text
stringlengths
4
267
ሞሻን ሎቶቜ ብቻ እንጂ ወንዶቜ ልጆቜ አልነበሩትም። ሞሻን፣ ያርሃ ዚተባለ ግብፃዊ አገልጋይ ነበሚው።
ሞሻን ለአገልጋዩ ለያርሃ ሎት ልጁን ዳሚለትፀ እሷም አታይን ወለደቜለት።
አታይ ናታንን ወለደ። ናታን ዛባድን ወለደ።
ዛባድ ኀፍላልን ወለደ። ኀፍላል ኢዮቀድን ወለደ።
ኢዮቀድ ኢዩን ወለደ። ኢዩ አዛርያስን ወለደ።
አዛርያስ ሄሌጜን ወለደ። ሄሌጜ ኀልዓሳን ወለደ።
ኀልዓሳ ሲስማይን ወለደ። ሲስማይ ሻሉምን ወለደ።
ሻሉም ዚቃምያህን ወለደ። ዚቃምያህ ኀሊሻማን ወለደ።
ዚዚራህምኀል ወንድም ዚካሌብ ወንዶቜ ልጆቜ፣ ዹዚፍ አባት ዹሆነው ዚበኩር ልጁ ሜሻ እንዲሁም ዚኬብሮን አባት ዚማሬሻህ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
ዚኬብሮን ወንዶቜ ልጆቜ ቆሬ፣ ታጱአ፣ ራቄም እና ሌማ ነበሩ።
ሌማ ዚዮርቀአምን አባት ራሃምን ወለደ። ራቄም ሻማይን ወለደ።
ዚሻማይ ልጅ ማኩን ነበር። ማኩን ቀትጹርን ወለደ።
ዚካሌብ ቁባት ኀፋ ካራንን፣ ሞጻንና ጋዜዝን ወለደቜ። ካራን ጋዜዝን ወለደ።
ዚያህዳይ ወንዶቜ ልጆቜ ሚጌም፣ ኢዮዓታም፣ ጌሻን፣ ጎሌጥ፣ ኀፋ እና ሻአፍ ነበሩ።
ዚካሌብ ቁባት ማአካ ሾበርን እና ቲርሃናን ወለደቜ።
ኹጊዜ በኋላም ዚማድማናን አባት ሻአፍን እንዲሁም ዹማክበናን እና ዚጊባዓን አባት ሻዌን ወለደቜ። ዚካሌብ ሎት ልጅ አክሳ ትባል ነበር።
ዚካሌብ ዘሮቜ እነዚህ ነበሩ። ዚኀፍራታ ዚበኩር ልጅ ዹሆነው ዹሁር ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ናቾው፩ ዚቂርያትዚአሪም አባት ሟባል፣
ዚቀተልሔም አባት ሳልማ እና ዚቀትጋዎር አባት ሃሬፍ።
ዚቂርያትዚአሪም አባት ዚሟባል ልጆቜ ሃሮኀ እና ዚመኑሆት ሰዎቜ እኩሌታ ነበሩ።
ዚቂርያትዚአሪም ወገኖቜ ይትራውያን፣ ፑታውያን፣ ሹማታውያን እና ሚሜራውያን ነበሩ። ጟራውያን እና ኀሜታዖላውያን ዚተገኙት ኚእነዚህ ወገኖቜ ነው።
ዚሳልማ ልጆቜ ቀተልሔም፣ ነጊፋውያን፣ አትሮት ቀት ዮአብ፣ ዚማናሃታውያን ሰዎቜ እኩሌታና ጟራውያን ነበሩ።
በያቀጜ ዚሚኖሩት ዚጞሐፍት ወገኖቜ ቲራታውያን፣ ሺመአታውያን እና ሱካታውያን ነበሩ። እነዚህ ዚሬካብ ቀት አባት ኹሆነው ኚሃማት ዚተገኙት ቄናውያን ና቞ው።
ፍልስጀማውያንም ኚእስራኀል ጋር እዚተዋጉ ነበር። ዚእስራኀልም ሰዎቜ ኚፍልስጀማውያን ፊት ሞሹፀ ብዙዎቹም በጊልቩአ ተራራ ላይ ተገደሉ።
ፍልስጀማውያን ሳኊልንና ወንዶቜ ልጆቹን እግር በእግር ተኚታተሏ቞ውፀ ፍልስጀማውያንም ዚሳኊልን ወንዶቜ ልጆቜ ዮናታንን፣ አቢናዳብንና ሜልኪሳን መተው ገደሏ቞ው።
ውጊያው በሳኊል ላይ በሚታፀ ቀስተኞቹም አገኙትፀ ደግሞም አቆሰሉት።
ኚዚያም ሳኊል ጋሻ ጃግሬውን “እነዚህ ያልተገሚዙ ሰዎቜ መጥተው በጭካኔ እንዳያሠቃዩኝ ሰይፍህን መዘህ ውጋኝ” አለው። ጋሻ ጃግሬው ግን እጅግ ፈርቶ ስለነበር ፈቃደኛ አልሆነም። በመሆኑም ሳኊል ሰይፉን ወስዶ በላዩ ላይ ወድቆ ሞተ።
ጋሻ ጃግሬው ሳኊል መሞቱን ሲያይ እሱም በራሱ ሰይፍ ላይ ወድቆ ሞተ።
ስለዚህ ሳኊልም ሆነ ሊስት ወንዶቜ ልጆቹ ሞቱፀ ዚቀቱም ሰዎቜ ሁሉ አብሚው ሞቱ።
በሾለቆው ውስጥ ዚነበሩት ዚእስራኀል ሰዎቜ ሁሉ ሠራዊቱ መሞሹን እንዲሁም ሳኊልና ልጆቹ መሞታ቞ውን ባዩ ጊዜ ኚተሞቻ቞ውን ጥለው ሞሹፀ ኚዚያም ፍልስጀማውያን መጥተው ኚተሞቹን ያዙ።
በማግስቱ ፍልስጀማውያን ዚሞቱትን ሰዎቜ ልብስና ትጥቅ ለመግፈፍ ሲመጡ ሳኊልንና ወንዶቜ ልጆቹን በጊልቩአ ተራራ ላይ ወድቀው አገኟ቞ው።
ስለሆነም ሳኊልን ገፈፉትፀ ራሱን ኚቆሚጡና ዹጩር ትጥቁን ኚወሰዱ በኋላ ወሬው ለጣዖቶቻ቞ውና ለሕዝቡ እንዲዳሚስ ወደ ፍልስጀም ምድር ሁሉ መልእክት ላኩ።
ኚዚያም ዹጩር ትጥቁን በአምላካ቞ው ቀት አስቀመጡትፀ ራሱን ደግሞ በዳጎን ቀት ላይ ቞ነኚሩት።
በጊልያድ በምትገኘው በኢያቢስ ዚሚኖሩ ሰዎቜ በሙሉ ፍልስጀማውያን በሳኊል ላይ ያደሚጉትን ሁሉ ሲሰሙ
ተዋጊዎቹ ሁሉ ተነሱፀ ዚሳኊልንና ዚልጆቹንም አስኚሬን ተሾክመው ወደ ኢያቢስ አመጡ። ኚዚያም አፅማቾውን በኢያቢስ በሚገኝ ትልቅ ዛፍ ሥር ቀበሩፀ ለሰባት ቀንም ጟሙ።
ስለዚህ ሳኊል ለይሖዋ ታማኝ ሳይሆን በመቅሚቱ ሞተፀ ምክንያቱም ዹይሖዋን ቃል አልታዘዘምፀ ደግሞም መናፍስት ጠሪን አማኚሚፀ
ይሖዋንም አልጠዚቀም። ስለሆነም ለሞት አሳልፎ ሰጠውፀ ንግሥናውም ለእሎይ ልጅ ለዳዊት እንዲተላለፍ አደሚገ።
ዚእውነተኛውን አምላክ ታቊት አምጥተው ዳዊት በተኚለለት ድንኳን ውስጥ አስቀመጡትፀ ኚዚያም ዹሚቃጠሉ መባዎቜንና ዚኅብሚት መሥዋዕቶቜን በእውነተኛው አምላክ ፊት አቀሚቡ።
ዳዊት ዚሚቃጠሉትን መባዎቜና ዚኅብሚት መሥዋዕቶቹን አቅርቩ ሲጚርስ ሕዝቡን በይሖዋ ስም ባሚኚ።
በተጚማሪም ለእስራኀላውያን ሁሉ፣ ለእያንዳንዱ ወንድና ሎት አንድ ዳቊ፣ አንድ ዹቮምር ጥፍጥፍና አንድ ዚዘቢብ ጥፍጥፍ አኚፋፈለ።
ኚዚያም ዚእስራኀልን አምላክ ይሖዋን ያኚብሩ፣ ያመሰግኑና ያወድሱ ዘንድ ዹተወሰኑ ሌዋውያንን በይሖዋ ታቊት ፊት እንዲያገለግሉ ሟመ።
መሪው አሳፍ ነበርፀ ኚእሱ ቀጥሎ ዘካርያስ ሁለተኛ ሆኖ ተሟመፀ ዚኢዔል፣ ሞሚራሞት፣ ዚሂኀል፣ ማቲትያህ፣ ኀልያብ፣ በናያህ፣ ኊቀድዔዶም እና ዚኢዔል ባለ አውታር መሣሪያዎቜና በገና ይጫወቱ ነበርፀ አሳፍ ደግሞ ሲምባል ይጫወት ነበርፀ
ካህናቱ በናያህ እና ያሃዚኀል በእውነተኛው አምላክ ዹቃል ኪዳን ታቊት ፊት ዘወትር መለኚት ይነፉ ነበር።
በዚያ ቀን ዳዊት ለመጀመሪያ ጊዜ ለይሖዋ ዚምስጋና መዝሙር በማቀናበር አሳፍና ወንድሞቹ እንዲዘምሩት ሰጣ቞ውፊ
“ይሖዋን አመስግኑፀ ስሙን ጥሩፀሥራውን በሕዝቊቜ መካኚል አስታውቁ!
ለእሱ ዘምሩፀ ዚውዳሎም መዝሙር ዘምሩለትፀአስደናቂ በሆኑት ሥራዎቹ ሁሉ ላይ አሰላስሉ።
በቅዱስ ስሙ ተኩራሩ። ይሖዋን ዹሚፈልጉ ሰዎቜ፣ ልባ቞ው ሐሎት ያድርግ።
ይሖዋንና ብርታቱን ፈልጉ። ፊቱን ሁልጊዜ እሹ።
ያኚናወና቞ውን አስደናቂ ሥራዎቜ፣ተአምራቱንና ዹተናገሹውን ፍርድ አስታውሱፀ
እናንተ ዚአገልጋዩ ዚእስራኀል ዘሮቜ፣እሱ ዚመሚጣቜሁ ዚያዕቆብ ልጆቜ፣ ይህን አስታውሱ።
እሱ ይሖዋ አምላካቜን ነው። ፍርዱ በመላው ምድር ላይ ነው።
ቃል ኪዳኑን ለዘላለም አስቡፀዚገባውን ቃል እስኚ ሺህ ትውልድ አስታውሱፀ
ኚአብርሃም ጋር ዚገባውን ቃል ኪዳን፣ለይስሐቅም በመሐላ ዚገባውን ቃል አስቡ።
ቃሉን ለያዕቆብ ድንጋጌ፣ለእስራኀልም ዘላቂ ቃል ኪዳን አድርጎ አቋቋመፀ
‘ዹኹነአንን ምድርርስትህ አድርጌ እሰጥሃለሁ’ አለ።
ይህን ዹተናገሹው በቁጥር ጥቂት፣አዎ፣ በጣም ጥቂት በነበራቜሁ ጊዜ ነውፀ በምድሪቱም ላይ ዚባዕድ አገር ሰዎቜ ነበራቜሁ።
እነሱም ኚአንዱ ብሔር ወደ ሌላው ብሔር፣ኚአንዱም መንግሥት ወደ ሌላው ሕዝብ ተንኚራተቱ።
ማንም እንዲጚቁና቞ው አልፈቀደምፀይልቁንም ለእነሱ ሲል ነገሥታትን ገሠጞፀ
‘ዚቀባኋ቞ውን አገልጋዮቌን አትንኩፀበነቢያ቎ም ላይ አንዳቜ ክፉ ነገር አታድርጉ’ አላ቞ው።
መላዋ ምድር ለይሖዋ ትዘምር! ማዳኑን በዹቀኑ አሳውቁ!
ክብሩን በብሔራት፣አስደናቂ ሥራዎቹንም በሕዝቊቜ ሁሉ መካኚል አስታውቁ።
ይሖዋ ታላቅ ነውናፀ ደግሞም እጅግ ሊወደስ ይገባዋል። ኚሌሎቜ አማልክት ሁሉ በላይ እጅግ ዚሚፈራ ነው።
ዚሌሎቜ ሕዝቊቜ አማልክት ሁሉ ኚንቱ ና቞ውፀይሖዋ ግን ሰማያትን ዚሠራ አምላክ ነው።
ሞገስና ግርማ በፊቱ ና቞ውፀብርታትና ደስታ እሱ በሚኖርበት ስፍራ ይገኛሉ።
እናንተ ዚሕዝብ ነገዶቜ፣ ለይሖዋ ዚሚገባውን ስጡፀኚክብሩና ኚብርታቱ ዚተነሳ ለይሖዋ ዚሚገባውን ስጡ።
ለስሙ ዚሚገባውን ክብር ለይሖዋ ስጡፀስጊታ ይዛቜሁ በፊቱ ቅሚቡ። ያጌጠ ዚቅድስና ልብስ ለብሳቜሁ ለይሖዋ ስገዱ።
ምድር ሁሉ በፊቱ ተንቀጥቀጪ! ምድር በጜኑ ተመሥርታለቜፀ ኚቊታዋ ልትንቀሳቀስ አትቜልም።
ሰማያት ሐሎት ያድርጉፀ ምድርም ደስ ይበላትፀበብሔራት መካኚል ‘ይሖዋ ነገሠ!’ ብላቜሁ አስታውቁ።
ባሕሩና በውስጡ ያለው ነገር ሁሉ ዚነጎድጓድ ድምፅ ያሰማፀመስኩና በላዩ ላይ ያለው ሁሉ ሐሎት ያድርግ።
ዚዱር ዛፎቜም በይሖዋ ፊት እልል ይበሉፀእሱ በምድር ላይ ለመፍሚድ እዚመጣ ነውና።
ይሖዋ ጥሩ ስለሆነ ምስጋና አቅርቡለትፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል።
እንዲህም በሉ፩ ‘አዳኝ አምላካቜን ሆይ፣ አድነንፀለቅዱስ ስምህ ምስጋና እንድናቀርብ፣አንተንም በማወደስ ሐሎት እንድናደርግ፣ኚብሔራት ሰብስበንፀ ኚእነሱም ታደገን።
ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋኹዘላለም እስኚ ዘላለም ይወደስ።’” ሕዝቡም ሁሉ “አሜን!” አሉፀ ይሖዋንም አወደሱ።
ኚዚያም ዳዊት በዕለታዊው ልማድ መሠሚት በታቊቱ ፊት ዘወትር እንዲያገለግሉ አሳፍንና ወንድሞቹን በዚያ በይሖዋ ዹቃል ኪዳን ታቊት ፊት ተዋ቞ው።
ኊቀድዔዶምና 68 ወንድሞቹ እንዲሁም ዚዚዱቱን ልጅ ኊቀድዔዶምና ሆሳ በር ጠባቂዎቜ ነበሩፀ
ካህኑ ሳዶቅና አብሚውት ዚሚያገለግሉት ካህናት ደግሞ በገባኊን በሚገኘው ኹፍ ያለ ቊታ፣ በይሖዋ ዚማደሪያ ድንኳን ፊት ነበሩፀ
ይህም ዹሆነው ዹሚቃጠል መባ በሚቀርብበት መሠዊያ ላይ ዘወትር ጠዋትና ማታ ለይሖዋ ዹሚቃጠል መባ እንዲያቀርቡና ይሖዋ ለእስራኀል በሰጠው ትእዛዝ መሠሚት በሕጉ ላይ ዹሰፈሹውን ሁሉ እንዲፈጜሙ ነው።
ይሖዋን ያመሰግኑ ዘንድ ሄማን እና ዚዱቱን እንዲሁም በስም ተጠቅሰው ዚተመሚጡት ዚቀሩት ሰዎቜ ኚእነሱ ጋር ነበሩፀ ምክንያቱም “ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል”ፀ
ደግሞም መለኚት፣ ሲምባልና እውነተኛውን አምላክ ለማወደስ ዚሚያገለግሉ ዹሙዚቃ መሣሪያዎቜን ይጫወቱ ዘንድ ሄማን እና ዚዱቱን ኚእነሱ ጋር ነበሩፀ ዚዚዱቱን ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ በር ላይ ተመድበው ነበር።
ኚዚያም ሕዝቡ ሁሉ ወደ ቀቱ ተመለሰፀ ዳዊትም ቀተሰቡን ለመባሚክ ወደ ቀቱ ሄደ።
ዚእስራኀል ዚበኩር ልጅ ዹሆነው ዚሮቀል ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ና቞ው። እሱ በኩር ቢሆንም እንኳ ዚአባቱን መኝታ ስላሚኚሰ ዚብኩርና መብቱ ለእስራኀል ልጅ ለዮሎፍ ወንዶቜ ልጆቜ ተሰጠፀ ኹዚህም ዚተነሳ በትውልድ ሐሹግ መዝገቡ ላይ ዚብኩርና መብት እንዳለው ተደርጎ አልተመዘገበም።
ይሁዳ ኚወንድሞቹ ዚሚበልጥ ኹመሆኑም ሌላ መሪ ዹሚሆነው ዹተገኘው ኚእሱ ነውፀ ሆኖም ዚብኩርና መብቱን ያገኘው ዮሎፍ ነበር።
ዚእስራኀል ዚበኩር ልጅ ዚሮቀል ወንዶቜ ልጆቜ ሃኖክ፣ ፓሉ፣ ኀስሮን እና ካርሚ ነበሩ።
ሞማያህ ዚኢዩኀል ልጅ ነበርፀ ዚሞማያህ ልጅ ጎግ፣ ዹጎግ ልጅ ሺምአይ፣
ዚሺምአይ ልጅ ሚክያስ፣ ዚሚክያስ ልጅ ሚአያህ፣ ዚሚአያህ ልጅ ባአል፣
ዚባአል ልጅ ቀኀራህ ነበርፀ ዹአሩር ንጉሥ ቎ልጌል቎ልፌልሶር ዚሮቀላውያን አለቃ ዹሆነውን ቀኀራህን በግዞት ወሰደው።
ወንድሞቹ በዚቀተሰቊቻ቞ውና በዹዘር ሐሹጋቾው ሲዘሚዘሩ እንደሚኚተለው ነው፩ መሪ ዹሆነው ዚኢዔል፣ ዘካርያስ፣
ዚኢዩኀል ልጅ፣ ዚሌማ ልጅ፣ ዹአዛዝ ልጅ ቀላፀ እሱ ኚአሮዔር አንስቶ እስኚ ነቩ እንዲሁም እስኚ በዓልመዖን ድሚስ ይኖር ነበር።
መንጎቻ቞ው በጊልያድ ምድር እጅግ በዝተው ስለነበር በስተ ምሥራቅ በኀፍራጥስ ወንዝ በኩል እስካለው፣ ምድሚ በዳው እስኚሚጀምርበት ቊታ ድሚስ ሰፈሚ።
በሳኊል ዘመን በአጋራውያን ላይ ጊርነት ኹፍተው ድል መቷ቞ውፀ በመሆኑም ኚጊልያድ በስተ ምሥራቅ ባለው ክልል ሁሉ በድንኳኖቻ቞ው ውስጥ ኖሩ።
ኚእነሱ ጋር ዚሚዋሰኑት ዚጋድ ዘሮቜ ደግሞ ኚባሳን አንስቶ እስኚ ሳልካ ባለው ምድር ላይ ኖሩ።
ኢዩኀል መሪ ነበርፀ ሁለተኛው ሻፋም ሲሆን ያናይ እና ሻፋጥ ደግሞ በባሳን መሪዎቜ ነበሩ።
ኚአባቶቻ቞ው ቀት ዚሆኑት ወንድሞቻ቞ውም ሚካኀል፣ መሹላም፣ ሳባ፣ ዮራይ፣ ያካን፣ ዚአ እና ኀቀር ሲሆኑ በአጠቃላይ ሰባት ነበሩ።
እነዚህ ዚቡዝ ልጅ፣ ዚያህዶ ልጅ፣ ዚዚሺሻይ ልጅ፣ ዚሚካኀል ልጅ፣ ዚጊልያድ ልጅ፣ ዚያሮሃ ልጅ፣ ዚሁሪ ልጅ፣ ዚአቢሃይል ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
ዚአባቶቻ቞ው ቀት መሪ ዹጉኒ ልጅ፣ ዚአብዲዔል ልጅ አሂ ነበር።
እነሱም በጊልያድ፣ በባሳን፣ በእነሱ ሥር ባሉት ኚተሞቜ እንዲሁም በሳሮን ዚግጊሜ መሬቶቜ ሁሉ እስኚ ዳርቻዎቻ቞ው ድሚስ ተቀመጡ።
እነዚህ ሁሉ በይሁዳ ንጉሥ በኢዮዓታም እና በእስራኀል ንጉሥ በኢዮርብዓም ዘመን በትውልድ መዝገቡ ላይ ሰፈሩ።
ሮቀላውያን፣ ጋዳውያንና ዹምናሮ ነገድ እኩሌታ 44,760 ኃያላን ተዋጊዎቜን ያቀፈ ሠራዊት ነበራ቞ውፀ እነሱም ጋሻና ሰይፍ ዚታጠቁ፣ ደጋን ያነገቡና ለውጊያ ዹሠለጠኑ ነበሩ።
እነዚህ ተዋጊዎቜ በአጋራውያን፣ በዚጡር፣ በናፊሜ እና በኖዳብ ላይ ጊርነት ኚፈቱ።
በጊርነቱ ወቅት አምላክ እንዲሚዳ቞ው ስለጠዚቁ እንዲሁም በእሱ ስለታመኑና እሱም ልመናቾውን ስለሰማ ኚእነሱ ጋር በሚዋጉበት ጊዜ እርዳታ አገኙፀ በመሆኑም አጋራውያንና ኚእነሱ ጋር ዚነበሩት ሁሉ እጃ቞ው ላይ ወደቁ።
እነሱም መንጎቻ቞ውን ይኾውም 50,000 ግመሎቜ፣ 250,000 በጎቜና 2,000 አህዮቜ እንዲሁም 100,000 ሰዎቜ ማሚኩ።