text
stringlengths
4
267
ኹምናሮ ነገድ እኩሌታ ላይ ደግሞ አኔርንና ዚግጊሜ መሬቶቿን እንዲሁም ቢልአምንና ዚግጊሜ መሬቶቿን ለቀሩት ዚቀአታውያን ቀተሰቊቜ ሰጧ቞ው።
ለጌርሳማውያን ኹምናሮ ነገድ እኩሌታ በባሳን ዚምትገኘውን ጎላንንና ዚግጊሜ መሬቶቿን እንዲሁም አስታሮትንና ዚግጊሜ መሬቶቿን መደቡላ቞ውፀ
ኚይሳኮር ነገድም ቃዎሜንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣ ዳብራትንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣
ራሞትንና ዚግጊሜ መሬቶቿን እንዲሁም አኔምንና ዚግጊሜ መሬቶቿን መደቡላ቞ውፀ
ኹአሮር ነገድም ማሻልንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣ አብዶንንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣
ሁቆቅንና ዚግጊሜ መሬቶቿን እንዲሁም ሬሆብንና ዚግጊሜ መሬቶቿን መደቡላ቞ውፀ
ኚንፍታሌም ነገድም በገሊላ ዚምትገኘውን ቃዎሜንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣ ሃሞንንና ዚግጊሜ መሬቶቿን እንዲሁም ቂርያታይምንና ዚግጊሜ መሬቶቿን ሰጧ቞ው።
ለቀሩት ሜራራውያን ኚዛብሎን ነገድ ላይ ሪሞኖንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣ ታቊርንና ዚግጊሜ መሬቶቿን መደቡላ቞ውፀ
ኚዮርዳኖስ ወንዝ በስተ ምሥራቅ፣ በኢያሪኮ ካለው ዚዮርዳኖስ አካባቢ ኚሮቀል ነገድ ላይ በምድሚ በዳ ዚምትገኘው ቀጌርና ዚግጊሜ መሬቶቿ፣ ያሃጜና ዚግጊሜ መሬቶቿ ተሰጧ቞ውፀ
ደግሞም ቀደሞትና ዚግጊሜ መሬቶቿ እንዲሁም መፋአትና ዚግጊሜ መሬቶቿ ተሰጧ቞ውፀ
ኚጋድ ነገድ ላይ ደግሞ በጊልያድ ዚምትገኘውን ራሞትንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣ ማሃናይምንና ዚግጊሜ መሬቶቿን፣
ሃሜቊንንና ዚግጊሜ መሬቶቿን እንዲሁም ያዜርንና ዚግጊሜ መሬቶቿን መደቡላ቞ው።
ንጉሥ ዳዊትም ለመላው ጉባኀ እንዲህ አለ፩ “አምላክ ዹመሹጠው ልጄ ሰለሞን ገና ወጣት ነውፀ ተሞክሮም ዚለውምፀ ሥራው ደግሞ ታላቅ ነውፀ ቀተ መቅደሱ ዚሚሠራው ለሰው ሳይሆን ለይሖዋ አምላክ ነውና።
እኔም አቅሜ በፈቀደው መጠን ለአምላኬ ቀት በወርቅ ለሚሠራው ወርቅ፣ በብር ለሚሠራው ብር፣ በመዳብ ለሚሠራው መዳብ፣ በብሚት ለሚሠራው ብሚትና በሳንቃ ለሚሠራው ሳንቃ እንዲሁም ኊኒክስ ድንጋዮቜ፣ በማያያዣ ዚሚጣበቁ ድንጋዮቜ፣ እንደ ጌጥ ዚሚያገለግሉ ልዩ ልዩ ሕብር ያላ቞ው ድንጋዮቜ፣ ማንኛውንም ዓይነት ዹኹበሹ ድንጋይና ዚአልባስጥሮስ ድንጋይ በብዛት አዘጋጅቻለሁ።
ኹዚህም በላይ ለአምላኬ ቀት ካለኝ ፍቅር ዚተነሳ ለቅዱሱ ቀት አስቀድሞ ካዘጋጀሁት በተጚማሪ ዹግል ሀብ቎ ዹሆነውን ወርቅና ብርም ለአምላኬ ቀት እሰጣለሁፀ
ኹዚህም ሌላ ዚቀቶቹን ግድግዳ ለመለበጥ 3,000 ታላንት ዹኩፊር ወርቅና 7,000 ታላንት ዚተጣራ ብር፣
በወርቅ ለሚሠራው ወርቅ፣ በብር ለሚሠራው ብር፣ ዚእጅ ጥበብ ባለሙያዎቜ ለሚሠሩትም ሥራ ሁሉ ዚሚያስፈልገውን እሰጣለሁ። ታዲያ ዛሬ ለይሖዋ ዚሚሰጥ ስጊታ በእጁ ይዞ ለመቅሚብ ፈቃደኛ ዹሆነ ማን ነው?”
በመሆኑም ዚአባቶቜ ቀቶቜ አለቆቜ፣ ዚእስራኀል ነገዶቜ አለቆቜ፣ ዚሺህ አለቆቜ፣ ዚመቶ አለቆቜና ዚንጉሡን ጉዳይ ዚሚያስፈጜሙት አለቆቜ በፈቃደኝነት ቀሚቡ።
ደግሞም ለእውነተኛው አምላክ ቀት አገልግሎት ዹሚውል 5,000 ታላንት ወርቅ፣ 10,000 ዳሪክ፣ 10,000 ታላንት ብር፣ 18,000 ታላንት መዳብና 100,000 ታላንት ብሚት ሰጡ።
ዚኚበሩ ድንጋዮቜ ያለው ሰው ሁሉ ጌድሶናዊው ዚሂኀል በኃላፊነት ለሚያስተዳድሚው በይሖዋ ቀት ላለው ግምጃ ቀት ሰጠ።
ሕዝቡ በፈቃደኝነት መባ በመስጠታ቞ው እጅግ ተደሰቱፀ በፈቃደኝነት ተነሳስተው ለይሖዋ መባ ዚሰጡት በሙሉ ልባ቞ው ነበርናፀ ንጉሥ ዳዊትም እጅግ ደስ አለው።
ኚዚያም ዳዊት በጉባኀው ሁሉ ፊት ይሖዋን አወደሰ። እንዲህም አለ፩ “ዚአባታቜን ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ ኹዘላለም እስኚ ዘላለም ውዳሎ ይድሚስህ።
ይሖዋ ሆይ፣ ታላቅነት፣ ኃያልነት፣ ውበት፣ ግርማና ሞገስ ዹአንተ ነውፀ በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ዹአንተ ነው። ይሖዋ ሆይ፣ መንግሥት ዹአንተ ነው። ኹሁሉም በላይ ኹፍ ኹፍ ያልክ ራስ ነህ።
ሀብትና ክብር ኹአንተ ነውፀ አንተም ሁሉንም ነገር ትገዛለህፀ ኃይልና ብርታት በእጅህ ነውፀ እጅህ ሁሉንም ታላቅ ማድሚግና ለሁሉም ብርታት መስጠት ይቜላል።
አሁንም አምላካቜን ሆይ፣ እናመሰግንሃለንፀ ውብ ዹሆነውን ስምህንም እናወድሳለን።
“ይሁንና በፈቃደኝነት ተነሳስተን እንዲህ ያለ መባ ማቅሚብ እንቜል ዘንድ እኔም ሆንኩ ሕዝቀ ማን ነን? ሁሉም ነገር ዹተገኘው ኹአንተ ነውናፀ ዹሰጠንህም ኹገዛ እጅህ ዹተቀበልነውን ነው።
እንደ አባቶቻቜን ሁሉ እኛም በፊትህ ዚባዕድ አገር ሰዎቜና ሰፋሪዎቜ ነንና። ዚሕይወት ዘመናቜን በምድር ላይ እንደ ጥላ ነውፀ ተስፋም ዚለውም።
አምላካቜን ይሖዋ ሆይ፣ ለቅዱስ ስምህ ቀት ለመሥራት ያዘጋጀነው ይህ ሁሉ ሀብት ዹተገኘው ኹገዛ እጅህ ነውፀ ሁሉም ዹአንተ ነው።
አምላኬ ሆይ፣ አንተ ልብን እንደምትመሚምርና በንጹሕ አቋም ደስ እንደምትሰኝ በሚገባ አውቃለሁ። እኔ በልቀ ቅንነት፣ በፈቃደኝነት ተነሳስቌ ይህን ሁሉ ነገር ሰጥቻለሁፀ ደግሞም እዚህ ዹተገኘው ሕዝብህ በፈቃደኝነት ተነሳስቶ ለአንተ መባ ሲያቀርብ በማዹቮ እጅግ ደስ ብሎኛል።
ዚአባቶቻቜን ዚአብርሃም፣ ዚይስሐቅና ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ ይህ ሕዝብ እንዲህ ያለ ዚፈቃደኝነት መንፈስና ዝንባሌ ይዞ ለዘላለም እንዲኖርና በሙሉ ልቡ እንዲያገለግልህ እርዳው።
ልጄ ሰለሞንም ትእዛዛትህን፣ ማሳሰቢያዎቜህንና ሥርዓቶቜህን እንዲጠብቅ ሙሉ ልብ ስጠውፀ እነዚህን ሁሉ ነገሮቜ እንዲያደርግና እኔ ባዘጋጀሁለት ነገሮቜ ቀተ መቅደስ እንዲገነባ እርዳው።”
ኚዚያም ዳዊት ለመላው ጉባኀ “አሁን፣ አምላካቜሁን ይሖዋን አወድሱ” አለ። ጉባኀውም ሁሉ ዚአባቶቻ቞ውን አምላክ ይሖዋን አወደሱፀ ለይሖዋና ለንጉሡም በግንባራ቞ው ተደፍተው ሰገዱ።
በማግስቱም ለይሖዋ መሥዋዕት መሠዋታ቞ውንና ለይሖዋ ዹሚቃጠል መባ ማቅሚባ቞ውን ቀጠሉፀ 1,000 ወይፈኖቜ፣ 1,000 አውራ በጎቜ፣ 1,000 ተባዕት ዹበግ ጠቊቶቜና ዚመጠጥ መባዎቜ አቀሚቡፀ ስለ እስራኀል ሁሉ ብዙ መሥዋዕት አቀሚቡ።
በዚያ ዕለት በይሖዋ ፊት በታላቅ ደስታ ይበሉና ይጠጡ ነበርፀ ደግሞም ዚዳዊትን ልጅ ሰለሞንን ለሁለተኛ ጊዜ አነገሡትፀ በይሖዋም ፊት መሪ አድርገው ቀቡትፀ ሳዶቅንም ካህን አድርገው ቀቡት።
ሰለሞንም በአባቱ በዳዊት ፋንታ በይሖዋ ዙፋን ላይ ንጉሥ ሆኖ ተቀመጠፀ እሱም ተሳካለትፀ እስራኀላውያንም ሁሉ ታዘዙለት።
መኳንንቱና ኃያላን ተዋጊዎቹ ሁሉ እንዲሁም ዚንጉሥ ዳዊት ወንዶቜ ልጆቜ ሁሉ ለንጉሥ ሰለሞን ተገዙለት።
ይሖዋም በእስራኀል ሁሉ ፊት ሰለሞንን እጅግ ታላቅ አደሚገውፀ ደግሞም በእስራኀል ኚእሱ በፊት ዚነበሩት ነገሥታት ያላገኙትን ንጉሣዊ ግርማ አጎናጞፈው።
በዚህ መንገድ ዚእሎይ ልጅ ዳዊት በእስራኀል ሁሉ ላይ ገዛፀ
በእስራኀልም ላይ ንጉሥ ሆኖ ዚገዛበት ጊዜ ርዝመት 40 ዓመት ነበር። በኬብሮን ለ7 ዓመት፣ በኢዚሩሳሌም ደግሞ ለ33 ዓመት ነገሠ።
እሱም አስደሳቜ ዹሆነ ብዙ ዘመን ኖሮ፣ ዕድሜ ጠግቩ እንዲሁም ብዙ ሀብትና ክብር አግኝቶ ሞተፀ ልጁ ሰለሞንም በእሱ ፋንታ ነገሠ።
ዚንጉሥ ዳዊት ታሪክ ኚመጀመሪያ አንስቶ እስኚ መጚሚሻ ድሚስ፣ ባለ ራእዩ ሳሙኀል፣ ነቢዩ ናታንና ባለ ራእዩ ጋድ ባዘጋጇ቞ው ጜሑፎቜ ውስጥ ሰፍሯልፀ
በተጚማሪም ስለ ንግሥናውና ስለ ኃያልነቱ ሁሉ እንዲሁም ኚእሱ፣ ኚእስራኀልና በዙሪያው ካሉ መንግሥታት ሁሉ ጋር በተያያዘ ስለተኚናወኑት ነገሮቜ ተጜፏል።
ቢንያም ዚበኩር ልጁን ቀላን፣ ሁለተኛ ልጁን አሜቀልን፣ ሊስተኛ ልጁን አሃራሕን፣
አራተኛ ልጁን ኖሃንና አምስተኛ ልጁን ራፋን ወለደ።
ዚቀላ ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ናቾው፩ አዳር፣ ጌራ፣ አቢሁድ፣
አቢሹዓ፣ ንዕማን፣ አሆዓሕ፣
ጌራ፣ ሌፉፋን እና ሁራም።
እነዚህ ዚኀሁድ ወንዶቜ ልጆቜ ይኾውም ወደ ማናሃት በግዞት ዚተወሰዱ በጌባ ይኖሩ ዚነበሩ ቀተሰቊቜ መሪዎቜ ናቾው፩
ንዕማን፣ አኪያህ እና ጌራፀ ሰዎቹን በዋነኝነት እዚመራ ወደ ግዞት ዚወሰዳ቞ው ጌራ ነበርፀ እሱም ዑዛን እና አሂሑድን ወለደ።
ሻሃራይም ሰዎቹን ኚሰደዳ቞ው በኋላ በሞዓብ ምድር ልጆቜ ወለደ። ሁሺም እና ባዓራ ሚስቶቹ ነበሩ።
ኚሚስቱ ኚሆዎሜ ዮባብን፣ ጺብያን፣ ሜሻን፣ ማልካምን፣
ዚኡጜን፣ ሳክያህን እና ሚርማን ወለደ። እነዚህ ወንዶቜ ልጆቹ ሲሆኑ ዚዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜ መሪዎቜ ነበሩ።
ኚሁሺም አቢጡብን እና ኀልጳዓልን ወለደ።
ዚኀልጳዓል ወንዶቜ ልጆቜ ኀቀር፣ ሚሻም፣ ኩኖን እንዲሁም ሎድንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜ ዹቆሹቆሹው ሻሜድ፣
በሪአ እና ሌማ ነበሩ። እነዚህ በአይሎን ይኖሩ ዚነበሩ ዚዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜ መሪዎቜ ና቞ው። ዚጌትን ነዋሪዎቜ ያሳደዱት እነሱ ነበሩ።
ደግሞም አሂዮ፣ ሻሻቅ፣ ዚሬሞት፣
ዘባድያህ፣ አራድ፣ ኀዎር፣
ሚካኀል፣ ይሜጳ እና ዮሃ ዚበሪአ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ
ዘባድያህ፣ መሹላም፣ ሂዝቂ፣ ሄቀር፣
ይሜመራይ፣ ይዝሊያ እና ዮባብ ዚኀልጳዓል ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ
ያቂም፣ ዚክሪ፣ ዛብዲ፣
ኀሊዔናይ፣ ጺለታይ፣ ኀሊዔል፣
አዳያህ፣ ቀራያህ እና ሺምራት ዚሺምአይ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ
ይሜጳን፣ ኀቀር፣ ኀሊዔል፣
አብዶን፣ ዚክሪ፣ ሃናን፣
ሃናንያህ፣ ኀላም፣ አንቶቲያህ፣
ይፍደያህ እና ጰኑኀል ዚሻሻቅ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩፀ
ሻምሞራይ፣ ሞሃሪያህ፣ ጎቶልያ፣
ያአሬሜያህ፣ ኀልያስ እና ዚክሪ ዚዚሮሃም ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
እነዚህ በትውልድ ሐሹግ መዝገቡ ላይ ተጜፎ በሚገኘው መሠሚት ዚዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜ መሪዎቜ ነበሩ። ዚሚኖሩትም በኢዚሩሳሌም ነበር።
ዚገባኊን አባት ዚኢዔል በገባኊን ይኖር ነበር። ዚሚስቱ ስም ማአካ ይባል ነበር።
ዚበኩር ልጁ አብዶን ሲሆን ሌሎቹ ልጆቹ ደግሞ ጹር፣ ቂስ፣ ባአል፣ ናዳብ፣
ጌዶር፣ አሂዮ እና ዛኹር ነበሩ።
ሚቅሎት ሺምአህን ወለደ። እነዚህ ሁሉ ኚሌሎቜ ወንድሞቻ቞ው ጋር ሆነው በወንድሞቻ቞ው አቅራቢያ በኢዚሩሳሌም ይኖሩ ነበር።
ኔር ቂስን ወለደፀ ቂስ ሳኊልን ወለደፀ ሳኊል ዮናታንን፣ ሜልኪሳን፣ አቢናዳብን እና ኀሜባዓልን ወለደ።
ዚዮናታን ልጅ መሪበኣል ነበር። መሪበኣል ሚክያስን ወለደ።
ዚሚክያስ ወንዶቜ ልጆቜ ፒቶን፣ ሜሌክ፣ ታሬአ እና አካዝ ነበሩ።
አካዝ ዚሆአዳን ወለደፀ ዚሆአዳ አለሜትን፣ አዝማዌትን እና ዚምሪን ወለደፀ ዚምሪ ሞጻን ወለደ።
ሞጻ ቢንአን ወለደፀ ቢንአ ራፋህን ወለደፀ ራፋህ ኀልዓሳን ወለደፀ ኀልዓሳ አዜልን ወለደ።
አዜል ስድስት ወንዶቜ ልጆቜ ዚነበሩት ሲሆን ስማ቞ውም አዝሪቃም፣ ቊኚሩ፣ እስማኀል፣ ሞአርያህ፣ አብድዩ እና ሃናን ነበር። እነዚህ ሁሉ ዹአዜል ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
ዚወንድሙ ዚኀሌቅ ወንዶቜ ልጆቜ ዚበኩር ልጁ ዑላም፣ ሁለተኛው ልጁ ዚኡሜ፣ ሊስተኛው ልጁ ኀሊፌሌት ነበሩ።
ዹዑላም ወንዶቜ ልጆቜ ቀስተኞቜና ኃያላን ተዋጊዎቜ ዚነበሩ ሲሆን 150 ልጆቜና ዹልጅ ልጆቜ ነበሯ቞ው። እነዚህ ሁሉ ዚቢንያም ዘሮቜ ነበሩ።
ልጁ ኢዮሳፍጥም በምትኩ ነገሠፀ በእስራኀልም ላይ ሥልጣኑን አጠናኚሚ።
በይሁዳ ባሉት ዹተመሾጉ ኚተሞቜ ሁሉ ዹጩር ሠራዊት አሰፈሚፀ በይሁዳ ምድርና አባቱ አሳ በያዛ቞ው በኀፍሬም ኚተሞቜም ዹጩር ሰፈሮቜ አቋቋመ።
ኢዮሳፍጥ፣ በቀድሞዎቹ ዘመናት አባቱ ዳዊት ዚሄደበትን መንገድ በመኹተሉና ባአልን ባለመፈለጉ ይሖዋ ኚእሱ ጋር ነበር።
ዚእስራኀልን ልማድ ኹመኹተል ይልቅ ዚአባቱን አምላክ ፈልጓልፀ ትእዛዙንም ተኚትሏል።
ይሖዋ መንግሥቱን በእጁ አጞናለትፀ ዚይሁዳም ሰዎቜ ሁሉ ለኢዮሳፍጥ ስጊታ ያመጡለት ነበርፀ እሱም ብዙ ሀብትና ታላቅ ክብር አገኘ።
ልቡም ዹይሖዋን መንገዶቜ በድፍሚት ተኚተለፀ ደግሞም ኹፍ ያሉትን ዚማምለኪያ ቊታዎቜና ዚማምለኪያ ግንዶቹን ኚይሁዳ አስወገደ።
በነገሠ በሊስተኛው ዓመት በይሁዳ ኚተሞቜ እንዲያስተምሩ መኳንንቱን ይኾውም ቀንሃይልን፣ አብድዩን፣ ዘካርያስን፣ ናትናኀልንና ሚካያህን አስጠራ቞ው።
ኚእነሱ ጋር ሌዋውያኑ ሞማያህ፣ ነታንያህ፣ ዘባድያህ፣ አሳሄል፣ ሞሚራሞት፣ ዚሆናታን፣ አዶንያስ፣ ጊቢያህ እና ቶብአዶኒያህ ይገኙ ነበርፀ ካህናቱ ኀሊሻማ እና ኢዮራምም አብሚዋ቞ው ነበሩ።
እነሱም በይሁዳ ማስተማር ጀመሩፀ ዹይሖዋን ሕግ መጜሐፍም ይዘው ነበርፀ በይሁዳ ኚተሞቜ ሁሉ እዚተዘዋወሩ ሕዝቡን ያስተምሩ ነበር።
ይሖዋም በይሁዳ ዙሪያ በሚገኙ አገሮቜ ባሉት መንግሥታት ሁሉ ላይ ፍርሃት ለቆባ቞ው ስለነበር ኚኢዮሳፍጥ ጋር አልተዋጉም።
ፍልስጀማውያንም ለኢዮሳፍጥ ስጊታ አመጡለትፀ ገንዘብም ገበሩለት። ዓሚቊቜ ኚመንጎቻ቞ው መካኚል 7,700 አውራ በጎቜንና 7,700 አውራ ፍዚሎቜን አመጡለት።
ኢዮሳፍጥ ኹጊዜ ወደ ጊዜ እያዚለ ሄደፀ በይሁዳም ምሜጎቜንና ዚማኚማቻ ኚተሞቜን መገንባቱን ተያያዘው።
በይሁዳ ኚተሞቜ መጠነ ሰፊ ዹሆነ ሥራ አኚናወነፀ በኢዚሩሳሌምም ኃያላን ተዋጊዎቜ ዹሆኑ ወታደሮቜ ነበሩት።
እነዚህ ሰዎቜ በዚአባቶቻ቞ው ቀት ተመድበው ነበር፩ ኚይሁዳ ዚሺህ አለቆቜ መካኚል አለቃው አድናህ ዹነበሹ ሲሆን ኚእሱ ጋር 300,000 ኃያላን ተዋጊዎቜ ነበሩ።
ኚእሱ ሥር ደግሞ ዹሆሃናን ዚተባለ አለቃ ዹነበሹ ሲሆን ኚእሱም ጋር 280,000 ሰዎቜ ነበሩ።
ደግሞም ኚእሱ ሥር ለይሖዋ አገልግሎት ራሱን በፈቃደኝነት ያቀሚበው ዚዚክሪ ልጅ አማስያህ ዹነበሹ ሲሆን ኚእሱም ጋር 200,000 ኃያላን ተዋጊዎቜ ነበሩ።
ኚቢንያምም ወገን ኃያል ተዋጊ ዹሆነው ኀሊያዳ ዹነበሹ ሲሆን ኚእሱም ጋር ቀስትና ጋሻ ዚታጠቁ 200,000 ሰዎቜ ነበሩ።
ኚእሱም ሥር ዚሆዛባድ ዹነበሹ ሲሆን ኚእሱም ጋር ለውጊያ ዚታጠቁ 180,000 ሰዎቜ ነበሩ።