text
stringlengths
4
267
ዚኀሊፋዝ ወንዶቜ ልጆቜ ቎ማን፣ ኊማር፣ ጞፎ፣ ጋታም፣ ቀናዝ፣ ቲምና እና አማሌቅ ነበሩ።
ዚሚኡዔል ወንዶቜ ልጆቜ ናሃት፣ ዛራ፣ ሻማህ እና ሚዛህ ነበሩ።
ዹሮይር ወንዶቜ ልጆቜ ሎጣን፣ ሟባል፣ ጺብኊን፣ አና፣ ዲሟን፣ ኀጌር እና ዲሻን ነበሩ።
ዚሎጣን ወንዶቜ ልጆቜ ሆሪ እና ሆማም ነበሩ። ዚሎጣን እህት ቲምና ትባል ነበር።
ዚሟባል ወንዶቜ ልጆቜ አልዋን፣ ማናሃት፣ ኀባል፣ ሌፎ እና ኩናም ነበሩ። ዚጺብኊን ወንዶቜ ልጆቜ አያ እና አና ነበሩ።
ዹአና ልጅ ዲሟን ነበር። ዚዲሟን ወንዶቜ ልጆቜ ሄምዳን፣ ኀሜባን፣ ይትራን እና ኬራን ነበሩ።
ዚኀጌር ወንዶቜ ልጆቜ ቢልሃን፣ ዛአዋን እና አቃን ነበሩ። ዚዲሻን ወንዶቜ ልጆቜ ዑጜ እና አራን ነበሩ።
እነዚህ በእስራኀላውያን ላይ ዚትኛውም ንጉሥ መግዛት ኚመጀመሩ በፊት በኀዶም ምድር ይገዙ ዚነበሩ ነገሥታት ናቾው፩ ዚቢዖር ልጅ ቀላ፣ ዹኹተማውም ስም ዲንሃባ ይባል ነበር።
ቀላ ሲሞት ዚቊስራው ዚዛራ ልጅ ዮባብ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ዮባብ ሲሞት ኚ቎ማናውያን ምድር ዚመጣው ሁሻም በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ሁሻም ሲሞት ምድያምን በሞዓብ ምድር ድል ያደሚገው ዚቀዳድ ልጅ ሃዳድ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ። ዹኹተማው ስም አዊት ይባል ነበር።
ሃዳድ ሲሞት ዚማስሚቃው ሳምላ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ሳምላ ሲሞት በወንዙ አጠገብ ያለው ዚሚሆቊቱ ሻኡል በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ሻኡል ሲሞት ዹአክቩር ልጅ ባአልሀናን በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ባአልሀናን ሲሞት ሃዳድ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ። ዹኹተማውም ስም ጳኡ ነበርፀ ዚሚስቱም ስም መሄጣቀል ሲሆን እሷም ዚመዛሃብ ሎት ልጅ ዚማጥሬድ ልጅ ናት።
ኚዚያም ሃዳድ ሞተ። ዚኀዶም አለቆቜ፣ አለቃ ቲምና፣ አለቃ አልዋህ፣ አለቃ ዚ቎ት፣
አለቃ ኊሆሊባማ፣ አለቃ ኀላህ፣ አለቃ ፒኖን፣
አለቃ ቀናዝ፣ አለቃ ቎ማን፣ አለቃ ሚብጻር፣
አለቃ ማግዲኀል እና አለቃ ኢራም ነበሩ። እነዚህ ዚኀዶም አለቆቜ ነበሩ።
ዚይሳኮር ወንዶቜ ልጆቜ ቶላ፣ ፑሃ፣ ያሹብና ሺምሮን ሲሆኑ በአጠቃላይ አራት ነበሩ።
ዚቶላም ወንዶቜ ልጆቜ ዑዚ፣ ሚፋያህ፣ ዚሪኀል፣ ያህማይ፣ ይብሳም እና ሞሙኀል ሲሆኑ ዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ ነበሩ። ዚቶላ ዘሮቜ ኃያላን ተዋጊዎቜ ነበሩፀ በዳዊት ዘመን ቁጥራ቞ው 22,600 ነበር።
ዹዑዚ ዘሮቜ ይዝራህያህ እና ዚይዝራህያህ ወንዶቜ ልጆቜ ይኾውም ሚካኀል፣ አብድዩ፣ ኢዩኀልና ይሜሺያህ ና቞ውፀ አምስቱም አለቆቜ ነበሩ።
እነሱም ብዙ ሚስቶቜና ወንዶቜ ልጆቜ ስለነበሯ቞ው በዚትውልድ ሐሹጋቾው ኚዚአባቶቻ቞ው ቀት ለመዋጋት ዝግጁ ዹሆኑ 36,000 ወታደሮቜን ያቀፈ ሠራዊት ነበራ቞ው።
ኚይሳኮር ቀተሰቊቜ በሙሉ በትውልድ ሐሹግ መዝገቡ ላይ ዚሰፈሩት ኃያላን ተዋጊዎቜ ዚሆኑት ወንድሞቻ቞ው በአጠቃላይ 87,000 ነበሩ።
ዚቢንያም ወንዶቜ ልጆቜ ቀላ፣ ቀኬር እና ዚዲአዔል ሲሆኑ በአጠቃላይ ሊስት ነበሩ።
ዚቀላ ወንዶቜ ልጆቜ ኀጜቊን፣ ዑዚ፣ ዑዚኀል፣ ዚሪሞት እና ኢሪ ሲሆኑ በአጠቃላይ አምስት ነበሩፀ እነሱም ዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ እንዲሁም ኃያላን ተዋጊዎቜ ነበሩፀ በትውልድ ሐሹግ መዝገቡም ላይ ዚሰፈሩት 22,034 ነበሩ።
ዚቀኬር ወንዶቜ ልጆቜ ዘሚራ፣ ኢዮአስ፣ ኀሊዔዘር፣ ኀሊዮዔናይ፣ ኊምሪ፣ ዚሬሞት፣ አቢያህ፣ አናቶት እና አለሜት ነበሩፀ እነዚህ ሁሉ ዚቀኬር ወንዶቜ ልጆቜ ና቞ው።
በዚትውልድ ሐሹጋቾውና በዚዘሮቻ቞ው ዚተመዘገቡት በዚአባቶቻ቞ው ቀት ያሉት መሪዎቜ 20,200 ኃያላን ተዋጊዎቜ ነበሩ።
ዚዚዲአዔል ወንዶቜ ልጆቜ ቢልሃን እና ዚቢልሃን ወንዶቜ ልጆቜ ይኾውም ዚኡሜ፣ ቢንያም፣ ኀሁድ፣ ኬናአና፣ ዜታን፣ ተርሎስ እና አሂሻሐር ነበሩ።
እነዚህ ሁሉ ዚዚዲአዔል ወንዶቜ ልጆቜ ሲሆኑ ዚዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜ መሪዎቜ እንዲሁም ሠራዊቱን ተቀላቅለው ለመዋጋት ዝግጁ ዹሆኑ 17,200 ኃያላን ተዋጊዎቜ ነበሩ።
ዚሹፒምና ዹሁፒም ቀተሰቊቜ ዚኢር ልጆቜ ነበሩፀ ዚሁሺም ልጆቜ ደግሞ ዹአሄር ዘሮቜ ነበሩ።
ዚንፍታሌም ወንዶቜ ልጆቜ ያህጺኀል፣ ጉኒ፣ ዚጌር እና ሻሉም ነበሩፀ እነዚህ ሰዎቜ ዚባላ ዘሮቜ ነበሩ።
ዹምናሮ ልጆቜፊ ሶርያዊት ቁባቱ ዚወለደቜለት አስሪዔል። (እሷ ዚጊልያድን አባት ማኪርን ወለደቜ።
ማኪር፣ ሁፒምንና ሹፒምን ሚስት አጋባ቞ውፀ ዚእህቱም ስም ማአካ ይባላል።) ሁለተኛው ሰለጰአድ ተብሎ ይጠራልፀ ሆኖም ሰለጰአድ ዹወለደው ሎት ልጆቜን ብቻ ነበር።
ዚማኪር ሚስት ማአካ ወንድ ልጅ ወለደቜፀ ስሙንም ፔሬሜ አለቜውፀ ዚወንድሙም ስም ሌሬሜ ይባል ነበርፀ ወንዶቜ ልጆቹም ዑላም እና ራቄም ነበሩ።
ዹዑላም ልጅ ቀዳን ነበር። እነዚህ ዹምናሮ ልጅ፣ ዚማኪር ልጅ ዚጊልያድ ዘሮቜ ነበሩ።
እህቱም ሞሌኬት ትባል ነበር። እሷም ኢሜሆድን፣ አቢዔዜርንና ማህላን ወለደቜ።
ዚሞሚዳ ወንዶቜ ልጆቜም አሂያን፣ ሎኬም፣ ሊቅሂ እና አኒዓም ነበሩ።
ሹተላ ዚኀፍሬም ልጅ ነበርፀ ዚሹተላ ልጅ ቀሬድ፣ ዚቀሬድ ልጅ ታሃት፣ ዚታሃት ልጅ ኀልዓዳ፣ ዚኀልዓዳ ልጅ ታሃት፣
ዚታሃት ልጅ ዛባድ፣ ዚዛባድ ልጅ ሹተላ ነበርፀ ኀጌር እና ኀልዓድም ዚኀፍሬም ልጆቜ ነበሩ። እነሱም መንጎቜ ለመዝሹፍ በወሚዱ ጊዜ ዚምድሪቱ ተወላጆቜ ዚሆኑት ዚጌት ሰዎቜ ገደሏ቞ው።
አባታ቞ው ኀፍሬም ለብዙ ቀናት አለቀሰፀ ወንድሞቹም እሱን ለማጜናናት ይመጡ ነበር።
ኚዚያም ኚሚስቱ ጋር ግንኙነት ፈጞመፀ እሷም ፀንሳ ወንድ ልጅ ወለደቜ። ሆኖም እሷ በወለደቜ ጊዜ በቀተሰቡ ላይ መኚራ ደርሶ ስለነበር ስሙን በሪአ አለው።
ዚሎት ልጁም ስም ሌኢራ ሲሆን እሷም ዚታቜኛውንና ዹላይኛውን ቀትሆሮንን እንዲሁም ዑዜንሌራን ዚገነባቜ ነቜ።
ሬፋህ እና ሬሌፍ ወንዶቜ ልጆቹ ነበሩፀ ሬሌፍ ቮላህን ወለደፀ ቮላህ ታሃንን ወለደፀ
ታሃን ላዳንን ወለደፀ ላዳን አሚሁድን ወለደፀ አሚሁድ ኀሊሻማን ወለደፀ
ኀሊሻማ ነዌን ወለደፀ ነዌ ኢያሱን ወለደ።
ርስታ቞ውና ሰፈራ቞ው ቀ቎ልንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜ፣ በስተ ምሥራቅ ናአራንን፣ በስተ ምዕራብ ደግሞ ጌዜርንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜ እንዲሁም ሎኬምንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜ ጚምሮ እስኚ አያህና በሥሯ እስካሉት ኚተሞቜ ይደርሳልፀ
በምናሮም ዘሮቜ ወሰን በኩል ቀትሌንና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ ታአናክና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ መጊዶና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ እንዲሁም ዶርና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ ነበሩ። በእነዚህ ስፍራዎቜ ዚእስራኀል ልጅ ዚዮሎፍ ዘሮቜ ይኖሩ ነበር።
ዹአሮር ወንዶቜ ልጆቜ ይምናህ፣ ይሜዋ፣ ይሜዊ እና በሪአ ሲሆኑ እህታ቞ውም ሎራህ ትባላለቜ።
ዚበሪአ ወንዶቜ ልጆቜ ሄቀር እና ዚቢርዛይት አባት ዹሆነው ማልኪኀል ነበሩ።
ሄቀር ያፍሌጥን፣ ሟሜርን፣ ሆታምንና እህታ቞ውን ሹአን ወለደ።
ዚያፍሌጥ ወንዶቜ ልጆቜ ፓሳክ፣ ቢምሃል እና አሜዋት ነበሩ። እነዚህ ዚያፍሌጥ ልጆቜ ነበሩ።
ዚሌሜር ወንዶቜ ልጆቜ አሂ፣ ሮህጋ፣ ዚሁባ እና አራም ነበሩ።
ዚወንድሙ ዹሄሌም ወንዶቜ ልጆቜ ጟፋ፣ ይምና፣ ሌሌሜ እና አማል ነበሩ።
ዚጟፋ ወንዶቜ ልጆቜ ሱአ፣ ሃርኔፌር፣ ሹአል፣ ቀሪ፣ ይምራ፣
ቀጌር፣ ሆድ፣ ሻማ፣ ሺልሻ፣ ይትራን እና ቀኀራ ነበሩ።
ዹዹቮር ወንዶቜ ልጆቜ ዚፎኒ፣ ፒስጳ እና አራ ነበሩ።
ዹዑላ ወንዶቜ ልጆቜ ኀራ፣ ሃኒኀል እና ሪጜያ ነበሩ።
እነዚህ ሁሉ ዹአሮር ወንዶቜ ልጆቜና ዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ ና቞ውፀ እንዲሁም ዚተመሚጡ ኃያላን ተዋጊዎቜ ሲሆኑ ዚሠራዊቱ አለቆቜ መሪዎቜ ነበሩፀ ደግሞም በቀተሰባ቞ው መዝገብ ላይ እንደተጻፈው ለውጊያ ዝግጁ ዹሆኑ 26,000 ሰዎቜ በሠራዊቱ ውስጥ ይገኙ ነበር።
በተጚማሪም ዳዊትና ዚአገልግሎት ቡድኖቹ አለቆቜ በበገና፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቜና በሲምባል ትንቢት በመናገር እንዲያገለግሉ ኚአሳፍ፣ ኹሄማን እና ኚዚዱቱን ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል አንዳንዶቹን ለዩ። ይህን አገልግሎት ዚሚያኚናውኑት ኃላፊነት ያላ቞ው ሰዎቜ ዝርዝር ዹሚኹተለው ነው፩
ኚአሳፍ ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ዛኩር፣ ዮሎፍ፣ ነታንያህ እና አሌርዔላፀ እነዚህ በአሳፍ አመራር ሥር ያሉ ዚአሳፍ ወንዶቜ ልጆቜ ሲሆኑ በንጉሡ አመራር ሥር ሆነው ትንቢት ይናገሩ ነበር።
ኚዚዱቱን፣ ዚዚዱቱን ወንዶቜ ልጆቜፊ ጎዶልያስ፣ ጞሪ፣ ዚሻያህ፣ ሺምአይ፣ ሃሻብያህ እና ማቲትያህፀ እነዚህ ስድስቱ በአባታ቞ው በዚዱቱን አመራር ሥር ሲሆኑ ይሖዋን እያመሰገኑና እያወደሱ በበገና ትንቢት ይናገሩ ነበር።
ኚሄማን፣ ዹሄማን ወንዶቜ ልጆቜፊ ቡቂያ፣ ማታንያህ፣ ዑዚኀል፣ ሞቡኀል፣ ዚሪሞት፣ ሃናንያህ፣ ሃናኒ፣ ኀሊዓታህ፣ ጊዳልቲ፣ ሮማምቲኀዘር፣ ዮሜበቃሻ፣ ማሎቲ፣ ሆቲር እና ማሃዚዮት።
እነዚህ ሁሉ ዹሄማን ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ እሱም ለአምላክ ክብር ያመጣ ዘንድ ዚእውነተኛውን አምላክ ቃል ዚሚገልጜ ዚንጉሡ ባለ ራእይ ነበርፀ እውነተኛውም አምላክ ለሄማን 14 ወንዶቜ ልጆቜና 3 ሎቶቜ ልጆቜ ሰጠው።
እነዚህ ሁሉ በእውነተኛው አምላክ ቀት ለሚቀርበው አገልግሎት በአባታ቞ው አመራር ሥር ሆነው በሲምባል፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቜና በበገና በይሖዋ ቀት ይዘምሩ ነበር። አሳፍ፣ ዚዱቱን እና ሄማን በንጉሡ አመራር ሥር ነበሩ።
ዚእነሱና ለይሖዋ በሚቀርበው መዝሙር ዚሠለጠኑት ወንድሞቻ቞ው ይኾውም በዚህ ዚተካኑት ሰዎቜ አጠቃላይ ቁጥር 288 ነበር።
በመሆኑም ኚሥራ቞ው ጋር በተያያዘ ታናሜም ሆነ ታላቅ፣ በሙያው ዚተካነም ሆነ ተማሪ ሳይባል ሁሉም ዕጣ ተጣጣሉ።
ዚመጀመሪያው ዕጣ ለአሳፍ ልጅ ለዮሎፍ ወጣፀ ሁለተኛው ለጎዶልያስ ወጣ (እሱና ወንድሞቹ እንዲሁም ወንዶቜ ልጆቹ 12 ነበሩ)ፀ
ሊስተኛው ለዛኩር፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አራተኛው ለይጜሪ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አምስተኛው ለነታንያህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ስድስተኛው ለቡቂያ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ሰባተኛው ለዚሳርኀላ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ስምንተኛው ለዚሻያህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ዘጠነኛው ለማታንያህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥሚኛው ለሺምአይ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ አንደኛው ለአዛርዔል፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ ሁለተኛው ለሃሻብያህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ ሊስተኛው ለሹባኀል፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ አራተኛው ለማቲትያህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ አምስተኛው ለዚሬሞት፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ ስድስተኛው ለሃናንያህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ ሰባተኛው ለዮሜበቃሻ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ ስምንተኛው ለሃናኒ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
አሥራ ዘጠነኛው ለማሎቲ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ሃያኛው ለኀሊዓታህ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ሃያ አንደኛው ለሆቲር፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ሃያ ሁለተኛው ለጊዳልቲ፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ሃያ ሊስተኛው ለማሃዚዮት፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበርፀ
ሃያ አራተኛው ለሮማምቲኀዘር፣ ለወንዶቜ ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣፀ ቁጥራ቞ውም 12 ነበር።
ዳዊት ኚሺህ አለቆቹና ኚመቶ አለቆቹ እንዲሁም ኚመሪዎቹ ሁሉ ጋር ተማኚሚ።
ኚዚያም ዳዊት ለመላው ዚእስራኀል ጉባኀ እንዲህ አለ፩ “ነገሩ መልካም መስሎ ኚታያቜሁና በአምላካቜን በይሖዋ ፊት ተቀባይነት ያለው ኚሆነ፣ በእስራኀል ምድር ሁሉ ያሉት ዚቀሩት ወንድሞቻቜን እንዲሁም ዚግጊሜ መሬቶቜ ባሏ቞ው ኚተሞቻ቞ው ዚሚኖሩት ካህናትና ሌዋውያን ወደ እኛ እንዲሰበሰቡ መልእክት እንላክባ቞ው።
ዚአምላካቜንንም ታቊት መልሰን እናምጣ።” በሳኊል ዘመን ታቊቱን ቜላ ብለውት ነበርና።
ነገሩ በሕዝቡ ሁሉ ፊት መልካም ሆኖ ስለተገኘ መላው ጉባኀ ይህን ለማድሚግ ተስማማ።
በመሆኑም ዳዊት ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት ኚቂርያትዚአሪም ለማምጣት ኚግብፅ ወንዝ አንስቶ እስኚ ሌቊሃማት ድሚስ ያለውን ዚእስራኀል ሕዝብ ሁሉ ሰበሰበ።
ዳዊትና መላው ዚእስራኀል ሕዝብ ኚኪሩቀል በላይ በዙፋን ዹሚቀመጠውን ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት ይኾውም ሰዎቜ ዹይሖዋን ስም ዚሚጠሩበትን ታቊት ለማምጣት በይሁዳ ምድር ወደምትገኘው ቂርያትዚአሪም ወደምትባለው ወደ ባዓላ ወጡ።
ይሁን እንጂ ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት በአዲስ ሠሹገላ ላይ ጭነው ኚአቢናዳብ ቀት አመጡትፀ ደግሞም ዖዛና አሂዮ ሠሹገላውን እዚነዱ ነበር።
ዳዊትና መላው ዚእስራኀል ሕዝብ በመዝሙር፣ በበገና፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቜ፣ በአታሞ፣ በሲምባልና በመለኚት ታጅበው በሙሉ ኃይላቾው በእውነተኛው አምላክ ፊት በደስታ ይጚፍሩ ነበር።
ወደ ኪዶን አውድማ ሲደርሱ ግን ኚብቶቹ ታቊቱን ሊጥሉት ተቃርበው ስለነበር ዖዛ እጁን ዘርግቶ ታቊቱን ያዘ።
በዚህ ጊዜ ዹይሖዋ ቁጣ በዖዛ ላይ ነደደፀ ታቊቱን ለመያዝ እጁን በመዘርጋቱም ቀሰፈውፀ እሱም በአምላክ ፊት እዚያው ሞተ።