text
stringlengths
4
267
ዚፍልስጀም ሠራዊት በሹፋይም ሾለቆ ሰፍሮ በነበሚበት ጊዜ፣ ኹ30ዎቹ መሪዎቜ መካኚል ሊስቱ ዓለታማ ወደሆነውና ዳዊት ወደሚገኝበት ወደ አዱላም ዋሻ ወሚዱ።
በዚያን ጊዜ ዳዊት በምሜጉ ውስጥ ነበርፀ ዚፍልስጀማውያንም ሠራዊት በቀተልሔም ነበር።
ኚዚያም ዳዊት “በቀተልሔም በር አቅራቢያ ካለው ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ዚምጠጣው ውኃ ባገኝ ምንኛ ደስ ባለኝ!” በማለት ምኞቱን ገለጞ።
በዚህ ጊዜ ሊስቱ ወደ ፍልስጀማውያን ሰፈር ጥሰው በመግባት በቀተልሔም በር አቅራቢያ ኹሚገኘው ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ውኃ ቀድተው ለዳዊት አመጡለትፀ ዳዊት ግን ለመጠጣት ፈቃደኛ አልሆነምፀ ኹዚህ ይልቅ ውኃውን ለይሖዋ አፈሰሰው።
እንዲህም አለ፩ “ለአምላኬ ካለኝ አክብሮት ዚተነሳ ይህን ማድሚግ ፈጜሞ ዚማላስበው ነገር ነው! ሕይወታ቞ውን አደጋ ላይ ጥለው ዚሄዱትን ዚእነዚህን ሰዎቜ ደም ልጠጣ ይገባል? ውኃውን ያመጡት በሕይወታ቞ው ቆርጠው ነውና።” በመሆኑም ውኃውን ለመጠጣት ፈቃደኛ አልሆነም። ሊስቱ ኃያላን ተዋጊዎቹ ያደሚጓ቞ው ነገሮቜ እነዚህ ነበሩ።
ዚኢዮዓብ ወንድም አቢሳ ዚሌሎቜ ሊስት ሰዎቜ መሪ ነበርፀ እሱም ጊሩን ሰብቆ 300 ሰው ገደለፀ እንደ ሊስቱም ሰዎቜ ዝነኛ ነበር።
ኚሌሎቹ ሊስት ሰዎቜ መካኚል እሱ ኚሁለቱ ዹበለጠ ታዋቂ ነበርፀ ዚእነሱም አለቃ ነበርፀ ይሁን እንጂ ዚመጀመሪያዎቹን ሊስት ሰዎቜ ያህል ማዕሹግ አላገኘም።
ዚዮዳሄ ልጅ በናያህ በቃብጜኀል ብዙ ጀብዱ ዹፈጾመ ደፋር ሰው ነበር። እሱም ዚሞዓቡን ዹአርዔልን ሁለት ወንዶቜ ልጆቜ ገደለፀ እንዲሁም በሚዶ በሚጥልበት ዕለት ወደ አንድ ዹውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ወርዶ አንበሳ ገደለ።
ደግሞም ቁመቱ አምስት ክንድ ዹሆነ እጅግ ግዙፍ ግብፃዊ ገደለ። ግብፃዊው ዹሾማኔ መጠቅለያ ዚሚመስል ጩር በእጁ ይዞ ዹነበሹ ቢሆንም በትር ብቻ ይዞ በመግጠም ዚግብፃዊውን ጩር ኚእጁ ቀምቶ በገዛ ጊሩ ገደለው።
ዚዮዳሄ ልጅ በናያህ ያደሚጋ቞ው ነገሮቜ እነዚህ ነበሩፀ እሱም እንደ ሊስቱ ኃያላን ተዋጊዎቜ ዝነኛ ነበር።
ኚሠላሳዎቹም ይበልጥ ታዋቂ ዹነበሹ ቢሆንም ዚሊስቱን ሰዎቜ ያህል ማዕሹግ አላገኘም። ይሁን እንጂ ዳዊት ዚራሱ ዚክብር ዘብ አለቃ አድርጎ ሟመው።
በሠራዊቱ ውስጥ ዚነበሩት ኃያላን ተዋጊዎቜ ዚሚኚተሉት ናቾው፩ ዚኢዮዓብ ወንድም አሳሄል፣ ዚቀተልሔሙ ዚዶዶ ልጅ ኀልሃናን፣
ሃሮራዊው ሻሞት፣ ጮሎናዊው ሄሌጜ፣
ዹተቆአዊው ዚኢቄሜ ልጅ ኢራ፣ አናቶታዊው አቢዔዜር፣
ሁሻዊው ሲበካይ፣ አሆሐያዊው ኢላይ፣
ነጩፋዊው ማህራይ፣ ዹነጩፋዊው ዚባአናህ ልጅ ሄሌድ፣
ኚቢንያማውያን ወገን ዹሆነው ዚጊብዓው ዚሪባይ ልጅ ኢታይ፣ ጲራቶናዊው በናያህ፣
ዚጋአሜ ደሹቅ ወንዞቜ ሰው ዹሆነው ሁራይ፣ አርባዊው አቢዔል፣
ባሁሪማዊው አዝማዌት፣ ሻአልቢማዊው ኀሊያህባ፣
ዹጊዞናዊው ዚሃሌም ወንዶቜ ልጆቜ፣ ዚሃራራዊው ዚሻጌ ልጅ ዮናታን፣
ዚሃራራዊው ዚሳካር ልጅ አሂዓም፣ ዹዑር ልጅ ኀሊፋል፣
መኚራታዊው ሄፌር፣ ጮሎናዊው አኪያህ፣
ቀርሜሎሳዊው ሄጜሮ፣ ዚኀዝባይ ልጅ ናአራይ፣
ዚናታን ወንድም ኢዩኀል፣ ዚሃግሪ ልጅ ሚብሃር፣
አሞናዊው ጌሌቅ፣ ዚጜሩያ ልጅ ዚኢዮዓብ ጋሻ ጃግሬ ቀሮታዊው ናሃራይፀ
ይትራዊው ኢራ፣ ይትራዊው ጋሬብ፣
ሂታዊው ኊርዮ፣ ዹአህላይ ልጅ ዛባድ፣
ዚሮቀላዊው ዚሺዛ ልጅ አዲና ዚሮቀላውያን መሪ ነበርፀ ኚእሱም ጋር 30 ሰዎቜ ነበሩፀ
ዚማአካ ልጅ ሃናን፣ ሚትናዊው ዮሳፍጥ፣
አስታሮታዊው ዑዚያ፣ ዚአሮዔራዊው ዚሆታም ልጆቜ ሻማ እና ዚኢዔልፀ
ዚሺምሪ ልጅ ዚዲአዔል፣ ቲጺያዊው ወንድሙ ዮሃፀ
ማሃዋዊው ኀሊዔል፣ ዚኀልናዓም ልጆቜ ዚሪባይ እና ዮሻውያህ፣ ሞዓባዊው ይትማፀ
ኀሊዔል፣ ኢዮቀድ እና መጟባዊው ያአሲዔል።
ዹበር ጠባቂዎቹ ምድብ እንደሚኚተለው ነው፩ ኚቆሬያውያን መካኚል ኚአሳፍ ልጆቜ አንዱ ዹሆነው ዹቆሹ ልጅ መሺሌሚያህ።
መሺሌሚያህም ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩትፊ ዚበኩር ልጁ ዘካርያስ፣ ሁለተኛው ዚዲአዔል፣ ሊስተኛው ዘባድያህ፣ አራተኛው ያትንኀል፣
አምስተኛው ኀላም፣ ስድስተኛው ዹሆሃናን እና ሰባተኛው ኀሊዚሆዔናይ።
ኊቀድዔዶምም ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩትፊ ዚበኩር ልጁ ሞማያህ፣ ሁለተኛው ዚሆዛባድ፣ ሊስተኛው ዮአስ፣ አራተኛው ሳካር፣ አምስተኛው ናትናኀል፣
ስድስተኛው አሚዔል፣ ሰባተኛው ይሳኮር እና ስምንተኛው ፐኡልታይፀ አምላክ እነዚህን ልጆቜ በመስጠት ኊቀድዔዶምን ባሚኚው።
ልጁም ሞማያህ ልጆቜ ወለደፀ እነሱም ብቃት ያላ቞ውና ኃያላን ነበሩፀ ዚዚቀተሰባ቞ውም መሪ ሆኑ።
ዚሞማያህ ወንዶቜ ልጆቜ ኊትኒ፣ ሚፋኀል፣ ኢዮቀድ እና ኀልዛባድ ነበሩፀ ዚኀልዛባድ ወንድሞቜ ዚሆኑት ኀሊሁ እና ሰማክያህም ብቃት ያላ቞ው ሰዎቜ ነበሩ።
እነዚህ ሁሉ ዚኊቀድዔዶም ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ እነሱም ሆኑ ወንዶቜ ልጆቻ቞ውና ወንድሞቻ቞ው አገልግሎቱን ለማኹናወን ቜሎታና ብቃት ያላ቞ው ሰዎቜ ነበሩፀ ኚኊቀድዔዶም ወገን 62 ነበሩ።
መሺሌሚያህም ብቃት ያላ቞ው ወንዶቜ ልጆቜና ወንድሞቜ ነበሩትፀ እነሱም 18 ነበሩ።
ዚሜራሪ ልጅ ዹሆነው ሆሳ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩት። ሺምሪ ዚበኩር ልጅ ባይሆንም እንኳ አባቱ ዚቀተሰቡ መሪ አድርጎ ሟመውፀ
ሁለተኛው ኬልቅያስ፣ ሊስተኛው ተባልያህ እና አራተኛው ዘካርያስ ነበሩ። ዚሆሳ ወንዶቜ ልጆቜና ወንድሞቜ በአጠቃላይ 13 ነበሩ።
ዹበር ጠባቂዎቹ ምድብ መሪዎቜ ልክ እንደ ወንድሞቻ቞ው በይሖዋ ቀት በሚቀርበው አገልግሎት ዚሚያኚናውኑት ሥራ ነበራ቞ው።
በመሆኑም ለእያንዳንዱ በር፣ ትንሜ ትልቅ ሳይባል ለሁሉም በዚአባቶቻ቞ው ቀት ዕጣ ተጣለ።
ኚዚያም ዚምሥራቁ በር ዕጣ ለሞሌምያህ ወጣ። አስተዋይ መካሪ ለሆነው ለልጁ ለዘካርያስ ዕጣ ጣሉፀ በዕጣውም መሠሚት ዹሰሜን በር ደሚሰው።
ኊቀድዔዶም በደቡብ በኩል ያለው በር ደሚሰውፀ ወንዶቜ ልጆቹ ደግሞ ግምጃ ቀቶቹ ደሚሷ቞ው።
ሹፒም እና ሆሳ በአቀበቱ መንገድ ባለው በሻለኚት በር አቅራቢያ ዹሚገኘው ዚምዕራብ በር ደሚሳ቞ውፀ ዚዘብ ጠባቂ ቡድኖቹ ጎን ለጎን ቆመው ይጠብቁ ነበርፀ
በምሥራቅ በኩል ስድስት ሌዋውያን ነበሩፀ በሰሜን በኩል በዹቀኑ አራት፣ በደቡብ በኩል በዹቀኑ አራት እንዲሁም ግምጃ ቀቶቹን ሁለት ሁለት ሆነው ይጠብቁ ነበርፀ
በምዕራብ በኩል ባለው መተላለፊያ በጎዳናው ላይ አራት፣ በመተላለፊያው ላይ ደግሞ ሁለት ሆነው ይጠብቁ ነበር።
ዚቆሬያውያንና ዚሜራራውያን ወንዶቜ ልጆቜ ዹበር ጥበቃ ምድብ ይህ ነበር።
ኚሌዋውያን መካኚል አኪያህ በእውነተኛው አምላክ ቀት ዚሚገኙት ግምጃ ቀቶቜና ቅዱስ ዹሆኑ ነገሮቜ ያሉባ቞ው ግምጃ ቀቶቜ ኃላፊ ነበር።
ዚላዳን ወንዶቜ ልጆቜፊ ዚላዳን ወገን ኚሆኑት ኚጌድሶናውያን ወንዶቜ ልጆቜ ማለትም ዚጌድሶናዊው ዚላዳን ወገን ኚሆኑት ዚዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜ መሪዎቜ መካኚል ዚሂኀሊ
እንዲሁም ዚዚሂኀሊ ወንዶቜ ልጆቜ ዜታምና ወንድሙ ኢዩኀል ነበሩ። እነሱም በይሖዋ ቀት ዚሚገኙት ግምጃ ቀቶቜ ኃላፊዎቜ ነበሩ።
ኚአምራማውያን፣ ኚይጜሃራውያን፣ ኚኬብሮናውያን እና ኚዑዚኀላውያን መካኚል፣
ዹሙሮ ልጅ፣ ዚጌርሳም ልጅ ሞቡኀል ዹግምጃ ቀቶቹ ኃላፊ ነበር።
ዚኀሊዔዘር ዘሮቜ ዚሆኑት ወንድሞቹ ሚሃቢያህ፣ ዚሻያህ፣ ዮራም፣ ዚክሪ እና ሞሎሞት ነበሩ።
ሞሎሞትና ወንድሞቹ ንጉሥ ዳዊት፣ ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ፣ ዚሺህ አለቆቹ፣ ዚመቶ አለቆቹና ዚሠራዊቱ አለቆቜ ዚቀደሷ቞ው ቅዱስ ነገሮቜ ዚሚገኙባ቞ው ግምጃ ቀቶቜ ሁሉ ኃላፊዎቜ ነበሩ።
ዹይሖዋን ቀት ለማደስ በጊርነት ኹተገኘው ምርኮ ውስጥ ዹተወሰነውን ቀደሱፀ
በተጚማሪም ባለ ራእዩ ሳሙኀል፣ ዚቂስ ልጅ ሳኊል፣ ዹኔር ልጅ አበኔር እና ዚጜሩያ ልጅ ኢዮዓብ ዚቀደሷ቞ውን ነገሮቜ ሁሉ በኃላፊነት ይይዙ ነበር። ማንኛውም ሰው ዹቀደሰው ነገር በሞሎሚት እና በወንድሞቹ እጅ ይሆን ነበር።
ኚይጜሃራውያን መካኚል ኬናንያ እና ወንዶቜ ልጆቹ ኹአምላክ ቀት ውጭ ባለው ዚአስተዳደር ሥራ ላይ በእስራኀል አለቆቜና ዳኞቜ ሆነው ተመደቡ።
ኚኬብሮናውያን መካኚል ብቁ ዚሆኑት ሃሻብያህ እና ወንድሞቹ 1,700 ነበሩፀ እነሱም ኚዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ባለው ዚእስራኀል ምድር ኹይሖዋ ሥራ ሁሉና ኚንጉሡ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ዚማስተዳደር ኃላፊነት ተሰጥቷ቞ው ነበር።
ዚሪያህ ዚኬብሮናውያን አባቶቜ ቀቶቜና ቀተሰቊቜ መሪ ነበር። በዳዊት ዘመነ መንግሥት 40ኛ ዓመት ምርመራ ተካሄደፀ በእነሱም መካኚል በጊልያድ፣ ያዜር በተባለ ቊታ ኃያላን ዹሆኑና ብቃት ያላ቞ው ሰዎቜ ተገኙ።
ዚአባቶቜ ቀቶቜ መሪዎቜ ዹሆኑ ብቃት ያላ቞ው ወንድሞቹ 2,700 ነበሩ። በመሆኑም ንጉሥ ዳዊት ኚእውነተኛው አምላክና ኚንጉሡ ጉዳዮቜ ሁሉ ጋር በተያያዘ በሮቀላውያን፣ በጋዳውያንና በምናሎያውያን ነገድ እኩሌታ ላይ ሟማ቞ው።
አዳም፣ሎት፣ሄኖስ፣
ቃይናን፣መላልኀል፣ያሬድ፣
ሄኖክ፣ማቱሳላ፣ላሜህ፣
ኖኅ፣ሎም፣ ካምና ያፌት።
ዚያፌት ወንዶቜ ልጆቜ ጎሜር፣ ማጎግ፣ ማዳይ፣ ያዋን፣ ቱባል፣ መሌቅ እና ቲራስ ነበሩ።
ዹጎሜር ወንዶቜ ልጆቜ አሜኚናዝ፣ ሪፋት እና ቶጋርማ ነበሩ።
ዚያዋን ወንዶቜ ልጆቜ ኀሊሻ፣ ተርሎስ፣ ኪቲም እና ሮዳኒም ነበሩ።
ዚካም ወንዶቜ ልጆቜ ኩሜ፣ ሚጜራይም፣ ፑጥ እና ኹነአን ነበሩ።
ዚኩሜ ወንዶቜ ልጆቜ ሎባ፣ ሃዊላ፣ ሳብታ፣ ራአማ እና ሳብተካ ነበሩ። ዚራአማ ወንዶቜ ልጆቜ ሳባ እና ዎዳን ነበሩ።
ኩሜ ናምሩድን ወለደ። እሱም በምድር ላይ ዚመጀመሪያው ኃያል ሰው ነበር።
ሚጜራይም ሉድን፣ አናሚምን፣ ለሃቢምን፣ ናፊቱሂምን፣
ጳትሩሲምን፣ ካስሉሂምን (ፍልስጀማውያን ዚተገኙት ኚእሱ ነው) እንዲሁም ካፍቶሪምን ወለደ።
ኹነአን ዚበኩር ልጁን ሲዶናን፣ ሄትን
እንዲሁም ኢያቡሳዊውን፣ አሞራዊውን፣ ገርጌሻዊውን፣
ሂዋዊውን፣ አርቃዊውን፣ ሲናዊውን፣
አርዋዳዊውን፣ ጞማራዊውን እና ሃማታዊውን ወለደ።
ዹሮም ወንዶቜ ልጆቜ ኀላም፣ አሹር፣ አርፋክስድ፣ ሉድ እና አራምእንዲሁም ዑጜ፣ ሁል፣ ጌተር እና ማሜ ነበሩ።
አርፋክስድ ሮሎምን ወለደፀ ሮሎምም ኀቀርን ወለደ።
ኀቀር ሁለት ወንዶቜ ልጆቜን ወለደ። ዹአንደኛው ስም ፋሌቅ ነበርፀ ምክንያቱም በእሱ ዚሕይወት ዘመን ምድር ተኹፋፍላ ነበር። ዚወንድሙ ስም ደግሞ ዮቅጣን ነበር።
ዮቅጣን አልሞዳድን፣ ሞሌፍን፣ ሃጻርማዌትን፣ ያራህን፣
ሃዶራምን፣ ዑዛልን፣ ዲቅላን፣
ኊባልን፣ አቢማዔልን፣ ሳባን፣
ኊፊርን፣ ሃዊላን እና ዮባብን ወለደፀ እነዚህ ሁሉ ዚዮቅጣን ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
ሎም፣አርፋክስድ፣ሎሎም፣
ኀቀር፣ፋሌቅ፣ሚኡ፣
ሎሮህ፣ናኮር፣ታራ፣
አብራም ማለትም አብርሃም።
ዚአብርሃም ወንዶቜ ልጆቜ ይስሐቅ እና እስማኀል ነበሩ።
ዚቀተሰብ ዹዘር ሐሹጋቾው ዹሚኹተለው ነው፩ ዚእስማኀል ዚበኩር ልጅ ነባዮት ኚዚያም ቄዳር፣ አድበዔል፣ ሚብሳም፣
ሚሜማ፣ ዱማ፣ ማሳ፣ ሃዳድ፣ ቎ማ፣
ዚጡር፣ ናፊሜ እና ቄድማ። እነዚህ ዚእስማኀል ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
ዚአብርሃም ቁባት ዚነበሚቜው ኬጡራ ዚወለደቻ቞ው ወንዶቜ ልጆቜ ዚምራን፣ ዮቅሻን፣ ሚዳን፣ ምድያም፣ ይሜባቅ እና ሹሃ ነበሩ። ዚዮቅሻን ወንዶቜ ልጆቜ ሳባ እና ዎዳን ነበሩ።
ዚምድያም ወንዶቜ ልጆቜ ኀፋ፣ ኀፌር፣ ሃኖክ፣ አቢዳዕ እና ኀልዳዓ ነበሩ። እነዚህ ሁሉ ዚኬጡራ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
አብርሃም ይስሐቅን ወለደ። ዚይስሐቅ ወንዶቜ ልጆቜ ኀሳው እና እስራኀል ነበሩ።
ዚኀሳው ወንዶቜ ልጆቜ ኀሊፋዝ፣ ሚኡዔል፣ ዚኡሜ፣ ያላም እና ቆሬ ነበሩ።