text
stringlengths
4
267
በተጚማሪም ንጉሥ አካዝ ዹዕቃ ማጓጓዣ ጋሪዎቹን ዹጎን መኚለያዎቜ ቆራሚጠፀ ዹውኃ ገንዳዎቹንም ኚላያ቞ው ላይ አነሳፀ ባሕሩንም ኚተቀመጠበት ዚመዳብ በሬዎቜ ላይ አውርዶ በድንጋይ ንጣፍ ላይ አስቀመጠው።
እንዲሁም በይሖዋ ቀት ውስጥ ሠርተውት ዹነበሹውን ለሰንበት ቀን ዚሚያገለግለውን መጠለያና በውጭ ያለውን ዚንጉሡን መግቢያ በአሩር ንጉሥ ዚተነሳ ወደ ሌላ ቊታ ወሰደው።
ዹቀሹው ዚአካዝ ታሪክ፣ ያደሚጋ቞ው ነገሮቜ በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፈው ይገኙ ዹለም?
በመጚሚሻም አካዝ ኚአባቶቹ ጋር አንቀላፋፀ በዳዊት ኹተማም ኚአባቶቹ ጋር ተቀበሚፀ በእሱም ምትክ ልጁ ሕዝቅያስ ነገሠ።
ዚሶርያ ንጉሥ ዚሠራዊት አለቃ ዹሆነው ንዕማን በጌታው ፊት ዹተኹበሹና ትልቅ ቊታ ዹሚሰጠው ሰው ነበርፀ ምክንያቱም ይሖዋ ለሶርያ ድል ያጎናጞፈው በእሱ አማካኝነት ነበር። ይህ ሰው ዚሥጋ ደዌ በሜተኛ ቢሆንም ኃያል ተዋጊ ነበር።
ሶርያውያን በአንድ ወቅት ወሚራ ሲያካሂዱ ኚእስራኀል ምድር አንዲት ትንሜ ልጅ ማርኹው ወስደው ነበርፀ እሷም ዹንዕማን ሚስት አገልጋይ ሆነቜ።
ይህቜ ልጅ እመቀቷን “ጌታዬ በሰማርያ ወዳለው ነቢይ ቢሄድ እኮ ጥሩ ነው! ኚሥጋ ደዌው ይፈውሰው ነበር” አለቻት።
እሱም ወደ ጌታው ሄዶ ኚእስራኀል ምድር ዚመጣቜው ልጅ ያለቜውን ነገሚው።
ዚሶርያም ንጉሥ “እንግዲያው ሂድ! እኔም ለእስራኀል ንጉሥ ደብዳቀ እልክለታለሁ” አለ። እሱም አሥር ታላንት ብር፣ 6,000 ሰቅል ወርቅና አሥር ቅያሪ ልብሶቜ ይዞ ሄደ።
ለእስራኀልም ንጉሥ “አገልጋዬን ንዕማንን ኚሥጋ ደዌው እንድትፈውሰው ኹዚህ ደብዳቀ ጋር ወደ አንተ ልኬዋለሁ” ዹሚለውን ደብዳቀ ሰጠው።
ዚእስራኀልም ንጉሥ ደብዳቀውን እንዳነበበ ልብሱን ቀደደፀ ኚዚያም “ይህን ሰው ኚሥጋ ደዌው እንድፈውስ ወደ እኔ ዹሚልኹው እኔ መግደልና ማዳን ዚምቜል አምላክ ሆኜ ነው? እንግዲህ ነገር ሲፈልገኝ እዩ” አለ።
ይሁንና ዚእውነተኛው አምላክ ሰው ኀልሳዕ ዚእስራኀል ንጉሥ ልብሱን እንደቀደደ ሲሰማ ወዲያውኑ “ልብስህን ዚቀደድኚው ለምንድን ነው? በእስራኀል ነቢይ መኖሩን እንዲያውቅ እባክህ ወደ እኔ ላኹው” ዹሚል መልእክት ወደ ንጉሡ ላኚ።
በመሆኑም ንዕማን ፈሚሶቹንና ዹጩር ሠሚገሎቹን ይዞ መጣፀ በኀልሳዕም ቀት ደጃፍ ላይ ቆመ።
ሆኖም ኀልሳዕ “ሄደህ ዮርዳኖስ ውስጥ ሰባት ጊዜ ታጠብፀ ሥጋህም ይፈወሳልፀ ንጹሕም ትሆናለህ” ብሎ እንዲነግሚው መልእክተኛ ላኚ።
በዚህ ጊዜ ንዕማን ተቆጥቶ ለመሄድ ተነሳፀ እንዲህም አለ፩ “እኔ እኮ ‘ወደ እኔ መጥቶ በመቆም ዚአምላኩን ዹይሖዋን ስም እዚጠራ ቁስሉ ያለበትን ቊታ በመዳሰስ ኚያዘኝ ዚሥጋ ደዌ ይፈውሰኛል’ ብዬ አስቀ ነበር።
ለዚህ ለዚህማ ዚደማስቆ ወንዞቜ አባና እና ፋርፋር በእስራኀል ኹሚገኙ ውኃዎቜ ሁሉ ዚተሻሉ አይደሉም? እነሱ ውስጥ ታጥቀ መንጻት አልቜልም ነበር?” ኚዚያም በቁጣ ተመልሶ ሄደ።
አገልጋዮቹም ቀርበው “አባ቎ ሆይ፣ ነቢዩ ያልተለመደ ነገር እንድታደርግ ቢነግርህ ኖሮ አታደርገውም ነበር? ታዲያ ‘ታጠብና ንጻ’ ቢልህ ምኑ ኹበደህ?” አሉት።
በዚህ ጊዜ ንዕማን ዚእውነተኛው አምላክ ሰው በነገሹው መሠሚት ወርዶ ዮርዳኖስ ውስጥ ሰባት ጊዜ ጠለቀ። ኚዚያም ሥጋው እንደ ትንሜ ልጅ ሥጋ ሆነፀ ደግሞም ነጻ።
ኚዚያ በኋላ አጃቢዎቹን አስኚትሎ ወደ እውነተኛው አምላክ ሰው ተመለሰፀ በፊቱም ቆሞ “በእስራኀል እንጂ በምድር ላይ በሌላ በዚትኛውም ቊታ አምላክ እንደሌለ አሁን አውቄአለሁ። እባክህ ኹአገልጋይህ ስጊታ ተቀበል” አለው።
እሱ ግን “በማገለግለውና ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ ምንም ነገር አልቀበልም” አለው። ንዕማን እንዲቀበለው ቢወተውተውም ፈቃደኛ አልሆነም።
በመጚሚሻም ንዕማን እንዲህ አለው፩ “እንግዲያው ዚማትቀበለኝ ኚሆነ፣ አገልጋይህ ኹአሁን በኋላ ለይሖዋ እንጂ ለሌሎቜ አማልክት ዹሚቃጠል መባም ሆነ መሥዋዕት ስለማያቀርብ እባክህ ለአገልጋይህ ኹዚህ ቊታ ዚሁለት በቅሎ ጭነት አፈር ይሰጠው።
ይሁንና ይሖዋ ስለ አንድ ነገር ብቻ አገልጋይህን ይቅር ይበለውፀ ይኾውም ጌታዬ ለመስገድ ወደ ሪሞን ቀት በሚገባበት ጊዜ ክንዮን ይደገፋልፀ እኔም በሪሞን ቀት መስገዎ አይቀርም። በሪሞን ቀት በምሰግድበት ጊዜ ይሖዋ ይህን ነገር አገልጋይህን ይቅር ይበለው።”
በዚህ ጊዜ ኀልሳዕ “በሰላም ሂድ” አለው። ኚእሱ ተለይቶ ዹተወሰነ ርቀት እንደተጓዘ
ዚእውነተኛው አምላክ ሰው ዚኀልሳዕ አገልጋይ ዹሆነው ግያዝ ‘ጌታዬ ሶርያዊው ንዕማን ያመጣውን ነገር ሳይቀበለው እንዲሁ አሰናበተው። ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ ተኚትዬው ሮጬ ዹሆነ ነገር እቀበለዋለሁ’ ብሎ አሰበ።
ስለዚህ ግያዝ ንዕማንን ተኚተለው። ንዕማንም አንድ ሰው በሩጫ እዚተኚተለው እንዳለ ሲያይ ሰውዹውን ለማግኘት ኹሠሹገላው ላይ ወርዶ “በደህና ነው?” አለው።
በዚህ ጊዜ ግያዝ እንዲህ አለው፩ “አዎ፣ በደህና ነው። ጌታዬ ‘ኚነቢያት ልጆቜ መካኚል ሁለት ወጣቶቜ ኚተራራማው ኚኀፍሬም አካባቢ አሁን ድንገት ወደ እኔ መጡ። ስለሆነም እባክህ አንድ ታላንት ብርና ሁለት ቅያሪ ልብስ ስጣ቞ው’ ብዬ እንድነግርህ ልኮኝ ነው።”
ንዕማንም “እባክህ፣ ሁለት ታላንት ውሰድ” አለው። አጥብቆም ለመነውፀ ኚዚያም ሁለት ታላንት ብር በሁለት ኚሚጢት ጠቅልሎ እንዲሁም ሁለት ቅያሪ ልብስ ጚምሮ ለሁለቱ አገልጋዮቹ ሰጣ቞ውፀ እነሱም ተሾክመው ኚፊት ኚፊቱ ሄዱ።
እሱም ኩፌል በደሹሰ ጊዜ ዕቃዎቹን ኚእጃ቞ው ላይ ወስዶ ቀት ውስጥ ካስቀመጠ በኋላ ሰዎቹን አሰናበታ቞ው። እነሱም ኚሄዱ በኋላ
ገብቶ ጌታው አጠገብ ቆመ። ኀልሳዕም “ግያዝ፣ ኚዚት ነው ዚመጣኞው?” አለው። እሱ ግን “ኧሹ አገልጋይህ ዚትም አልሄደም” አለ።
ኀልሳዕም እንዲህ አለው፩ “ሰውዹው አንተን ለማግኘት ኹሠሹገላው ላይ ሲወርድ ልቀ በዚያ ኹአንተ ጋር አልነበሹም? ለመሆኑ ጊዜው ብር ወይም ልብስ፣ ዚወይራ ወይም ዹወይን እርሻ፣ በግ ወይም ኚብት አሊያም ደግሞ ወንድ ወይም ሎት አገልጋዮቜ ዚሚቀበሉበት ነው?
ስለሆነም ዹንዕማን ዚሥጋ ደዌ በአንተና በዘርህ ላይ ለዘላለም ይጣበቃል።” ግያዝም በሥጋ ደዌ ዚተነሳ እንደ በሚዶ ነጭ ሆኖ ወዲያውኑ ኚፊቱ ወጣ።
ዚእስራኀል ንጉሥ ዚኢዮዓካዝ ልጅ ኢዮዓስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት ዚይሁዳ ንጉሥ ዚኢዮዓስ ልጅ አሜስያስ ነገሠ።
አሜስያስ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው 25 ዓመት ነበርፀ በኢዚሩሳሌምም ሆኖ ለ29 ዓመት ገዛ። እናቱ ዚሆዓዲን ዚተባለቜ ዚኢዚሩሳሌም ተወላጅ ነበሚቜ።
እሱም እንደ አባቱ እንደ ዳዊት ባይሆንም በይሖዋ ፊት ትክክል ዹሆነውን ነገር ፈጞመ። ሁሉንም ነገር አባቱ ኢዮዓስ እንዳደሚገው አደሚገ።
ሆኖም ኹፍ ያሉት ዚማምለኪያ ቊታዎቜ አልተወገዱም ነበርፀ ሕዝቡ አሁንም ኹፍ ባሉት ዚማምለኪያ ቊታዎቜ ላይ ይሠዋ እንዲሁም ዚሚጚስ መሥዋዕት ያቀርብ ነበር።
እሱም መንግሥቱ በእጁ እንደጞናለት፣ ንጉሥ ዹነበሹውን አባቱን ዚገደሉትን አገልጋዮቹን ገደላ቞ው።
ይሁንና “አባቶቜ በልጆቻ቞ው ኃጢአት መገደል ዚለባ቞ውምፀ ልጆቜም በአባቶቻ቞ው ኃጢአት መገደል ዚለባ቞ውምፀ ይልቁንም እያንዳንዱ ሰው በገዛ ኃጢአቱ ይገደል” በሚለው በሙሮ ዹሕግ መጜሐፍ ላይ በተጻፈው ዹይሖዋ ትእዛዝ መሠሚት ዚገዳዮቹን ልጆቜ አልገደላ቞ውም።
እሱም 10,000 ኀዶማውያንን በጹው ሾለቆ መታፀ ተዋግቶም ሮላን በቁጥጥሩ ሥር አደሚገፀ እሷም እስኚ ዛሬ ድሚስ ዮቅተኀል ተብላ ትጠራለቜ።
ኚዚያም አሜስያስ ዚእስራኀል ንጉሥ ወደሆነው ወደ ኢዩ ልጅ ወደ ኢዮዓካዝ ልጅ ወደ ኢዮዓስ “ናፀ ውጊያ እንግጠም” በማለት መልእክተኞቜ ላኚ።
ዚእስራኀል ንጉሥ ኢዮዓስ ደግሞ ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ አሜስያስ ይህን መልእክት ላኹ፩ “በሊባኖስ ዹሚገኘው ኩርንቜት በሊባኖስ ወደሚገኘው አርዘ ሊባኖስ ‘ሎት ልጅህን ለወንድ ልጄ ዳርለት’ ዹሚል መልእክት ላኚ። ይሁን እንጂ በሊባኖስ ዹነበሹ አንድ ዚዱር አውሬ በዚያ ሲያልፍ ያን ኩርንቜት ሚገጠው።
እርግጥ ኀዶምን መተሃልፀ በመሆኑም ልብህ ታብዮአል። ክብርህን ጠብቀህ አርፈህ ቀትህ ተቀመጥ። በራስህ ላይ ለምን ጥፋት ትጋብዛለህ? ደግሞስ ራስህንም ሆነ ይሁዳን ለምን ለውድቀት ትዳርጋለህ?”
አሜስያስ ግን አልሰማም። በመሆኑም ዚእስራኀል ንጉሥ ኢዮዓስ ወጣፀ እሱና ዚይሁዳ ንጉሥ አሜስያስም በይሁዳ በምትገኘው በቀትሌሜሜ ተጋጠሙ።
ይሁዳ በእስራኀል ድል ተመታፀ እያንዳንዳ቞ውም ወደዚቀታ቞ው ሞሹ።
ዚእስራኀል ንጉሥ ኢዮዓስ ዚአካዝያስ ልጅ፣ ዚኢዮዓስ ልጅ ዹሆነውን ዚይሁዳን ንጉሥ አሜስያስን ቀትሌሜሜ ላይ ያዘው። ኚዚያም ወደ ኢዚሩሳሌም መጡፀ እሱም ዚኢዚሩሳሌምን ቅጥር፣ ኚኀፍሬም በር አንስቶ እስኚ ማዕዘን በር ድሚስ አፈሚሰፀ ርዝመቱም 400 ክንድ ያህል ነበር።
በይሖዋ ቀትና በንጉሡ ቀት ግምጃ ቀቶቜ ዹተገኘውን ወርቅ፣ ብርና ዕቃ ሁሉ እንዲሁም ዚታገቱትን ሰዎቜ ወሰደ። ኚዚያም ወደ ሰማርያ ተመለሰ።
ዹቀሹው ዚኢዮዓስ ታሪክ፣ ያደሚጋ቞ው ነገሮቜና ኃያልነቱ እንዲሁም ኚይሁዳ ንጉሥ ኚአሜስያስ ጋር እንዎት እንደተዋጋ በእስራኀል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፈው ይገኙ ዹለም?
በመጚሚሻም ኢዮዓስ ኚአባቶቹ ጋር አንቀላፋፀ ኚእስራኀልም ነገሥታት ጋር በሰማርያ ተቀበሚፀ ልጁም ኢዮርብዓም በእሱ ምትክ ነገሠ።
ዚእስራኀል ንጉሥ ዚኢዮዓካዝ ልጅ ኢዮዓስ ኹሞተ በኋላ፣ ዚይሁዳ ንጉሥ ዚኢዮዓስ ልጅ አሜስያስ 15 ዓመት ኖሚ።
ዹቀሹው ዚአሜስያስ ታሪክ በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፎ ይገኝ ዹለም?
ኹጊዜ በኋላ ኢዚሩሳሌም ውስጥ በእሱ ላይ ሎራ ተጠነሰሰፀ እሱም ወደ ለኪሶ ሞሞፀ እነሱ ግን ተኚታትለው እንዲይዙት ሰዎቜን ወደ ለኪሶ ላኩፀ በዚያም ገደሉት።
ኚዚያም በፈሚሶቜ ላይ ጭነው አመጡትፀ እሱም በዳዊት ኹተማ ኚአባቶቹ ጋር በኢዚሩሳሌም ተቀበሚ።
ኚዚያም ዚይሁዳ ሕዝብ ሁሉ በወቅቱ ዹ16 ዓመት ልጅ ዹነበሹውን አዛርያስን ወስደው በአባቱ በአሜስያስ ምትክ አነገሡት።
እሱም፣ ንጉሡ ኚአባቶቹ ጋር ካንቀላፋ በኋላ ኀላትን መልሶ በመገንባት ወደ ይሁዳ መለሳት።
ዚይሁዳ ንጉሥ ዚኢዮዓስ ልጅ አሜስያስ በነገሠ በ15ኛው ዓመት ዚእስራኀል ንጉሥ ዚኢዮዓስ ልጅ ኢዮርብዓም በሰማርያ ነገሠፀ እሱም 41 ዓመት ገዛ።
በይሖዋ ፊት መጥፎ ዹሆነውን ነገር አደሚገ። ዚናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም እስራኀላውያን እንዲፈጜሙ ካደሚጋ቞ው ኃጢአት ሁሉ ዞር አላለም።
ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ዚጋትሔፌር ነቢይ በሆነው በአሚታይ ልጅ፣ በአገልጋዩ በዮናስ አማካኝነት በተናገሹው ቃል መሠሚት ኚሌቊሃማት አንስቶ እስኚ አሚባ ባሕር ድሚስ ያለውን ዚእስራኀልን ወሰን አስመለሰ።
ይሖዋ በእስራኀል ላይ እዚደሚሰ ያለውን ኚባድ ሥቃይ ተመልክቶ ነበርና። በዚያም እስራኀልን ሌላው ቀርቶ ምስኪኑንና ደካማውን ዚሚሚዳ አልነበሚም።
ሆኖም ይሖዋ ዚእስራኀልን ስም ኹሰማይ በታቜ ጠራርጎ እንደማያጠፋ ቃል ገብቶ ነበር። በመሆኑም በኢዮዓስ ልጅ በኢዮርብዓም አማካኝነት አዳና቞ው።
ዹቀሹው ዚኢዮርብዓም ታሪክ፣ ያደሚጋ቞ው ነገሮቜ ሁሉና ኃያልነቱ እንዲሁም እንዎት እንደተዋጋ ብሎም ደማስቆንና ሃማትን ለይሁዳና ለእስራኀል እንዎት እንዳስመለሰ በእስራኀል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፈው ይገኙ ዹለም?
በመጚሚሻም ኢዮርብዓም ኚአባቶቹ ኚእስራኀል ነገሥታት ጋር አንቀላፋፀ ልጁም ዘካርያስ በእሱ ምትክ ነገሠ።
ኢዮስያስ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው ስምንት ዓመት ነበርፀ በኢዚሩሳሌምም ሆኖ ለ31 ዓመት ገዛ። እናቱ ይዲዳ ትባል ነበርፀ እሷም ዚቊጜቃት ሰው ዹሆነው ዚአዳያህ ልጅ ነበሚቜ።
ኢዮስያስም በይሖዋ ፊት ትክክል ዹሆነውን ነገር አደሚገፀ በአባቱም በዳዊት መንገድ ሄደፀ ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አላለም።
ንጉሥ ኢዮስያስ፣ በነገሠ በ18ኛው ዓመት ዚመሹላም ልጅ፣ ዚአዜልያ ልጅ ዹሆነውን ጾሐፊውን ሳፋንን እንዲህ ሲል ወደ ይሖዋ ቀት ላኹው፩
“ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ኬልቅያስ ሂድፀ በር ጠባቂዎቹ ኚሕዝቡ ላይ ዚሰበሰቡትንና ወደ ይሖዋ ቀት ዚገባውን ገንዘብ በአጠቃላይ እንዲሰበስብ አድርግ።
ገንዘቡን በይሖዋ ቀት ዹሚኹናወነውን ሥራ እንዲቆጣጠሩ ለተሟሙት ሰዎቜ ይስጧ቞ውፀ እነሱ ደግሞ በይሖዋ ቀት ውስጥ ዹፈሹሰውን ለሚጠግኑት ሠራተኞቜ ይስጡፀ
ይኾውም ለእጅ ጥበብ ባለሙያዎቹ፣ ለግንባታ ባለሙያዎቹና ለግንበኞቹ ያስሚክቡፀ እነሱም ገንዘቡን ለቀቱ ጥገና ዚሚያስፈልጉትን ሳንቃዎቜና ጥርብ ድንጋዮቜ ለመግዛት ይጠቀሙበታል።
ነገር ግን ሰዎቹ እምነት ዚሚጣልባ቞ው ስለሆኑ ለተሰጣ቞ው ገንዘብ ስሌት እንዲያቀርቡ መጠዹቅ አያስፈልግም።”
በኋላም ሊቀ ካህናቱ ኬልቅያስ ጾሐፊውን ሳፋንን “ዹሕጉን መጜሐፍ በይሖዋ ቀት ውስጥ አገኘሁት” አለው። ኬልቅያስም መጜሐፉን ለሳፋን ሰጠውፀ እሱም ያነበው ጀመር።
ኚዚያም ጾሐፊው ሳፋን ወደ ንጉሡ ሄዶ “አገልጋዮቜህ በቀቱ ውስጥ ዹተገኘውን ገንዘብ በሙሉ አውጥተው በይሖዋ ቀት ዹሚኹናወነውን ሥራ እንዲቆጣጠሩ ለተሟሙት ሰዎቜ አስሚክበዋል” አለው።
በተጚማሪም ጾሐፊው ሳፋን ንጉሡን “ካህኑ ኬልቅያስ ዹሰጠኝ አንድ መጜሐፍ አለ” አለው። ኚዚያም ሳፋን መጜሐፉን በንጉሡ ፊት ማንበብ ጀመሚ።
ንጉሡ ዹሕጉን መጜሐፍ ቃል ሲሰማ ልብሱን ቀደደ።
ኚዚያም ንጉሡ ካህኑን ኬልቅያስን፣ ዚሳፋንን ልጅ አኪቃምን፣ ዚሚካያህን ልጅ አክቊርን፣ ጾሐፊውን ሳፋንን እና ዚንጉሡን አገልጋይ አሳያህን እንዲህ ሲል አዘዛቾው፩
“ሄዳቜሁ በተገኘው በዚህ መጜሐፍ ላይ ዹሰፈሹውን ቃል በተመለኹተ እኔን፣ ሕዝቡንና መላውን ይሁዳ ወክላቜሁ ይሖዋን ጠይቁፀ ምክንያቱም አባቶቻቜን በዚህ መጜሐፍ ላይ እኛን አስመልክቶ ዹሰፈሹውን ቃል ስላልታዘዙ ዹይሖዋ ታላቅ ቁጣ በእኛ ላይ ነዷል።”
በመሆኑም ካህኑ ኬልቅያስ፣ አኪቃም፣ አክቊር፣ ሳፋንና አሳያህ ወደ ነቢዪቱ ሕልዳና ሄዱ። ሕልዳና ዚሃርሐስ ልጅ፣ ዚቲቅዋ ልጅ፣ ዚአልባሳት ጠባቂው ዚሻሉም ሚስት ስትሆን ኢዚሩሳሌም ውስጥ በሁለተኛው ክፍል ትኖር ነበርፀ እነሱም በዚያ አነጋገሯት።
እሷም እንዲህ አለቻ቞ውፊ “ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ወደ እኔ ዚላካቜሁን ሰው እንዲህ በሉትፊ
“ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘በዚህ ቊታና በነዋሪዎቹ ላይ መኚራ አመጣለሁፀ ዚይሁዳ ንጉሥ ባነበበው መጜሐፍ ላይ ዹሰፈሹውን ቃል ሁሉ እፈጜማለሁ።
እኔን በመተው በእጆቻ቞ው ሥራ ሁሉ ያስቆጡኝ ዘንድ ለሌሎቜ አማልክት ዚሚጚስ መሥዋዕት ስለሚያቀርቡ ቁጣዬ በዚህ ቊታ ላይ ይነዳልፀ ደግሞም አይጠፋም።’”
ይሖዋን እንድትጠይቁ ለላካቜሁ ለይሁዳ ንጉሥ ግን እንዲህ በሉትፊ “ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ዹሰማኾውን ቃል በተመለኚተ፣
ይህን ቊታም ሆነ ነዋሪዎቹን መቀጣጫ እንደማደርግና እንደምሚግም ዚተናገርኩትን ነገር ስትሰማ ልብህ ስለተነካ፣ በይሖዋም ፊት ራስህን ስላዋሚድክ እንዲሁም ልብስህን ስለቀደድክና በፊቮ ስላለቀስክ እኔም ሰምቌሃለሁ ይላል ይሖዋ።
ወደ አባቶቜህ ዚምሰበስብህ በዚህ ዚተነሳ ነውፀ አንተም በሰላም በመቃብርህ ታርፋለህፀ በዚህ ቊታ ላይ ዚማመጣውን መኚራ ሁሉ ዓይኖቜህ አያዩም።’”’” ኚዚያም ሰዎቹ መልሱን ለንጉሡ አመጡለት።
ዚእስራኀል ንጉሥ ኢዮርብዓም በነገሠ በ27ኛው ዓመት ዚይሁዳ ንጉሥ ዚአሜስያስ ልጅ አዛርያስ ነገሠ።
እሱም በነገሠ ጊዜ ዕድሜው 16 ዓመት ነበርፀ በኢዚሩሳሌምም ሆኖ ለ52 ዓመት ገዛ። እናቱ ይኮልያ ዚተባለቜ ዚኢዚሩሳሌም ተወላጅ ነበሚቜ።
እሱም አባቱ አሜስያስ እንዳደሚገው ሁሉ በይሖዋ ፊት ትክክል ዹሆነውን ነገር አደሚገ።
ሆኖም ኹፍ ያሉት ዚማምለኪያ ቊታዎቜ አልተወገዱም ነበርፀ ሕዝቡ አሁንም ኹፍ ባሉት ዚማምለኪያ ቊታዎቜ ላይ ይሠዋ እንዲሁም ዚሚጚስ መሥዋዕት ያቀርብ ነበር።
ይሖዋ ንጉሡን ቀሰፈውፀ እስኚ ዕለተ ሞቱም ድሚስ ዚሥጋ ደዌ በሜተኛ ሆኖ ኖሚፀ በአንድ ዹተለዹ ቀትም ውስጥ ተገልሎ ተቀመጠፀ በዚህ ጊዜ ዚንጉሡ ልጅ ኢዮዓታም በቀቱ ላይ ተሹሞ በምድሪቱ በሚኖሹው ሕዝብ ላይ ይፈርድ ነበር።
ዹቀሹው ዚአዛርያስ ታሪክ፣ ያደሚጋ቞ው ነገሮቜ በሙሉ በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፈው ይገኙ ዹለም?
በመጚሚሻም አዛርያስ ኚአባቶቹ ጋር አንቀላፋፀ እነሱም በዳዊት ኹተማ ኚአባቶቹ ጋር ቀበሩትፀ በእሱም ምትክ ልጁ ኢዮዓታም ነገሠ።
ዚይሁዳ ንጉሥ አዛርያስ በነገሠ በ38ኛው ዓመት ዚኢዮርብዓም ልጅ ዘካርያስ በሰማርያ፣ በእስራኀል ላይ ነገሠፀ ለስድስት ወርም ገዛ።
አባቶቹ እንዳደሚጉት በይሖዋ ፊት መጥፎ ዹሆነውን ነገር አደሚገ። ዚናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም እስራኀላውያን እንዲፈጜሟ቞ው ካደሚጋ቞ው ኃጢአቶቜ ዞር አላለም።
ኚዚያም ዚኢያቢስ ልጅ ሻሉም በእሱ ላይ በማሮር ይብለአም ላይ መትቶ ገደለው። ኹገደለው በኋላ በእሱ ምትክ ነገሠ።
ዹቀሹው ዚዘካርያስ ታሪክ በእስራኀል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፏል።
ይህም ይሖዋ ለኢዩ “ልጆቜህ እስኚ አራተኛ ትውልድ ድሚስ በእስራኀል ዙፋን ላይ ይቀመጣሉ” በማለት ዹተናገሹው ቃል ፍጻሜ ነው። ዹሆነውም ልክ እንደዚሁ ነው።
ዚይሁዳ ንጉሥ ዖዝያ በነገሠ በ39ኛው ዓመት ዚኢያቢስ ልጅ ሻሉም ነገሠፀ እሱም በሰማርያ ሆኖ ድፍን አንድ ወር ገዛ።
ኚዚያም ዚጋዲ ልጅ መናሄም ኚቲርጻ ወደ ሰማርያ መጥቶ ዚኢያቢስን ልጅ ሻሉምን ሰማርያ ላይ መትቶ ገደለው። ኹገደለውም በኋላ በእሱ ምትክ ነገሠ።
ዹቀሹው ዚሻሉም ታሪክና ዹጠነሰሰው ሎራ በእስራኀል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጞሙት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ መጜሐፍ ውስጥ ተጜፏል።
በዚያን ጊዜ መናሄም ኚቲርጻ ወጥቶ ቲፍሳን እንዲሁም በውስጧና በዙሪያዋ ዚነበሩትን ሁሉ መታፀ ይህን ያደሚገው በሮቿን ለእሱ ለመክፈት ፈቃደኛ ባለመሆኗ ነው። እሱም ቲፍሳን መታትፀ ዹነፍሰ ጡሮቿንም ሆድ ቀደደ።
ዚይሁዳ ንጉሥ አዛርያስ በነገሠ በ39ኛው ዓመት ዚጋዲ ልጅ መናሄም በእስራኀል ላይ ነገሠፀ በሰማርያም ሆኖ ለአሥር ዓመት ገዛ።
እሱም በይሖዋ ፊት መጥፎ ዹሆነውን ነገር አደሚገ። በዘመኑም ሁሉ፣ ዚናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም እስራኀላውያን እንዲፈጜሟ቞ው ካደሚጋ቞ው ኃጢአቶቜ ዞር አላለም።
በዚህ ጊዜ ዹአሩር ንጉሥ ፑል ወደ ምድሩ መጣፀ መናሄምም መንግሥቱን ለማጜናት ድጋፍ እንዲሰጠው ለፑል 1,000 ዚብር ታላንት ሰጠው።
መናሄም ብሩን ያገኘው ኚእስራኀላውያን ይኾውም ስመ ጥርና ሀብታም ዹሆኑ ሰዎቜ እንዲያዋጡ በማስገደድ ነው። በእያንዳንዱ ሰው 50 ዚብር ሰቅል አስቊ ለአሩር ንጉሥ ሰጠው። ኚዚያም ዹአሩር ንጉሥ ተመልሶ ሄደፀ በምድሪቱም አልቆዚም።