text
stringlengths
4
267
ያቀጜ እንዲህ ሲል ዚእስራኀልን አምላክ ተማጾነ፩ “እንድትባርኚኝና ግዛቮን እንድታሰፋልኝ እንዲሁም ጉዳት እንዳይደርስብኝ እጅህ ኚእኔ ጋር እንድትሆንና ኚጥፋት እንድትጠብቀኝ እለምንሃለሁ!” አምላክም ዹለመነውን ሰጠው።
ዚሹሃ ወንድም ኚሉብ መሂርን ወለደፀ መሂርም ኀሜቶንን ወለደ።
ኀሜቶን ቀትራፋን፣ ፓሰአህን እና ዚኢርናሃሜ አባት ዹሆነውን ተሂናን ወለደ። እነዚህ ዚሚካ ሰዎቜ ነበሩ።
ዹቀናዝ ወንዶቜ ልጆቜ ኊትኒኀል እና ሰራያህ ነበሩፀ ዚኊትኒኀል ልጅ ደግሞ ሃታት ነበር።
መኊኖታይ ኊፍራን ወለደ። ሰራያህ ዚገሃራሺም አባት ዹሆነውን ኢዮዓብን ወለደፀ እንዲህ ተብለው ዚተጠሩት ዚእጅ ጥበብ ባለሙያዎቜ ስለነበሩ ነው።
ዹዹፎኒ ልጅ ዚካሌብ ወንዶቜ ልጆቜ ኢሩ፣ ኀላህ እና ናአም ነበሩፀ ዚኀላህ ልጅ ቀናዝ ነበር።
ዹይሃሌልዔል ወንዶቜ ልጆቜ ዚፍ፣ ዚፋ፣ ቲሪያ እና አሳርኀል ነበሩ።
ዚኀዝራ ወንዶቜ ልጆቜ ዚ቎ር፣ መሬድ፣ ኀፌር እና ያሎን ነበሩፀ እሷ ሚርያምን፣ ሻማይን እና ዚኀሜተሞዓ አባት ዹሆነውን ይሜባን ወለደቜ።
(አይሁዳዊት ሚስቱ ደግሞ ዚጌዶርን አባት ዚሬድን፣ ዚሶኮን አባት ሄቀርን እና ዹዛኖሃን አባት ዚቁቲኀልን ወለደቜ።) እነዚህ ዚመሬድ ሚስት ዚሆነቜው ዹፈርዖን ልጅ ዚቢትያ ወንዶቜ ልጆቜ ና቞ው።
ዹናሃም እህት ዚሆነቜው ዚሆዲያህ ሚስት ወንዶቜ ልጆቜ ዚጋርሚያዊው ዚቀኢላና ዚማአካታዊው ዚኀሜተሞዓ አባቶቜ ነበሩ።
ዚሺሞን ወንዶቜ ልጆቜ አምኖን፣ ሪና፣ ቀንሃናን እና ቲሎን ነበሩ። ዚይሜኢ ወንዶቜ ልጆቜ ዞሄት እና ቀንዞሄት ነበሩ።
ዚይሁዳ ልጅ ዹሆነው ዹሮሎም ወንዶቜ ልጆቜ ዚሚኚተሉት ናቾው፩ ዹለቃ አባት ኀር፣ ዚማሬሻህ አባት ላአዳ እንዲሁም (ጥራት ያለው ጹርቅ ዚሚያመርቱት ሠራተኞቜ ወገን ዚሆኑት) ዚአሜቀዓ ቀት ሰዎቜ፣
ዮቂም፣ ዚኮዜባ ሰዎቜ፣ ሞዓባውያን ሎቶቜን ያገቡት ዮአስ እና ሳራፍ እንዲሁም ያሹቢላሔም። እነዚህ መዛግብት ጥንታዊ ና቞ው።
እነሱም በነጣኢም እና በገዎራ ዚሚኖሩ ሾክላ ሠሪዎቜ ነበሩ። ለንጉሡ እዚሠሩ በዚያ ይኖሩ ነበር።
ዚስምዖን ወንዶቜ ልጆቜ ነሙኀል፣ ያሚን፣ ያሪብ፣ ዛራ እና ሻኡል ና቞ው።
ዚሻኡል ልጅ ሻሉም፣ ዚሻሉም ልጅ ሚብሳም እና ዚሚብሳም ልጅ ሚሜማ ነበሩ።
ሃሙኀል ዚሚሜማ ልጅ ነበርፀ ዚሃሙኀል ልጅ ዛኩር፣ ዚዛኩር ልጅ ሺምአይ ነበር።
ሺምአይ 16 ወንዶቜና 6 ሎቶቜ ልጆቜ ነበሩትፀ ወንድሞቹ ግን ብዙ ወንዶቜ ልጆቜ አልነበሯ቞ውምፀ ኚቀተሰቊቻ቞ውም መካኚል እንደ ይሁዳ ሰዎቜ ብዙ ልጆቜ ያለው አልነበሚም።
እነሱ ዚኖሩባ቞ው ቊታዎቜ እነዚህ ናቾው፩ ቀርሳቀህ፣ ሞላዳ፣ ሃጻርሹአል፣
ባላ፣ ኀጌም፣ ቶላድ፣
ባቱኀል፣ ሆርማ፣ ጺቅላግ፣
ቀትማርካቊት፣ ሃጻርሱሲም፣ ቀትቢርኢ እና ሻአራይም። ዳዊት እስኚ ነገሠበት ጊዜ ድሚስ በእነዚህ ኚተሞቜ ይኖሩ ነበር።
ሰፈሮቻ቞ው ኀጣም፣ አይን፣ ሪሞን፣ ቶኚን እና አሻን ሲሆኑ በአጠቃላይ አምስት ኚተሞቜ ነበሩፀ
በእነዚህም ኚተሞቜ ዙሪያ ያሉት ሰፈሮቻ቞ው እስኚ ባአል ድሚስ ይደርሱ ነበር። ዚትውልድ መዝገባ቞ውና ዚመኖሪያ ቊታዎቻ቞ው ዝርዝር ይህ ነው።
በተጚማሪም መሟባብ፣ ያምሌክ፣ ዚአሜስያስ ልጅ ዮሻ፣
ኢዩኀል፣ ዚአሲዔል ልጅ፣ ዚሰራያህ ልጅ፣ ዚዮሜቢያህ ልጅ ኢዩ፣
ኀሊዮዔናይ፣ ያዕቆባ፣ ዚሟሃያህ፣ አሳያህ፣ አዲዔል፣ ዚሲሚኀል፣ በናያህ፣
ዚሞማያህ ልጅ፣ ዚሺምሪ ልጅ፣ ዚዚዳያህ ልጅ፣ ዹአሎን ልጅ፣ ዚሺፊ ልጅ ዚዛፀ
እነዚህ በስም ዚተዘሚዘሩት ሰዎቜ ዚዚቀተሰቊቻ቞ው አለቆቜ ና቞ውፀ ዚወገኖቻ቞ውም ቁጥር እዚበዛ ሄደ።
እነሱም ለመንጎቻ቞ው ዚግጊሜ መሬት ለማግኘት እስኚ ጌዶር መግቢያ፣ በሾለቆው በስተ ምሥራቅ በኩል እስካለው ስፍራ ድሚስ ሄዱ።
በመጚሚሻም ለም ዹሆነ ጥሩ ዚግጊሜ መሬት አገኙፀ ምድሪቱም እጅግ ሰፊ እንዲሁም ሰላምና ጞጥታ ዚሰፈነባት ነበሚቜ። በቀድሞ ዘመን በዚያ ዚሚኖሩት ዚካም ዝርያዎቜ ነበሩ።
እነዚህ በስም ዚተዘሚዘሩት በይሁዳ ንጉሥ በሕዝቅያስ ዘመን መጥተው ዚካም ዝርያዎቜን ድንኳንና በዚያ ይኖሩ ዚነበሩትን መኡኒማውያንን መቱ። ፈጜመውም አጠፏ቞ውፀ እስኚ ዛሬም ድሚስ ደብዛ቞ው ዚለምፀ በዚያ ለመንጎቻ቞ው ዹሚሆን ዚግጊሜ መሬት ስለነበር በእነሱ ቊታ ላይ ሰፈሩ።
ኚስምዖናውያን መካኚል ዚተወሰኑት ይኾውም 500 ወንዶቜ በይሜኢ ወንዶቜ ልጆቜ በጰላጥያህ፣ በነአርያህ፣ በሚፋያህ እና በዑዚኀል መሪነት ወደ ሮይር ተራራ ወጡ።
እነሱም ኚአማሌቃውያን መካኚል አምልጠው ዚቀሩትን ሰዎቜ መቱፀ እስኚ ዛሬም ድሚስ በዚያ ይኖራሉ።
በዓመቱ መባቻ፣ ነገሥታት ለውጊያ በሚዘምቱበት ወቅት ኢዮዓብ ዹጩር ሠራዊቱን በመምራት ዚአሞናውያንን ምድር አወደመፀ ወደ ራባ ሄዶም ኚበባትፀ በዚህ ጊዜ ዳዊት ኢዚሩሳሌም ቀርቶ ነበር። ኢዮዓብም በራባ ላይ ጥቃት ሰንዝሮ አፈራሚሳት።
ኚዚያም ዳዊት ዚማልካምን ዘውድ ኚራሱ ላይ ወሰደፀ ዚዘውዱም ክብደት አንድ ታላንት ወርቅ ነበርፀ በላዩም ላይ ዚኚበሩ ድንጋዮቜ ነበሩፀ ዘውዱም በዳዊት ራስ ላይ ተደሚገ። በተጚማሪም ኹኹተማዋ በጣም ብዙ ምርኮ ወሰደ።
ነዋሪዎቿንም አውጥቶ ድንጋይ እንዲቆርጡ፣ ስለት ባላ቞ው ዚብሚት መሣሪያዎቜና በመጥሚቢያ እንዲሠሩ አደሚጋ቞ው። ዳዊት በአሞናውያን ኚተሞቜ ሁሉ እንዲሁ አደሚገ። በመጚሚሻም ዳዊትና ሠራዊቱ ሁሉ ወደ ኢዚሩሳሌም ተመለሱ።
ኹዚህ በኋላ ኚፍልስጀማውያን ጋር በጌዜር ጊርነት ተኚፈተ። በዚህ ጊዜ ሁሻዊው ሲበካይ ዹሹፋይም ዘር ዹሆነውን ሲፓይን ገደለውፀ ፍልስጀማውያንም ድል ተመቱ።
ዳግመኛም ኚፍልስጀማውያን ጋር ጊርነት ተካሄደፀ ዚያኢር ልጅ ኀልሃናን ዹሾማኔ መጠቅለያ ዚሚመስል ዘንግ ያለው ጩር ይዞ ዹነበሹውን ዚጎልያድን ወንድም ጌታዊውን ላህሚን ገደለው።
እንደገናም በጌት ጊርነት ተቀሰቀሰፀ በዚያም በእጆቹ ላይ ስድስት ስድስት ጣቶቜ በእግሮቹም ላይ ስድስት ስድስት ጣቶቜ፣ በድምሩ 24 ጣቶቜ ያሉት በጣም ግዙፍ ዹሆነ ሰው ነበርፀ እሱም ዹሹፋይም ዘር ነበር።
ይህ ሰው እስራኀልን ይገዳደር ስለነበር ዚዳዊት ወንድም ዚሺምአ ልጅ ዮናታን ገደለው።
እነዚህ በጌት ዚሚኖሩ ዹሹፋይም ዘሮቜ ነበሩፀ እነሱም በዳዊት እጅና በአገልጋዮቹ እጅ ወደቁ።
ዳዊት ኚቂስ ልጅ ኚሳኊል ዚተነሳ ተደብቆ ይኖር በነበሚበት ጊዜ እሱ ወዳለበት ወደ ጺቅላግ ዚመጡት ሰዎቜ እነዚህ ና቞ውፀ እነሱም በጊርነት ኚሚዱት ኃያላን ተዋጊዎቜ መካኚል ነበሩ።
ቀስት ዚታጠቁ ነበሩፀ በቀኝ እጃ቞ውም ሆነ በግራ እጃ቞ው ድንጋይ መወንጹፍ ወይም ፍላጻ ማስፈንጠር ይቜሉ ነበር። እነሱ ኚቢንያም ነገድ ሲሆኑ ዚሳኊል ወንድሞቜ ነበሩ።
መሪያ቞ው አሂዔዜር ሲሆን ኚእሱ ጋር ዮአስ ነበርፀ ሁለቱም ዚጊብዓዊው ዹሾማህ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ ደግሞም ዚአዝማዌት ወንዶቜ ልጆቜ ዚዚኀል እና ጎሌጥ፣ ቀራካ፣ አናቶታዊው ኢዩ፣
ኚሠላሳዎቹ አለቆቜ መካኚል ኃያል ተዋጊና ዚሠላሳዎቹ መሪ ዹሆነው ገባኊናዊው ይሜማያህፀ በተጚማሪም ኀርምያስ፣ ያሃዚኀል፣ ዮሃናን፣ ገዎራዊው ዮዛባድ፣
ኀልዑዛይ፣ ዚሪሞት፣ በአልያህ፣ ሞማርያህ፣ ሃሪፋዊው ሰፋጥያህ፣
ቆሬያውያን ዚሆኑት ሕልቃና፣ ይሜሺያህ፣ አዛርዔል፣ ዮኀዘር፣ ያሟብአምፀ
ዚጌዶር ሰው ዹሆነው ዚዚሮሃም ወንዶቜ ልጆቜ ዮኀላ እና ዘባድያህ ነበሩ።
አንዳንድ ጋዳውያን ዳዊት ወዳለበት በምድሚ በዳ ወደሚገኘው ምሜግ መጥተው ኚእሱ ጎን ተሰለፉፀ እነሱም ኃያላን ተዋጊዎቜና ለጊርነት ዹሠለጠኑ ወታደሮቜ ሲሆኑ ትልቅ ጋሻና ሹጅም ጩር ታጥቀው ዚሚጠባበቁ ነበሩፀ ፊታ቞ው እንደ አንበሳ ፊት ነበርፀ በተራሮቜም ላይ እንደ ሜዳ ፍዹል ፈጣኖቜ ነበሩ።
ኀጌር መሪ ነበርፀ ሁለተኛው አብድዩ፣ ሊስተኛው ኀልያብ፣
አራተኛው ሚሜማና፣ አምስተኛው ኀርምያስ፣
ስድስተኛው አታይ፣ ሰባተኛው ኀሊዔል፣
ስምንተኛው ዮሃናን፣ ዘጠነኛው ኀልዛባድ፣
አሥሚኛው ኀርምያስ፣ አሥራ አንደኛው ማክባናይ ነበሩ።
እነዚህ ዚሠራዊቱ መሪዎቜ ዹሆኑ ጋዳውያን ነበሩ። ታናሜ ዹሆነው 100 ወታደሮቜን፣ ታላቅ ዹሆነውም 1,000 ወታደሮቜን ይቋቋም ነበር።
በመጀመሪያው ወር ዮርዳኖስ ኹአፍ እስኚ ገደፉ ሞልቶ እዚፈሰሰ ሳለ፣ ወንዙን አቋርጠው በቆላው ዚሚኖሩትን ሰዎቜ ሁሉ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ ያባሚሩት እነዚህ ነበሩ።
በተጚማሪም ኚቢንያምና ኚይሁዳ ሰዎቜ መካኚል አንዳንዶቹ ዳዊት ወደሚኖርበት ወደ ምሜጉ መጡ።
ዳዊትም ወደ እነሱ ወጥቶ እንዲህ አላቾው፩ “ዚመጣቜሁት በሰላም ኹሆነና እኔን ለመርዳት ኹሆነ ልቀ ኚእናንተ ጋር አንድ ይሆናል። ሆኖም እጄ ኹበደል ንጹሕ ሆኖ ሳለ ለጠላቶቌ አሳልፋቜሁ ልትሰጡኝ ኹሆነ ዚአባቶቻቜን አምላክ ጉዳዩን አይቶ ይፍሚድ።”
ኚዚያም ዚሠላሳዎቹ መሪ በሆነው በአማሳይ ላይ መንፈስ ወሚደበትፀ እሱም እንዲህ አለ፩ “ዳዊት ሆይ፣ እኛ ዹአንተ ነንፀ ዚእሎይ ልጅ ሆይ፣ እኛ ኹአንተ ጋር ነን። ሰላም፣ አዎ ሰላም ለአንተ ይሁንፀ አንተን ለሚሚዳም ሰላም ይሁንፀአምላክህ እዚሚዳህ ነውና።” ስለዚህ ዳዊት ተቀበላ቞ውፀ በሠራዊቱም መሪዎቜ መካኚል ሟማ቞ው።
ኹምናሮ ነገድ ዹሆኑ አንዳንድ ሰዎቜም ኚድተው ወደ እሱ መጡፀ በዚህ ጊዜ ዳዊት ኚፍልስጀማውያን ጋር ሆኖ ሳኊልን ለመውጋት ወጥቶ ነበርፀ ሆኖም ፍልስጀማውያንን አልሚዳ቞ውምፀ ምክንያቱም ዚፍልስጀም ገዢዎቜ ኚተመካኚሩ በኋላ “ኚድቶ ወደ ጌታው ወደ ሳኊል በመሄድ እኛን ያስጚርሰናል” ሲሉ መልሰውት ነበር።
ዳዊት ወደ ጺቅላግ በሄደ ጊዜ ኹምናሮ ነገድ ኚድተው ወደ እሱ ዚመጡት አድናህ፣ ዮዛባድ፣ ዚዲአዔል፣ ሚካኀል፣ ዮዛባድ፣ ኀሊሁ እና ጺለታይ ሲሆኑ እነሱም ኹምናሮ ነገድ ዹሆኑ ዚሺህ አለቆቜ ነበሩ።
ሁሉም ኃያልና ደፋር ስለነበሩ ዳዊት ኚወራሪ ኃይሎቜ ጋር በሚያደርገው ውጊያ ሚዱት። ኚዚያም በሠራዊቱ ውስጥ አለቆቜ ሆኑ።
ሠራዊቱም እንደ አምላክ ሠራዊት ታላቅ እስኪሆን ድሚስ፣ ዳዊትን ለመርዳት በዚዕለቱ ብዙ ሰዎቜ ይጎርፉ ነበር።
በይሖዋ ትእዛዝ መሠሚት ዚሳኊልን ንግሥና ወደ ዳዊት ለማስተላለፍ በኬብሮን ወደሚገኘው ወደ ዳዊት ዚመጡት ለውጊያ ዚታጠቁ መሪዎቜ ቁጥር ይህ ነው።
ትልቅ ጋሻና ሹጅም ጩር ዚያዙ ለውጊያ ዚታጠቁ ዚይሁዳ ሰዎቜ 6,800 ነበሩ።
ኚስምዖናውያን መካኚል ኚሠራዊቱ ጋር ዹተቀላቀሉ 7,100 ኃያልና ደፋር ሰዎቜ ነበሩ።
ኚሌዋውያን 4,600 ነበሩ።
ዮዳሄ ዚአሮን ልጆቜ መሪ ዹነበሹ ሲሆን ኚእሱም ጋር 3,700 ሰዎቜ ነበሩፀ
በተጚማሪም ሳዶቅ ዚተባለው ኃያልና ደፋር ወጣት ኚአባቶቹ ቀት ኚተውጣጡ 22 አለቆቜ ጋር መጣ።
ዚሳኊል ወንድሞቜ ኚሆኑት ቢንያማውያን መካኚል 3,000 ነበሩፀ ቀደም ሲል ብዙዎቹ ዚሳኊልን ቀት በታማኝነት ይደግፉ ነበር።
ኚኀፍሬማውያን መካኚል ኚአባቶቻ቞ው ቀት ዚተውጣጡ 20,800 ኃያል፣ ደፋርና ስመ ጥር ሰዎቜ ነበሩ።
ኹምናሮ ነገድ እኩሌታ ዳዊትን ለማንገሥ ዚመጡ በስም ዚተጠቀሱ 18,000 ሰዎቜ ነበሩ።
ኚይሳኮር ነገድ መካኚል ዘመኑን ያስተዋሉና እስራኀል ምን ማድሚግ እንዳለበት ዚተገነዘቡ 200 መሪዎቜ ነበሩፀ ወንድሞቻ቞ውም ሁሉ እነሱን ይታዘዙ ነበር።
ኚዛብሎን ነገድ በሠራዊቱ ውስጥ ማገልገል ዚሚቜሉ፣ ለውጊያ ዝግጁ ዹሆኑና ልዩ ልዩ ዓይነት መሣሪያዎቜ ዚታጠቁ 50,000 ሰዎቜ ነበሩፀ ሁሉም ወደ ዳዊት ዚመጡት በፍጹም ታማኝነት ነበር።
ኚንፍታሌም ነገድ 1,000 አለቆቜ ነበሩፀ ኚእነሱም ጋር ትልቅ ጋሻና ጩር ዚያዙ 37,000 ሰዎቜ ነበሩ።
ኚዳናውያን ለጊርነት ዝግጁ ዹሆኑ 28,600 ሰዎቜ ነበሩ።
ኹአሮር ነገድ ደግሞ ለጊርነት ዝግጁ ሆነው በሠራዊቱ ውስጥ ማገልገል ዚሚቜሉ 40,000 ሰዎቜ ነበሩ።
ኚዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ካሉት ኚሮቀላውያን፣ ኚጋዳውያንና ኹምናሮ ነገድ እኩሌታ ለጊርነት ዚሚያስፈልጉ ዚተለያዩ መሣሪያዎቜን ዚታጠቁ 120,000 ወታደሮቜ ነበሩ።
እነዚህ ሁሉ በአንድነት ለውጊያ ዹተሰለፉና ለጊርነት ዝግጁ ዹሆኑ ወታደሮቜ ነበሩፀ ዳዊትን በመላው እስራኀል ላይ ለማንገሥ በአንድ ልብ ሆነው ወደ ኬብሮን መጡፀ በተጚማሪም ዹቀሹው ዚእስራኀል ሕዝብ ሁሉ በአንድ ልብ ሆኖ ዳዊትን ለማንገሥ ተነሳ።
ወንድሞቻ቞ው አዘጋጅተውላቾው ስለነበር በዚያ እዚበሉና እዚጠጡ ኚዳዊት ጋር ሊስት ቀን ቆዩ።
በተጚማሪም በአቅራቢያ቞ው ያሉትም ሆኑ እስኚ ይሳኮር፣ ዛብሎንና ንፍታሌም ድሚስ ርቀው ዚሚገኙት ሰዎቜ በአህያ፣ በግመል፣ በበቅሎና በኚብት ምግብ ጭነው መጡፀ ይኾውም ኹፍተኛ መጠን ያለው ዱቄት፣ ዚበለስና ዚዘቢብ ጥፍጥፍ፣ ዹወይን ጠጅ፣ ዘይት፣ ኚብትና በግ ነበርፀ በእስራኀል ታላቅ ደስታ ሰፍኖ ነበርና።
ኹጊዜ በኋላም ዳዊት ፍልስጀማውያንን ድል በማድሚግ በቁጥጥር ሥር አዋላ቞ውፀ ጌትንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜም ኚፍልስጀማውያን እጅ ወሰደ።
ኚዚያም ሞዓብን ድል አደሚገፀ ሞዓባውያንም ዚዳዊት አገልጋዮቜ ሆኑፀ ግብርም ገበሩለት።
ዚጟባህ ንጉሥ ሃዳድኀዜር በኀፍራጥስ ወንዝ ላይ ያለውን ዚበላይነት ለማጠናኹር በሄደ ጊዜ ዳዊት በሃማት አቅራቢያ ድል አደሚገው።
ዳዊት ኚእሱ ላይ 1,000 ሠሚገሎቜ፣ 7,000 ፈሚሰኞቜና 20,000 እግሚኛ ወታደሮቜ ማሚኚ። ኚዚያም ዳዊት 100 ዹሠሹገላ ፈሚሶቜን ብቻ አስቀርቶ ሌሎቹን በሙሉ ቋንጃቾውን ቆሚጠ።
ዚደማስቆዎቹ ሶርያውያን፣ ዚጟባህን ንጉሥ ሃዳድኀዜርን ለመርዳት በመጡ ጊዜ ዳዊት ኚሶርያውያን መካኚል 22,000 ሰዎቜን ገደለ።
ኚዚያም ዳዊት በደማስቆ ሶርያ ዹጩር ሰፈሮቜ አቋቋመፀ ሶርያውያንም ዚዳዊት አገልጋዮቜ ሆኑፀ ግብርም ገበሩለት። ይሖዋ ዳዊትን በሄደበት ሁሉ ድል አቀዳጀው።
በተጚማሪም ዳዊት ኚሃዳድኀዜር አገልጋዮቜ ላይ ኹወርቅ ዚተሠሩ ክብ ጋሻዎቜን ወሰደፀ ወደ ኢዚሩሳሌምም አመጣ቞ው።
ዳዊት ዚሃዳድኀዜር ኚተሞቜ ኚሆኑት ኚጢብሃትና ኚኩን እጅግ ብዙ መዳብ ወሰደ። ሰለሞን ዚመዳቡን ባሕር፣ ዓምዶቹንና ዚመዳብ ዕቃዎቹን ዚሠራው በዚህ ነበር።
ዚሃማት ንጉሥ ቶዑ፣ ዳዊት ዚጟባህን ንጉሥ ዚሃዳድኀዜርን ሠራዊት በሙሉ ድል እንዳደሚገ በሰማ ጊዜ
ደህንነቱን እንዲጠይቅና ኚሃዳድኀዜር ጋር ተዋግቶ ድል በማድሚጉ ዹተሰማውን ደስታ እንዲገልጜለት ልጁን ሃዶራምን ወዲያውኑ ወደ ንጉሥ ዳዊት ላኹው (ሃዳድኀዜር ኚቶዑ ጋር ብዙ ጊዜ ይዋጋ ነበርና)ፀ እሱም ኚወርቅ፣ ኚብርና ኚመዳብ ዚተሠሩ ብዙ ዓይነት ዕቃዎቜን ይዞ መጣ።
ንጉሥ ዳዊት እነዚህን ዕቃዎቜ ኹሁሉም ብሔራት ይኾውም ኚኀዶም፣ ኚሞዓብ፣ ኚአሞናውያን፣ ኚፍልስጀማውያንና ኚአማሌቃውያን ኹማሹኹው ብርና ወርቅ ጋር ለይሖዋ ቀደሰ።
ዚጜሩያ ልጅ አቢሳ በጹው ሾለቆ 18,000 ኀዶማውያንን ገደለ።
እሱም በኀዶም ዹጩር ሰፈሮቜ አቋቋመፀ ኀዶማውያንም ሁሉ ዚዳዊት አገልጋዮቜ ሆኑ። ይሖዋ ዳዊትን በሄደበት ሁሉ ድል አቀዳጀው።
ዳዊት በመላው እስራኀል ላይ መግዛቱን ቀጠለፀ ለሕዝቡም ሁሉ ፍትሕንና ጜድቅን አሰፈነላ቞ው።
ዚጜሩያ ልጅ ኢዮዓብ ዚሠራዊቱ አዛዥ ነበርፀ ዚአሂሉድ ልጅ ኢዮሳፍጥ ታሪክ ጾሐፊ ነበርፀ
ዚአኪጡብ ልጅ ሳዶቅና ዚአብያታር ልጅ አሂሜሌክ ካህናት ነበሩፀ ሻውሻ ደግሞ ጾሐፊ ነበር።
ዚዮዳሄ ልጅ በናያህ ዚኚሪታውያንና ዚጎሌታውያን አዛዥ ነበር። ዚዳዊት ወንዶቜ ልጆቜም ኚንጉሡ ቀጥሎ ዋና ባለሥልጣናት ነበሩ።
ዳዊት በሾመገለና ዚሕይወቱ ፍጻሜ በተቃሹበ ጊዜ ልጁን ሰለሞንን በእስራኀል ላይ አነገሠው።