text
stringlengths
4
267
ሆኖም ዹይሖዋ ቁጣ በዖዛ ላይ ስለነደደ ዳዊት ተበሳጚፀ ያም ቊታ እስኚ ዛሬ ድሚስ ጎሬዝዖዛ ተብሎ ይጠራል።
ዳዊትም በዚያን ዕለት እውነተኛውን አምላክ ፈርቶ “ታዲያ ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት እንዎት ወደ እኔ ማምጣት እቜላለሁ?” አለ።
ዳዊት ታቊቱን እሱ ወዳለበት ወደ ዳዊት ኹተማ አላመጣውምፀ ይልቁንም ዚጌት ሰው ወደሆነው ወደ ኊቀድዔዶም ቀት እንዲወሰድ አደሚገ።
ዚእውነተኛው አምላክ ታቊት ኚኊቀድዔዶም ቀተሰብ ጋር በቀቱ ለሊስት ወራት ያህል ተቀመጠፀ ይሖዋም ዚኊቀድዔዶምን ቀተሰብና ያለውን ሁሉ ባሚኚ።
ኚዚያም ሰይጣን እስራኀልን ለማጥቃት ቆርጩ ተነሳፀ ደግሞም እስራኀልን እንዲቆጥር ዳዊትን አነሳሳው።
በመሆኑም ዳዊት ኢዮዓብንና ዚሕዝቡን አለቆቜ “ሂዱና ኚቀርሳቀህ አንስቶ እስኚ ዳን ድሚስ ያሉትን እስራኀላውያን ቁጠሩፀ ኚዚያም ቁጥራ቞ውን አውቅ ዘንድ ንገሩኝ” አላ቞ው።
ኢዮዓብ ግን እንዲህ አለ፩ “ይሖዋ ሕዝቡን 100 እጥፍ ያብዛው! ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፣ ሁሉም ዚጌታዬ አገልጋዮቜ አይደሉም? ጌታዬ ይህን ማድሚግ ለምን ፈለገ? በእስራኀልስ ላይ ለምን በደል ያመጣል?”
ይሁን እንጂ ዚንጉሡ ቃል በኢዮዓብ ላይ አዚለ። በመሆኑም ኢዮዓብ ወጥቶ በመላው እስራኀል ተጓዘፀ ኚዚያም ወደ ኢዚሩሳሌም ተመለሰ።
ኢዮዓብም ዹተመዘገበውን ዚሕዝቡን ቁጥር ለዳዊት ሰጠው። በመላው እስራኀል ሰይፍ ዚታጠቁ 1,100,000 ወንዶቜ ነበሩፀ በይሁዳ ደግሞ ሰይፍ ዚታጠቁ 470,000 ወንዶቜ ነበሩ።
ይሁንና ኢዮዓብ ዚንጉሡን ቃል ተጾይፎ ስለነበር ሌዊንና ቢንያምን በቆጠራው ውስጥ አላካተተም።
ይህ ነገር እውነተኛውን አምላክ በጣም አስቆጣውፀ በመሆኑም እስራኀልን መታ።
በዚህ ጊዜ ዳዊት እውነተኛውን አምላክ እንዲህ አለ፩ “ይህን በማድሚጌ ኚባድ ኃጢአት ፈጜሜአለሁ። አሁንም እባክህ ዹአገልጋይህን በደል ይቅር በልፀ ታላቅ ዚሞኝነት ድርጊት ፈጜሜአለሁና።”
ይሖዋም ዚዳዊት ባለ ራእይ ዹሆነውን ጋድን እንዲህ አለው፩
“ሂድና ዳዊትን እንዲህ በለው፩ ‘ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ሊስት ምርጫዎቜን ሰጥቌሃለሁ። በአንተ ላይ አመጣብህ ዘንድ አንዱን ምሚጥ።”’”
ስለዚህ ጋድ ወደ ዳዊት ገብቶ እንዲህ አለው፩ “ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ኚእነዚህ ውስጥ አንዱን ምሚጥፀ
ለሊስት ዓመት ሚሃብ ይሁን ወይስ ዚጠላቶቜህ ሰይፍ አሾንፎህ ለሊስት ወራት ጠላቶቜህ ጥፋት ያድርሱብህ ወይስ ለሊስት ቀናት ዹይሖዋ ሰይፍ ይኾውም ቾነፈር በምድሪቱ ላይ መጥቶ ዹይሖዋ መልአክ በመላው ዚእስራኀል ግዛት ጥፋት ያምጣ?’ እንግዲህ አሁን ለላኹኝ ምን መልስ እንደምሰጥ አስብበት።”
ስለዚህ ዳዊት ጋድን እንዲህ አለው፩ “ሁኔታው በጣም አስጚንቆኛል። ምሕሚቱ እጅግ ታላቅ ስለሆነ እባክህ በይሖዋ እጅ ልውደቅፀ ሰው እጅ ላይ ግን አትጣለኝ።”
ኚዚያም ይሖዋ በእስራኀል ላይ ቾነፈር ላኚፀ በዚህም ዚተነሳ ኚእስራኀል 70,000 ሰዎቜ ሞቱ።
በተጚማሪም እውነተኛው አምላክ ኢዚሩሳሌምን እንዲያጠፋ መልአክ ላኚፀ ሆኖም መልአኩ ሊያጠፋት ሲል ይሖዋ ሁኔታውን አይቶ በደሹሰው ጥፋት ተጞጞተፀ ስለሆነም ዚሚያጠፋውን መልአክ “ይብቃ! አሁን እጅህን መልስ” አለው። ዹይሖዋ መልአክ በኢያቡሳዊው በኩርናን አውድማ አጠገብ ቆሞ ነበር።
ዳዊት ቀና ብሎ ሲመለኚት ዹይሖዋ መልአክ በምድርና በሰማያት መካኚል ቆሞ አዚፀ እሱም በኢዚሩሳሌም ላይ ዹተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ነበር። ዳዊትና ሜማግሌዎቹ ማቅ እንደለበሱ ወዲያውኑ በግንባራ቞ው መሬት ላይ ተደፉ።
ዳዊትም እውነተኛውን አምላክ እንዲህ አለ፩ “ሕዝቡ እንዲቆጠር ያዘዝኩት እኔ አይደለሁም? ኃጢአት ዚሠራሁት እኔ ነኝፀ በደል ዚፈጞምኩትም እኔ ነኝፀ ታዲያ እነዚህ በጎቜ ምን አደሹጉ? አምላኬ ይሖዋ ሆይ፣ እባክህ እጅህ በእኔና በአባ቎ ቀት ላይ ትሁንፀ በሕዝብህ ላይ ግን ይህን መቅሰፍት አታውርድ።”
በዚህ ጊዜ ዹይሖዋ መልአክ፣ ዳዊት ወጥቶ በኢያቡሳዊው በኩርናን አውድማ ላይ ለይሖዋ መሠዊያ እንዲሠራ ለዳዊት እንዲነግሚው ጋድን አዘዘው።
ዳዊትም ጋድ በይሖዋ ስም በነገሹው ቃል መሠሚት ወጣ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኩርናን ዞር ሲል መልአኩን አዚውፀ ኚእሱ ጋር ዚነበሩት አራት ወንዶቜ ልጆቹም ተሞሞጉ። በዚህ ጊዜ ኩርናን ስንዎ እዚወቃ ነበር።
ኩርናን ቀና ብሎ ሲመለኚት ዳዊት ወደ እሱ ሲመጣ አዚፀ ወዲያውኑም ኚአውድማው ወጥቶ በግንባሩ መሬት ላይ በመደፋት ለዳዊት ሰገደ።
ዳዊትም ኩርናንን እንዲህ አለው፩ “ለይሖዋ መሠዊያ እንድሠራበት አውድማውን ሜጥልኝ። በሕዝቡ ላይ ዹሚወርደው መቅሰፍት እንዲቆም ሙሉውን ዋጋ ኚፍዬ ልግዛው።”
ኩርናን ግን ዳዊትን እንዲህ አለው፩ “በነፃ ውሰደውፀ ጌታዬ ንጉሡ መልካም መስሎ ዚታዚውን ያድርግ። እነሆ ኚብቶቹን ለሚቃጠል መባ፣ ማሄጃውን ለማገዶ፣ ስንዎውን ደግሞ ለእህል መባ አቀርባለሁ። ሁሉንም ነገር እኔ እሰጣለሁ።”
ይሁን እንጂ ንጉሥ ዳዊት ኩርናንን እንዲህ አለው፩ “በፍጹም አይሆንም! ሙሉውን ዋጋ ሰጥቌ እገዛዋለሁፀ ምክንያቱም ዹአንተ ዹሆነውን ነገር ወስጄ ለይሖዋ አልሰጥም ወይም ምንም ያልኚፈልኩበትን ነገር ዹሚቃጠል መሥዋዕት አድርጌ አላቀርብም።”
በመሆኑም ዳዊት ዚቊታውን ዋጋ 600 ዹወርቅ ሰቅል መዝኖ ለኩርናን ሰጠው።
ዳዊትም በዚያ ለይሖዋ መሠዊያ ሠርቶ ዹሚቃጠሉ መሥዋዕቶቜና ዚኅብሚት መሥዋዕቶቜ አቀሚበፀ ዹይሖዋንም ስም ጠራፀ እሱም ዹሚቃጠል መባ በሚቀርብበት መሠዊያ ላይ ኚሰማያት በእሳት መለሰለት።
ኚዚያም ይሖዋ መልአኩን ሰይፉን ወደ ሰገባው እንዲመልስ አዘዘው።
በዚህ ጊዜ ዳዊት፣ ይሖዋ በኢያቡሳዊው በኩርናን አውድማ መልስ እንደሰጠው ባዚ ጊዜ በዚያ ቊታ ላይ መሥዋዕት ማቅሚቡን ቀጠለ።
ሆኖም ሙሮ በምድሚ በዳ ዚሠራው ዹይሖዋ ዚማደሪያ ድንኳንና ዹሚቃጠል መባ ዚሚቀርብበት መሠዊያ በዚያን ጊዜ በገባኊን ባለው ኹፍ ያለ ቊታ ላይ ይገኝ ነበር።
ይሁንና ዳዊት ኹይሖዋ መልአክ ሰይፍ ዚተነሳ እጅግ ፈርቶ ስለነበር አምላክን ለመጠዹቅ ወደዚያ መሄድ አልቻለም።
ዳዊት በኬብሮን ሳለ ዚተወለዱለት ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ናቾው፩ ዚበኩር ልጁ አምኖንፀ እናቱ ኢይዝራኀላዊቷ አኪኖዓም ነበሚቜፀ ሁለተኛው ልጁ ዳንኀልፀ እናቱ ቀርሜሎሳዊቷ አቢጋኀል ነበሚቜፀ
ዚገሹር ንጉሥ ዚታልማይ ልጅ ኚሆነቜው ኚማአካ ዹወለደው ሊስተኛው ልጁ አቢሎሎምፀ ኚሃጊት ዹወለደው አራተኛው ልጁ አዶንያስፀ
አምስተኛው ልጁ ሰፋጥያህፀ እናቱ አቢጣል ነበሚቜፀ ስድስተኛው ልጁ ይትሚአምፀ እናቱ ዚዳዊት ሚስት ኀግላ ነበሚቜ።
እነዚህ ስድስቱ በኬብሮን ሳለ ዚተወለዱለት ና቞ውፀ በዚያም ለ7 ዓመት ኹ6 ወር ነገሠፀ በኢዚሩሳሌም ደግሞ 33 ዓመት ነገሠ።
በኢዚሩሳሌም ዚተወለዱለት እነዚህ ናቾው፩ ሺምአ፣ ሟባብ፣ ናታን እና ሰለሞንፀ ዚእነዚህ ዚአራቱ ልጆቜ እናት ዹአሚዔል ልጅ ቀርሳቀህ ነበሚቜ።
ሌሎቹ ዘጠኝ ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ ይብሃር፣ ኀሊሻማ፣ ኀሊፌሌት፣
ኖጋ፣ ኔፌግ፣ ያፊአ፣
ኀሊሻማ፣ ኀሊያዳ እና ኀሊፌሌት ና቞ው።
ኚቁባቶቹ ኚወለዳ቞ው ወንዶቜ ልጆቜ ሌላ እነዚህ ሁሉ ዚዳዊት ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ እህታ቞ውም ትዕማር ትባል ነበር።
ዹሰለሞን ልጅ ሮብዓም፣ ዚሮብዓም ልጅ አቢያህ፣ ዚአቢያህ ልጅ አሳ፣ ዚአሳ ልጅ ኢዮሳፍጥ፣
ዚኢዮሳፍጥ ልጅ ኢዮራም፣ ዚኢዮራም ልጅ አካዝያስ፣ ዚአካዝያስ ልጅ ኢዮዓስ፣
ዚኢዮዓስ ልጅ አሜስያስ፣ ዚአሜስያስ ልጅ አዛርያስ፣ ዚአዛርያስ ልጅ ኢዮዓታም፣
ዚኢዮዓታም ልጅ አካዝ፣ ዚአካዝ ልጅ ሕዝቅያስ፣ ዚሕዝቅያስ ልጅ ምናሎ፣
ዹምናሮ ልጅ አምዖን፣ ዹአምዖን ልጅ ኢዮስያስ።
ዚኢዮስያስ ወንዶቜ ልጆቜ ዚበኩር ልጁ ዮሃናን፣ ሁለተኛው ልጁ ኢዮዓቄም፣ ሊስተኛው ልጁ ሎዎቅያስ እና አራተኛው ልጁ ሻሉም ነበሩ።
ዚኢዮዓቄም ወንዶቜ ልጆቜ ልጁ ኢኮንያን እና ልጁ ሎዎቅያስ ነበሩ።
ዚእስሚኛው ዚኢኮንያን ወንዶቜ ልጆቜ ሰላትያል፣
ማልኪራም፣ ፐዳያህ፣ ሞናጻር፣ ዚቃምያህ፣ ሆሻማ እና ነዳብያህ ነበሩ።
ዚፐዳያህ ወንዶቜ ልጆቜ ዘሩባቀል እና ሺምአይ ነበሩፀ ዚዘሩባቀል ወንዶቜ ልጆቜም መሹላም እና ሃናንያህ ነበሩ (ሞሎሚትም እህታ቞ው ነበሚቜ)ፀ
ሌሎቹ አምስት ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ ሃሹባ፣ ኊሄል፣ ቀራክያህ፣ ሃሳድያህ እና ዮሻብሄሎድ ነበሩ።
ዚሃናንያህ ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ ጰላጥያህ እና ዚሻያህ ነበሩፀ ዚዚሻያህ ልጅ ሚፋያህ ነበርፀ ዚሚፋያህ ልጅ አርናን ነበርፀ ዹአርናን ልጅ አብድዩ ነበርፀ ዚአብድዩ ልጅ ሞካንያህ ነበርፀ
ዚሞካንያህ ዘሮቜ ሞማያህና ዚሞማያህ ልጆቜ ና቞ውፀ እነሱም ሃጡሜ፣ ይግዓል፣ ባሪያህ፣ ነአርያህ እና ሻፋጥ ሲሆኑ በአጠቃላይ ስድስት ነበሩ።
ዚነአርያህ ወንዶቜ ልጆቜ ኀሊዮዔናይ፣ ሂዝቅያህ እና አዝሪቃም ሲሆኑ በአጠቃላይ ሊስት ነበሩ።
ዚኀሊዮዔናይ ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ ሆዳውያህ፣ ኀልያሺብ፣ ፐላያህ፣ አቁብ፣ ዮሃናን፣ ደላያህ እና አናኒ ሲሆኑ በአጠቃላይ ሰባት ነበሩ።
እስራኀላውያን በሙሉ በዚትውልድ ሐሹጋቾው ተመዘገቡፀ በእስራኀል ነገሥታት መጜሐፍም ላይ ተጻፉ። ዚይሁዳም ሰዎቜ ታማኝ ባለመሆና቞ው ዚተነሳ ወደ ባቢሎን በግዞት ተወሰዱ።
በኚተሞቻ቞ው ወደሚገኙት ርስቶቻ቞ው ዚተመለሱት ዚመጀመሪያዎቹ ነዋሪዎቜ አንዳንድ እስራኀላውያን፣ ካህናቱ፣ ሌዋውያኑና ዚቀተ መቅደሱ አገልጋዮቜ ነበሩ።
ዹተወሰኑ ዚይሁዳ፣ ዚቢንያም፣ ዚኀፍሬምና ዹምናሮ ዘሮቜ በኢዚሩሳሌም ተቀመጡፊ
ኚይሁዳ ልጅ፣ ኚፋሬስ ዘሮቜ መካኚል ዚባኒ ልጅ፣ ዚኢምሪ ልጅ፣ ዚኊምሪ ልጅ፣ ዚአሚሁድ ልጅ ዑታይ።
ኚሎሎናውያንም ዚበኩር ልጅ ዹሆነው አሳያህ እና ወንዶቜ ልጆቹ።
ኚዛራ ልጆቜ መካኚል ደግሞ፣ ዚኡዔል እና 690 ወንድሞቻ቞ው ነበሩ።
በዚያ ዚተቀመጡት ዚቢንያም ዘሮቜም ዚሚኚተሉት ናቾው፩ ዚሃስኑአ ልጅ፣ ዚሆዳውያህ ልጅ፣ ዚመሹላም ልጅ ሳሉፀ
ዚዚሮሃም ልጅ ይብኔያህ፣ ዚሚክሪ ልጅ፣ ዹዑዚ ልጅ ኀላህ፣ ዚይብኒያህ ልጅ፣ ዚሚኡዔል ልጅ፣ ዚሰፋጥያህ ልጅ መሹላም።
በዘር ሐሹጉ መዝገብ ላይ ዚሰፈሩት ወንድሞቻ቞ውም 956 ነበሩ። እነዚህ ሁሉ ወንዶቜ በዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ ነበሩ።
ኚካህናቱም ዚዳያህ፣ ዚሆያሪብ፣ ያኪን፣
ዚእውነተኛው አምላክ ቀት መሪ ዹሆነው ዚአኪጡብ ልጅ፣ ዚመራዮት ልጅ፣ ዚሳዶቅ ልጅ፣ ዚመሹላም ልጅ፣ ዚኬልቅያስ ልጅ አዛርያስ፣
ዚማልኪያህ ልጅ፣ ዚጳስኮር ልጅ፣ ዚዚሮሃም ልጅ አዳያህ፣ ዚኢሜር ልጅ፣ ዚመሺሌሚት ልጅ፣ ዚመሹላም ልጅ፣ ዚያህዜራ ልጅ፣ ዚአዲዔል ልጅ ማአሳይ፣
እንዲሁም ዚዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ ዚሆኑት ወንድሞቻ቞ው ነበሩፀ እነሱም 1,760 ሲሆኑ ለእውነተኛው አምላክ ቀት አገልግሎት ዝግጁ ዹሆኑ ኃያላንና ብቁ ሰዎቜ ነበሩ።
ኚሌዋውያኑም ኚሜራሪ ዘሮቜ መካኚል ዚሚኚተሉት ይገኙበታልፊ ዚሃሻብያህ ልጅ፣ ዚአዝሪቃም ልጅ፣ ዚሃሹብ ልጅ ሞማያህ፣
ባቅባቃር፣ ሄሬሜ፣ ጋላል፣ ዚአሳፍ ልጅ፣ ዚዚክሪ ልጅ፣ ዚሚካ ልጅ ማታንያህ፣
ዚዚዱቱን ልጅ፣ ዹጋላል ልጅ፣ ዚሞማያህ ልጅ አብድዩ እንዲሁም ዹሕልቃና ልጅ፣ ዚአሳ ልጅ ቀራክያህ። እሱም በነጊፋውያን ሰፈር ይኖር ነበር።
በር ጠባቂዎቹ ሻሉም፣ አቁብ፣ ታልሞን እና አሂማን ነበሩፀ ወንድማ቞ው ሻሉምም መሪ ነበርፀ
እሱም እስኚዚያን ጊዜ ድሚስ በስተ ምሥራቅ በኩል በሚገኘው በንጉሡ በር ላይ ነበር። እነዚህ ዚሌዋውያንን ሰፈሮቜ ዚሚጠብቁ በር ጠባቂዎቜ ነበሩ።
ዚቆሬ ልጅ፣ ዚኀቢያሳፍ ልጅ፣ ዹቆሹ ልጅ ሻሉም እና ዚአባቱ ቀት ወገን ዚሆኑት ወንድሞቹ ቆሬያውያን ዚድንኳኑ በር ጠባቂዎቜ በመሆን በዚያ ዹሚኹናወነውን አገልግሎት በበላይነት ይቆጣጠሩ ነበርፀ አባቶቻ቞ው ደግሞ ዚመግቢያው ጠባቂዎቜ በመሆን ዹይሖዋን ሰፈር በበላይነት ይቆጣጠሩ ነበር።
ኹዚህ በፊት ዚእነሱ መሪ ዹነበሹው ዹአልዓዛር ልጅ ፊንሃስ ሲሆን ይሖዋም ኚእሱ ጋር ነበር።
ዚመሺሌሚያህ ልጅ ዘካርያስ ዹመገናኛ ድንኳኑ መግቢያ በር ጠባቂ ነበር።
በደጆቹ ላይ ቆመው እንዲጠብቁ ዚተመሚጡት በአጠቃላይ 212 ነበሩ። እነሱም በትውልድ ሐሹግ መዝገቡ ላይ ተጜፎ በሚገኘው መሠሚት በሰፈሮቻ቞ው ውስጥ ይኖሩ ነበር። ዳዊትና ባለ ራእዩ ሳሙኀል እነዚህን ሰዎቜ ታማኝነት በሚጠይቀው ቊታ ላይ ሟሟ቞ው።
እነሱና ወንዶቜ ልጆቻ቞ው ዹይሖዋን ቀት ይኾውም ዚማደሪያ ድንኳኑን በሮቜ ዹመጠበቅ ኃላፊነት ተሰጥቷ቞ው ነበር።
በር ጠባቂዎቹ በአራቱም አቅጣጫዎቜ ማለትም በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜንና በደቡብ በኩል ነበሩ።
በዚሰፈሮቻ቞ው ዚሚኖሩት ወንድሞቻ቞ው ለሰባት ቀናት አብሚዋ቞ው ለማገልገል አልፎ አልፎ ይመጡ ነበር።
ታማኝነት በሚጠይቀው ቊታ ላይ ዚሚያገለግሉ አራት ዹበር ጠባቂ አለቆቜ ነበሩ። እነሱም ሌዋውያን ሲሆኑ በእውነተኛው አምላክ ቀት ዚሚገኙትን ክፍሎቜና ግምጃ ቀቶቜ ዹመጠበቅ ኃላፊነት ተሰጥቷ቞ው ነበር።
በእውነተኛው አምላክ ቀት ዙሪያ በተመደቡበት ቊታ ላይ ሆነው ያድሩ ነበርፀ ዚጥበቃውን ሥራ ዚሚያኚናውኑት እንዲሁም ቁልፉ ዚተሰጣ቞ውና ቀቱን በዚጠዋቱ ዚሚኚፍቱት እነሱ ነበሩ።
ኚእነሱ መካኚል ዚተወሰኑት ለአገልግሎት ዚሚውሉትን ዕቃዎቜ ዚመቆጣጠር ኃላፊነት ነበሚባ቞ውፀ እነሱም ዕቃዎቹን በሚያስገቡበትም ሆነ በሚያወጡበት ጊዜ ይቆጥሯ቞ው ነበር።
ዚተወሰኑት ደግሞ ሌሎቹን ዕቃዎቜ፣ ቅዱስ ዚሆኑትን ዕቃዎቜ በሙሉ፣ ዹላመውን ዱቄት፣ ዹወይን ጠጁን፣ ዘይቱን፣ ነጭ ዕጣኑንና ዚበለሳን ዘይቱን እንዲቆጣጠሩ ተሹመው ነበር።
ኚካህናቱ ልጆቜ መካኚል አንዳንዶቹ ዚበለሳን ዘይት ዚተቀላቀለበት ቅባት ያዘጋጁ ነበር።
ዚቆሬያዊው ዚሻሉም ዚበኩር ልጅ ዹሆነው ሌዋዊው ማቲትያህ በምጣድ ላይ ኚሚጋገሩት ነገሮቜ ጋር በተያያዘ ታማኝነት በሚጠይቀው ቊታ ላይ ተመድቊ ነበር።
ወንድሞቻ቞ው ኚሆኑት ኚቀዓታውያን አንዳንዶቹ ዚሚነባበሚውን ዳቊ በዚሰንበቱ ዚማዘጋጀት ኃላፊነት ነበራ቞ው።
እነዚህ ዚሌዋውያን አባቶቜ ቀት መሪዎቜ ዹሆኑ ዘማሪዎቜ ነበሩፀ ኚሌሎቜ ሥራዎቜ ነፃ እንዲሆኑ ዚተደሚጉት እነዚህ ሰዎቜ በክፍሎቹ ውስጥ ይቀመጡ ነበር። ምክንያቱም ቀንም ሆነ ሌሊት በሥራ቞ው ላይ ዚመገኘት ኃላፊነት ነበሚባ቞ው።
እነዚህ በትውልድ ሐሹጉ መዝገብ ላይ እንደሰፈሚው ዚሌዋውያን ቀተሰቊቜ መሪዎቜ ነበሩ። ዚሚኖሩትም በኢዚሩሳሌም ነበር።
ዚገባኊን አባት ዚኢዔል በገባኊን ይኖር ነበር። ዚሚስቱ ስም ማአካ ይባል ነበር።
ዚበኩር ልጁ አብዶን ሲሆን ሌሎቹ ልጆቹ ደግሞ ጹር፣ ቂስ፣ ባአል፣ ኔር፣ ናዳብ፣
ጌዶር፣ አሂዮ፣ ዘካርያስ እና ሚቅሎት ነበሩ።
ሚቅሎት ሺምአምን ወለደ። እነዚህ ሁሉ ኚሌሎቜ ወንድሞቻ቞ው ጋር ሆነው በወንድሞቻ቞ው አቅራቢያ በኢዚሩሳሌም ይኖሩ ነበር።
ኔር ቂስን ወለደፀ ቂስ ሳኊልን ወለደፀ ሳኊል ዮናታንን፣ ሜልኪሳን፣ አቢናዳብን እና ኀሜባዓልን ወለደ።
ዚዮናታን ልጅ መሪበኣል ነበር። መሪበኣል ሚክያስን ወለደ።
ዚሚክያስ ወንዶቜ ልጆቜ ፒቶን፣ ሜሌክ፣ ታህሬአ እና አካዝ ነበሩ።
አካዝ ያራን ወለደፀ ያራ አለሜትን፣ አዝማዌትንና ዚምሪን ወለደ። ዚምሪ ሞጻን ወለደ።