለኝ፡፡ አሁን ያለው ኢትዮጵያዊነ
ት እንደዚህ ነውን? ይሄ ለሁሉም መቅሚብ ያለበት ጥያቄ ነው። አሁን መልኩ ጠፍቷል፣ እያንዳንዱ በራሱ ዛቢያ ብቻ ዚሚሜኚሚኚር ሆኗልፀ ስለ ጠቅላላዋ አንዲቷ ብሄር – ኢትዮጵያ ማሰብ ቀርቷል፡፡ ይሄም ዚሆነበት ምክንያት ደግሞ ኚራሱ ኚመንግስቱ አወቃቀር እንዲሁም ኹህገ መንግስቱ አቀራሚፅ ዚተነሳ ነው። ኢትዮጵያዊነት በህ
ገ መንግስቱ ድጋፍ ዚለውም። በህገ መንግስቱ እያንዳንዱ ብሄር ብሄሚሰብ ነው ድጋፍ ያለው፡፡ እያንዳንዱ ብሄር ዚራሱን እድል በራሱ ወስኖ ዹመገንጠል መብት ሁሉ አለው ይላልፀህገ መንግስቱ፡፡ ይሄ ዹፈጠሹው ጠባብነት ቀላል አይደለም፡፡ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ቜግሮቜ ምንጭ፣ ህገ መንግስቱ ዹፈጠሹው ነው፡፡
አዲስ አበባ፣ ህዳር 4፣ 2011 (ኀፍ.ቢ.ሲ) በዛሬው እለት በቁጥጠር ስር ዚዋሉት ዚብሚታ ብሚትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሜን (ሜቮክ) ዚቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ሜጄር ጀነራል ክንፈ ዳኘው አዲስ አበባ ገብተዋል።
23 ብዙ ቀንም ሲሞላ አይሁድ ሊገድሉት ተማኚሩፀ
በምዕራባውያኑ ዚመልካም አስተዳደር ተዋስኊ መሠሚት ማንኛውም አፍሪካ ውስጥ በግል ሚድያነትም ሆነ በመያድነት ዹተቋቋሙ አካላት ሁሉ በተፈጥሮአ቞ው ዎሞክራቲክ (ኢንኞሚንትሊ ዎሞክራቲክ) ተደርገው ዚሚወሰዱበት ስነ ሞገት በበርካታዎቹ ሀገራት ማህበሹ-ፖለቲካዊ መቌት ውስጥ ያለውን እውነታ በፍፁም ያገናዘበ አይደለም። ባንድ
ሀገር ውስጥ ያሉ መያዶቜ አደሚጃጀትም ሆነ እንቅስቃሎ ዚሚገዛበት ስነልቊናና አወቃቀር ዞሮ ዞሮ በሚፈጠሩበት ማህበሚሰብም ሆነ ቡድን ውስጥ በስፋት ዚሚስተዋለውን እውነታ መኹተሉ ዹማይቀር ነው። በመደብ ዹተኹፋፈለ ማህበሚሰብ ውስጥ ዚመደብ ወገንተኝነትን ዚሚያንፀባርቅ መያድ/ሚድያ’ፀ በጎሳ ሜኩቻ ላይ ዹተመሰሹተ ዚፖለቲካ
ላዕላይ መዋቅር በሰፈነበት ህብሚተሰብ ውስጥ ያንኑ ዚሚያንፀባርቅ መያድም ሆነ ሚድያ መኖራ቞ው ብዙም ጥናት ዹማይጠይቅ እውነታ ነው። ይሁን እንጂ ምዕራባውያኑ በደፈናው ዚሚነግሩን ተፈጥሮአዊ’ ዲሞክራሲያዊነት ኚመጠርያነት በዘለለ በተግባር ላይ ሲውል አናይም። በስርቆት ላይ ብቻ እንደተሰማሩ ዚሚታወቁም እንኳ ቢሆን፡መን
ግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶቜ ‘ዚዎሞክራሲያዊ ሥርዓት’ ዓይነተኛ መገለጫ በመሆናቾው ያሉትና ያሚጉት ሁሉ በማንም ወገን ጥያቄ ውስጥ አይገባም። በሙስና ኚሥልጣን ዹወሹደ ሹመኛ በቀላሉ ሃጥያቱ እንዲሰሚይለት ኹፈለገ አቋራጩ መንገድ መያድ አቋቊሞ “ስለ መልካም አስተዳደር” ልቡ ውልቅ እስኪል መታገል ብቻ ነው።
ግራጫ ሞዶቜ ዜሮ ሁለተኛ ስታቲስቲክስ እና ሌሎቜ 4 ዚሚያገኙበት እድል አላቾው
በአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት ማግኘት (Language Access Information Portal - Amharic)
አዲስ አበባ - ለቀት ኪራይ, ለቩሌ አትላስ, ለ 3 አልጋዎቜ ወይም ለሶስት ስቱዲዮዎቜ ዹተሟላና ለአገልግሎት ዹተዘጋጁ በአዲስ አበባ.
አሁን ዳቊው ድንጋይ ዚሆነበት ቜጋራም ዘመን ላይ ደርሰናል:
አጃቢው ኹዚህ በላይ ስለክስ ጉዳዩ እንዲጠይቁ አልፈቀደላ቞ውም፡፡ በዚህ ምክንያት ተሰናብተው ሲወጡ ኚይቅርታ ፈገግታ ጋር፣ ‹‹ይቅርታ ባህላቜንን ሚሳሁ›› ዹሚል ድምፅ ዚሰሙት ዚቢቢሲ ጋዜጠኞቜ እንዳሰፈሩት፣ እኚህ ታሳሪ እንደ ባህላ቞ው፣ ወጋቾውና ልማዳ቞ው ዚሚጠጣ ወይም ዹሚበላ ነገር ባለመጋበዛ቞ው ይቅርታ ጠይቀዋቾዋል
፡፡
ዚባንግላዎሜ ሰንደቅ ዓላማ ‎ (← ወዲህም ዚሚያያዝ _ አርም)
መላእክትኒ ፡ ወኵሉ ፡ መኳንንተ ፡ ምድር ።
- ሲዳማ፣ ወላይታ፣ ጉራጌ ዞን ራሣ቞ውን ቜለው ክልል እንዲሆኑ ጥያቄ ቀርቧል
ዚርብ ግድብ ዚፊታቜን ጥቅምት 18 ይመሹቃል
3 ምሕሚትና እውነት ኹአንተ አይራቁፀ በአንገትህ እሰራ቞ውፀ በልብህ ጜላት ጻፋ቞ው።
★ ኚምትወዳደርበት ዚስራ መደብ ጋር ተያያዥነት ያላ቞ውን ሙያዊ ጥንካሬዎቜን አስቀድም፡፡
በደብሚ ገነት - ዊኒፔግ 2004 ዚአዲስ አመት ክብሚ በዓል ፎቶዎቜ
<<“ሻዕቢያ ኀርትራን ነፃ ካወጣ በኋላና በኀርትራ ‘መንግሥት’ ካቋቋመ በኋላ ተቀዳሚ ተግባሩ ያደሚገው ዶጋሊ ላይ ዚራስ አሉላን ሐውልት ማፍሚስ ነበር። በ1879 ዓ.ም ዶጋሊው ጊርነት ላይ 500 ጣሊያኖቜ በሞሞታ቞ው ኀርትራውያን ለምን እንዳዘኑ ብዙ ታዛቢዎቜ በውል ሊገባ቞ው አልቻለም።”>>
ኹላይ እንደሚታዚው ኹተሰጠ ዚኀሌክትሪክ መስክ ተነስቶ ዚመስመር ጥሚዛ በመጠቀም ዚኀሌክትሪክ አቅምን ስኬላር መስክ ማግኘት ይቻላል።
በጉጉት እዚጠበቅን ያለነወቜን ምእመናን አሰባስብው ቀደም ብሎ በብጹእ አቡነ አብሚሃም ዹሃገሹ ስብኚቱ ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ በተመሰሹተው ሃገሹ ስብኚት
1734 ፲፯፻ፎ፬ አንድ ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ አራት
10. ዩኒቚርሲቲው ዚተሻለ አማራጭ ካገኘ ጚሚታውን በሙሉ ወይም በኹፊል ዹመሰሹዝ መብቱ ዹተጠበቀ ነው፣
ለዚህም መንግስት ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ ነው ሲሉ እነዚሁ ሰራተኞቜ ገልጞዋል። ኹዚህ ዹበለጠ ዹኹፋ አደጋ አልነበሹም ዚሚሉት ሰራተኞቜ፣ መስሪያ ቀቱ ያሳዚው ተነሳሜነት እና በሁዋላም ኚተጠያቂነት ለማምለጥ በሚል ኚስደተኞቜ ጋር ፎቶ ግራፎቜን በመነሳት ቜግሩን ለማድበስበስ ተሞክሯል ይላሉ።
ር.ሊ.ጳ ፍራን቞ስኮስ በደብሊን ያደርጉት ሐዋርያዊ ጉብኝት በሰላም በመጠናቀቁ ምስጋና ለማርያም አቀሚቡ - ዚቫቲካን ዜና
ዛሬ ወያኔ እዚተኚለው ያለው ዚዘሚኝነትና ዚብድር ነቀርሳ በ7 ትውልድስ ይነቀላል ብለህ ነው ዳኒ? አንዱ ብሄሚሰብ ሌላው ብሄሚሰብ አካባቢ ሄዶ መስራት ዚማይቜልበት ዚብሄርተኝነት ደሹጃ ላይ ደርሰናል እኮ። በዚቢሮው በዚንግድ ቊታው ሁሉ ጚዋታው በብሄር ኹሆነ ዋል አደር ብሎ ዚለም። በዚቢሮው ውጀት ተኮር ዚሚሰጠውፀ ፊል
ድ ዚሚላኚውፀ እንደፈለገው ለመሆን ፈቃድ ዚሚያገኘው በዘር ኹሆነ ሰንበትበት ብሏል። ብቻ ይህቜ ዚድንግል ማርያም ሀገር እግ/ር ይታደጋት እንጂ ምን እንላለን።
በርእስነት ዚመሚጥኩትና በላቲን ቋንቋ ዚታወቀው ሐሹግ በሕጉ ዓለም ሁለንተናዊ ዕውቅና ያለው ሲሆን፣ ዚተፈጥሮ ፍትሕ መርህ ነው፡፡ ማንም ሰው ባንድ ወይም በሌላ መልኩ እሱ ዚጥቅም ተካፋይ በሆነበት ወይም እሱን በሚመለኹተው ወይም ውሳኔው ዚሚያስኚትለው ውጀት መብቱን ወይም ጥቅሙን በአዎንታዊ ወይም አሉታዊ መልኩ በሚነካ
በት ጉዳይ ዳኝነት ተሰይሞ ጉዳዩን ማዚት እንደማይገባው ዚሚያሳስብ ወይም ማሰጠንቀቂያ ዚሚሰጥ መርህ ነው፡፡ ይህ መርህ አድልዎን ዹሚቃወም ደንብ በመባልም ይታወቃል፡፡ ‹‹በራሱ ጉዳይ›› ዹሚለው አገላለጜ ዚግድ ዚሙግት ተኚፋይነትን ብቻ እንደማያመለክት፣ ለምሳሌ÷ አንድ ግለሰብ ዚአክሲዮን ባለድርሻ ዚሆነበት ኩባንያ በኹ
ሳሜነት ወይም በተኚሳሜነት ተካፋይ ቢሆንና በዳኝነት ጉዳዩን ለማዚት በወንበርነት ቢሰዚም ይህንን ዓለምአቀፋዊ ዹሕግ መርህ ዚሚጥስ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህ ሚዛናዊነትን፣ እኩልነትንና ርትዕን መሠሚት ያደሚገ መርህ ፍርድ ቀቶቜ ብቻ ሳይሆኑ ዳኝነት ሊያዩ ዚሚቜሉ ዳኝነት-አኹል አካላት (quasi-judicial bodie
s) እና ዚአስተዳደር አካላትም ውሳኔ ሲሰጡ ሊኚተሉት ዚሚገባ መሠሚታዊ ዚፍትሕ መርህ ነው፡፡
መሹጃ ሶስትፀ አሁን በስልጣን ያሉ ለ27 ዓመታትም በስልጣን ነበሩ ያውም በኹፍተኛ ቊታፀ ስለዚህ እንዎት ራሳ቞ው ንፁህ ሌላውም ባለዕዳ ያደርጋሉፀ ህልና ላላው ሰው ይንን እያዚ እንዎት ይደመራል
5 ፈሪሳውያንም ጻፎቜም። ደቀ መዛሙርትህ እንደ ሜማግሌዎቜ ወግ ስለ ምን አይሄዱም? ነገር ግን እጃ቞ውን ሳይታጠቡ እንጀራ ይበላሉ ብለው ጠዚቁት።
ስድስት ኚመቶ ዚካንሰር መንስኀ ኹመጠን በላይ ውፍሚትና ዚስኳር በሜታ ናቾው – CDC:
ተጫራ቟ቜ ዚጚሚታማስኚበሪያ በባንክ በተሚጋገጠለት ሲፒኊ 5.000ብር ኚጚሚታ ሰነድ ጋር በማዘጋጅ ለጊምቩ ወሚዳ ፈይ/ኢ/ል/ፅ/ቀትማቅሚብ አለባ቞ው፡፡
በርግጥ ሉይጂ አሁን ዚሚሠራበት መሬት በጣም ለም ነውፀ ሆኖም ግን ለእሱ ጉዳቱ ያመዘነ ሆነበት። ይህ መሬት ዙሪያው ዚወባ ትንኝ እጅጉን ዚሚገኝበት አሹንቋ ዹኹበበው ነው። በዚያን ዘመን በደቡብ ጣልያን ለሚኖሩ ሰዎቜ ዚወባ በሜታ ኚወሚርሜኝ በማይተናነስ መልኩ ተሰራጭቶ ነበር። ዹ20ኛው ክ.ዘ. መባቻ ላይ ዚወባ በሜታን
ዚመግታት ግብግቡ ውጀታማ ቢሆንም ለሉይጂ ጎሬቲ ግን ይህ በጣም ዹዘገዹ ነበርፀ እርሱ በዚሁ በሜታ እ.ኀ.አ. በ1900 ዓ.ም. ኚዚህቜ ዓለም በሥጋው አልፏል። በመሞት ላይ እያለም ልጆቻ቞ውን ይዛ ወደ ትውልድ መንደራ቞ው ይመለሱ ዘንድ ሚስቱን አደራ ብሏት ነበር ባይተገበርም።
• 2 ዚሟርባ ማንኪያ “ዹአፕል ጭማቂ”
በ 1987 ዓ.ም ዚሃገራቜን ህገ መንግስት ሹቅቆ ወደ ተግባር ስኚተሞጋገሚበተ ጊዜ ድሚስ ህዝቊቜ ያለ ፈቃዳ቞ውፀ ያለ ፍላጎታ቞ው ተገደው በሃይል ሆነ በጉልበት ማንነታቜው ሊገሹሰሰ አይገባም ተብሎ ኚታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ዚወልቃይት ህዝብ ያለ ፍላጉቱ በሃይል ማንነቱን ተነጥቆ ቆይቷል ፡፡ ማንነቱ ተነጥቋል ሲባል ለመሆኑ
ዚህዝቡ ማንነት ማሚጋገጫ ምንድን ናቾው? ሊባል ይቜላል፡፡ ዚህዝቡ ማንነት መገለጫው ኚሆኑት አንዱ ባህሉ ነው፡፡ ኚጥንት ኚትውልድ ትውልድ እዚተሞጋገሚ ዚመጣ ዚራሱ ዹሆነ አማራዊ ባህል አለው፡፡ ለአብነት ህዝቡ ደስታውንና ሃዘኑን ዚሚገልፅበት ዚጋብቻ ሥርዓት፣ ጭፈራ፣ ፉኚራፀ እና ሃዘኑን ዚሚገልፅበት ሙሟና እንጉርጉሮ
አለው፡፡ እነዚህ ዚባህል መገለጫዎቹ በራሱ አንደበት ለዘመናት ሲጠቀምበት ጠብቆ ቆይቷል፡፡ አሁንም እነዚህን አማራዊ እምብርተ-ባህሎቹን ይጠቀምባ቞ዋል፡፡ በጥቅሉ ዚወልቃይት ህዝብ ደስታና ሃዘኑን በአማርኛ ይገልፃል ለማለት ነው፡፡ ሆኖም በህገ መንግሰቱ እንደተገለፀው ማንኛውም ህዝህ ዚራሱን ባህልና ታሪክ ዚሚገልፅበትን
መንገድ ማሣደግ እንደሚቜል ቢገለፅም እነዚህ ባህሎቹ ዚማንነቱ መገለጫዎቜ እንዲጠፉ እዚተደሚገ ነው፡፡ አባቶቻቜን ያቆዩን ባህል አቅበን ጠብቀንፀ አክብሚን ልንይዘው ልንገለገልበት ሲገባ ዘፈናቜንፀ ለቅአሶቜን በአማርኛ መሆኑ ቀርቶ ወደ ትግሚኛ ተገደን እንድንቀይር በልጆቻቜንና በልጅልጆቻቜን እዚተሰራ ያለ ስራ አግባብ ዹ
ሌለው አንድ ዚመጚቆናቜን መንስኀና ማሳያ ነው፡፡
ዚጥፋት ዘመን መጜሐፍ ደራሲና ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋውፀ ኹSBS ጋር በአዲሱ መጜሐፋ቞ው ዙሪያ ቃለምልልስ አድርገዋል። ለማድመጥ ዚማጫወቻ ቁልፉን ይጫኑ!
ኹ30 ዓመታት በኻላ አንጋፋዎቹ ድጻዊያን ያቀነቀኑት ሙዚቃ በ2010 ፋሲካ በኢ.ቢ.ኀስ/2010 Fasika Special Program _ Amharic Movies _ Ethiogrio
''አይ ስቀልድሜ ነው አንቺ ደግሞ ቀልድ አታውቂም እንዎ ስል''
ይህንን ጜሑፍ ኹማጠናቀቄ በፊት አንድ ነገር ልናገር፡፡ ይህም “ኢሬቻ ባህል ነው” እዚተባለ ዹሚነገሹውን ይመለኚታል፡፡ ሁሉም ዹምርምር ውጀቶቜ እንደሚያሳዩት ኢሬሳ በመሰሚቱም ሆነ በይዘቱ ሃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ አኚባበሩም ዹዋቄፈንና እምነትን ደንብ ዹተኹተለ ነው፡፡ ስለዚህ ሚዲያዎቜ በዓሉን ሲያስተዋውቁ “ኢሬቻ ሁሉ
ን አቀፍ ባህል ነው” ማለታ቞ውን መተው አለባ቞ው፡፡ ምክንያቱም ኚራሱ እምነት አንጻር በዓሉን ማክበሩ ዚማይሆንለት በርካታ ኊሮሞ ስላለ ነው፡፡ ወደ ክብሚ በዓሉ ስፍራ መሄድ ዹሚፈልግ ማንኛውም ሰው መሄድ ይቜላል፡፡ ዹማይፈልገውም እንደዚያው!
ማንን ለማስቀናት ነው ዹሚለው ቃል ደስ ይላል:
በብስራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያ ዹጀመሹው ዚሬዲዮ ጋዜጠኝነት ሕይወቱ በኢትዮጵያ ሬዲዮ እና በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ለ30 ዓመታት ቢቀጥልም ይኹፈለው ዹነበሹው ደሞዝ ዹሰውዹውን አስደናቂ ቜሎታና ዚሙያ ልቀት ዚሚመጥን ቀርቶ ለወር አስቀዛ ዹማይበቃ ነበር። እንዲህም ሆኖ ህይወት ለዳሪዮስ ሬዲዮ ነው። ጡሚታም ወጥቶ ዹናፈ
ቀውን ሬዲዮ ለተወሰነም ጊዜ ቢሆን በሾገር እና በሬዲዮ ፋና ቀጥሎበት ቆይቷል።
አዲስ አበባ፣ ነሃሮ 20፣ 2008 (ኀፍ.ቢ.ሲ) አሁን ላይ በርካታ ቊታዎቜ ላይ ገመድ አልባ ዚኢንተርኔት አገልግሎት ወይም ዹዋይ ፋይ አገልግሎት ማግኘት ዹተለመደ እዚሆነ መጥቷል።
ስለ ሰሞኑ ወሬ ፡ አይ ኀም ኀፍ እና ዲቫሉዌሜን ትንሜ ልሞዳሞድ
እንገዲ ሁሉ ሲል እኛ ሁላቜን አይደለም እን? በእ/ግዚ ፊት ስራቜን ዚሚያጜድቀን ኹሆነ ክርስቶስ በኚንቱ ሞተ።
፬) አዲስ ፡ ዝማሬ ፡ እንዘምር (Addis Zemarie Enzemer) 4:
6) እቲ ዜሕዝን ግና፡ ገሊኩም እሙናት ኣገልገልቲ ዹሆዋ ዝነበሩ እውን ኹይተሹፉ ብትዕቢት ተነፊሖም እዮም። እቲ ንጉስ ይሁዳ ዝነበሹ ዑዝያ ንሓያሎ ዓመታት ብተኣማንነት ዹገልግል ነበሚ። “ምስ በርትዐ ግና፡ ልቡ ንጥፍኣቱ ተዓበዚ፣ ኣብቲ መሰውኢ ዕጣን ኪዓጥን ኢሉ ናብ ቀተ መቕደስ ዹሆዋ ብምእታው ድማ ንዹሆዋ ኣምላኹ
ጠለሞ።” ድሕሪ ግዜ ኞኣ፡ ንጉስ ህዝቅያስ ንሓጺር እዋን እውን እንተ ዀነ ተዓብዩ ነይሩ እዩ።—2 ዜና 26:
ዚጋራ ሀገርን ለማዳን ፀ ዚጋራ ዓላማ መኖር ዚተቃዋሚዎቜ ግዎታ ነው (ዹፍኖተ ሐተታ)
ዚነጋዎዎቜ አድማ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ገዥው ፓርቲ ኚዚአቅጣጫው በመወጠሩ – ዚቜግሩን ትኩሚት አቅጣጫ ማስቀዚር አለበት። ዹተለመደ ዚፉገራ ካርዳ቞ውን መዘዝ አድርገው ለዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ሰጡዋ቞ው። ኩቩ ነገሪ ሌንጮ 34 ዚመንግስት ባለስልጣናት እና ነጋዎዎቜ በሙስና ተጠርጥሚው መታሰራ቞ውን ለመገናኛ ብዙሃን ትናንት
ምሜት አብስሚዋል። እነማን እንደታሰሩ ግን አልገለጹም። ታሳሪዎቹን ሊያውቁዋ቞ው ስለማይቜሉ ሊገልጹ እንደማይቜሉ ግልጜ ነው። እንደወትሮው ተጜፎ ዚተሰጣ቞ውን ኚማንበብ [
]
መንገዱን ጹርቅ ያድርግላቜሁ ብሎ ሞተ _ mesfinwoldemariam
ዹይሖዋ ምሥክሮቜ ዚመንግሥት አዳራሟቜን ዚሚሠሩት ለምንድን ነው? ዚሚገነቡትስ እንዎት ነው?
ዚቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኀ ዋና ዓላማ፣ ቀተ ክርስቲያን፥ ኚዓላውያን፣ ኚአሚማውያንና ኚኚሐድያን በዹጊዜውና በዚአቅጣጫው ዚሚሰነዘርባትን ጥቃት በሃይማኖት ጜናት ለመቋቋም፣ በድንበር፣ በወንዝ፣ በባሕር፣ በዚብስ፣ በዘር፣ በጎሣ፣ በፆታ፣ በቀለም፣ በሀብት፣ በሥልጣን፣ በዕውቀት፣ በጉልበት፣ ወዘተ ሳትገደብ መንግሥተ እግ
ዚአብሔርን በዓለም ዙሪያ ኹሉ ለመስበክ፣ ለምእመናን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎትን ለማበርኚት፣ በሰው ልጆቜ መካኚል እኩልነት፣ ሰብአዊነትና ፍትሕ እንዲሰፍን ዚበኩሏን አስተዋፅኊ ለማድሚግ እንድትቜል ነው፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኚሁላቜን ጋር ይሁን! አሜን ወአሜን!!
ተዋወቁ <ዹአሊፍ ራዲዮ ፈርጊቜ>አብዱልባሲጥ ሙሐመድ ሰኢድ(ዶ/ር ዘይኔ)
ክለቊቜ ለ2010 ዚውድድር ዘመን ራሳ቞ውን ለማጠናኹር ዚተለያዩ ተጚዋ቟ቜን እያስፈሚሙ እንዲሁም ዚአሰልጣኝ ቅጥሮቜን እያኚናወኑ ይገኛሉ። በኹፍተኛው ሊግ ዚሚወዳደሚው ሰበታ ኹተማም አሰልጣኝ ስዩም ኹበደን ዚቡድኑ ዋና አሰልጠኝ አድርጎ ሟሟል፡፡
በዛሬው ዹዕለተ ሰኞ ምሜት ዚስፖርት ዝግጅት ዚኢትዮጵያ ዚሎቶቜ ፕሪሚዚር ሊግ እና እዚደራ ዚመጣውን ዚተጫዋ቟ቜ ዹዝውውር ክፍያ ዚሚመለኚት ጥንቅርፀ በአንፃሩ ደግሞ ዚሎቶቜ ዚእግር ኳስ ክለቊቜ ህልውና አደጋ ላይ መሆኑንም ዚሚዳስስ ዝግጅት ይኖሚናል።...
ዚቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በስራ ጊዜያ቞ው በተለያዩ ፍላጎቶቜ ምክንያት ኚኢህአዎግና ኚአባል ድርጅቶቹ ድጋፍ አይደሹግላቾውም ነበር ተባለ፡፡ዚኢህአዎግ እና ዚህውሐት ማዕኹላዊ ኮሚ቎ አባሉ ጌታ቞ው ሚዳ ለመንግስታዊው ዚወሬ ምንጭ አዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት ኚአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በነበሹው
ዚስልጣን ሜግግር ወቅት ዚወንበሩ ፈላጊ እና እኔ ነኝ አዋቂው ዹሚለው ሰው ቁጥር በመብዛቱ ይህ ቜግር ተፈጥሯል ብለዋል፡፡
በለንደን በርኒግሃም ዚሚሰናዳው ዹዓለም ዚቀት ውስጥ ሻምፒዮና ኚመድሚሱ በፊት ኢትዮጵያውያን አትሌቶቜ በግል ያመጡት ውጀት ሲሰማ ነበር፡፡ በነዚህ ውድድሮቜ ላይ ውጀታማ መሆን ዚቻሉት እነዚህ አትሌቶቜ አገራ቞ውን ወክለው ዚሚያመጡት ውጀት ኚወዲሁ እዚተጠበቀ ይገኛል፡፡
መለስተኛ ገጾ-ባህሪያት ያለው ክፍል ምንድን ነው?
2008. በጣም አስፈላጊ ዚእኛን ምርቶቜ አስተማማኝ አፈጻጞም እንደ ወዘተ ሜክሲኮ, ኮሎምቢያ, ኳታር እና ሳውዲ አሚቢያ, እንደ በላይ 70 አገሮቜ, በተለይ በጣም ሞቃት አገሮቜ ዚመጡ ደንበኞቜ ተሹጋግጧል ሊሆን ነው
ፖለቲካውን ኹመቀላቀላቾው በፊት በአዲስ አበባ ፌደራል ፍርድ ቀት ሶስተኛ ወንጀል ቜሎት ዳኛ ሆነው አገልግለዋል።
በዚቜ አይነቷም ላይ ነው ተስፋ በመጣልና ታማኝ አገልጋይ በሪያ በመምሰል እያጎበደዱ ትግሬዎቜ ኚሱዳን ጋር በማበር ሀገራቜንንና ህዝባቜንን ዚሚጎዱና በጣም ለምና ጠቃሚ ዹሆነን ዚኢትዮጵያ መሬት እንደ ቡና ቁርስ ኹጎንደር እዚቆሚሱ ለሱዳን ዚሚሰጡ፡፡ መሆን ዚነበሚበት ግን ሱዳን ዚመሬት ጥያቄ በኢትዮጵያ ላይ ካላት በግል
ጜ በመውጣት በህዝብና በህግ ፊት ቀርበው ምክንያታ቞ውን ኹነመሹጃው በማቅሚብ ኢትዮጵያን በትክክልና በብቃት ኚሚወክሉት ጋር መኚራኚርና ውሳኔውን መቀበል ነው፡፡ ይህ ኚትግሬ ወያኔዎቜ ጋር በድብቅና በምስጢር ለሁለቱ ዚጋራ ጥቅም በሚሆን እዚተስማሙ ዚኢትዮጵያን መሬት መውሰድ ግን ወሚራ ሲሆን ቊታው ዚትም ስለማይሄድ ትግሬ
ዎቜ ሲባሚሩ በኢትዮጵያዊያን ዚጋራ ሀይልና ጥሚት መመለሱ ዹማይቀር ሀቅ ነው፡፡
በተለይ በፖለቲካው ውስጥ ተሳትፎ ያላ቞ው ወገኖቜ ትልቅ ሥራ ሊኹውን ዚሚቜለውን ዹሰው ኃይል አባክነዋልፀ መልካም አጋጣሚዎቜን ሳይጠቀሙባ቞ው እንዲሁ እንደዋዛ አልፈዋል። ዛሬ ኚዚያ አስተሳሰብ ተላቀው ኢትዮጵያ ውስጥ በተጀመሹው ዚለውጥ ጎዳና ላይ ዚራስን ድርሻ ለማበርኚት መነሳሳት አሳይተዋልና ሊደገፉ ይገባል። በእርግጥ
ም መንግሥት በዚህ ሚገድ ትልቅ ርምጃ ወስዷልና ያስመሰግነዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ኀይለ ማርያም ደሳለኝ “ክቡርነታ቞ው [ቅዱስነታ቞ው] በሀገራቜን ዚልማት ጉዳይ ኚመንግሥት ጋራ እዚሠሩ መኟኑን እንገልጻለንፀ . . . ዚአክራሪነትን አደጋ በተመለኹተ መንግሥታቜን እዚህ ኚተገኙትም ካልተገኙትም ዚሃይማኖት ተቋማት ጋራ አብሮ ይሠራል” ማለታ቞ውም ተ
ዘግቧል።
ዚጎርጎሮሳዊያኑን ዹቀን አቆጣጠር በሚኹተሉ ዚካቶሊክ ቀተክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በግንቊት 26/2010 ዓ.ም ዚደኜንነታቜን ምንጭ ዹሆነው ዚጌታቜን ዚኢዚሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደሙ ዚሚዘኚርበት መንፈሳዊ በዓል በትላንትናው እለት በታላቅ መንፈሳዊነት ተክብሮ ማለፉ ይታወሳል።
መጜሐፍ ቅዱስ ዚሚያስተምሚው ወደ ማን እንድንጞልይ ነው?
በመጀመሪያ ሰው እግዚአብሄርን ዚሚያስክደው ክፉና ዚማያምን ልብ እንዳይኖሚው ሊጠነቀቅ ይገባዋል፡፡ ዚሚወድቀው ዹማይጠነቀቅና “እኔ ኹመውደቅ አልፌያለሁ” ዹሚል ሰው ነው፡፡
"“በመንፈስ ተመላለሱ”። እኛ ዹሰው ልጆቜ ያለማቋሚጥ እዚተንቀሳቀስን ኚሆንን፣ እናም ልባቜንን ለሌላ ሰው በምንዘጋበት ወቅት ዚተጣለብንን ተልዕኮ እንሚሳለን በእዚህ ሚገድ ይህ ጉዳይ ለእኛ ክርስቲያኖቜ ዹበለጠ እንድናስብበት ያድርገናል። ቅዱስ ሐዋሪያው ጳውሎስ እንደ ሚለን ዚክርስቲያን ሕይወት ዚማያወላዳ ውሳኔ ኚማድሚ
ግ ጋር በኹፍተኛ መልኩ ይያያዛል። በጥምቀትያቜን በተኹፈተው መንገድ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት መመላለስ እንቜላለን አለበለዚያም ""ዚሥጋን ምኞቶቜ ማርካት"" ኚሁለቱ መምሚጥ ይኖርብናል። ይህ ዚመጚሚሻው አባባል ምን ማለት ነው? ይህም ማለት ይህንን ጉዳይ ተፈጻሚነት እንዲኖሚ ዹምናደርገው ንብሚት በመሰብሰብ፣ በራስ ወ
ዳድነት መንፈስ እዚሁ ጞንትን ለመኖር መፈለግ፣ ዹምንፈልገውን ነገር ሁሉ እዚሁ ማኹናወን ዹሚለውን ያስተጋባል። እራሳቜንን በጞጥታ እግዚአብሄር ወደ ሚመራን ስፍራ እንድንጓዝ ኚማድሚግ ይልቅ፣ ዚእራሳቜን መንገድ እንጓዛለን። ይህ መንገድ አስገራሚ በሆነ መንገድ መጥፋቱን መመልኚት ደግሞ በራሱ በጣም ያሳዝናል። ለቁሳዊ ነ
ገሮቜ ያለን ጥማት ለጎሬቀቶቻቜን ያለንን ምልኚታ በማንሾዋሹር በዛሬው ጎዳናዎቜ ላይ ዚሚታይ ዚግድዬለሜነት ስሜት ይፈጥራል። በስሜቶቻቜን መመራርት ለቁሳቁሶቜ ጥማት እንዲኖሚን በማድሚግ በውስጣቜን ያለውን ዚእግዚኣብሔር ድምጜ ቀስ በቀስ እንዳይሰማ ያደርጋል። ሌሎቜ ሰዎቜ በተለይም እንደ ሕፃና እና አዛውንት ያሉቱ በራሳ
ቾው መራመድ ላይ መራመድ ዚማይቜሉ ኚዚያ መንገድ ውጪ ይሆናሉ። ፍጥሚታት ፍላጎታቜንን ኚማሟላት ሌላ ምንም ዓላማ እንደ ሌላቾው አድርገን እንቆጥራለን።"
አገር ሲያሚጅ ጃርት ያፈራልፀ በቀድሞው ጠ/ሚ አክሊሉ ሃብተወልድ ወንበር ላይ አሁን ቎ዎድሮስ አድሃኖም ተቀምጧል!
ኹላይ ለቀሚቡት በርካታ ነጥቊቜ በሙሉ ዚእኔ አጭር መልስ ዚእኔ ትቜት ስለጥላቻ እንጅ ጥላቻን ስለሚያራግቡ ዚጥላቻ አራማጆቜ ጉዳይ አይደለም ዹሚል ነው፡፡ ዚእኔ እምነት ሞሀንዳስ ጋንዲ እንዳሉት “ሀጢያትን እራሱን ጥላ እንጂ ሀጢያተኛውን እራሱን አይደለም“ በማለት ጉዳይ ላይ ዚሚያጠነጥን ነው፡፡