text
stringlengths
4
267
ይህን ዹማደርገው እስራኀላውያን አባቶቻ቞ው እንዳደሚጉት እነሱም በይሖዋ መንገድ በመሄድ መንገዱን ይጠብቁ እንደሆነና እንዳልሆነ ለመፈተን ነው።”
ስለዚህ ይሖዋ እነዚህ ብሔራት እዚያው እንዲኖሩ ፈቀደ። ወዲያውኑም አላስወጣ቞ውምፀ ለኢያሱም አሳልፎ አልሰጣ቞ውም።
ኚአቢሜሌክ በኋላ ዚዶዶ ልጅ፣ ዹፑሃ ልጅ ዚይሳኮር ሰው ዹሆነው ቶላ እስራኀልን ለማዳን ተነሳ። እሱም በኀፍሬም ተራራማ አካባቢዎቜ በምትገኘው በሻሚር ይኖር ነበር።
በእስራኀልም ውስጥ ለ23 ዓመት ፈራጅ ሆኖ አገለገለ። ኚዚያም ሞተፀ በሻሚርም ተቀበሚ።
ኚእሱም በኋላ ጊልያዳዊው ያኢር ተነሳፀ በእስራኀልም ውስጥ ለ22 ዓመት ፈራጅ ሆኖ አገለገለ።
ያኢር በ30 አህዮቜ ዚሚጋልቡ 30 ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩትፀ እነሱም እስኚ ዛሬ ድሚስ ሃዎትያኢር ተብለው ዚሚጠሩ 30 ኚተሞቜ ነበሯ቞ውፀ ኚተሞቹም ዚሚገኙት በጊልያድ ምድር ነው።
ኚዚያም ያኢር ሞተፀ በቃሞንም ተቀበሚ።
እስራኀላውያንም በይሖዋ ፊት እንደገና መጥፎ ነገር አደሚጉፀ ባአልን፣ ዚአስታሮትን ምስሎቜ፣ ዚአራምን አማልክት፣ ዚሲዶናን አማልክት፣ ዚሞዓብን አማልክት፣ ዚአሞናውያንን አማልክትና ዚፍልስጀማውያንን አማልክት ማገልገል ጀመሩ። ይሖዋን ተዉትፀ እሱንም አላገለገሉም።
ዹይሖዋም ቁጣ በእስራኀል ላይ ነደደፀ እነሱንም ለፍልስጀማውያንና ለአሞናውያን ሞጣ቞ው።
ስለሆነም በዚያ ዓመት እስራኀላውያንን አደቀቋ቞ውፀ ክፉኛም ጚቆኗ቞ውፀ ኚዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ በጊልያድ በሚገኘው በአሞራውያን ምድር ዚነበሩትን እስራኀላውያን በሙሉ ለ18 ዓመት ጚቆኗ቞ው።
በተጚማሪም አሞናውያን ይሁዳን፣ ቢንያምንና ዚኀፍሬምን ቀት ለመውጋት ዮርዳኖስን ይሻገሩ ነበርፀ እስራኀላውያንም እጅግ ተጹንቀው ነበር።
ኚዚያም እስራኀላውያን “አንተን አምላካቜንን ትተን ባአልን በማገልገላቜን በአንተ ላይ ኃጢአት ሠርተናል” በማለት ይሖዋ እንዲሚዳ቞ው ጮኹ።
ሆኖም ይሖዋ እስራኀላውያንን እንዲህ አላቾው፩ “ግብፃውያን፣ አሞራውያን፣ አሞናውያን፣ ፍልስጀማውያን፣
ሲዶናውያን፣ አማሌቃውያንና ምድያማውያን በጚቆኗቜሁ ጊዜ አላዳንኳቜሁም? ወደ እኔ ስትጮኹ ኚእጃ቞ው ታደግኳቜሁ።
እናንተ ግን እኔን ትታቜሁ ሌሎቜ አማልክትን አገለገላቜሁ። ዳግመኛ ዚማላድናቜሁም በዚህ ዚተነሳ ነው።
ወደመሚጣቜኋ቞ው አማልክት ሂዱና እንዲሚዷቜሁ ጠይቋ቞ው። በጭንቀታቜሁ ጊዜ እነሱ ያድኗቜሁ።”
እስራኀላውያን ግን ይሖዋን “ኃጢአት ሠርተናል። መልካም መስሎ ዚታዚህን ማንኛውንም ነገር አድርግብን። እባክህ፣ ዚዛሬን ብቻ አድነን” አሉት።
እነሱም ኚመካኚላ቞ው ባዕዳን አማልክትን አስወግደው ይሖዋን አገለገሉፀ በመሆኑም በእስራኀል ላይ እዚደሚሰ ዹነበሹውን መኚራ ሊታገሥ አልቻለም።
ኹጊዜ በኋላም አሞናውያን ተሰባስበው በጊልያድ ሰፈሩ። በመሆኑም እስራኀላውያን ተሰባስበው በምጜጳ ሰፈሩ።
ዚጊልያድ ሕዝብና መኳንንት እርስ በርሳ቞ው እንዲህ ተባባሉፊ “ኚአሞናውያን ጋር ዹሚደሹገውን ውጊያ ግንባር ቀደም ሆኖ ዚሚመራው ማን ነው? ይህ ሰው በጊልያድ ነዋሪዎቜ ሁሉ ላይ አለቃ ይሁን።”
አንድ ቀን ሳምሶን ወደ ጋዛ ሄደፀ በዚያም አንዲት ዝሙት አዳሪ አይቶ ወደ እሷ ገባ።
ኚዚያም ጋዛውያን “ሳምሶን እዚህ መጥቷል” ዹሚል ወሬ ደሚሳ቞ው። እነሱም ኚበውት በኹተማዋ በር ላይ ሌሊቱን ሙሉ አድፍጠው ሲጠባበቁ አደሩ። ለራሳ቞ውም “ጎህ ሲቀድ እንገድለዋለን” በማለት ሌሊቱን ሙሉ ድምፃ቞ውን አጥፍተው አደሩ።
ይሁንና ሳምሶን እስኚ እኩለ ሌሊት ድሚስ ተኛ። ኚዚያም እኩለ ሌሊት ላይ ተነስቶ ዹኹተማዋን በሮቜ ያዘፀ በሮቹን ኚነመቃኖቹና ኚነመቀርቀሪያዎቹ ነቀለ። በትኚሻው ኹተሾኹማቾውም በኋላ በኬብሮን ትይዩ እስኚሚገኘው ተራራ አናት ድሚስ ይዟቾው ወጣ።
ኹዚህ በኋላ ሳምሶን በሶሚቅ ሾለቆ ዚምትገኝ ደሊላ ዚምትባል አንዲት ሎት ወደደ።
ዚፍልስጀም ገዢዎቜም ወደ እሷ ቀርበው እንዲህ አሏትፊ “እስቲ አታለሜ እንዲህ ያለ ኹፍተኛ ጥንካሬ ዹሰጠው ምን እንደሆነ እንዲሁም እንዎት ልናሞንፈው፣ ልናስሚውና በቁጥጥር ሥር ልናውለው እንደምንቜል ለማወቅ ሞክሪ። ይህን ካደሚግሜ እያንዳንዳቜን 1,100 ዚብር ሰቅል እንሰጥሻለን።”
ኹጊዜ በኋላም ደሊላ ሳምሶንን “ዚታላቅ ኃይልህ ሚስጥር ምን እንደሆነ እንዲሁም አንተን በምን ማሰርና በቁጥጥር ሥር ማዋል እንደሚቻል እስቲ ንገሹኝ” አለቜው።
ሳምሶንም “ገና እርጥብ በሆኑ ባልደሚቁ ሰባት ጅማቶቜ ቢያስሩኝ እንደ ማንኛውም ሰው ደካማ እሆናለሁ” አላት።
በመሆኑም ዚፍልስጀም ገዢዎቜ ገና እርጥብ ዹሆኑ ያልደሚቁ ሰባት ጅማቶቜ አመጡላትፀ እሷም በጅማቶቹ አሰሚቜው።
እነሱም በውስጠኛው ክፍል ውስጥ አድፍጠው ይጠባበቁ ነበርፀ እሷም “ሳምሶን፣ ፍልስጀማውያን መጡብህ!” ብላ ጮኞቜ። በዚህ ጊዜ ሳምሶን ዹተፈተለ ዚበፍታ ክር እሳት ሲነካው በቀላሉ እንደሚበጣጠስ ጅማቶቹን በጣጠሳ቞ው። ዹኃይሉም ሚስጥር ሊታወቅ አልቻለም።
ደሊላም ሳምሶንን “አሞኝተኞኛል፣ ደግሞም ዋሜተኞኛል። እሺ አሁን በምን ልትታሰር እንደምትቜል እባክህ ንገሹኝ” አለቜው።
እሱም “ሥራ ላይ ባልዋሉ አዲስ ገመዶቜ ቢያስሩኝ እንደ ማንኛውም ሰው ደካማ እሆናለሁ” አላት።
ደሊላም አዲስ ገመዶቜ ወስዳ አሰሚቜውፀ ኚዚያም “ሳምሶን፣ ፍልስጀማውያን መጡብህ!” ብላ ጮኞቜ። (በዚህ ጊዜ ሁሉ በውስጠኛው ክፍል ውስጥ አድፍጠው ዚሚጠባበቁ ሰዎቜ ነበሩ።) ሳምሶንም ገመዶቹን ልክ እንደ ክር ኚእጆቹ ላይ በጣጠሳ቞ው።
ኹዚህ በኋላ ደሊላ ሳምሶንን “አሁንም አሞኘኞኝፀ ዋሞኞኝ። በምን ልትታሰር እንደምትቜል ንገሹኝ” አለቜው። እሱም “ዚራስ ፀጉሬን ሰባት ጉንጉኖቜ በመሾመኛ ላይ ኚድር ጋር አብሚሜ ሾምኛቾው” አላት።
በመሆኑም ደሊላ ጉንጉኖቹን በሾማኔ ዘንግ አጠበቀቻ቞ውፀ ኚዚያም “ሳምሶን፣ ፍልስጀማውያን መጡብህ!” ብላ ጮኞቜ። እሱም ኚእንቅልፉ ነቃፀ ዘንጉንና ድሩንም መዞ አወጣው።
እሷም “ልብህ ኚእኔ ጋር ሳይሆን እንዎት ‘እወድሻለሁ’ ትለኛለህ? ይኾው ሊስት ጊዜ አሞኘኞኝፀ ዚታላቁ ኃይልህን ሚስጥር አልነገርኹኝም” አለቜው።
ዕለት ዕለት ስለነዘነዘቜውና ለጭንቀት ስለዳሚገቜው ሞቱን እስኪመኝ ድሚስ ተመሚሚ።
በመጚሚሻም ዚልቡን ሁሉ አውጥቶ እንዲህ ሲል ነገራትፊ “ኚተወለድኩበት ጊዜ አንስቶ ለአምላክ ናዝራዊ ስለሆንኩ ራሎን ምላጭ ነክቶት አያውቅም። ፀጉሬን ኹተላጹሁ ኃይሌን አጣለሁፀ አቅምም አይኖሚኝምፀ እንደ ሌሎቜ ሰዎቜ ሁሉ እሆናለሁ።”
ደሊላም ሳምሶን ዚልቡን ሁሉ አውጥቶ እንደነገራት ስታውቅ “ዚልቡን ሁሉ አውጥቶ ስለነገሚኝ በቃ አሁን መምጣት ትቜላላቜሁ” በማለት ዚፍልስጀም ገዢዎቜን ወዲያውኑ አስጠራቻ቞ው። ዚፍልስጀም ገዢዎቜም ገንዘቡን ይዘው ወደ እሷ መጡ።
እሷም ሳምሶንን ጭኗ ላይ አስተኛቜውፀ ሰውዹውንም ጠርታ ዚራስ ፀጉሩን ሰባት ጉንጉኖቜ እንዲላጫ቞ው አደሚገቜ። ኚዚያ በኋላ ኃይሉ ኚእሱ ስለተለዚ በቁጥጥሯ ሥር አዋለቜው።
እሷም “ሳምሶን፣ ፍልስጀማውያን መጡብህ!” አለቜው። በዚህ ጊዜ ኚእንቅልፉ ነቅቶ “እንደ ሌላው ጊዜ እወጣለሁፀ ራሎንም ነፃ አደርጋለሁ” አለ። ሆኖም ይሖዋ እንደተወው አላወቀም ነበር።
በመሆኑም ፍልስጀማውያን ይዘው ዓይኖቹን አወጡ። ኚዚያም ወደ ጋዛ ይዘውት በመውሚድ ኚመዳብ በተሠሩ ሁለት ዚእግር ብሚቶቜ አሰሩትፀ እሱም እስር ቀት ውስጥ እህል ፈጪ ሆነ።
ሆኖም ተላጭቶ ዹነበሹው ዚሳምሶን ፀጉር እንደገና ማደግ ጀመሚ።
ዚፍልስጀም ገዢዎቜ “አምላካቜን ጠላታቜንን ሳምሶንን በእጃቜን አሳልፎ ሰጠን!” በማለት ለአምላካ቞ው ለዳጎን ታላቅ መሥዋዕት ለመሠዋትና ለመደሰት አንድ ላይ ተሰብስበው ነበር።
ሕዝቡም ሳምሶንን ባዩት ጊዜ “አምላካቜን ምድራቜንን ያጠፋውንና ብዙ ወገኖቻቜንን ዚገደለብንን ጠላታቜንን በእጃቜን አሳልፎ ሰጠን” በማለት አምላካ቞ውን አወደሱ።
እነሱም ልባ቞ው ሐሎት በማድሚጉ “እስቲ ሳምሶንን ጥሩትና ትንሜ ያዝናናን” አሉ። በመሆኑም እንዲያዝናና቞ው ሳምሶንን ኚእስር ቀት ጠሩትፀ በዓምዶቹም መካኚል አቆሙት።
ኚዚያም ሳምሶን እጁን ይዞት ዹነበሹውን ልጅ “ቀቱ ዚቆመባ቞ውን ዓምዶቜ አስይዘኝና ልደገፍባ቞ው” አለው።
(እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቀቱ በወንዶቜና በሎቶቜ ተሞልቶ ነበር። ዚፍልስጀም ገዢዎቜም በሙሉ እዚያ ነበሩፀ በተጚማሪም ሳምሶን ሕዝቡን ሲያዝናና ይመለኚቱ ዚነበሩ 3,000 ወንዶቜና ሎቶቜ ጣሪያው ላይ ነበሩ።)
ሳምሶንም እንዲህ በማለት ወደ ይሖዋ ጮኞፊ “ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ እባክህ አስበኝፀ አምላክ ሆይ፣ እባክህ ለአሁን ብቻ አንድ ጊዜ ብርታት ስጠኝና ኚሁለቱ ዓይኖቌ ስለ አንዱ ፍልስጀማውያንን ልበቀላ቞ው።”
ኚዚያም ሳምሶን ቀቱን ደግፈው ያቆሙትን መሃል ላይ ዚሚገኙትን ሁለቱን ዓምዶቜ፣ አንዱን በቀኝ እጁ ሌላውን ደግሞ በግራ እጁ አቅፎ ተደገፈባ቞ው።
እሱም “ኚፍልስጀማውያን ጋር ልሙት!” ብሎ ጮኞ። ኚዚያም ዓምዶቹን ባለ በሌለ ኃይሉ ገፋ቞ውፀ ቀቱም በገዢዎቹና በውስጡ በነበሩት ሰዎቜ ሁሉ ላይ ወደቀ። በመሆኑም ሳምሶን በሕይወት ሳለ ኹገደላቾው ሰዎቜ ይልቅ በሞተበት ጊዜ ዹገደላቾው ሰዎቜ በለጡ።
በኋላም ወንድሞቹና ዚአባቱ ቀተሰቊቜ በሙሉ ሊወስዱት ወደዚያ ወሚዱ። እነሱም ወስደው በጟራ እና በኀሜታዖል መካኚል በሚገኘው በአባቱ በማኑሄ ዚመቃብር ስፍራ ቀበሩት። እሱም በእስራኀል ውስጥ ለ20 ዓመት ፈራጅ ሆኖ አገለገለ።
በዚያን ቀን ዲቊራ ኚአቢኖዓም ልጅ ኚባርቅ ጋር ሆና ይህን መዝሙር ዘመሚቜፊ
“በእስራኀል ስላለው ዹተለቀቀ ፀጉር፣ሕዝቡም ፈቃደኛ ስለሆነ፣ይሖዋን አወድሱ!
እናንተ ነገሥታት ስሙ! እናንተ ገዢዎቜ ጆሯቜሁን ስጡ! ለይሖዋ እዘምራለሁ። ለእስራኀል አምላክ ለይሖዋ ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁ።
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ኹሮይር በወጣህ ጊዜ፣ኚኀዶም ክልል እዚገሰገስክ በመጣህ ጊዜ፣ምድር ተናወጠቜፀ ሰማያትም ውኃ አወሚዱፀደመናትም ውኃ አንዠቀዠቁ።
ተራሮቜ በይሖዋ ፊት ቀለጡ፣ሲናም ሳይቀር በእስራኀል አምላክ በይሖዋ ፊት ቀለጠ።
በአናት ልጅ በሻምጋር ዘመን፣በኢያዔል ዘመን ጎዳናዎቹ ጭር ያሉ ነበሩፀተጓዊቜም በውስጥ ለውስጥ መንገዶቜ ይሄዱ ነበር።
እኔ ዲቊራ እስክነሳ ድሚስ፣እኔ በእስራኀል እናት ሆኜ እስክነሳ ድሚስ፣ዚመንደር ነዋሪዎቜ ኚእስራኀል ደብዛ቞ው ጠፋ።
እነሱ አዳዲስ አማልክትን መሚጡፀበበሮቹም ላይ ጊርነት ነበር። በ40,000 ዚእስራኀል ወንዶቜ መካኚል፣አንድ ጋሻ ወይም አንድ ጩር ሊታይ አልቻለም።
ልቀ ኚእስራኀል አዛዊቜ፣ኚሕዝቡ ጋር በፈቃደኝነት ኚወጡት ጋር ነው። ይሖዋን አወድሱ!
እናንተ፣ ነጣ ባሉ ቡናማ አህዮቜ ዚምትጋልቡ፣እናንተ፣ ባማሩ ምንጣፎቜ ላይ ዚምትቀመጡ፣እናንተ፣ በመንገድ ላይ ዚምትሄዱ፣ይህን ልብ በሉ!
ዹውኃ ቀጂዎቜ ድምፅ በውኃ መቅጃው ስፍራ ተሰማፀእነሱም በዚያ ዹይሖዋን ዚጜድቅ ሥራዎቜ፣በእስራኀል መንደሮቜ ውስጥ ዚሚኖሩ ሕዝቊቹን ዚጜድቅ ሥራዎቜ መተሹክ ጀመሩ። ዹይሖዋም ሕዝቊቜ ወደ በሮቹ ወሚዱ።
ዲቊራ ሆይ፣ ንቂ፣ ንቂ! ንቂ፣ ንቂ፣ መዝሙርም ዘምሪ! ዚአቢኖዓም ልጅ ባርቅ ሆይ፣ ተነስ! ምርኮኞቜህን እዚመራህ ሂድ!
ዚተሚፉትም ሰዎቜ ወደ መኳንንቱ ወሚዱፀዚይሖዋ ሕዝቊቜ ኃያላኑን ለመውጋት ወደ እኔ ወሚዱ።
 በሾለቆው ዚነበሩ ሰዎቜ ምንጫ቞ው ኀፍሬም ነበርፀቢንያም ሆይ፣ እነሱ በሕዝቊቜህ መካኚል እዚተኚተሉህ ነው። ኚማኪር አዛዊቜ፣ኚዛብሎንም ዚመልማዮቜን በትር ዚያዙ ሰዎቜ ወሚዱ።
ዚይሳኮር መኳንንት ኚዲቊራ ጋር ነበሩፀእንደ ይሳኮር ሁሉ ባርቅም ኚእሷ ጋር ነበር። እሱም በእግር ወደ ሾለቋማው ሜዳ ተላኚ። ዚሮቀል ቡድኖቜ ልባ቞ው በእጅጉ አመንትቶ ነበር።
አንተ በመንታ ጭነት መካኚል ዚተቀመጥኚው ለምንድን ነው?ለመንጎቹ ዋሜንታ቞ውን ሲነፉ ለማዳመጥ ነው? ዚሮቀል ቡድኖቜ እንደሆነ ልባ቞ው በእጅጉ አመንትቷል።
ጊልያድ ኚዮርዳኖስ ማዶ አርፎ ተቀምጧልፀዳን ኚመርኚቊቜ ጋር ዹተቀመጠው ለምንድን ነው? አሮር በባሕር ዳርቻ ላይ ሥራ ፈቶ ተቀምጧልፀበወደቊቹም ላይ ይኖራል።
ዛብሎን እስኚ ሞት ድሚስ ሕይወቱን ለአደጋ ዚሚያጋልጥ ሕዝብ ነበርፀንፍታሌምም ቢሆን በገላጣ ኮሚብቶቜ ላይ ነው።
ነገሥታት መጡፀ ተዋጉምፀበዚያን ጊዜ ዹኹነአን ነገሥታት፣በመጊዶ ውኃዎቜ አጠገብ በታአናክ ተዋጉ። ምንም ብር ማርኹው አልወሰዱም።
ኚዋክብት ኹሰማይ ተዋጉፀበምሕዋራ቞ው ላይ ሆነው ኚሲሳራ ጋር ተዋጉ።
ዚቂሟን ወንዝ፣ጥንታዊው ወንዝ፣ ዚቂሟን ወንዝ ጠራርጎ ወሰዳ቞ው። ነፍሮ ሆይ፣ ብርቱዎቹን ሚገጥሜ።
ዚፈሚሶቜ ኮ቎ ሲሚግጥ ዹተሰማው ያን ጊዜ ነበር፣ድንጉላ ፈሚሶቹ በኃይል ይጋልቡ ነበር።
ዹይሖዋ መልአክ እንዲህ አለ፩ ‘መሮዝን እርገሙፀነዋሪዎቿንም እርገሙ፣ይሖዋን ለመርዳት አልመጡምና፣ይሖዋን ለመርዳት ኚኃያላኑ ጋር አልመጡም።’
ዹቄናዊው ዚሄቀር ሚስት ኢያዔልኚሎቶቜ ሁሉ እጅግ ዚተባሚኚቜ ነቜፀ በድንኳን ኚሚኖሩ ሎቶቜ ሁሉ ይልቅ ዚተባሚኚቜ ነቜ።
ውኃ ጠዚቀ፣ ወተት ሰጠቜው። ለመኳንንት በሚቀርብበት ጎድጓዳ ሳህን እርጎ ሰጠቜው።
እጇን ዘርግታ ዚድንኳን ካስማ አነሳቜ፣በቀኝ እጇም ዚሠራተኛ መዶሻ ያዘቜ። ሲሳራንም ቞ነኚሚቜው፣ ጭንቅላቱንም ፈሚኚሰቜው፣ሰሪሳራውንም ተሚኚኚቜውፀ በሳቜው።
እሱም በእግሮቿ መካኚል ተደፋፀ በወደቀበት በዚያው ቀሚፀበእግሮቿ መካኚል ተደፋ፣ ወደቀፀእዚያው በተደፋበት ተሾንፎ ቀሚ።
አንዲት ሎት በመስኮት ተመለኚተቜ፣ዚሲሳራ እናት በፍርግርጉ አጮልቃ ወደ ውጭ ተመለኚተቜ፣‘ዚጊር ሠሚገሎቹ ሳይመጡ ለምን ዘገዩ? ዚሠሚገሎቹ ኮ቎ ድምፅስ ምነው ይህን ያህል ዘገዹ?’
ጥበበኛ ዚሆኑት ዚተኚበሩ ወይዛዝርቷ ይመልሱላታልፀአዎ፣ እሷም ለራሷ እንዲህ ትላለቜ፣
‘ያገኙትን ምርኮ እዚተኚፋፈሉ መሆን አለበት፣ለእያንዳንዱ ተዋጊ አንድ ልጃገሚድ እንዲያውም ሁለት ልጃገሚዶቜ፣ለሲሳራም ኚምርኮው ላይ ቀለም ዚተነኚሩ ልብሶቜ፣ አዎ ቀለም ዚተነኚሩ ልብሶቜ፣ምርኮውን ለማሚኩት ሰዎቜ አንገት፣ቀለም ዹተነኹሹ ባለ ጥልፍ ልብስ፣ እንዲያውም ሁለት ባለ ጥልፍ ልብስ እዚተሰጠ ነው።’
ይሖዋ ሆይ፣ ጠላቶቜህ ሁሉ ይጥፉ፣አንተን ዚሚወዱ ግን ደምቃ እንደምትወጣ ፀሐይ ይሁኑ።” ኚዚያ በኋላ ምድሪቱ ለ40 ዓመት አሚፈቜ።
ኚዚያም ሳምሶን ወደ ቲምና ወሚደፀ በቲምናም አንዲት ፍልስጀማዊት ሎት አዚ።
ወጥቶም አባቱንና እናቱን “በቲምና ያለቜ አንዲት ፍልስጀማዊት ዓይኔን ማርካዋለቜፀ እሷን እንድታጋቡኝ እፈልጋለሁ” አላ቞ው።
ሆኖም አባቱና እናቱ “ኚዘመዶቜህና ኚእኛ ሕዝብ መካኚል ለአንተ ዚምትሆን ሎት አጥተህ ነው? ዚግድ ሄደህ ካልተገሚዙት ፍልስጀማውያን መካኚል ሚስት ማግባት አለብህ?” አሉት። ሳምሶን ግን አባቱን “ልቀን ዚማሚኚቜው እሷ ስለሆነቜ እሷን አጋባኝ” አለው።
በዚያን ጊዜ በእስራኀል ላይ ይገዙ ዚነበሩት ፍልስጀማውያን ስለነበሩ አባቱና እናቱ ነገሩ ኹይሖዋ መሆኑንና እሱም ኚፍልስጀማውያን ጋር ግጭት ዚሚፈጠርበትን አጋጣሚ እዚፈለገ እንደነበር አላወቁም።
ስለዚህ ሳምሶን ኚአባቱና ኚእናቱ ጋር ወደ ቲምና ወሚደ። በቲምና ወዳለው ዹወይን እርሻ ሲደርስም አንድ ደቩል አንበሳ እያገሳ መጣበት።
ኚዚያም ዹይሖዋ መንፈስ ኃይል ሰጠውፀ አንድ ሰው በባዶ እጁ ዹፍዹልን ጠቊት ለሁለት እንደሚገነጥል እሱም አንበሳውን ለሁለት ገነጠለው። ሆኖም ያደሚገውን ነገር ለአባቱም ሆነ ለእናቱ አልነገራ቞ውም።
ኚዚያም ወርዶ ሎቲቱን አነጋገራትፀ አሁንም ዚሳምሶን ልብ በእሷ እንደተማሚኚ ነበር።
ኹተወሰነ ጊዜ በኋላም ወደ ቀቱ ሊያመጣት ተመልሶ ሲሄድ ዚአንበሳውን በድን ለማዚት ኚመንገድ ዞር አለፀ በአንበሳውም በድን ውስጥ ዚንብ መንጋና ማር ነበር።
እሱም ማሩን ዛቅ አድርጎ መዳፉ ላይ በማድሚግ በመንገድ ላይ እዚበላ ሄደ። ኚአባቱና ኚእናቱ ጋር እንደተገናኘም ኚማሩ ሰጣ቞ውፀ እነሱም በሉ። ሆኖም ማሩን ዹወሰደው ኚአንበሳ በድን ውስጥ እንደሆነ አልነገራ቞ውም ነበር።
አባቱም ወደ ሎቲቱ ወሚደፀ ሳምሶንም በዚያ ግብዣ አዘጋጀፀ ምክንያቱም ወጣቶቜ እንዲህ ዚማድሚግ ልማድ ነበራ቞ው።
እነሱም ባዩት ጊዜ አብሚውት እንዲሆኑ 30 ሚዜዎቜን አመጡ።
ሳምሶንም እንዲህ አላቾው፩ “እስቲ አንድ እንቆቅልሜ ልንገራቜሁ። ግብዣው በሚቆይበት በዚህ ሰባት ቀን ውስጥ ፍቺውን ካወቃቜሁና መልሱን ኚነገራቜሁኝ 30 ዚበፍታ ልብሶቜንና 30 ዚክት ልብሶቜን እሰጣቜኋለሁ።
መልሱን ልትነግሩኝ ካልቻላቜሁ ግን 30 ዚበፍታ ልብሶቜንና 30 ዚክት ልብሶቜን ትሰጡኛላቜሁ።” እነሱም “እንቆቅልሜህን ንገሚንፀ እስቲ እንስማው” አሉት።
እሱም እንዲህ አላቾው፩ “ኹበላተኛው መብል ወጣፀ ኚብርቱውም ውስጥ ጣፋጭ ነገር ወጣ።” እነሱም እስኚ ሊስት ቀን ድሚስ እንቆቅልሹን ሊፈቱት አልቻሉም።
በአራተኛውም ቀን ዚሳምሶንን ሚስት እንዲህ አሏትፊ “ባልሜን አታለሜ ዚእንቆቅልሹን ፍቺ እንዲነግሚን አድርጊ። አለዚያ አንቺንም ሆነ ዚአባትሜን ቀት በእሳት እናቃጥላለን። እዚህ ዚጋበዛቜሁን ንብሚታቜንን ልትዘርፉን ነው?”
ዚሳምሶንም ሚስት ላዩ ላይ እያለቀሰቜ “አንተ ትጠላኛለህፀ ደግሞም አትወደኝም። ለሕዝቀ አንድ እንቆቅልሜ ነግሹሃቾው ነበርፀ መልሱን ግን ለእኔ አልነገርኹኝም” አለቜው። እሱም በዚህ ጊዜ “እንዎ፣ ለገዛ አባ቎ና እና቎ እንኳ አልነገርኳ቞ውም! ታዲያ ለአንቺ ለምን እነግርሻለሁ?” አላት።
እሷ ግን ግብዣው እስኚቆዚበት እስኚ ሰባተኛው ቀን ድሚስ ስታለቅስበት ሰነበተቜ። በመጚሚሻም አጥብቃ ስለነዘነዘቜው በሰባተኛው ቀን ነገራት። እሷም ዚእንቆቅልሹን ፍቺ ለሕዝቧ ነገሚቜ።
ዹኹተማዋም ሰዎቜ ሳምሶንን በሰባተኛው ቀን ፀሐይዋ ኚመጥለቋ በፊት እንዲህ አሉትፊ “ኹማር ይልቅ ዚሚጣፍጥ ምን ተገኝቶ?ኚአንበሳስ ይልቅ ዚበሚታ ኚዚት መጥቶ?” እሱም መልሶ እንዲህ አላቾው፩ “በጊደሬ ባላሚሳቜሁ፣እንቆቅልሌን ባልፈታቜሁ።”