text
stringlengths
4
267
በኋላም አቢሎሎም ኚዳዊት አገልጋዮቜ ጋር ድንገት ተገናኘ። አቢሎሎም በበቅሎ ላይ ተቀምጩ ይሄድ ነበርፀ በቅሎዋም ጥቅጥቅ ያለ ቅርንጫፍ ባለው አንድ ትልቅ ዛፍ ሥር ስታልፍ ዛፉ ዚአቢሎሎምን ፀጉር ያዘውፀ በመሆኑም ዚተቀመጠባት በቅሎ ስታልፍ እሱ አዹር ላይ ተንጠልጥሎ ቀሚ።
ኚዚያም አንድ ሰው ይህን አይቶ ለኢዮዓብ “አቢሎሎምን አንድ ትልቅ ዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ አዚሁት!” ብሎ ነገሚው።
በዚህ ጊዜ ኢዮዓብ ይህን ዹነገሹውን ሰው “እና ካዚኞው ያኔውኑ መትተህ መሬት ላይ ያልጣልኚው ለምንድን ነው? እንዲህ ብታደርግ ኖሮ አሥር ሰቅል ብርና ቀበቶ እሞልምህ ነበር” አለው።
ሰውዹው ግን ኢዮዓብን እንዲህ አለው፩ “1,000 ዚብር ሰቅል ቢሰጠኝ እንኳ በንጉሡ ልጅ ላይ እጄን አላነሳምፀ ምክንያቱም ንጉሡ አንተን፣ አቢሳንና ኢታይን ‘ማናቜሁም ብትሆኑ በወጣቱ በአቢሎሎም ላይ ጉዳት እንዳታደርሱበት ተጠንቀቁ’ ብሎ ሲያዛቜሁ ሰምተናል።
ትእዛዙን በመተላለፍ ዹልጁን ሕይወት አጥፍቌ ቢሆን ኖሮ ይህ ጉዳይ ኚንጉሡ ተሰውሮ ሊቀር አይቜልም ነበርፀ አንተም ብትሆን ልታስጥለኝ አትቜልም።”
ኢዮዓብም “ኹዚህ በላይ ኹአንተ ጋር ጊዜ አላጠፋም!” አለው። ኚዚያም ሊስት ቀስቶቜ ይዞ በመሄድ አቢሎሎም በትልቁ ዛፍ መሃል ተንጠልጥሎ ገና በሕይወት እያለ ቀስቶቹን ልቡ ላይ ሰካ቞ው።
ኚዚያም ኚኢዮዓብ ጋሻ ጃግሬዎቜ አሥሩ መጥተው አቢሎሎምን መትተው ገደሉት።
ኢዮዓብም ቀንደ መለኚት ነፋፀ ሰዎቹም እስራኀላውያንን ኚማሳደድ ተመለሱፀ በዚህ መንገድ ኢዮዓብ ሰዎቹን አስቆማ቞ው።
እነሱም አቢሎሎምን ወስደው ጫካው ውስጥ በሚገኝ አንድ ትልቅ ጉድጓድ ውስጥ ጣሉትፀ በላዩም ላይ በጣም ትልቅ ዚድንጋይ ቁልል ኚመሩበት። እስራኀላውያንም በሙሉ ወደዚቀታ቞ው ሞሹ።
አቢሎሎም በሕይወት ሳለ “ስሜ ዚሚታወስበት ልጅ ዹለኝም” በማለት በንጉሡ ሾለቆ ለራሱ ዓምድ አቁሞ ነበር። ዓምዱንም በራሱ ስም ሰይሞት ነበርፀ እስኚ ዛሬም ድሚስ ዚአቢሎሎም ሐውልት በመባል ይጠራል።
ዚሳዶቅ ልጅ አኪማዓስም “ይሖዋ ንጉሡን ኚጠላቶቹ እጅ ነፃ በማውጣት ስለፈሚደለት እባክህ እዚሮጥኩ ሄጄ ወሬውን ልንገሹው” አለ።
ኢዮዓብ ግን “ዛሬ ወሬውን ዚምትነግሚው አንተ አይደለህም። ወሬውን ሌላ ቀን ትነግሚዋለህፀ ዚንጉሡ ልጅ ስለ ሞተ ዛሬ ወሬውን መናገር ዚለብህም” አለው።
ኚዚያም ኢዮዓብ አንድ ኩሻዊ ጠርቶ “ሂድ፣ ያዚኞውን ነገር ለንጉሡ ንገሹው” አለው። በዚህ ጊዜ ኩሻዊው ለኢዮዓብ ኹሰገደ በኋላ እዚሮጠ ሄደ።
ዚሳዶቅ ልጅ አኪማዓስም እንደገና ኢዮዓብን “እባክህ፣ ዚመጣው ይምጣ እኔም ኩሻዊውን ተኚትዬ ልሩጥ” አለው። ሆኖም ኢዮዓብ “ልጄ ሆይ፣ ዚምትናገሚው ነገር ሳይኖር ለምን ትሮጣለህ?” አለው።
እሱ ግን አሁንም “ምንም ይሁን ምን፣ እባክህ ልሩጥ” አለው። ስለዚህ ኢዮዓብ “በቃ ሩጥ!” አለው። አኪማዓስም ዚዮርዳኖስን አውራጃ አቋርጩ ዚሚያልፈውን መንገድ ይዞ መሮጥ ጀመሚፀ በኋላም ኩሻዊውን አልፎት ሄደ።
በዚህ ጊዜ ዳዊት በሁለቱ ዹኹተማዋ በሮቜ መካኚል ተቀምጩ ነበርፀ ጠባቂውም ኚቅጥሩ ጋር ተያይዞ ወደተሠራው ዚበሩ ሰገነት ወጣ። ቀና ብሎም ሲመለኚት ብቻውን ዚሚሮጥ አንድ ሰው አዚ።
ጠባቂውም ተጣርቶ ይህንኑ ለንጉሡ ነገሚውፀ ንጉሡም “ብቻውን ኹሆነ ወሬ ይዞ ዚመጣ መሆን አለበት” አለ። ሰውዹውም እዚቀሚበ ሲመጣ
ጠባቂው ሌላ ሰው ሲሮጥ ተመለኚተ። በመሆኑም ዹበር ጠባቂውን ተጣርቶ “ይኾው ሌላም ሰው ብቻውን እዚሮጠ በመምጣት ላይ ነው!” አለው። ንጉሡም “ይህም ሰው ቢሆን ወሬ ይዞ ዚመጣ መሆን አለበት” አለ።
ጠባቂውም “ዚመጀመሪያው ሰው አሯሯጥ ዚሳዶቅን ልጅ ዚአኪማዓስን አሯሯጥ ይመስላል” አለፀ በመሆኑም ንጉሡ “እሱማ ጥሩ ሰው ነውፀ ምሥራቜ ሳይዝ አይመጣም” አለው።
አኪማዓስም ንጉሡን ተጣርቶ “ሁሉም ነገር ሰላም ነው!” አለው። ኚዚያም በግንባሩ መሬት ላይ ተደፍቶ ለንጉሡ ሰገደ። ቀጥሎም “በጌታዬ በንጉሡ ላይ ያመፁትን ሰዎቜ አሳልፎ ዹሰጠህ አምላክህ ይሖዋ ይወደስ!” አለ።
ሆኖም ንጉሡ “ለመሆኑ ወጣቱ አቢሎሎም ደህና ነው?” አለው። በዚህ ጊዜ አኪማዓስ “ኢዮዓብ ዚንጉሡን አገልጋይና እኔን አገልጋይህን በላኹ ጊዜ ኹፍተኛ ትርምስ አይቻለሁፀ ምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም” አለ።
ንጉሡም “እሺ፣ እልፍ በልና እዚያ ቁም” አለው። እሱም እልፍ ብሎ ቆመ።
ኚዚያም ኩሻዊው ደሚሰፀ እሱም “ጌታዬ ንጉሡ፣ ያመጣሁትን ይህን ወሬ ይስማፊ ዛሬ ይሖዋ፣ በአንተ ላይ ካመፁብህ ሰዎቜ ሁሉ እጅ ነፃ በማውጣት ፈርዶልሃል” አለ።
ይሁንና ንጉሡ ኩሻዊውን “ለመሆኑ ወጣቱ አቢሎሎም ደህና ነው?” አለው። በዚህ ጊዜ ኩሻዊው “ዚጌታዬ ዚንጉሡ ጠላቶቜ ሁሉና በአንተ ላይ ጉዳት ለማድሚስ ያመፁብህ ሁሉ እንደዚያ ወጣት ይሁኑ!” አለ።
ይህም ንጉሡን ሚበሞውፀ በውጭው በር ሰገነት ላይ ወዳለው ክፍልም ወጥቶ አለቀሰፀ ወዲያ ወዲህ እያለም “ልጄ አቢሎሎም፣ ልጄ፣ ልጄ አቢሎሎም! ምነው በአንተ ፋንታ እኔ በሞትኩፀ ልጄ አቢሎሎም፣ ልጄ!” ይል ነበር።
ዚዳዊት ዚመጚሚሻ ቃላት እነዚህ ናቾው፩ “ዚእሎይ ልጅ ዚዳዊት ቃል፣ኚፍ ኹፍ ዹተደሹገው ሰው ቃል፣ዚያዕቆብ አምላክ ዚቀባው፣ዚእስራኀል መዝሙሮቜ ተወዳጅ ዘማሪ።
ዹይሖዋ መንፈስ በእኔ ተናገሚፀቃሉ በአንደበቮ ላይ ነበሚ።
ዚእስራኀል አምላክ ተናገሚ፣ዚእስራኀል ዓለት እንዲህ አለኝ፩ ‘ዹሰው ልጆቜን ዹሚገዛው ጻድቅ ሲሆን፣አምላክን በመፍራት ሲገዛ፣
ፀሐይ በምትፈነጥቅበት ጊዜ እንደሚኖሚው ዚማለዳ ብርሃን፣ደመና እንደሌለበት ማለዳ ይሆናል። ሣርን ኚምድር እንደሚያበቅል፣ዝናብ ካባራ በኋላ ፍንትው ብሎ እንደሚወጣ ዹፀሐይ ብርሃን ነው።’
ዚእኔስ ቀት በአምላክ ፊት እንዲሁ አይደለም? እሱ ኚእኔ ጋር ዘላለማዊ ቃል ኪዳን ገብቷልናፀቃል ኪዳኑም ዚተስተካኚለና አስተማማኝ ነው። ምክንያቱም ይህ ለእኔ ዹተሟላ መዳንና ፍጹም ደስታ ነውፀደግሞስ ቀ቎ እንዲለመልም ዚሚያደርገው ለዚህ አይደለም?
ዚማይሚቡ ሰዎቜ ሁሉ ልክ እንደ እሟህ ቁጥቋጊ ወዲያ ይጣላሉፀበእጅ ሊሰበሰቡ አይቜሉምና።
ዚሚነካ቞ው ሰውዚብሚት መሣሪያ መታጠቅና ዹጩር ዘንግ መያዝ አለበትፀእነሱም ባሉበት ሙሉ በሙሉ በእሳት መቃጠል አለባ቞ው።”
ዚዳዊት ኃያላን ተዋጊዎቜ ስም ይህ ነው፩ ዚሊስቱ መሪ ዹሆነው ታህክሞናዊው ዮሌብባሌቀት። እሱም ጊሩን ሰብቆ በአንድ ጊዜ 800 ሰው ገደለ።
ኚእሱ ቀጥሎ ዹአሆሐይ ልጅ ዹሆነው ዚዶዶ ልጅ አልዓዛር ነበርፀ እሱም ፍልስጀማውያንን በተገዳደሩበት ጊዜ ኚዳዊት ጋር ኚነበሩት ሊስት ኃያላን ተዋጊዎቜ አንዱ ነው። ፍልስጀማውያንም በዚያ ለጊርነት ተሰብስበው ነበርፀ ዚእስራኀል ሰዎቜ ባፈገፈጉ ጊዜ
እሱ ካለበት ንቅንቅ ሳይል እጁ እስኪዝልና ኹጹበጠው ሰይፍ ላይ መላቀቅ እስኪያቅተው ድሚስ ፍልስጀማውያንን ጚፈጚፋ቞ው። በመሆኑም ይሖዋ በዚያ ቀን ታላቅ ድል አጎናጞፈፀ ሕዝቡም ኚተገደሉት ሰዎቜ ላይ ለመግፈፍ ኚእሱ ኋላ ተመልሶ መጣ።
ኚእሱ ቀጥሎ ዚሃራራዊው ዹአጌ ልጅ ሻማህ ነበር። ፍልስጀማውያን ሊሃይ በተባለ ስፍራ ምስር በሞላበት አንድ ማሳ ውስጥ ተሰብስበው ነበርፀ ሕዝቡም በፍልስጀማውያን ዚተነሳ ሞሞ።
እሱ ግን በእርሻው መካኚል ካለበት ንቅንቅ ሳይል መሬቱ እንዳይያዝ አደሚገፀ ፍልስጀማውያንንም መታ቞ውፀ በመሆኑም ይሖዋ ታላቅ ድል አጎናጞፈ።
በመኹር ወቅት ኹ30ዎቹ መሪዎቜ መካኚል ሊስቱ ዳዊት ወደሚገኝበት ወደ አዱላም ዋሻ ወሚዱፀ አንድ ዚፍልስጀማውያን ቡድንም በሹፋይም ሾለቆ ሰፍሮ ነበር።
በዚህ ጊዜ ዳዊት በምሜጉ ውስጥ ነበርፀ ዚፍልስጀማውያንም ዹጩር ሰፈር በቀተልሔም ነበር።
ኚዚያም ዳዊት “በቀተልሔም በር አቅራቢያ ካለው ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ዚምጠጣው ውኃ ባገኝ ምንኛ ደስ ባለኝ!” በማለት ምኞቱን ገለጞ።
በዚህ ጊዜ ሊስቱ ኃያላን ተዋጊዎቜ ወደ ፍልስጀማውያን ሰፈር ጥሰው በመግባት በቀተልሔም በር አቅራቢያ ኹሚገኘው ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ውኃ ቀድተው ለዳዊት አመጡለትፀ እሱ ግን ለመጠጣት ፈቃደኛ አልሆነምፀ ኹዚህ ይልቅ ውኃውን ለይሖዋ አፈሰሰው።
ኚዚያም “ይሖዋ ሆይ፣ ይህን ማድሚግ ፈጜሞ ዚማላስበው ነገር ነው! ሕይወታ቞ውን አደጋ ላይ ጥለው ዚሄዱትን ዚእነዚህን ሰዎቜ ደም ልጠጣ ይገባል?” አለ። በመሆኑም ውኃውን ለመጠጣት ፈቃደኛ አልሆነም። ሊስቱ ኃያላን ተዋጊዎቹ ያደሚጓ቞ው ነገሮቜ እነዚህ ነበሩ።
ዚጜሩያ ልጅ ዚኢዮዓብ ወንድም አቢሳ ዚሌሎቜ ሊስት ሰዎቜ መሪ ነበርፀ እሱም ጊሩን ሰብቆ 300 ሰው ገደለፀ እንደ ሊስቱም ሰዎቜ ዝነኛ ነበር።
ምንም እንኳ ኚሌሎቹ ሊስት ሰዎቜ ይበልጥ ታዋቂና ዚእነሱ አለቃ ዹነበሹ ቢሆንም ዚመጀመሪያዎቹን ሊስት ሰዎቜ ያህል ማዕሹግ አላገኘም።
ዚዮዳሄ ልጅ በናያህ በቃብጜኀል ብዙ ጀብዱ ዹፈጾመ ደፋር ሰው ነበር። እሱም ዚሞዓቡን ዹአርዔልን ሁለት ወንዶቜ ልጆቜ ገደለፀ እንዲሁም በሚዶ በሚጥልበት ዕለት ወደ አንድ ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ወርዶ አንበሳ ገደለ።
በተጚማሪም እጅግ ግዙፍ ዹሆነ ግብፃዊ ገደለ። ግብፃዊው በእጁ ጩር ይዞ ዹነበሹ ቢሆንም እሱ ግን በትር ብቻ ይዞ በመሄድ ገጠመውፀ ዚግብፃዊውንም ጩር ኚእጁ ቀምቶ በገዛ ጊሩ ገደለው።
ዚዮዳሄ ልጅ በናያህ ያደሚጋ቞ው ነገሮቜ እነዚህ ነበሩፀ እሱም እንደ ሊስቱ ኃያላን ተዋጊዎቜ ዝነኛ ነበር።
ኚሠላሳዎቹ ይበልጥ ታዋቂ ዹነበሹ ቢሆንም ዚሊስቱን ሰዎቜ ያህል ማዕሹግ አላገኘም። ይሁን እንጂ ዳዊት ዚራሱ ዚክብር ዘብ አለቃ አድርጎ ሟመው።
ዚኢዮዓብ ወንድም አሳሄል ኚሠላሳዎቹ አንዱ ነበርፀ ኚኃያላኑ ሰዎቜ መካኚል ዚሚኚተሉት ይገኙበታልፊ ዚቀተልሔሙ ዚዶዶ ልጅ ኀልሃናን፣
ሃሮዳዊው ሻማህ፣ ሃሮዳዊው ኀሊቃ፣
ጳሌጣዊው ሄሌጜ፣ ዹተቆአዊው ዚኢቄሜ ልጅ ኢራ፣
አናቶታዊው አቢዔዜር፣ ሁሻዊው መቡናይ፣
አሆሐያዊው ጻልሞን፣ ነጩፋዊው ማህራይ፣
ዹነጩፋዊው ዚባአናህ ልጅ ሄሌብ፣ ኚቢንያማውያን ዚጊብዓው ዚሪባይ ልጅ ኢታይ፣
ጲራቶናዊው በናያህ፣ ዚጋአሜ ደሹቅ ወንዞቜ ሰው ዹሆነው ሂዳይ፣
አርባዊው አቢዓልቊን፣ ባርሁማዊው አዝማዌት፣
ሻአልቢማዊው ኀሊያህባ፣ ዚያሌን ልጆቜ፣ ዮናታን፣
ሃራራዊው ሻማህ፣ ዚሃራራዊው ዚሻራር ልጅ አሂዓም፣
ዚማአካታዊው ልጅ፣ ዚአሃስባይ ልጅ ኀሊፌሌት፣ ዹጊሎአዊው ዚአኪጊፌል ልጅ ኀሊያም፣
ቀርሜሎሳዊው ሄጜሮ፣ ዓሚባዊው ፓአራይ፣
ዚጟባህዊው ዚናታን ልጅ ይግዓል፣ ጋዳዊው ባኒ፣
አሞናዊው ጌሌቅ፣ ዚጜሩያ ልጅ ዚኢዮዓብ ጋሻ ጃግሬ በኀሮታዊው ናሃራይ፣
ይትራዊው ኢራ፣ ይትራዊው ጋሬብ
እንዲሁም ሂታዊው ኊርዮፀ በአጠቃላይ 37 ነበሩ።
ዳዊትም በእስራኀል ውስጥ ያሉትን ምርጥ ዹሆኑ ተዋጊዎቜ በሙሉ በድጋሚ ሰበሰበፀ ብዛታ቞ውም 30,000 ነበር።
ኚዚያም አብሮት ኹነበሹው ሕዝብ ሁሉ ጋር ተነስቶ ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት ለማምጣት በዙፋን ላይ ኚኪሩቀል በላይ ዹተቀመጠው ዚሠራዊት ጌታ ዹይሖዋ ስም ወደተጠራበት ወደ በዓለይሁዳ ሄደ።
ይሁን እንጂ ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት በኮሚብታ ላይ ካለው ኚአቢናዳብ ቀት ለማምጣት በአዲስ ሠሹገላ ላይ ጫኑትፀ ዚአቢናዳብ ልጆቜ ዚሆኑት ዖዛ እና አሂዮም አዲሱን ሠሹገላ ይነዱ ነበር።
በመሆኑም ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት በኮሚብታ ላይ ኹነበሹው ኚአቢናዳብ ቀት ይዘው ጉዞ ጀመሩፀ አሂዮም ኚታቊቱ ፊት ፊት ይሄድ ነበር።
ዳዊትና መላው ዚእስራኀል ቀት ኚጥድ እንጚት በተሠሩ ዚተለያዩ መሣሪያዎቜ፣ በበገና፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቜ፣ በአታሞ፣ በጞናጜልና በሲምባል ታጅበው በይሖዋ ፊት በደስታ ይጚፍሩ ነበር።
ወደ ናኮን አውድማ ሲደርሱ ግን ኚብቶቹ ታቊቱን ሊጥሉት ተቃርበው ስለነበር ዖዛ እጁን ዘርግቶ ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት ያዘ።
በዚህ ጊዜ ዹይሖዋ ቁጣ በዖዛ ላይ ነደደፀ በመሆኑም ዖዛ እንዲህ ያለ ዚድፍሚት ድርጊት በመፈጾሙ እውነተኛው አምላክ እዚያው ቀሰፈውፀ እሱም በእውነተኛው አምላክ ታቊት አጠገብ እዚያው ሞተ።
ሆኖም ዹይሖዋ ቁጣ በዖዛ ላይ ስለነደደ ዳዊት ተበሳጚፀ ያም ቊታ እስኚ ዛሬ ድሚስ ጎሬዝዖዛ ተብሎ ይጠራል።
ዳዊትም በዚያን ዕለት ይሖዋን ፈርቶ “ታዲያ ዹይሖዋ ታቊት እንዎት ወደ እኔ ይመጣል?” አለ።
ዳዊትም ዹይሖዋ ታቊት እሱ ወዳለበት ወደ ዳዊት ኹተማ እንዲመጣ አልፈለገም። ይልቁንም ታቊቱ ዚጌት ሰው ወደሆነው ወደ ኊቀድዔዶም ቀት እንዲወሰድ አደሚገ።
ዹይሖዋም ታቊት ዚጌት ሰው በሆነው በኊቀድዔዶም ቀት ለሊስት ወር ተቀመጠፀ ይሖዋም ኊቀድዔዶምን እና ቀተሰቡን በሙሉ ባሚኚ።
በመጚሚሻም ዳዊት “ይሖዋ በእውነተኛው አምላክ ታቊት ዚተነሳ ዚኊቀድዔዶምን ቀትና ዚእሱ ዹሆነውን ነገር ሁሉ ባርኳል” ተብሎ ተነገሚው። ስለሆነም ዳዊት ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት ኚኊቀድዔዶም ቀት ወደ ዳዊት ኹተማ በታላቅ ደስታ ለማምጣት ሄደ።
ዹይሖዋን ታቊት ዚተሞኚሙት ሰዎቜ ስድስት እርምጃ ኚተራመዱ በኋላ ዳዊት አንድ በሬና አንድ ዚሰባ ጥጃ ሠዋ።
ዳዊትም በሙሉ ኃይሉ በይሖዋ ፊት ይጹፍር ነበርፀ በዚህ ጊዜ ሁሉ ኚበፍታ ዚተሠራ ኀፉድ ለብሶ ነበር።
ዳዊትና ዚእስራኀል ቀት በሙሉ ዹይሖዋን ታቊት በእልልታና በቀንደ መለኚት አጅበው አመጡት።
ይሁንና ዹይሖዋ ታቊት ወደ ዳዊት ኹተማ በመጣ ጊዜ ዚሳኊል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ሆና ወደ ታቜ ተመለኚተቜፀ እሷም ንጉሥ ዳዊት በይሖዋ ፊት ሲዘልና ሲጚፍር አይታ በልቧ ናቀቜው።
በዚህ መንገድ ዹይሖዋን ታቊት አምጥተው ዳዊት በተኚለለት ድንኳን ውስጥ በተዘጋጀለት ቊታ ላይ አስቀመጡት። ኚዚያም ዳዊት ዹሚቃጠሉ መባዎቜንና ዚኅብሚት መሥዋዕቶቜን በይሖዋ ፊት አቀሚበ።
ዳዊት ዚሚቃጠሉትን መባዎቜና ዚኅብሚት መሥዋዕቶቹን አቅርቩ ሲጚርስ ሕዝቡን በሠራዊት ጌታ በይሖዋ ስም ባሚኚ።
በተጚማሪም ለሕዝቡ ሁሉ ይኾውም ለተሰበሰቡት እስራኀላውያን በሙሉ፣ ለእያንዳንዱ ወንድና ሎት አንድ ዳቊ፣ አንድ ዹቮምር ጥፍጥፍና አንድ ዚዘቢብ ጥፍጥፍ አኚፋፈለፀ ኚዚያም ሕዝቡ ሁሉ ወደዚቀቱ ሄደ።
በዚህ ጊዜ ዳዊት ዚራሱን ቀት ለመባሚክ ተመለሰፀ ዚሳኊል ልጅ ሜልኮልም ዳዊትን ልትቀበለው ወጥታ “ዛሬ ዚእስራኀል ንጉሥ እንደ አንድ ተራ ሰው በአገልጋዮቹ ሎት ባሪያዎቜ ፊት እርቃኑን በመሆኑ እንዎት ራሱን አስኚብሯል!” አለቜው።
በዚህ ጊዜ ዳዊት ሜልኮልን እንዲህ አላትፊ “ዚጚፈርኩት እኮ ኚአባትሜና በቀቱ ካሉት ሁሉ ይልቅ እኔን መርጩ በይሖዋ ሕዝብ በእስራኀል ላይ መሪ አድርጎ በሟመኝ በይሖዋ ፊት ነውፀ አሁንም ቢሆን በይሖዋ ፊት እጚፍራለሁ።
እንዲያውም ኹዚህ ዚባሰ ራሎን አዋርዳለሁፀ ራሎንም እንቃለሁ። ሆኖም አንቺ በጠቀስሻ቞ው ሎት ባሪያዎቜ ፊት እኚበራለሁ።”
ዚሳኊል ልጅ ሜልኮልም እስኚሞተቜበት ቀን ድሚስ ልጅ አልወለደቜም።
ኹጊዜ በኋላም ዳዊት ፍልስጀማውያንን ድል በማድሚግ በቁጥጥር ሥር አዋላ቞ውፀ መተግአማህንም ኚፍልስጀማውያን እጅ ወሰደ።
ሞዓባውያንንም ድል አደሚጋ቞ውፀ እነሱንም መሬት ላይ አጋድሞ በገመድ ለካ቞ው። ይህን ያደሚገው በገመዱ ርዝመት ሁለት እጅ ዚሚሆኑትን ለመግደል እንዲሁም በገመዱ ርዝመት አንድ እጅ ዚሚሆኑትን በሕይወት ለመተው ነው። ሞዓባውያንም ዚዳዊት አገልጋዮቜ ሆኑፀ ግብርም ገበሩለት።
ዚሬሆብ ልጅ ዹሆነው ዚጟባህ ንጉሥ ሃዳድኀዜር በኀፍራጥስ ወንዝ ላይ ያለውን ዚበላይነት ዳግመኛ ለማሚጋገጥ በሄደ ጊዜ ዳዊት ድል አደሚገው።
ዳዊትም ኚእሱ ላይ 1,700 ፈሚሰኞቜንና 20,000 እግሚኛ ወታደሮቜን ማሚኚ። ኚዚያም ዳዊት 100 ዹሠሹገላ ፈሚሶቜን ብቻ አስቀርቶ ሌሎቹን በሙሉ ቋንጃቾውን ቆሚጠ።
ዚደማስቆዎቹ ሶርያውያን፣ ዚጟባህን ንጉሥ ሃዳድኀዜርን ለመርዳት በመጡ ጊዜ ዳዊት ኚሶርያውያን መካኚል 22,000 ሰዎቜን ገደለ።
ኚዚያም ዳዊት በደማስቆ ሶርያ ዹጩር ሰፈሮቜ አቋቋመፀ ሶርያውያንም ዚዳዊት አገልጋዮቜ ሆኑፀ ግብርም ገበሩለት። ይሖዋ ዳዊትን በሄደበት ሁሉ ድል አቀዳጀው።
በተጚማሪም ዳዊት ኚሃዳድኀዜር አገልጋዮቜ ላይ ኹወርቅ ዚተሠሩ ክብ ጋሻዎቜን ወሰደፀ ወደ ኢዚሩሳሌምም አመጣ቞ው።
ደግሞም ንጉሥ ዳዊት ዚሃዳድኀዜር ኚተሞቜ ኚሆኑት ኚቀጣህ እና ኚበሮታይ እጅግ ብዙ መዳብ ወሰደ።
በዚህ ጊዜ ዚሃማት ንጉሥ ቶአይ ዳዊት ዚጟባህን ንጉሥ ዚሃዳድኀዜርን ሠራዊት በሙሉ ድል እንዳደሚገ ሰማ።
በመሆኑም ቶአይ ዚንጉሥ ዳዊትን ደህንነት እንዲጠይቅና ኚሃዳድኀዜር ጋር ተዋግቶ ድል በማድሚጉ ዹተሰማውን ደስታ እንዲገልጜለት ልጁን ዮራምን ወደ ዳዊት ላኹው (ምክንያቱም ሃዳድኀዜር ኚቶአይ ጋር ብዙ ጊዜ ይዋጋ ነበር)ፀ እሱም ኚብር፣ ኹወርቅና ኚመዳብ ዚተሠሩ ዕቃዎቜን ይዞ መጣ።
ንጉሥ ዳዊት እነዚህን ዕቃዎቜ ተገዢዎቹ ካደሚጋ቞ው ብሔራት ሁሉ ላይ ወስዶ ኹቀደሰው ብርና ወርቅ ጋር አብሮ ለይሖዋ ቀደሳ቞ውፀ
ዕቃዎቹም ኚሶርያ፣ ኚሞዓብ፣ ኚአሞናውያን፣ ኚፍልስጀማውያንና ኚአማሌቃውያን ላይ ዚወሰዳ቞ው እንዲሁም ዚሬሆብ ልጅ ኹሆነው ኚጟባህ ንጉሥ ኚሃዳድኀዜር ላይ ዚማሚካ቞ው ና቞ው።
ዳዊት በጹው ሾለቆ 18,000 ኀዶማውያንን ገድሎ ኹተመለሰ በኋላ ስሙ ገነነ።