text
stringlengths
4
267
ሞጻ ቢንአን ወለደፀ ቢንአ ሚፋያህን ወለደፀ ሚፋያህ ኀልዓሳን ወለደፀ ኀልዓሳ አዜልን ወለደ።
አዜል ስድስት ወንዶቜ ልጆቜ ዚነበሩት ሲሆን ስማ቞ውም አዝሪቃም፣ ቊኚሩ፣ እስማኀል፣ ሞአርያህ፣ አብድዩ እና ሃናን ነበር። እነዚህ ዹአዜል ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
ዚአሮን ዘሮቜ ምድብ ይህ ነበር፩ ዚአሮን ወንዶቜ ልጆቜ ናዳብ፣ አቢሁ፣ አልዓዛር እና ኢታምር ነበሩ።
ይሁንና ናዳብ እና አቢሁ ኚአባታ቞ው በፊት ሞቱፀ ወንዶቜ ልጆቜም አልነበሯ቞ውምፀ አልዓዛር እና ኢታምር ግን ካህናት ሆነው ማገልገላቾውን ቀጠሉ።
ዳዊት፣ ኹአልዓዛር ወንዶቜ ልጆቜ አንዱ ኹሆነው ኚሳዶቅ እንዲሁም ኚኢታምር ወንዶቜ ልጆቜ አንዱ ኹሆነው ኹአሂሜሌክ ጋር ሆኖ ዚአሮንን ዘሮቜ በተሰጣ቞ው ዚአገልግሎት ኃላፊነት መሠሚት መደባ቞ው።
ዹአልዓዛር ወንዶቜ ልጆቜ፣ ኚኢታምር ወንዶቜ ልጆቜ ይልቅ ብዙ መሪዎቜ ስለነበሯ቞ው መሪዎቹን በዚሁ መሠሚት መደቧቾው፩ ዹአልዓዛር ወንዶቜ ልጆቜ ዚዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ ዹሆኑ 16 መሪዎቜ፣ ዚኢታምር ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ ዚዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪዎቜ ዹሆኑ 8 መሪዎቜ ነበሯ቞ው።
በተጚማሪም ኹአልዓዛር ወንዶቜ ልጆቜም ሆነ ኚኢታምር ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል በቅዱሱ ስፍራ ዚሚያገለግሉ አለቆቜና እውነተኛውን አምላክ ዚሚያገለግሉ አለቆቜ ስለነበሩ አንደኛውን ቡድን ኹሌላው ቡድን ጋር በዕጣ መደቧ቞ው።
ኚዚያም ዚሌዋውያን ጾሐፊ ዹሆነው ዚናትናኀል ልጅ ሞማያህ በንጉሡ፣ በመኳንንቱ፣ በካህኑ በሳዶቅ፣ በአብያታር ልጅ በአሂሜሌክ እንዲሁም በካህናቱና በሌዋውያኑ አባቶቜ ቀት መሪዎቜ ፊት ስማ቞ውን መዘገበፀ አንድ ዚአባቶቜ ቀት ኹአልዓዛር ወገን ሲመሚጥ፣ አንድ ዚአባቶቜ ቀት ደግሞ ኚኢታምር ወገን ተመሚጠ።
ዚመጀመሪያው ዕጣ ለዚሆያሪብ ወጣፀ ሁለተኛው ለዚዳያህ፣
ሊስተኛው ለሃሪም፣ አራተኛው ለሰኊሪም፣
አምስተኛው ለማልኪያህ፣ ስድስተኛው ለሚያሚን፣
ሰባተኛው ለሃቆጜ፣ ስምንተኛው ለአቢያህ፣
ዘጠነኛው ለዚሹዋ፣ አሥሚኛው ለሞካንያህ፣
አሥራ አንደኛው ለኀልያሺብ፣ አሥራ ሁለተኛው ለያቂም፣
አሥራ ሊስተኛው ለሁፓ፣ አሥራ አራተኛው ለዚሌብአብ፣
አሥራ አምስተኛው ለቢልጋ፣ አሥራ ስድስተኛው ለኢሜር፣
አሥራ ሰባተኛው ለሄዚር፣ አሥራ ስምንተኛው ለሃፒጌጜ፣
አሥራ ዘጠነኛው ለፐታያህ፣ ሃያኛው ለዚሄዝቄል፣
ሃያ አንደኛው ለያኪን፣ ሃያ ሁለተኛው ለጋሙል፣
ሃያ ሊስተኛው ለደላያህ እና ሃያ አራተኛው ለማአዝያህ ወጣ።
ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ባዘዘው መሠሚት አባታ቞ው አሮን ወደ ይሖዋ ቀት ሲገቡ ዚአገልግሎት ኃላፊነታ቞ውን ዚሚያኚናውኑበትን ሥርዓት በተመለኹተ ያወጣው ደንብ ይህ ነበር።
ኚቀሩት ሌዋውያን መካኚል ዚሚኚተሉት ይገኙበታልፊ ኚአምራም ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ሹባኀልፀ ኚሹባኀል ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ዚህድያፀ
ኚሚሃቢያህፊ ኚሚሃቢያህ ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል፣ መሪ ዹሆነው ይሜሺያህፀ
ኚይጜሃራውያን መካኚል ሞሎሞትፀ ኚሞሎሞት ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ያሃትፀ
ኚኬብሮን ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል፣ መሪ ዹሆነው ዚሪያ፣ ሁለተኛው አማርያህ፣ ሊስተኛው ያሃዚኀል እና አራተኛው ዚቃምአምፀ
ኚዑዚኀል ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ሚክያስፀ ኚሚክያስ ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ሻሚር።
ይሜሺያህ ዚሚክያስ ወንድም ነበርፀ ኚይሜሺያህ ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል ዘካርያስ።
ዚሜራሪ ወንዶቜ ልጆቜ ማህሊ እና ሙሺ ነበሩፀ ዚያአዚያሁ ልጅ ቀኖ።
ዚሜራሪ ወንዶቜ ልጆቜፊ ኚያአዚያሁ ልጆቜ መካኚል ቀኖ፣ ሟሃም፣ ዛኩር እና ኢብሪፀ
ኹማህሊ ልጆቜ መካኚል አልዓዛርፀ እሱ ወንዶቜ ልጆቜ አልነበሩትምፀ
ኚቂስፊ ዚቂስ ልጅ ዚራህምኀልፀ
ዚሙሺ ወንዶቜ ልጆቜ ማህሊ፣ ኀዎር እና ዚሪሞት ነበሩ። በአባቶቻ቞ው ቀት መሠሚት ዚተዘሚዘሩት ዹሌዊ ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ነበሩ።
እነሱም ወንድሞቻ቞ው ዚሆኑት ዚአሮን ወንዶቜ ልጆቜ እንዳደሚጉት በንጉሥ ዳዊት፣ በሳዶቅ፣ በአሂሜሌክ እንዲሁም በካህናቱና በሌዋውያኑ አባቶቜ ቀት መሪዎቜ ፊት ዕጣ ጣሉ። በዚህ ሚገድ በመሪው አባት ቀት ወይም በትልቁ ቀተሰብ መሪና በታናሜ ወንድሙ አባት ቀት ወይም በአነስተኛው ቀተሰብ መሪ መካኚል ምንም ልዩነት አልነበሚም።
ዚእስራኀላውያን ቁጥር ይኾውም ዚአባቶቜ ቀቶቜ መሪዎቜ፣ ዚሺህ አለቆቜ፣ ዚመቶ አለቆቜና ዓመቱን ሙሉ በዚወሩ ዚሚገቡትንም ሆነ ዚሚወጡትን ምድቊቜ በመምራት ንጉሡን ዚሚያገለግሉት አለቆቻ቞ው ቁጥር ይህ ነውፀ በእያንዳንዱ ምድብ 24,000 ነበሩ።
በመጀመሪያው ወር ዚመጀመሪያው ምድብ አዛዥ ዚዛብድኀል ልጅ ያሟብአም ነበርፀ በእሱም ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
እሱ ኚፋሬስ ወንዶቜ ልጆቜ መካኚል በመጀመሪያው ወር እንዲያገለግሉ ዚተመደቡት ዚቡድኖቹ አለቆቜ ሁሉ መሪ ነበር።
አሆሐያዊው ዶዳይ ዹሁለተኛው ወር ምድብ አዛዥ ነበር። መሪው ሚቅሎት ሲሆን በእሱ ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በሊስተኛው ወር እንዲያገለግል ዹተመደበው ዚሊስተኛው ቡድን አዛዥ ዚካህናት አለቃው ዚዮዳሄ ልጅ በናያህ ነበርፀ በእሱም ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በናያህ ኚሠላሳዎቹ ኃያላን ተዋጊዎቜ አንዱ ዹነበሹ ሲሆን ዚሠላሳዎቹ አለቃ ነበርፀ ልጁ አሚዛባድም በእሱ ምድብ ውስጥ ዹበላይ ነበር።
በአራተኛው ወር፣ አራተኛው አዛዥ ዚኢዮዓብ ወንድም አሳሄል ሲሆን ልጁ ዘባድያህ ዚእሱ ተተኪ ነበርፀ በምድቡም ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በአምስተኛው ወር፣ አምስተኛው አዛዥ ይዝራሃዊው ሻምሁት ነበርፀ በእሱም ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በስድስተኛው ወር፣ ስድስተኛው አዛዥ ዹተቆአዊው ዚኢቄሜ ልጅ ኢራ ሲሆን በእሱ ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በሰባተኛው ወር፣ ሰባተኛው አዛዥ ኚኀፍሬማውያን ወገን ዹሆነው ጮሎናዊው ሄሌጜ ሲሆን በእሱ ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በስምንተኛው ወር፣ ስምንተኛው አዛዥ ኚዛራውያን ወገን ዹሆነው ሁሻዊው ሲበካይ ነበርፀ በእሱም ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በዘጠነኛው ወር፣ ዘጠነኛው አዛዥ ኚቢንያማውያን ወገን ዹሆነው አናቶታዊው አቢዔዜር ሲሆን በእሱ ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በአሥሚኛው ወር፣ አሥሚኛው አዛዥ ኚዛራውያን ወገን ዹሆነው ነጩፋዊው ማህራይ ሲሆን በእሱ ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በ11ኛው ወር፣ 11ኛው አዛዥ ኚኀፍሬም ልጆቜ ወገን ዹሆነው ጲራቶናዊው በናያህ ነበርፀ በእሱም ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
በ12ኛው ወር፣ 12ኛው አዛዥ ኚኊትኒኀል ቀተሰብ ዹሆነው ነጩፋዊው ሄልዳይ ሲሆን በእሱ ምድብ ውስጥ 24,000 ሰዎቜ ነበሩ።
ዚእስራኀል ነገዶቜ መሪዎቜ እነዚህ ናቾው፩ ኚሮቀላውያን ዚዚክሪ ልጅ ኀሊዔዘር መሪ ነበርፀ ኚስምዖናውያን ዚማአካ ልጅ ሰፋጥያህፀ
ኹሌዊ ዚቀሙኀል ልጅ ሃሻብያህፀ ኚአሮን ቀተሰብ ሳዶቅፀ
ኚይሁዳ ኚዳዊት ወንድሞቜ አንዱ ዹሆነው ኀሊሁፀ ኚይሳኮር ዚሚካኀል ልጅ ኊምሪፀ
ኚዛብሎን ዚአብድዩ ልጅ ይሜማያህፀ ኚንፍታሌም ዹአዝርዔል ልጅ ዚሪሞትፀ
ኚኀፍሬማውያን መካኚል ዚአዛዝያ ልጅ ሆሺአፀ ኹምናሮ ነገድ እኩሌታ ዚፐዳያህ ልጅ ኢዩኀልፀ
በጊልያድ ካለው ዹምናሮ ነገድ እኩሌታ ዚዘካርያስ ልጅ ኢዶፀ ኚቢንያም ዹአበኔር ልጅ ያአሲዔልፀ
ኚዳን ዚዚሮሃም ልጅ አዛርዔል። እነዚህ ዚእስራኀል ነገዶቜ አለቆቜ ነበሩ።
ይሖዋ እስራኀልን በሰማያት እንዳሉ ኚዋክብት እንደሚያበዛ ቃል ገብቶ ስለነበር ዳዊት 20 ዓመትና ኚዚያ በታቜ ዹሆናቾውን አልቆጠሚም።
ዚጜሩያ ልጅ ኢዮዓብ ቆጠራውን ጀምሮ ዹነበሹ ቢሆንም አልፈጞመውም። ዹአምላክ ቁጣ በእስራኀል ላይ ስለነደደ በንጉሥ ዳዊት ዘመን ስለተኚናወኑት ነገሮቜ በሚተርኹው ዚታሪክ ዘገባ ላይ ቁጥሩ አልሰፈሚም።
ዚአዲዔል ልጅ አዝማዌት በንጉሡ ግምጃ ቀቶቜ ላይ ተሹሞ ነበር። ዚዖዝያ ልጅ ዮናታን ደግሞ በገጠሩ፣ በኚተሞቹ፣ በመንደሮቹና በማማዎቹ ውስጥ በሚገኙት ግምጃ ቀቶቜ ላይ ተሹሞ ነበር።
ዚኚሉብ ልጅ ኀዝሪ መሬቱን ለማልማት በመስክ በሚሠሩት ሠራተኞቜ ላይ ተሹሞ ነበር።
ራማዊው ሺምአይ በወይን እርሻዎቹ ላይ ተሹሞ ነበርፀ ሲፍሞታዊው ዛብዲ ለወይን ጠጅ አቅርቊት በሚውለው ዹወይን እርሻዎቹ ምርት ላይ ተሹሞ ነበር።
ጌዎራዊው ባአልሀናን በሾፌላ በነበሩት ዚወይራ ዛፎቜና ዚሟላ ዛፎቜ ላይ ተሹሞ ነበርፀ ዮአስ ደግሞ በዘይት ማኚማቻዎቹ ላይ ተሹሞ ነበር።
ሳሮናዊው ሺጥራይ በሳሮን ዚግጊሜ መሬት በሚሰማሩት ኚብቶቜ ላይ ተሹሞ ነበርፀ ዚአድላይ ልጅ ሻፋጥ ደግሞ በሾለቋማ ሜዳዎቹ ላይ በሚሰማሩት ኚብቶቜ ላይ ተሹሞ ነበር።
እስማኀላዊው ኊቢል በግመሎቹ ላይ ተሹሞ ነበርፀ መሮኖታዊው ዚህድያ በአህዮቹ ላይ ተሹሞ ነበር።
አጋራዊው ያዚዝ በመንጎቹ ላይ ተሹሞ ነበር። እነዚህ ሁሉ በንጉሥ ዳዊት ንብሚት ላይ ዚተሟሙ አለቆቜ ነበሩ።
ዚዳዊት ዚወንድሙ ልጅ ዮናታን አስተዋይ ዹሆነ አማካሪና ጾሐፊ ነበርፀ ዹሃክሞኒ ልጅ ዚሂኀል ዚንጉሡ ልጆቜ ተንኚባካቢ ነበር።
አኪጊፌል ዚንጉሡ አማካሪ ነበርፀ አርካዊው ኩሲ ደግሞ ዚንጉሡ ወዳጅ ነበር።
ኚአኪጊፌል በኋላ አማካሪ ሆነው ዚተሟሙት ዚበናያህ ልጅ ዮዳሄ እና አብያታር ነበሩፀ ኢዮዓብ ደግሞ ዚንጉሡ ሠራዊት ዋና አዛዥ ነበር።
ዚእስራኀል ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ነበሩፊ ሮቀል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፣
ዳን፣ ዮሎፍ፣ ቢንያም፣ ንፍታሌም፣ ጋድ እና አሎር።
ዚይሁዳ ወንዶቜ ልጆቜ ኀር፣ ኩናን እና ሮሎም ነበሩ። እነዚህ ሊስቱ ኚኚነአናዊቷ ኚሹአ ሎት ልጅ ዚተወለዱለት ና቞ው። ዚይሁዳ ዚበኩር ልጅ ዹሆነው ኀር ግን ይሖዋን አሳዘነፀ እሱም ቀሰፈው።
ዚይሁዳ ምራት ትዕማር ፋሬስን እና ዛራን ወለደቜለት። ዚይሁዳ ወንዶቜ ልጆቜ በአጠቃላይ አምስት ነበሩ።
ዚፋሬስ ወንዶቜ ልጆቜ ኀስሮን እና ሃሙል ነበሩ።
ዚዛራ ወንዶቜ ልጆቜ ዚምሪ፣ ኀታን፣ ሄማን፣ ካልኮል እና ዳራ ነበሩ። በአጠቃላይ አምስት ነበሩ።
ዚካርሚ ልጅ አካር ነበርፀ እሱም ለጥፋት ኹተለዹው ነገር ጋር በተያያዘ እምነት በማጉደሉ በእስራኀል ላይ መዓት አምጥቷል።
ዚኀታን ልጅ አዛርያስ ነበር።
ለኀስሮን ዚተወለዱለት ወንዶቜ ልጆቜ ዚራህምኀል፣ ራም እና ኚሉባይ ነበሩ።
ራም አሚናዳብን ወለደፀ አሚናዳብ ዚይሁዳ ዘሮቜ አለቃ ዚሆነውን ነአሶንን ወለደ።
ነአሶን ሳልማን ወለደ። ሳልማ ቩዔዝን ወለደ።
ቩዔዝ ኢዮቀድን ወለደ። ኢዮቀድ እሎይን ወለደ።
እሎይ ዚበኩር ልጁን ኀልያብን፣ ሁለተኛውን ልጁን አቢናዳብን፣ ሊስተኛውን ልጁን ሺምአን፣
አራተኛውን ልጁን ናትናኀልን፣ አምስተኛውን ልጁን ራዳይን፣
ስድስተኛውን ልጁን ኊጌምን እና ሰባተኛውን ልጁን ዳዊትን ወለደ።
እህቶቻ቞ው ጜሩያ እና አቢጋኀል ነበሩ። ዚጜሩያ ወንዶቜ ልጆቜ ሊስት ሲሆኑ እነሱም አቢሳ፣ ኢዮዓብ እና አሳሄል ነበሩ።
አቢጋኀልም አሜሳይን ወለደቜፀ ዚአሜሳይ አባት እስማኀላዊው ዹቮር ነበር።
ዚኀስሮን ልጅ ካሌብ ኚሚስቱ ኚአዙባ እና ኚይሪዖት ወንዶቜ ልጆቜ ወለደፀ ዚእሷም ወንዶቜ ልጆቜ ዚሌር፣ ሟባብ እና አርዶን ነበሩ።
አዙባ ስትሞት ካሌብ ኀፍራታን አገባፀ እሷም ሁርን ወለደቜለት።
ሁር ዖሪን ወለደ። ዖሪ ባስልኀልን ወለደ።
ኚዚያም ኀስሮን ዚጊልያድ አባት ኹሆነው ኚማኪር ሎት ልጅ ጋር ግንኙነት ፈጞመ። እሷን ያገባት በ60 ዓመቱ ነበርፀ እሷም ሰጉብን ወለደቜለት።
ሰጉብ ያኢርን ወለደፀ እሱም በጊልያድ ምድር 23 ኚተሞቜ ነበሩት።
በኋላም ገሹር እና ሶርያ ቄናትንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜ ጚምሮ ሃዎትያኢርን ይኾውም 60 ኚተሞቜን ወሰዱባ቞ው። እነዚህ ሁሉ ዚጊልያድ አባት ዹሆነው ዚማኪር ዘሮቜ ነበሩ።
ኀስሮን በካሌብ ኀፍራታ ኹሞተ በኋላ ዚኀስሮን ሚስት ዚሆነቜው አቢያህ፣ ዹተቆአ አባት ዹሆነውን አሜሁርን ወለደቜለት።
ዚኀስሮን ዚበኩር ልጅ ዚራህምኀል ዚወለዳ቞ው ወንዶቜ ልጆቜ ዚበኩር ልጁ ራም፣ ቡናህ፣ ኊሬን፣ ኊጌም እና አኪያህ ነበሩ።
ዚራህምኀል፣ አታራ ዚተባለቜ ሌላ ሚስት አገባ። እሷም ዹኩናም እናት ነበሚቜ።
ዚዚራህምኀል ዚበኩር ልጅ ዚራም ወንዶቜ ልጆቜ ማአጜ፣ ያሚን እና ኀቄር ነበሩ።
ዹኩናም ወንዶቜ ልጆቜ ሻማይ እና ያዳ ነበሩ። ዚሻማይ ወንዶቜ ልጆቜ ናዳብ እና አቢሹር ነበሩ።
ዚአቢሹር ሚስት አቢሃይል ትባል ነበርፀ እሷም አህባንን እና ሞሊድን ወለደቜለት።
ዚናዳብ ወንዶቜ ልጆቜ ሰሌድ እና አፋይም ነበሩ። ሆኖም ሰሌድ ወንዶቜ ልጆቜ ሳይወልድ ሞተ።
ዹአፋይም ልጅ ይሜኢ ነበር። ዚይሜኢ ልጅ ሞሻን ነበርፀ ዚሞሻን ልጅ አህላይ ነበር።
ዚሻማይ ወንድም ዚያዳ ወንዶቜ ልጆቜ ዹቮር እና ዮናታን ነበሩ። ዹቮር ግን ወንዶቜ ልጆቜ ሳይወልድ ሞተ።
ዚዮናታን ወንዶቜ ልጆቜ ፐሌት እና ዛዛ ነበሩ። እነዚህ ዚዚራህምኀል ዘሮቜ ነበሩ።