text
stringlengths
4
267
የáŠĒáˆĢም አገልጋዮá‰Ŋ የሰለሞንን መርከá‰Ļá‰Ŋ áŠĨየነዱ ወደ ተርሴáˆĩ ይጓዙ ነበርáĸ áŠĨነዚህ የተርሴáˆĩ መርከá‰Ļá‰Ŋ በáˆĻáˆĩá‰ĩ ዓመá‰ĩ አንá‹ĩ ጊዜ á‹ˆáˆ­á‰…áŖ á‰Ĩáˆ­áŖ የዝሆን áŒĨርáˆĩáŖ áŒĻáŒŖáŠ“ áŒŖá‹Žáˆĩ ጭነው ይመጡ ነበርáĸ
በመሆኑም ንጉáˆĨ ሰለሞን በá‰ĨልáŒŊግናና በáŒĨበá‰Ĩ ምá‹ĩር ላይ áŠĢሉ ሌሎá‰Ŋ ነገáˆĨá‰ŗá‰ĩ ሁሉ ይበልáŒĨ ነበርáĸ
የምá‹ĩር ነገáˆĨá‰ŗá‰ĩም ሁሉ áŠĨውነተኛው አምላክ በሰለሞን ልá‰Ĩ ውáˆĩáŒĨ á‹Ģኖረውን áŒĨበá‰Ĩ ይሰሙ ዘንá‹ĩ ከáŠĨሹ ጋር ለመገናኘá‰ĩ ይጓጉ ነበርáĸ
ወደ áŠĨሹ የሚመጡá‰ĩም ሰዎá‰Ŋ በየዓመቱ የá‰Ĩር ዕቃዎá‰ŊáŖ የወርቅ ዕቃዎá‰ŊáŖ ልá‰Ĩáˆļá‰ŊáŖ የáŒĻር á‰ĩáŒĨቆá‰ŊáŖ á‹¨á‰ áˆˆáˆŗáŠ• ዘይá‰ĩáŖ ፈረáˆļá‰Ŋና በቅሎዎá‰Ŋ áˆĩáŒĻá‰ŗ አá‹ĩርገው á‹Ģመጡ ነበርáĸ
ሰለሞንም ለፈረáˆļቹ የሚሆኑ 4,000 áŒ‹áŒŖá‹Žá‰ŊáŖ ሠረገሎá‰Ŋና 12,000 ፈረáˆļá‰Ŋ ነበሩá‰ĩ፤ áŠĨነሱንም በሠረገላ ከተሞá‰Ŋና በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ በንጉሡ አቅáˆĢá‰ĸá‹Ģ አኖáˆĢቸውáĸ
áŠĨሱም ከወንዙ አንáˆĩá‰ļ áŠĨáˆĩከ ፍልáˆĩጤማውá‹Ģን ምá‹ĩርና áŠĨáˆĩከ ግá‰Ĩፅ ወሰን á‹ĩረáˆĩ á‰Ŗáˆ‰á‰ĩ ነገáˆĨá‰ŗá‰ĩ ሁሉ ላይ ገዛáĸ
ንጉሡ በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ á‹Ģለውን á‰Ĩር ከá‰Ĩዛቱ á‹¨á‰°áŠáˆŗ በየá‰Ļá‰ŗá‹ áŠĨንደሚገኝ á‹ĩንጋይ አደረገው፤ የአርዘ áˆŠá‰ŖáŠ–áˆąáŠ•áˆ á‰Ĩዛá‰ĩ በሸፌላ áŠĨንደሚገኘው የሾላ ዛፍ አደረገውáĸ
ደግሞም ለሰለሞን ከግá‰Ĩፅና ከሌሎá‰Ŋ አገሮá‰Ŋ ሁሉ ፈረáˆļá‰Ŋን á‹Ģመጡለá‰ĩ ነበርáĸ
ከመጀመáˆĒá‹Ģ አንáˆĩá‰ļ áŠĨáˆĩከ መጨረáˆģ á‹ĩረáˆĩ á‹Ģለው የቀረው የሰለሞን á‰ŗáˆĒክ ነá‰ĸዩ áŠ“á‰ŗáŠ• á‰Ŗá‹˜áŒ‹áŒ€á‹ áŒŊáˆ‘ááŖ የሴሎ ሰው የሆነው አáŠĒá‹Ģህ በተናገረው á‰ĩንá‰ĸá‰ĩና á‰Ŗáˆˆ áˆĢáŠĨዩ áŠĸá‹ļ áˆĩለ áŠ“á‰ŖáŒĨ ልጅ áˆĩለ áŠĸዮርá‰Ĩዓምá‹Ģየው áˆĢáŠĨይ በሰፈረበá‰ĩ á‹˜áŒˆá‰Ŗ ላይ ተáŒŊፎ የለም?
ሰለሞን በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ ሆኖ በመላው áŠĨáˆĩáˆĢኤል ላይ ለ40 ዓመá‰ĩ ገዛáĸ
በመጨረáˆģም ሰለሞን áŠ¨áŠ á‰Ŗá‰ļቹ ጋር አንቀላፋáĸ á‰ áŠ á‰Ŗá‰ąáˆ á‰ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ከተማ ቀበሩá‰ĩ፤ በáŠĨሱም ምá‰ĩክ ልጁ ሎá‰Ĩዓም ነገሠáĸ
áŠĸዮዓáˆĩ በነገሠ ጊዜ ዕá‹ĩሜው áˆ°á‰Ŗá‰ĩ ዓመá‰ĩ ነበር፤ በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ ሆኖ 40 ዓመá‰ĩ ገዛáĸ áŠĨናቱ áŒēá‰Ĩá‹Ģ á‹¨á‰°á‰Ŗáˆˆá‰Ŋ á‹¨á‰¤áˆ­áˆŗá‰¤áˆ… ተወላጅ ነበረá‰Ŋáĸ
áŠĸዮዓáˆĩ áŠĢህኑ á‹Žá‹ŗáˆ„ በነበረበá‰ĩ ዘመን ሁሉ በይሖዋ ፊá‰ĩ መልáŠĢም የሆነውን ነገር አደረገáĸ
á‹Žá‹ŗáˆ„ ሁለá‰ĩ ሚáˆĩá‰ļá‰Ŋ መረጠለá‰ĩ፤ áŠĨሱም ወንá‹ļá‰Ŋና ሴá‰ļá‰Ŋ ልጆá‰Ŋ ወለደáĸ
ከጊዜ በኋላ áŠĸዮዓáˆĩ የይሖዋን ቤá‰ĩ ለማደáˆĩ áˆá‰Ŗá‹Š ፍላጎá‰ĩ አደረበá‰ĩáĸ
በመሆኑም áŠĢህናቱንና ሌዋውá‹Ģኑን ሰá‰Ĩáˆĩá‰Ļ áŠĨንዲህ አላቸውáĻ “ወደ á‹­áˆá‹ŗ ከተሞá‰Ŋ áˆ„á‹ŗá‰Ŋሁ የአምላáŠĢá‰Ŋሁን ቤá‰ĩ በየዓመቱ ለማደáˆĩ ከáŠĨáˆĩáˆĢኤል ሁሉ ገንዘá‰Ĩ ሰá‰Ĩáˆĩቡ፤ áŠĨናንተም በአáˆĩá‰¸áŠŗá‹­ ይህንኑ አá‹ĩርጉáĸ” ሌዋውá‹Ģኑ ግን áŠ á‹áŒŖáŠ áŠĨርምጃ አልወሰዱምáĸ
áˆĩለዚህ ንጉሡ የáŠĢህናቱን አለቃ á‹Žá‹ŗáˆ„áŠ• ጠርá‰ļ áŠĨንዲህ አለውáĻ “የይሖዋ አገልጋይ የሆነው ሙሴ á‹Ģዘዘውንና ለምáˆĨክሩ á‹ĩáŠ•áŠŗáŠ• የሚውለውን የተቀደሰ ግá‰Ĩር ይኸውም የáŠĨáˆĩáˆĢኤልን áŒ‰á‰ŖáŠ¤ የተቀደሰ ግá‰Ĩር áŠ¨á‹­áˆá‹ŗáŠ“ ከáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ áŠĨንዲá‹Ģመጡ ሌዋውá‹Ģኑን á‹ĢላዘዝáŠĢቸው ለምንá‹ĩን ነው?
የዚá‹Ģá‰Ŋ ክፉ ሴá‰ĩ የጎá‰ļልá‹Ģ ወንá‹ļá‰Ŋ ልጆá‰Ŋ ወደ áŠĨውነተኛው አምላክ ቤá‰ĩ ሰá‰Ĩረው á‰ áˆ˜áŒá‰Ŗá‰ĩ በይሖዋ ቤá‰ĩ የነበሩá‰ĩን የተቀደሱ ዕቃዎá‰Ŋ በሙሉ áˆˆá‰ŖáŠ áˆ አገልግሎá‰ĩ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹‹áˆ‰ á‰ŗá‹á‰ƒáˆˆáˆ…áĸ”
ከዚá‹Ģም በንጉሡ á‰ĩáŠĨዛዝ መሠረá‰ĩ áˆŖáŒĨን ተሠርá‰ļ በይሖዋ ቤá‰ĩ በር አጠገá‰Ĩ በውጭ በኩል ተቀመጠáĸ
ከዚህ በኋላ የáŠĨውነተኛው አምላክ አገልጋይ ሙሴ በምá‹ĩረ á‰ á‹ŗ áˆŗáˆ‰ በáŠĨáˆĩáˆĢኤል ላይ á‹¨áŒŖáˆˆá‹ የተቀደሰ ግá‰Ĩር ለይሖዋ áŠĨንዲሰáŒĨ በመላው á‹­áˆá‹ŗáŠ“ áŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ አዋጅ ተነገረáĸ
áˆ˜áŠŗáŠ•áŠ•á‰ą ሁሉና ሕዝቡ ሁሉ ሐሴá‰ĩ አደረጉ፤ áˆŖáŒĨኑ áŠĨáˆĩáŠĒሞላም á‹ĩረáˆĩ መዋጮ áŠĨá‹Ģመጡ ይጨምሩ ነበርáĸ
ሌዋውá‹Ģኑ áˆŖáŒĨኑን ወደ ንጉሡ በሚá‹Ģመጡበá‰ĩና በውáˆĩጡ á‰Ĩዙ ገንዘá‰Ĩ መኖሩን በሚá‹Ģዩበá‰ĩ ጊዜ ሁሉ የንጉሡ ጸሐፊና የáŠĢህናቱ አለቃ ሹም መáŒĨተው áˆŖáŒĨኑን áŠĢጋቡ በኋላ ወደ á‰Ļá‰ŗá‹ ይመልሱá‰ĩ ነበርáĸ በየዕለቱ áŠĨንዲህ á‹Ģደርጉ ነበር፤ áŠĨጅግ á‰Ĩዙ ገንዘá‰Ĩም ሰበሰቡáĸ
ከዚá‹Ģም ንጉሡና á‹Žá‹ŗáˆ„ ገንዘቡን በይሖዋ ቤá‰ĩ አገልግሎá‰ĩ የሚከናወነውን áˆĨáˆĢ áˆˆáˆšá‰†áŒŖáŒ áˆŠá‰ĩ ሰዎá‰Ŋ ይሰጧቸው ነበር፤ áŠĨነሱ ደግሞ የይሖዋን ቤá‰ĩ ለማደáˆĩ á‹ĩንጋይ ጠáˆĢá‰ĸዎá‰Ŋንና የáŠĨጅ áŒĨበá‰Ĩ á‰Ŗáˆˆáˆ™á‹Ģዎá‰Ŋን áŠĨንዲሁም የይሖዋን ቤá‰ĩ ለመጠገን የá‰Ĩረá‰ĩና á‹¨áˆ˜á‹ŗá‰Ĩ ሠáˆĢተኞá‰Ŋን ይቀáŒĨሊ ነበርáĸ
áˆĨáˆĢውን á‹¨áˆšá‰†áŒŖáŒ áˆŠá‰ĩ ሰዎá‰Ŋም áˆĨáˆĢው áŠĨንዲጀመር አደረጉ፤ የáŒĨገናውም áˆĨáˆĢ በáŠĨነሱ አመáˆĢር áˆĨር ተፋጠነ፤ የáŠĨውነተኛውን አምላክ ቤá‰ĩ በማደáˆĩ ወደ ቀá‹ĩሞው áˆáŠ”á‰ŗ መለሹá‰ĩ፤ ቤቱንም አጠናከሩá‰ĩáĸ
áˆĨáˆĢውን áŠĨንደጨረሱም የተረፈውን ገንዘá‰Ĩ ወደ ንጉሡና ወደ á‹Žá‹ŗáˆ„ አመጡ፤ áŠĨነሱም ለይሖዋ ቤá‰ĩ የሚá‹Ģáˆĩፈልጉ ዕቃዎá‰ŊáŠ•áŖ ለአገልግሎá‰ĩና áˆ˜á‰Ŗ ለማቅረá‰Ĩ የሚá‹Ģáˆĩፈልጉ ዕቃዎá‰ŊáŠ•áŖ áŒŊዋዎá‰Ŋን áŠĨንዲሁም የወርቅና የá‰Ĩር ዕቃዎá‰Ŋን ለመáˆĨáˆĢá‰ĩ ተጠቀሙበá‰ĩáĸ á‹Žá‹ŗáˆ„ በነበረበá‰ĩ ዘመን ሁሉ በይሖዋ ቤá‰ĩ የሚቃጠሉ መáˆĨዋዕá‰ļá‰Ŋን ዘወá‰ĩር á‹Ģቀርቡ ነበርáĸ
á‹Žá‹ŗáˆ„ ሸምግሎና ዕá‹ĩሜ ጠግá‰Ļ ሞተ፤ በሞተ ጊዜ ዕá‹ĩሜው 130 ዓመá‰ĩ ነበርáĸ
ከáŠĨውነተኛው አምላክና ከአምላክ ቤá‰ĩ ጋር በተá‹Ģá‹Ģዘ በáŠĨáˆĩáˆĢኤል መልáŠĢም ነገር áˆĩላደረገ á‰ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ከተማ ከነገáˆĨá‰ŗá‰ĩ ጋር ቀበሩá‰ĩáĸ
áŠ¨á‹Žá‹ŗáˆ„ ሞá‰ĩ በኋላ á‹¨á‹­áˆá‹ŗ áˆ˜áŠŗáŠ•áŠ•á‰ĩ መáŒĨተው ንጉሡን áŠĨጅ ነሱ፤ ንጉሡም áŠĨነሱ á‹Ģሉá‰ĩን ሰማáĸ
áŠĨነሱም á‹¨áŠ á‰Ŗá‰ļá‰ģቸውን አምላክ የይሖዋን ቤá‰ĩ á‰ĩተው የማምለáŠĒá‹Ģ ግንá‹ļá‰Ŋንና áŒŖá‹–á‰ļá‰Ŋን ማገልገል ጀመሩ፤ ከፈጸሙá‰ĩ በደል á‹¨á‰°áŠáˆŗ á‰ á‹­áˆá‹ŗáŠ“ በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ ላይ የአምላክ á‰áŒŖ áˆ˜áŒŖáĸ
ይሖዋ ወደ áŠĨሹ áŠĨንዲመልሷቸው ነá‰ĸá‹Ģá‰ĩን ይልክላቸው ነበር፤ áŠĨነሱም á‹Ģáˆĩጠነቅቋቸው ነበር፤ ሕዝቡ ግን ለመáˆĩማá‰ĩ ፈቃደኛ አልነበረምáĸ
የአምላክ መንፈáˆĩ በáŠĢህኑ á‰ á‹Žá‹ŗáˆ„ ልጅ በዘáŠĢርá‹Ģáˆĩ ላይ ወረደ፤ áŠĨሱም በሕዝቡ ፊá‰ĩ ከፍ á‹Ģለ á‰Ļá‰ŗ ላይ ቆሞ áŠĨንዲህ አላቸውáĻ “áŠĨውነተኛው አምላክ áŠĨንዲህ ይላልáĻ ‘የይሖዋን á‰ĩáŠĨዛዛá‰ĩ የምá‰ĩተላለፉá‰ĩ ለምንá‹ĩን ነው? áŠ á‹­áˆŗáŠĢላá‰Ŋሁም! ይሖዋን áˆĩለተዋá‰Ŋሁ áŠĨሱም ይተዋá‰Ŋኋልáĸ’”
áŠĨነሱ ግን በáŠĨሹ ላይ አሴሩ፤ ንጉሡም በሰጠው á‰ĩáŠĨዛዝ መሠረá‰ĩ በይሖዋ ቤá‰ĩ ግá‰ĸ ውáˆĩáŒĨ በá‹ĩንጋይ ወገሩá‰ĩáĸ
ንጉáˆĨ áŠĸዮዓáˆĩáŖ áŠ á‰Ŗá‰ą á‹Žá‹ŗáˆ„ á‹Ģáˆŗá‹¨á‹áŠ• á‰ŗáˆ›áŠ ፍቅር አላሰበም፤ ልጁንም ገደለው፤ áŠĨሱም ሊሞá‰ĩ ሲል “ይሖዋ ይየው፤ የáŠĨጅህንም ይáˆĩáŒĨህ” አለáĸ
በዓመቱ መጀመáˆĒá‹Ģ ላይ የáˆļርá‹Ģ ሠáˆĢዊá‰ĩ በáŠĸዮዓáˆĩ ላይ ዘመተ፤ áŠĨነሱም á‹­áˆá‹ŗáŠ•áŠ“ áŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆáŠ• ወረሩáĸ ከዚá‹Ģም የሕዝቡን áˆ˜áŠŗáŠ•áŠ•á‰ĩ ሁሉ አጠፉ፤ የማረኩá‰ĩንም ሁሉ ወደ ደማáˆĩቆ ንጉáˆĨ ላኩáĸ
ወáˆĢáˆĒው የáˆļርá‹Ģ ሠáˆĢዊá‰ĩ አነáˆĩተኛ ቁáŒĨር የነበረው á‰ĸሆንም ይሖዋ áŠĨጅግ á‰Ĩዙ የሆነውን ሠáˆĢዊá‰ĩ በáŠĨጁ áŠ áˆŗáˆáŽ ሰጠው፤ ይህም የሆነው á‹¨áŠ á‰Ŗá‰ļá‰ģቸውን አምላክ ይሖዋን በመተዋቸው ነው፤ áŠĨነሱም በáŠĸዮዓáˆĩ ላይ የተላለፈውን ፍርá‹ĩ ፈጸሙáĸ
áŠĨነሱም áŒĨለውá‰ĩ በሄዱ ጊዜ (ክፉኛ አቁáˆĩለውá‰ĩ ነበርና) የገዛ አገልጋዮቹ የáŠĢህኑን á‹¨á‹Žá‹ŗáˆ„áŠ• ልጆá‰Ŋ ደም በማፍሰሱ አሴሩበá‰ĩáĸ አልጋው ላይ áŠĨáŠ•á‹ŗáˆˆ ገደሉá‰ĩáĸ ከሞተም በኋላ á‰ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ከተማ ቀበሩá‰ĩ፤ በነገáˆĨá‰ŗá‰ą የመቃá‰Ĩር áˆĩፍáˆĢ ግን አልቀበሩá‰ĩምáĸ
በáŠĨሹ ላይ á‹Ģሴሊá‰ĩ የአሞናዊቷ የáˆēምዓá‰ĩ ልጅ á‹›á‰Ŗá‹ĩና á‹¨áˆžá‹“á‰Ŗá‹Šá‰ˇ የáˆēምáˆĒá‰ĩ ልጅ á‹¨áˆ†á‹›á‰Ŗá‹ĩ ነበሩáĸ
áˆĩለ ወንá‹ļá‰Ŋ áˆáŒ†á‰šáŖ በáŠĨሹ ላይ áˆĩለተላለፉá‰ĩ በርáŠĢá‰ŗ የፍርá‹ĩ መልáŠĨክá‰ļá‰Ŋና የáŠĨውነተኛውን አምላክ ቤá‰ĩ áˆĩለማደሱ የሚገልጸው á‰ŗáˆĒክ ሁሉ በነገáˆĨá‰ŗá‰ą መáŒŊሐፍ á‹˜áŒˆá‰Ŗá‹Žá‰Ŋ ላይ ሰፍሯልáĸ በáŠĨሱም ምá‰ĩክ ልጁ አሜáˆĩá‹Ģáˆĩ ነገሠáĸ
áŠĸá‹Žá‹“á‰ŗáˆ በነገሠ ጊዜ ዕá‹ĩሜው 25 ዓመá‰ĩ ነበር፤ በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆáˆ ሆኖ ለ16 ዓመá‰ĩ ገዛáĸ áŠĨናቱም የሩáˆģህ á‰ĩá‰Ŗáˆ ነበር፤ áŠĨሷም á‹¨áˆŗá‹ļቅ ልጅ ነበረá‰Ŋáĸ
áŠĸá‹Žá‹“á‰ŗáˆ áŠ á‰Ŗá‰ą ዖዝá‹Ģ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹°áˆ¨áŒˆá‹ ሁሉ በይሖዋ ፊá‰ĩ á‰ĩክክል የሆነውን ነገር አደረገ፤ ይሁንና áˆĨርዓቱን áŒĨáˆļ ወደ ይሖዋ ቤተ መቅደáˆĩ áŠ áˆáŒˆá‰Ŗáˆáĸ ሕዝቡ ግን ክፉ á‹ĩርጊá‰ĩ መፈጸሙን አልተወም ነበርáĸ
áŠĨሱም የይሖዋን ቤá‰ĩ የላይኛውን በር ሠáˆĢ፤ በáŠĻፌልም ቅáŒĨር ላይ መጠነ ሰፊ á‹¨áŒáŠ•á‰Ŗá‰ŗ áˆĨáˆĢ አከናወነáĸ
በተጨማáˆĒም በተáˆĢáˆĢማው á‹¨á‹­áˆá‹ŗ ክልል ከተሞá‰Ŋን ሠáˆĢ፤ በደን በተሸፈኑá‰ĩ áˆĩፍáˆĢዎá‰Ŋም ምáˆŊጎá‰Ŋንና ማማዎá‰Ŋን áŒˆáŠá‰Ŗáĸ
ከአሞናውá‹Ģንም ንጉáˆĨ ጋር ተዋጋ፤ በመጨረáˆģም አሸነፋቸው፤ በመሆኑም አሞናውá‹Ģን በዚá‹Ģ ዓመá‰ĩ 100 የá‰Ĩር á‰ŗáˆ‹áŠ•á‰ĩáŖ 10,000 የቆሮáˆĩ መáˆĩፈáˆĒá‹Ģ áˆĩንዴና 10,000 የቆሮáˆĩ መáˆĩፈáˆĒá‹Ģ ገá‰Ĩáˆĩ ሰጡá‰ĩáĸ በተጨማáˆĒም አሞናውá‹Ģን በሁለተኛውና በáˆĻáˆĩተኛው ዓመá‰ĩ ይህንኑ ግá‰Ĩር አመጡለá‰ĩáĸ
áŠĸá‹Žá‹“á‰ŗáˆ በአምላኩ በይሖዋ ፊá‰ĩ መንገዱን áˆĩላጸና ከጊዜ ወደ ጊዜ áŠĨá‹¨á‰ áˆ¨á‰ŗ ሄደáĸ
የቀረው የáŠĸá‹Žá‹“á‰ŗáˆ á‰ŗáˆĒáŠ­áŖ á‹ĢáŠĢáˆ„á‹ŗá‰¸á‹ áŒĻርነá‰ļá‰Ŋና የተከተለው መንገá‹ĩ ሁሉ በáŠĨáˆĩáˆĢኤልና á‰ á‹­áˆá‹ŗ ነገáˆĨá‰ŗá‰ĩ መáŒŊሐፍ ውáˆĩáŒĨ ተáŒŊፈዋልáĸ
áŠĨሹ በነገሠ ጊዜ ዕá‹ĩሜው 25 ዓመá‰ĩ ነበር፤ በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆáˆ ሆኖ ለ16 ዓመá‰ĩ ገዛáĸ
በመጨረáˆģም áŠĸá‹Žá‹“á‰ŗáˆ áŠ¨áŠ á‰Ŗá‰ļቹ ጋር አንቀላፋ፤ á‰ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ከተማም ቀበሩá‰ĩáĸ በáŠĨሱም ምá‰ĩክ ልጁ አáŠĢዝ ነገሠáĸ
ሰለሞን ለይሖዋ áˆĩም ቤá‰ĩáŖ ለመንግáˆĨቱም ቤá‰ĩ áŠĨንዲሠáˆĢ አዘዘáĸ
ሰለሞን 70,000 ተáˆĢ የጉልበá‰ĩ ሠáˆĢተኞá‰Ŋና በተáˆĢሮቹ ላይ á‹ĩንጋይ የሚጠርቡ 80,000 ሰዎá‰Ŋ መረጠ፤ በáŠĨነሱም ላይ 3,600 ሰዎá‰Ŋን የበላይ ተመልáŠĢቾá‰Ŋ አá‹ĩርጎ ሞመáĸ
ደግሞም ሰለሞን áŠĨንዲህ የሚል መልáŠĨክá‰ĩ ወደ áŒĸሎáˆĩ ንጉáˆĨ ወደ áŠĒáˆĢም ላከáĻ â€œáŠ á‰Ŗá‰´ á‹ŗá‹Šá‰ĩ የሚኖርበá‰ĩን ቤá‰ĩ ሲሠáˆĢ የአርዘ áˆŠá‰ŖáŠ–áˆĩ áŠĨንጨá‰ĩ áŠĨንደላክለá‰ĩ ሁሉ ለáŠĨኔም áŠĨንዲሁ አá‹ĩርግልኝáĸ
áŠĨáŠáˆ†áŖ በፊቱ áŒĨሊ መዓዛ á‹Ģለው á‹•áŒŖáŠ• áˆˆáˆ›áŒ áŠ•áŖ á‹¨áˆšáŠá‰Ŗá‰ áˆ¨á‹áŠ• á‹ŗá‰Ļ ዘወá‰ĩር በዚá‹Ģ ለማáˆĩቀመáŒĨ áŠĨንዲሁም በየጠዋቱና á‰ á‹¨áˆ›á‰ŗá‹áŖ á‰ á‹¨áˆ°áŠ•á‰ á‰ąáŖ በየወር áˆ˜á‰Ŗá‰ģውና በአምላáŠĢá‰Ŋን በይሖዋ የበዓላá‰ĩ ወቅá‰ļá‰Ŋ የሚቃጠል áˆ˜á‰Ŗ ለማቅረá‰Ĩ ለአምላáŠŦ ለይሖዋ áˆĩም ቤá‰ĩ ልሠáˆĢና ለáŠĨሹ ልቀá‹ĩሰው አáˆĩቤአለሁáĸ ይህም áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģን ሁልጊዜ ሊፈáŒŊሙá‰ĩ á‹¨áˆšáŒˆá‰Ŗ áŒá‹´á‰ŗ ነውáĸ
አምላáŠĢá‰Ŋን ከሌሎá‰Ŋ አማልክá‰ĩ ሁሉ ይበልáŒĨ á‰ŗáˆ‹á‰… áˆĩለሆነ የምሠáˆĢውም ቤá‰ĩ á‰ŗáˆ‹á‰… ይሆናልáĸ
ለáŠĨሹ ቤá‰ĩ መáˆĨáˆĢá‰ĩ የሚá‰Ŋል ማነው? ሰማá‹Ģá‰ĩና የሰማá‹Ģá‰ĩ ሰማይ ሊይዙá‰ĩ አይá‰Ŋሉምና፤ በፊቱ የሚጨáˆĩ መáˆĨዋዕá‰ĩ የሚቀርá‰Ĩበá‰ĩ áˆĩፍáˆĢ áŠĢልሆነ በáˆĩተቀር ለáŠĨሹ ቤá‰ĩ áŠĨሠáˆĢለá‰ĩ ዘንá‹ĩ áŠĨኔ ማን ነኝ?
አሁንም á‰ á‹ˆáˆ­á‰…áŖ በá‰Ĩáˆ­áŖ á‰ áˆ˜á‹ŗá‰ĨáŖ በá‰Ĩረá‰ĩáŖ በሐምáˆĢዊ áˆąááŖ በደማቅ ቀይ ክርና በሰማá‹Ģዊ ክር áˆĨáˆĢ የተáŠĢነ áŠĨንዲሁም ቅርáŒģ ቅርáŒŊ የመáˆĨáˆĢá‰ĩ á‰ŊáˆŽá‰ŗ á‹Ģለው የáŠĨጅ áŒĨበá‰Ĩ á‰Ŗáˆˆáˆ™á‹Ģ ላክልኝáĸ áŠĨሱም áŠ á‰Ŗá‰´ á‹ŗá‹Šá‰ĩ áŠĢዘጋጃቸው የተáŠĢኑ የáŠĨጅ áŒĨበá‰Ĩ á‰Ŗáˆˆáˆ™á‹Ģዎá‰ŧ ጋር á‰ á‹­áˆá‹ŗáŠ“ በáŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ አá‰Ĩሎ ይሠáˆĢልáĸ
የአርዘ áˆŠá‰ŖáŠ–áˆĩáŖ የáŒĨá‹ĩና የሰንደል ዛፍ áˆŗáŠ•á‰ƒ áŠ¨áˆŠá‰ŖáŠ–áˆĩ ላክልኝ፤ አገልጋዮá‰Ŋህ á‹¨áˆŠá‰ŖáŠ–áˆĩን ዛፎá‰Ŋ በመቁረáŒĨ ረገá‹ĩ የተáŠĢኑ መሆናቸውን á‰ áˆšáŒˆá‰Ŗ አውቃለሁáĸ አገልጋዮá‰ŧ ከአገልጋዮá‰Ŋህ ጋር አá‰Ĩረው በመáˆĨáˆĢá‰ĩ
በርáŠĢá‰ŗ áˆŗáŠ•á‰ƒá‹Žá‰Ŋን á‹Ģዘጋጁልኛል፤ የምሠáˆĢው ቤá‰ĩ áŠĨጅግ á‰ŗáˆ‹á‰… ነውናáĸ
áŠĨáŠáˆ†áŖ ዛፍ ቆáˆĢጭና áŠĨንጨá‰ĩ ፈላጭ ለሆኑá‰ĩ አገልጋዮá‰Ŋህ ቀለá‰Ĩ áŠĨንዲሆናቸው 20,000 የቆሮáˆĩ መáˆĩፈáˆĒá‹Ģ áˆĩáŠ•á‹´áŖ 20,000 የቆሮáˆĩ መáˆĩፈáˆĒá‹Ģ ገá‰ĨáˆĩáŖ 20,000 á‹¨á‰Ŗá‹ļáˆĩ መáˆĩፈáˆĒá‹Ģ የወይን ጠጅና 20,000 á‹¨á‰Ŗá‹ļáˆĩ መáˆĩፈáˆĒá‹Ģ ዘይá‰ĩ áŠĨáˆ°áŒŖá‰¸á‹‹áˆˆáˆáĸ”
በዚህ ጊዜ የáŒĸሎáˆĩ ንጉáˆĨ áŠĒáˆĢም የሚከተለውን መልáŠĨክá‰ĩ በáŒŊሑፍ ለሰለሞን ላከለá‰ĩáĻ “ይሖዋ ሕዝቡን áˆĩለሚወá‹ĩ አንተን በáŠĨነሱ ላይ ንጉáˆĨ አá‹ĩርጎ ሾመህáĸ”
ከዚá‹Ģም áŠĒáˆĢም áŠĨንዲህ አለáĻ “ሰማá‹Ģá‰ĩንና ምá‹ĩርን የሠáˆĢው የáŠĨáˆĩáˆĢኤል አምላክ ይሖዋ á‹á‹ŗáˆ´ ይá‹ĩረሰው፤ ምክንá‹Ģቱም ለይሖዋ ቤá‰ĩáŖ ለመንግáˆĨቱም ቤá‰ĩ የሚሠáˆĢ áˆá‰ŖáˆáŠ“ አáˆĩተዋይ የሆነ áŒĨበበኛ ልጅ ለንጉáˆĨ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ሰáŒĨቷልáĸ
አሁንም አáˆĩተዋይ የሆነውን áŠĒáˆĢምአá‰ĸ á‹¨á‰°á‰Ŗáˆˆá‹áŠ• የáŠĨጅ áŒĨበá‰Ĩ á‰Ŗáˆˆáˆ™á‹Ģ ልáŠŦልሃለሁ፤
áŠĨናቱ áŠ¨á‹ŗáŠ• ወገን áˆĩá‰ĩሆን áŠ á‰Ŗá‰ą ግን የáŒĸሎáˆĩ ሰው ነው፤ áŠĨሱም á‰ á‹ˆáˆ­á‰…áŖ በá‰Ĩáˆ­áŖ á‰ áˆ˜á‹ŗá‰ĨáŖ በá‰Ĩረá‰ĩáŖ በá‹ĩáŠ•áŒ‹á‹­áŖ á‰ áˆŗáŠ•á‰ƒáŖ በሐምáˆĢዊ áˆąááŖ በሰማá‹Ģዊ áŠ­áˆ­áŖ áŒĨáˆĢá‰ĩ á‰Ŗáˆˆá‹ ጨርቅና በደማቅ ቀይ ክር áˆĨáˆĢ ልምá‹ĩ á‹ĢáŠĢበተ ነውáĸ ማንኛውንም ቅርáŒģ ቅርáŒŊ መቅረáŒŊ áŠĨንዲሁም የተሰጠውን ማንኛውንም ንá‹ĩፍ መáˆĨáˆĢá‰ĩ ይá‰Ŋላልáĸ አንተ ጋ áŠĢሉá‰ĩም ሆነ áŠ¨áŒŒá‰ŗá‹Ŧ ይኸውም áŠ¨áŠ á‰Ŗá‰ĩህ áŠ¨á‹ŗá‹Šá‰ĩ የተáŠĢኑ የáŠĨጅ áŒĨበá‰Ĩ á‰Ŗáˆˆáˆ™á‹Ģዎá‰Ŋ ጋር ሆኖ ይሠáˆĢልáĸ
አሁንም áŒŒá‰ŗá‹Ŧ ቃል á‰ áŒˆá‰Ŗá‹ መሠረá‰ĩ áˆĩáŠ•á‹´á‹áŠ•áŖ ገá‰ĨáˆąáŠ•áŖ ዘይቱንና የወይን ጠጁን ለአገልጋዮቹ ይላክáĸ
áŠĨኛም የምá‰ĩፈልገውን á‹Ģህል áŠ¨áˆŠá‰ŖáŠ–áˆĩ ዛፎá‰Ŋ ቆርጠን አንá‹ĩ ላይ በማሰር á‰ á‰Ŗáˆ•áˆ­ ላይ áŠĨá‹ĢáŠ•áˆŗáˆááŠ• ወደ áŠĸዮጴ áŠĨáŠ“áˆ˜áŒŖáˆáˆƒáˆˆáŠ•á¤ አንተም ወደ áŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ ልá‰ĩወáˆĩደው á‰ĩá‰Ŋላለህáĸ”
በዚህ ጊዜ ሰለሞን áŠ á‰Ŗá‰ą á‹ŗá‹Šá‰ĩ áŠĢደረገው ቆጠáˆĢ በኋላ በáŠĨáˆĩáˆĢኤል ምá‹ĩር የሚኖሩá‰ĩን á‹¨á‰Ŗá‹•á‹ĩ አገር ወንá‹ļá‰Ŋ ሁሉ ቆጠረ፤ ቁáŒĨáˆĢቸውም 153,600 ሆነáĸ
ከáŠĨነሱም መáŠĢከል 70,000ዎቹን ተáˆĢ የጉልበá‰ĩ ሠáˆĢተኞá‰ŊáŖ 80,000ዎቹን በተáˆĢሮቹ ላይ á‹ĩንጋይ ጠáˆĢá‰ĸዎá‰ŊáŖ 3,600ዎቹን ደግሞ ሰዎቹን የሚá‹Ģሠሊ የበላይ ተመልáŠĢቾá‰Ŋ አá‹ĩርጎ ሾማቸውáĸ
áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģን በሙሉ ሎá‰Ĩዓምን ለማንገáˆĨ ወደ ሴáŠŦም መáŒĨተው áˆĩለነበር áŠĨሱም ወደ ሴáŠŦም ሄደáĸ
á‹¨áŠ“á‰ŖáŒĨ ልጅ áŠĸዮርá‰Ĩዓም ይህን áŠĨንደሰማ (ምክንá‹Ģቱም በወቅቱ áŠĸዮርá‰Ĩዓም ከንጉáˆĨ ሰለሞን ሸáˆŊá‰ļ በግá‰Ĩፅ ይኖር ነበር)áŖ ከግá‰Ĩፅ ተመልáˆļ áˆ˜áŒŖáĸ
ከዚá‹Ģም ሰዎá‰Ŋ ልከው አáˆĩጠሩá‰ĩ፤ áŠĸዮርá‰Ĩዓምና መላው áŠĨáˆĩáˆĢኤልም መáŒĨተው ሎá‰Ĩዓምን áŠĨንዲህ አሉá‰ĩáĻ
â€œáŠ á‰Ŗá‰ĩህ ቀንበáˆĢá‰Ŋንን አክá‰Ĩá‹ļá‰Ĩን ነበርáĸ አንተ ግን áŠ á‰Ŗá‰ĩህ የሰጠንን አáˆĩቸጋáˆĒ áˆĨáˆĢና በላá‹Ģá‰Ŋን የáŒĢነá‰Ĩንን áŠ¨á‰Ŗá‹ĩ ቀንበር á‹¨áˆá‰ŗá‰€áˆáˆáŠ• ከሆነ áŠĨናገለግልሃለንáĸ”
በዚህ ጊዜ “ከáˆĻáˆĩá‰ĩ ቀን በኋላ á‰°áˆ˜áˆáˆŗá‰Ŋሁ ኑ” አላቸውáĸ በመሆኑም ሕዝቡ ሄደáĸ
ከዚá‹Ģም ንጉáˆĨ ሎá‰Ĩዓም áŠ á‰Ŗá‰ą ሰለሞን በሕይወá‰ĩ በነበረበá‰ĩ ጊዜ ሲá‹Ģገለግሉá‰ĩ የነበሩá‰ĩን áˆŊማግሌዎá‰Ŋ “ለዚህ ሕዝá‰Ĩ ምን ምላáˆŊ áŠĨንá‹ĩሰáŒĨ á‰ĩመክሩኛላá‰Ŋሁ?” በማለá‰ĩ ምክር ጠየቀáĸ
áŠĨነሱም “ለዚህ ሕዝá‰Ĩ áŒĨሊ á‰Ĩá‰ĩሆንና ደáˆĩ á‰Ĩá‰ŗáˆ°áŠ›á‰¸á‹ áŠĨንዲሁም መልáŠĢም ምላáˆŊ á‰Ĩá‰ĩáˆ°áŒŖá‰¸á‹ ምንጊዜም አገልጋዮá‰Ŋህ ይሆናሉ” በማለá‰ĩ መለሹለá‰ĩáĸ
ሆኖም ሎá‰Ĩዓም áˆŊማግሌዎቹ የሰጡá‰ĩን ምክር á‰ĩá‰ļ አá‰Ĩሎ አደጎቹ ከነበሩá‰ĩና አሁን የáŠĨሹ አገልጋዮá‰Ŋ ከሆኑá‰ĩ á‹ˆáŒŖá‰ļá‰Ŋ ጋር ተማከረáĸ
áŠĨሱም áŠĨንዲህ ሲል ጠየቃቸውáĻ â€œâ€˜áŠ á‰Ŗá‰ĩህ የáŒĢነá‰Ĩንን ቀንበር አቅልልልን’ ለሚለኝ ለዚህ ሕዝá‰Ĩ ምን ምላáˆŊ áŠĨንá‹ĩንሰáŒĨ á‰ĩመክሩኛላá‰Ŋሁ?”
አá‰Ĩሎ አደጎቹ የሆኑá‰ĩ á‹ˆáŒŖá‰ļá‰Ŋም áŠĨንዲህ አሉá‰ĩáĻ â€œâ€˜áŠ á‰Ŗá‰ĩህ ቀንበáˆĢá‰Ŋንን አክá‰Ĩá‹ļá‰Ĩን ነበር፤ አንተ ግን ቀንበáˆĢá‰Ŋንን አቅልልልን’ ለሚልህ ሕዝá‰Ĩ áŠĨንዲህ በለውáĻ ‘á‰ĩንáˆŋ áŒŖá‰´ áŠ¨áŠ á‰Ŗá‰´ ወገá‰Ĩ á‰ĩወፍáˆĢለá‰Ŋáĸ
áŠ á‰Ŗá‰´ áŠ¨á‰Ŗá‹ĩ ቀንበር áŒ­áŠ–á‰Ŗá‰Ŋሁ ነበር፤ áŠĨኔ ግን ቀንበáˆĢá‰Ŋሁን á‹¨á‰Ŗáˆ° አከá‰Ĩደዋለሁáĸ áŠ á‰Ŗá‰´ በአለንጋ ገርፏá‰Ŋሁ ነበር፤ áŠĨኔ ግን በáŠĨሾህ አለንጋ áŠĨገርፋá‰Ŋኋለሁáĸ’”
áŠĸዮርá‰Ĩዓምና መላው ሕዝá‰Ĩ ንጉሡ “በáˆĻáˆĩተኛው ቀን á‰°áˆ˜áˆáˆŗá‰Ŋሁ ኑ” á‰Ŗáˆ‹á‰¸á‹ መሠረá‰ĩ በáˆĻáˆĩተኛው ቀን ወደ ሎá‰Ĩዓም መጡáĸ
ይሁንና ንጉሡ መáŒĨፎ ምላáˆŊ áˆ°áŒŖá‰¸á‹áĸ በዚህ መንገá‹ĩ ንጉáˆĨ ሎá‰Ĩዓም áˆŊማግሌዎቹ የሰጡá‰ĩን ምክር áˆŗá‹­á‰€á‰ áˆ ቀረáĸ
á‹ˆáŒŖá‰ļቹ በሰጡá‰ĩ ምክር መሠረá‰ĩ “ቀንበáˆĢá‰Ŋሁን አከá‰Ĩደዋለሁ፤ ከቀá‹ĩሞውም የከፋ አደርገዋለሁáĸ áŠ á‰Ŗá‰´ በአለንጋ ገርፏá‰Ŋሁ ነበር፤ áŠĨኔ ግን በáŠĨሾህ አለንጋ áŠĨገርፋá‰Ŋኋለሁ” አላቸውáĸ
በመሆኑም ንጉሡ ሕዝቡን áˆŗá‹­áˆ°áˆ› ቀረ፤ ይህም የሆነው ይሖዋ በሴሎናዊው በአáŠĒá‹Ģህ አማáŠĢኝነá‰ĩ áˆˆáŠ“á‰ŖáŒĨ ልጅ ለáŠĸዮርá‰Ĩዓም የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንá‹ĩ áŠĨውነተኛው አምላክ áŠĨነዚህ ነገሮá‰Ŋ በዚህ መንገá‹ĩ áŠĨንዲከናወኑ áˆĩላደረገ ነውáĸ
áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģን ሁሉ ንጉሡ ሊሰማቸው ፈቃደኛ አለመሆኑን ሲá‹Ģዩ ንጉሡን áŠĨንዲህ አሉá‰ĩáĻ â€œáŠ¨á‹ŗá‹Šá‰ĩ ምን á‹ĩርáˆģ አለን? ከáŠĨሴይ ልጅ ምንም ርáˆĩá‰ĩ የለንምáĸ áŠĨáˆĩáˆĢኤል áˆ†á‹­áŖ áŠĨá‹ĢáŠ•á‹ŗáŠ•á‹ĩህ ወደ አማልክá‰ĩህ ተመለáˆĩ! á‹ŗá‹Šá‰ĩ áˆ†á‹­áŖ áŠĨንግዲህ የገዛ ቤá‰ĩህን ጠá‰Ĩቅ!” ከዚá‹Ģም áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģን ሁሉ á‹ˆá‹°á‹¨á‰¤á‰ŗá‰¸á‹ ተመለሱáĸ
ይሁንና ሎá‰Ĩዓም á‰ á‹­áˆá‹ŗ ከተሞá‰Ŋ በሚኖሩá‰ĩ áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģን ላይ መግዛቱን ቀጠለáĸ
ከዚá‹Ģም ንጉáˆĨ ሎá‰Ĩዓም á‹¨áŒá‹ŗáŒ… áˆĨáˆĢ áŠĨንዲሠሩ የተመለመሉá‰ĩ ሰዎá‰Ŋ አለቃ የነበረውን ሃá‹ļáˆĢምን ላከው፤ ሆኖም áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģን በá‹ĩንጋይ ወግረው ገደሉá‰ĩáĸ ንጉáˆĨ ሎá‰Ĩዓም ግን áŠĨንደ ምንም á‰Ĩሎ ሠረገላው ላይ á‰ áˆ˜á‹áŒŖá‰ĩ ወደ áŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ ሸሸáĸ
áŠĨáˆĩáˆĢኤላውá‹Ģንም áŠĨáˆĩከዚህ ቀን á‹ĩረáˆĩ á‰ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ቤá‰ĩ ላይ áŠĨáŠ•á‹ŗáˆ˜á ናቸውáĸ
áŠ áˆŗ በነገሠ በ36ኛው ዓመá‰ĩ የáŠĨáˆĩáˆĢኤል ንጉáˆĨ á‰ŖáŠĻáˆĩ á‰ á‹­áˆá‹ŗ ላይ ዘመተ፤ áŠĨሱም ማንም ወደ á‹­áˆá‹ŗ ንጉáˆĨ ወደ áŠ áˆŗ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹­áŒˆá‰ŖáŠ“ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹­á‹ˆáŒŖ ለማá‹ĩረግ áˆĢማን áˆ˜áŒˆáŠ•á‰Ŗá‰ĩ ጀመረáĸ
በዚህ ጊዜ áŠ áˆŗ ከይሖዋ ቤá‰ĩና ከንጉሡ ቤá‰ĩ ግምጃ ቤá‰ļá‰Ŋ á‰Ĩርና ወርቅ አውáŒĨá‰ļ በደማáˆĩቆ ወደሚገኘው የáˆļርá‹Ģ ንጉáˆĨ ወደ á‰¤áŠ•áˆƒá‹ŗá‹ĩ áŠĨንዲህ ሲል ላከáĻ
“በáŠĨኔና በአንተ áŠĨንዲሁም á‰ áŠ á‰Ŗá‰´áŠ“ á‰ áŠ á‰Ŗá‰ĩህ መáŠĢከል ውል አለáĸ áŠĨኔ á‰Ĩርና ወርቅ ልáŠŦልሃለሁáĸ áˆĩለዚህ áŠ“áŖ የáŠĨáˆĩáˆĢኤል ንጉáˆĨ á‰ŖáŠĻáˆĩ ከáŠĨኔ áŠĨንዲርቅ ከáŠĨሹ ጋር á‹¨áŒˆá‰ŖáŠ¸á‹áŠ• ውል አፍርáˆĩáĸ”
á‰¤áŠ•áˆƒá‹ŗá‹ĩ የንጉáˆĨ áŠ áˆŗáŠ• áˆáˆŗá‰Ĩ ተቀá‰Ĩሎ የáŒĻር ሠáˆĢዊቱን አለቆá‰Ŋ በáŠĨáˆĩáˆĢኤል ከተሞá‰Ŋ ላይ አዘመተ፤ áŠĨነሱም áŠĸá‹ŽáŠ•áŠ•áŖ á‹ŗáŠ•áŠ•áŖ አቤልማይምን áŠĨና á‰ áŠ•áá‰ŗáˆŒáˆ ከተሞá‰Ŋ ውáˆĩáŒĨ á‹Ģሉá‰ĩን የማከማá‰ģ áˆĩፍáˆĢዎá‰Ŋ ሁሉ መቱáĸ
á‰ŖáŠĻáˆĩም ይህን ሲሰማ ወዲá‹Ģውኑ áˆĢማን áˆ˜áŒˆáŠ•á‰Ŗá‰ąáŠ• አቆመ፤ áˆĨáˆĢውንም አቋረጠáĸ
ከዚá‹Ģም ንጉሡ áŠ áˆŗ á‹¨á‹­áˆá‹ŗáŠ• ሰዎá‰Ŋ ሁሉ ይዞ ሄደ፤ áŠĨነሱም á‰ŖáŠĻáˆĩ áŠĨá‹¨áŒˆáŠá‰Ŗá‰Ŗá‰¸á‹ የነበሩá‰ĩን የáˆĢማን á‹ĩንጋዮá‰Ŋና áˆŗáŠ•á‰ƒá‹Žá‰Ŋ አጋዙ፤ áŠĨሱም በá‹ĩንጋዮቹና á‰ áˆŗáŠ•á‰ƒá‹Žá‰š áŒŒá‰ŖáŠ•áŠ“ ምáŒŊáŒŗáŠ• áŒˆáŠá‰Ŗáĸ
በዚህ ጊዜ á‰Ŗáˆˆ áˆĢáŠĨዩ ሃናኒ ወደ á‹­áˆá‹ŗ ንጉáˆĨ ወደ áŠ áˆŗ መáŒĨá‰ļ áŠĨንዲህ አለውáĻ “በአምላክህ በይሖዋ áŠ¨áˆ˜á‰ŗáˆ˜áŠ• ይልቅ በáˆļርá‹Ģ ንጉáˆĨ áˆĩáˆˆá‰ŗáˆ˜áŠ•áŠ­ የáˆļርá‹Ģ ንጉáˆĨ ሠáˆĢዊá‰ĩ ከáŠĨጅህ አምልጧልáĸ
áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģንና ሊá‰ĸá‹Ģውá‹Ģን á‰Ĩዙ ሠረገሎá‰Ŋና ፈረሰኞá‰Ŋ á‹Ģሏቸው á‰ŗáˆ‹á‰… ሠáˆĢዊá‰ĩ አልነበሩም? ይሁንና በይሖዋ á‰ áˆ˜á‰ŗáˆ˜áŠ•áˆ… በáŠĨጅህ áŠ áˆŗáˆáŽ áˆ°áŒŖá‰¸á‹áĸ
áŠ á‹ŽáŖ በሙሉ áˆá‰Ŗá‰¸á‹ ወደ áŠĨሹ ላዘነበሉá‰ĩ ሰዎá‰Ŋ á‰Ĩáˆ­á‰ŗá‰ąáŠ• á‹Ģáˆŗá‹­ ዘንá‹ĩ የይሖዋ ዓይኖá‰Ŋ በምá‹ĩር ሁሉ ላይ á‹­áˆ˜áˆ‹áˆˆáˆŗáˆ‰áĸ በዚህ ረገá‹ĩ የሞኝነá‰ĩ á‹ĩርጊá‰ĩ ፈáŒŊመሃል፤ ከáŠĨንግዲህ ወዲá‹Ģ áŒĻርነá‰ĩ አይለይህምáĸ”
ሆኖም áŠ áˆŗ á‰ á‰Ŗáˆˆ áˆĢáŠĨዩ á‰°á‰†áŒŖá¤ በዚህ áŒ‰á‹ŗá‹­ á‰ áŒŖáˆ áˆĩለተናደደበá‰ĩም áŠĨáˆĩር ቤá‰ĩ አáˆĩáŒˆá‰Ŗá‹áĸ በዚá‹Ģ ወቅá‰ĩ áŠ áˆŗ በሌሎá‰Ŋ ሰዎá‰Ŋም ላይ በደል መፈጸም ጀመረáĸ
ከመጀመáˆĒá‹Ģ አንáˆĩá‰ļ áŠĨáˆĩከ መጨረáˆģ á‹ĩረáˆĩ á‹Ģለው á‹¨áŠ áˆŗ á‰ŗáˆĒክ á‰ á‹­áˆá‹ŗáŠ“ በáŠĨáˆĩáˆĢኤል ነገáˆĨá‰ŗá‰ĩ መáŒŊሐፍ ተáŒŊፏልáĸ
áŠ áˆŗ በ39ኛው የግዛá‰ĩ ዘመኑ áŠĨግሩን á‰ŗáˆ˜áˆ˜á¤ ሕመሙም ጠናበá‰ĩ፤ á‰ŗáˆž áˆŗáˆˆáˆ áŠĨáŠ•áŠŗ á‹¨á‰Ŗáˆˆ መá‹ĩኃኒá‰ļá‰Ŋን áŠĨንጂ የይሖዋን áŠĨáˆ­á‹ŗá‰ŗ አልፈለገምáĸ
በመጨረáˆģም áŠ áˆŗ áŠ¨áŠ á‰Ŗá‰ļቹ ጋር አንቀላፋ፤ በ41ኛው የግዛá‰ĩ ዘመኑም ሞተáĸ
áŠĨነሱም á‰ á‹ŗá‹Šá‰ĩ ከተማ ለáˆĢሹ á‰Ŗáˆĩቆፈረው á‰ŗáˆ‹á‰… የመቃá‰Ĩር á‰Ļá‰ŗ ቀበሩá‰ĩ፤ á‹¨á‰ áˆˆáˆŗáŠ• ዘይá‰ĩ áŠĨንዲሁም ከተለá‹Ģዩ ቅመሞá‰Ŋ የተዘጋጀ ልዩ á‰…á‰Ŗá‰ĩ በሞላበá‰ĩ ቃáˆŦዛ ላይ አኖሩá‰ĩáĸ በተጨማáˆĒም ለክá‰Ĩሊ á‰ŗáˆ‹á‰… áŠĨáˆŗá‰ĩ አነደዱለá‰ĩáĸ
በዚህ áˆáŠ”á‰ŗ ሰለሞን ከይሖዋ ቤá‰ĩ ጋር በተá‹Ģá‹Ģዘ መáˆĨáˆĢá‰ĩ á‹¨áˆšáŒˆá‰Ŗá‹áŠ• áˆĨáˆĢ በሙሉ ሠርá‰ļ አጠናቀቀáĸ ከዚá‹Ģም ሰለሞን áŠ á‰Ŗá‰ą á‹ŗá‹Šá‰ĩ á‹¨á‰€á‹°áˆŗá‰¸á‹áŠ• ነገሮá‰Ŋ ወደዚá‹Ģ አáˆĩáŒˆá‰Ŗá¤ á‰ĨáˆŠáŠ•áŖ ወርቁንና ዕቃዎቹን በሙሉ በáŠĨውነተኛው አምላክ ቤá‰ĩ ግምጃ ቤá‰ļá‰Ŋ ውáˆĩáŒĨ አáˆĩቀመጠáĸ
በዚህ ጊዜ ሰለሞን የáŠĨáˆĩáˆĢኤልን áˆŊማግሌዎá‰ŊáŖ የነገá‹ļቹን መáˆĒዎá‰Ŋ ሁሉና የáŠĨáˆĩáˆĢኤልን á‹¨áŠ á‰Ŗá‰ļá‰Ŋ ቤá‰ĩ አለቆá‰Ŋ ሰበሰበáĸ áŠĨነሱም የይሖዋን የቃል áŠĒá‹ŗáŠ• á‰ŗá‰Ļá‰ĩ áŠ¨á‹ŗá‹Šá‰ĩ ከተማ ማለá‰ĩም ከáŒŊዮን áˆˆáˆ›áˆáŒŖá‰ĩ ወደ áŠĸá‹¨áˆŠáˆŗáˆŒáˆ መጡáĸ