text
stringlengths 4
267
|
|---|
ልበ ንጹሕ መሆን የምንችለው እንዴት ነው?
|
ውስጣችንን ንጹሕ በማድረግና ማንኛውንም መጥፎ ምግባር በማስወገድ ነው።
|
መንፈሳዊነታችን ይበልጥ እየተጠናከረ ሲሄድና ትክክለኛ ምግባር ስናሳይ አምላክን ማየት ከሚችሉ ሰዎች መካከል እንሆናለን።
|
ጴጥሮስ በውኃው ላይ ሲራመድ በዙሪያው የነበረው ነፋስና ማዕበል ክርስቲያኖች ከሚያጋጥሟቸው ፈተናዎችና መከራዎች ጋር ሊመሳሰል ይችላል።
|
ፈተናውና መከራው እጅግ ከባድ ቢሆንም እንኳ በይሖዋ እርዳታ ጸንተን መቆም እንችላለን።
|
ጴጥሮስ መስመጥ የጀመረው ከኃይለኛ ነፋሱ ወይም ሞገዱ የተነሳ አለመሆኑን አስታውስ።
|
የተከሰተውን ሁኔታ በቅደም ተከተል ለማሰብ ሞክር፤ ጴጥሮስ አውሎ ነፋሱን ሲያይ ፈራ።
|
ጴጥሮስ ትኩረቱን በኢየሱስ ላይ ማድረግ ባቃተው ጊዜ እምነቱ ተናወጠ።
|
እኛም አውሎ ነፋሱን ማየት ከጀመርን በሌላ አባባል በማዕበሉ ኃይለኝነት ላይ ካተኮርንና ይሖዋ እንደሚደግፈን ከተጠራጠርን መስመጥ ልንጀምር እንችላለን።
|
መጽሐፍ ቅዱስ የእምነት መዳከምን ወይም እምነት ማጣትን በቀላሉ ተብትቦ የሚይዘን ኃጢአት ብሎ ይጠራዋል፤ ይህም እምነታችንን ሊያዳክም የሚችልን የትኛውንም ሁኔታ አቅልለን ማየት እንደሌለብን ያስገነዝበናል።
|
ጴጥሮስ ከደረሰበት ሁኔታ ማየት እንደሚቻለው ትኩረታችን በተሳሳተ ነገር ላይ ካረፈ እምነታችን በቀላሉ ሊዳከም ይችላል።
|
የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከመካከላቸው ማን ታላቅ እንደሆነ በተደጋጋሚ ይከራከሩ የነበረ ቢሆንም ኢየሱስ ተስፋ አልቆረጠባቸውም።
|
የሰጣቸውን ምክር እንዳልሠሩበት ሲያይም ሁኔታውን በቸልታ አላለፈውም።
|
ኢየሱስ አመቺ ጊዜና ቦታ መርጦ በፍቅርና በደግነት እርማት ሰጥቷቸዋል።
|
እናንተም ለልጆቻችሁ ተግሣጽ በመስጠት እንደምትወዷቸው አሳዩአቸው።
|
አንዳንድ ጊዜ፣ አንድ ድርጊት ትክክል ወይም ስህተት የሆነበትን ምክንያት ማስረዳቱ ብቻ በቂ ሊሆን ይችላል።
|
በእርግጥ ልጆቻችሁ የነገራችኋቸውን ተግባራዊ ሳያደርጉ የሚቀሩበት ጊዜ ይኖራል።
|
እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥማችሁ የኢየሱስን ምሳሌ ተከተሉ።
|
ተስማሚ ጊዜና ቦታ መርጣችሁ ልጆቻችሁን ገሥጿቸው፤ ይህን የምታደርጉት በፍቅር፣ በደግነት ብሎም በትዕግሥት መመሪያ፣ ሥልጠናና እርማት በመስጠት ነው።
|
በደቡብ አፍሪካ የምትኖር ኢሌን የተባለች እህት ወላጆቼ በቁጣ ወይም ምክንያቱን ሳያስረዱኝ ተግሣጽ ሰጥተውኝ አያውቁም ብላለች።
|
ይህም ሳልፈራ ተረጋግቼ እንድኖር አድርጎኛል።
|
ማለፍ የሌለብኝ ገደብ ምን እንደሆነ እንዲሁም ከእኔ ምን እንደሚጠበቅ አውቃለሁ።
|
የይሖዋ ምሥክሮችን የሚደግፉም ሆነ አምርረው የሚቃወሙ ሰዎች ሊክዱ የማይችሉት አንድ ሐቅ አለ፤ ይኸውም የይሖዋ ምሥክሮች በስብከቱ ሥራቸው በቡድን ደረጃ በስፋት የታወቁ መሆናቸው ነው።
|
በምናምንባቸው ነገሮች ባይስማሙም በምናከናውነው ሥራ እንደሚያከብሩን የሚናገሩ ሰዎች በአገልግሎት ላይ አጋጥመውህ ያውቁ ይሆናል።
|
ኢየሱስ የመንግሥቱ ምሥራች በመላው ምድር እንደሚሰበክ አስቀድሞ እንደተናገረ እናውቃለን።
|
ወንጌሉን ወይም ምሥራቹን እየሰበኩ እንዳሉ የሚሰማቸው በርካታ ሃይማኖታዊ ቡድኖች አሉ።
|
አብዛኛውን ጊዜ ግን የሚያከናውኑት የስብከት ሥራ ስለ ራሳቸው ተሞክሮ ምሥክርነት ከመስጠት፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከመስበክ አሊያም በመገናኛ ብዙኃን ይኸውም በቴሌቪዥን ወይም በኢንተርኔት አማካኝነት ፕሮግራም ከማቅረብ ያለፈ አይደለም።
|
ሌሎች ደግሞ የሚያከናውኗቸውን የበጎ አድራጎት ሥራዎች አሊያም በሕክምና እና በትምህርት መስኮች የሚያደርጉትን እርዳታ ይጠቅሳሉ።
|
ጽናት የሚፈጽመው ሥራ ምንድን ነው?
|
ጽናት በሁሉም ረገድ ምንም የማይጎድለን ፍጹማንና እንከን የለሽ እንድንሆን ይረዳናል።
|
አብዛኛውን ጊዜ ፈተናዎች፣ ምን ድክመት እንዳለብን እንዲሁም ልናሻሽላቸው የሚገቡን ባሕርያት የትኞቹ እንደሆኑ እንድንገነዘብ ያደርጋሉ።
|
የሚደርሱብንን ፈተናዎች በጽናት የምንወጣ ከሆነ ክርስቲያናዊ ባሕርያትን ይበልጥ በተሟላ መንገድ ማዳበር እንችላለን።
|
ለምሳሌ ያህል፣ ይበልጥ ታጋሾች፣ አድናቂዎችና ሩኅሩኆች እንድንሆን ሊረዱን ይችላሉ።
|
ጽናት ጥሩ ክርስቲያኖች እንድንሆን በመቅረጽ ረገድ አስፈላጊ የሆነ ሥራ ይፈጽማል፤ በመሆኑም የሚደርሱብንን ፈተናዎች ለማስቆም ስንል ቅዱስ ጽሑፋዊ መሠረታዊ ሥርዓቶችን ከመጣስ ልንቆጠብ ይገባል።
|
ለምሳሌ ያህል፣ ርኩስ የሆኑ ሐሳቦች ወደ አእምሮህ እየመጡ ቢያስቸግሩህ ምን ታደርጋለህ?
|
በፈተናው ከመሸነፍ ይልቅ እነዚህን ምኞቶች ለማስወገድ እንዲረዳህ ወደ ይሖዋ ጸልይ።
|
እንዲህ በማድረግ፣ ራስን የመግዛት ባሕርይ ታዳብራለህ።
|
ከማያምን የቤተሰብህ አባል ተቃውሞ እየደረሰብህ ነው?
|
በተጽዕኖው ከመሸነፍ ይልቅ በሙሉ ልብህ ይሖዋን ማምለክህን ለመቀጠል ቁርጥ ውሳኔ አድርግ።
|
የአምላክን ሞገስ ለማግኘት፣ መጽናት እንዳለብን አስታውስ።
|
ስለ ዘር፣ ባሕል ወይም አገር ተገቢ ያልሆነ ኩራት ማዳበር ይሖዋ ለሰብዓዊ አገዛዝና ለሰው ዘር ካለው አመለካከት ጋር እንደሚጋጭ እናውቃለን።
|
እርግጥ ነው፣ አምላክ ያደግንበትን ባሕል እንድንተው አይጠብቅብንም።
|
እንዲያውም የተለያዩ ባሕሎች መኖራቸው በሰብዓዊው ቤተሰብ መካከል ያለውን አስደናቂ ልዩነት ያጎላል።
|
ያም ቢሆን በአምላክ ዓይን ሁሉም ሰው እኩል መሆኑን ማስታወስ ይገባናል።
|
ከትውልድ ቦታችን ጋር በተያያዘ ተገቢ ያልሆነ ኩራት ማዳበር ብሔራዊ ስሜት እንዲያድርብን ያደርጋል፤ ይህ ደግሞ አቋማችንን ወደማላላት ሊመራን ይችላል።
|
ክርስቲያኖችም ቢሆን እንዲህ ዓይነት ኩራት ወጥመድ ሊሆንባቸው ይችላል፤ በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበረው ጉባኤ አንዳንድ አባላት እንኳ ከእነሱ የተለየ ዜግነት ባላቸው ወንድሞቻቸው ላይ አድልዎ ፈጽመዋል።
|
ተገቢ ያልሆነ ኩራት በልባችን ውስጥ እያቆጠቆጠ መሆኑን እንዴት ማወቅ እንችላለን?
|
ለምሳሌ የሌላ አገር ዜጋ የሆነ ክርስቲያን አንድ ሐሳብ አቀረበልን እንበል።
|
እኛ ነገሮችን የምናከናውንበት መንገድ የተሻለ ነው በማለት ሐሳቡን ወዲያውኑ ውድቅ እናደርገዋለን?
|
የተሻለው አካሄድ ሁላችንም በዛሬው የዕለት ጥቅስ ላይ ያለውን በመንፈስ መሪነት የተሰጠ ምክር ተግባራዊ ማድረጋችን ነው።
|
ለወጣቶች በሚዘጋጁ ጽሑፎች ላይ የሚጠቀሱት አብዛኞቹ ችግሮች ሌሎቻችንንም ያጋጥሙናል።
|
ሁላችንም ለእምነታችን ጥብቅና መቆም፣ ስሜታችንን መቆጣጠር፣ ጎጂ የሆነ የእኩዮች ተጽዕኖን መቋቋም እንዲሁም ከመጥፎ ጓደኛና መዝናኛ መራቅ ይኖርብናል።
|
እነዚህና ሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ለወጣቶች በተዘጋጁት ጽሑፎች ላይ ተብራርተዋል።
|
በዕድሜ ከፍ ያሉ ክርስቲያኖች፣ ለወጣቶች የተዘጋጁ ጽሑፎች ለእነሱ እንደማይመጥኑ ሊሰማቸው ይገባል?
|
በፍጹም! ትምህርቱ የተዘጋጀው ወጣቶችን በሚማርክ መልኩ ቢሆንም ምክሩ የተመሠረተው ጊዜ በማይሽራቸው የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ላይ ነው፤ ስለዚህ ሁላችንም ከዚህ መንፈሳዊ ዝግጅት ጥቅም ማግኘት እንችላለን።
|
ጽሑፎቻችን ወጣቶች የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች እንዲቋቋሙ የሚያግዟቸው ከመሆኑም ሌላ መንፈሳዊ እድገት እንዲያደርጉና ወደ ይሖዋ እንዲቀርቡ ይረዷቸዋል።
|
በዕድሜ ከፍ ያሉ ክርስቲያኖችም በዚህ ረገድ ጥቅም ማግኘት ይችላሉ።
|
አምላካችን ይሖዋ አንድ ይሖዋ ነው።
|
ይህ ትልቅ ትርጉም ያዘለ ጥቅስ ነው! ይህ ሐሳብ እስራኤላውያን ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲገቡና ምድሪቱን ሲቆጣጠሩ ያጋጠሟቸውን ተፈታታኝ ሁኔታዎች ለመቋቋም የሚያስችል ብርታት ሰጥቷቸዋል።
|
እኛም ይህን ጥቅስ ልብ ማለታችን፣ ከፊታችን የሚጠብቀንን ታላቅ መከራ ለማለፍ የሚያስችል ብርታት እንድናገኝና ገነት በምትሆነው ምድር ላይ ለሚኖረው ሰላምና አንድነት አስተዋጽኦ እንድናደርግ ይረዳናል።
|
ይሖዋን በሙሉ ነፍሳችን በመውደድና በማገልገል እንዲሁም በወንድማማች ማኅበራችን መካከል ያለው አንድነት ተጠብቆ እንዲኖር ልባዊ ጥረት በማድረግ፣ እሱን ብቻ ማምለካችንን እንቀጥል።
|
እንዲህ የምናደርግ ከሆነ ኢየሱስ በግ እንደሆኑ ለሚፈርድላቸው ሰዎች የተናገረው የሚከተለው ሐሳብ የሚፈጸምበትን ጊዜ በልበ ሙሉነት መጠባበቅ እንችላለን፦ እናንተ አባቴ የባረካችሁ ኑ፤ ዓለም ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
|
ኢየሱስን ያዳምጡ የነበሩ ሰዎች፣ ሊያስጨንቃቸው ስለማይገባ ነገር ይጨነቁ ነበር።
|
ስለዚህ ኢየሱስ መጨነቃቸውን እንዲተዉ እያሳሰባቸው ነው፤ ይህን ያለው ያለ ምክንያት አይደለም።
|
ሊያሳስቡን ስለሚገቡ ነገሮችም እንኳ ከልክ በላይ መጨነቅ፣ ትኩረታችን እንዲሰረቅና ይበልጥ አስፈላጊ የሆኑ መንፈሳዊ ነገሮችን ችላ እንድንል ሊያደርገን ይችላል።
|
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ከልብ ስለሚያስብ፣ በተራራ ስብከቱ ላይ ይህን አደገኛ ዝንባሌ በተመለከተ አራት ጊዜ ማሳሰቢያ ሰጥቷቸዋል።
|
ኢየሱስ ሰዎች በየዕለቱ ምን እንደሚያስፈልጋቸው በሚገባ ያውቃል።
|
ከዚህም በላይ ለመቋቋም የሚያስቸግር በዓይነቱ ልዩ የሆነ ዘመን በተባለው በዚህ የመጨረሻ ቀን ውስጥ የሚኖሩ ተከታዮቹ ምን ዓይነት አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንደሚያጋጥሟቸው ይረዳል።
|
ብዙዎች ከሚያጋጥሟቸው ነገሮች መካከል እንደ ሥራ ማጣት፣ የኑሮ ውድነት፣ የምግብ እጥረትና የከፋ ድህነት ያሉ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ይገኙበታል።
|
ያም ሆኖ ኢየሱስ ሕይወት ከምግብ፣ ሰውነት ከልብስ እንደሚበልጥ ተገንዝቦ ነበር።
|
መንፈሳዊ ገነት የሚለው ሐሳብ ከምንጠቀምባቸው ቲኦክራሲያዊ አገላለጾች አንዱ ሆኗል።
|
ይህ አገላለጽ ከአምላክና ከወንድሞቻችን ጋር ሰላማዊ ግንኙነት እንዲኖረን የሚያደርገውን ልዩ የሆነና በመንፈሳዊ የበለጸገ ሁኔታ ያመለክታል።
|
እርግጥ ነው፣ መንፈሳዊ ገነት እና መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ የሚሉት ሐሳቦች አንድ እንደሆኑ አድርገን ልንደመድም አይገባም።
|
መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ የሚባለው አምላክ ከእውነተኛው አምልኮ ጋር በተያያዘ ያደረገው ዝግጅት ነው።
|
በሌላ በኩል ደግሞ መንፈሳዊው ገነት አምላክ ሞገሱን የሚያሳያቸውን እንዲሁም በመንፈሳዊው ቤተ መቅደሱ እሱን የሚያገለግሉትን ሰዎች በግልጽ ለመለየት ይረዳል።
|
ጋብቻ በታሪክ ዘመናት ሁሉ የነበረ ነገር ነው።
|
ጋብቻ እንዴት እንደተጀመረና ዓላማው ምን እንደሆነ መመርመራችን፣ የጋብቻን ጥምረት በተመለከተ ትክክለኛ አመለካከት እንዲኖረንና የሚያስገኛቸውን በረከቶች ይበልጥ ማጣጣም እንድንችል ይረዳናል።
|
አምላክ የመጀመሪያውን ሰው አዳምን ከፈጠረ በኋላ ለእንስሳቱ ስም እንዲያወጣላቸው ወደ እሱ አመጣቸው።
|
ለሰው ግን ማሟያ የሚሆን ረዳት አልነበረውም።
|
በመሆኑም አምላክ፣ አዳም ከባድ እንቅልፍ እንዲወስደው ካደረገ በኋላ ከጎድን አጥንቶቹ አንዷን ወስዶ ሴት አድርጎ ሠራት፤ ከዚያም ወደ አዳም አመጣት።
|
ከዚህ ማየት እንደሚቻለው የጋብቻ መሥራች አምላክ ነው።
|
ይሖዋ ሰው ከአባቱና ከእናቱ ይለያል፤ ከሚስቱም ጋር ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ ብሎ ተናግሮ ነበር፤ ኢየሱስም ይህንኑ መሠረታዊ ሥርዓት በድጋሚ ተናግሯል።
|
አምላክ የመጀመሪያዋን ሴት ሔዋንን የፈጠራት ከአዳም የጎድን አጥንት መሆኑ፣ ባልና ሚስት ምን ያህል የጠበቀ ጥምረት እንዳላቸው ለመጀመሪያዎቹ ጥንዶች አስገንዝቧቸው መሆን አለበት።
|
አምላክ፣ ባልና ሚስት እንዲፋቱ ወይም በትዳር ጓደኛቸው ላይ ሌላ ደርበው እንዲያገቡ ዓላማው አልነበረም።
|
አንድ ባልና ሚስት በትዳራቸው ውስጥ እልባት ያላገኘ ከባድ ችግር በሚኖርበት ጊዜ ከሁለት አንዳቸው አሊያም ሁለቱም ለመለያየት ወይም ለመፋታት ሊያስቡ ይችላሉ።
|
ባለትዳሮች ከትዳር ጓደኛቸው ጋር መለያየትን እንደ ቀላል ነገር ሊያዩት አይገባም።
|
በትዳር ውስጥ ከባድ ችግሮች በሚኖሩበት ጊዜ መለያየት መፍትሔ ቢመስልም እንዲህ ማድረጉ በአብዛኛው ተጨማሪ ችግሮች ያስከትላል።
|
ይሖዋ፣ ሰው አባትና እናቱን ትቶ ከሚስቱ ጋር እንደሚጣበቅ ተናግሯል፤ ኢየሱስም ይህን ሐሳብ በድጋሚ ከተናገረ በኋላ አምላክ ያጣመረውን ማንም ሰው አይለያየው ብሏል።
|
ይህ ጥቅስ ባልና ሚስት ራሳቸውም ቢሆኑ አምላክ ያጣመረውን መለያየት እንደሌለባቸው ያጎላል።
|
በይሖዋ ፊት ጋብቻ የዕድሜ ልክ ጥምረት ነው።
|
ማናችንም ብንሆን በአምላክ ፊት ተጠያቂዎች ነን፤ ባለትዳሮች ይህን ማስታወሳቸው፣ ችግሮች ተባብሰው ከባድ ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ዛሬ ነገ ሳይሉ መፍትሔ ለማግኘት ከልባቸው ጥረት እንዲያደርጉ ይረዳቸዋል።
|
ዳንኤልና ጓደኞቹ በግዞት በተወሰዱበት ወቅት ባቢሎናውያን፣ እነዚህን ወጣቶች የከለዳውያንን ቋንቋ በማስተማር ከባሕሉ ጋር እንዲዋሃዱ ለማድረግ ሞክረው ነበር።
|
ከዚህም ሌላ እንዲያሠለጥናቸው የተመደበው የቤተ መንግሥት ባለሥልጣን የባቢሎናውያን ስም አወጣላቸው።
|
ለዳንኤል የተሰጠው ስም የባቢሎን ዋነኛ አምላክ ከሆነው ከቤል ጋር የተያያዘ ነበር።
|
ንጉሥ ናቡከደነጾር ይህን ያደረገው በዳንኤል አስተሳሰብ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ይኸውም አምላኩ ይሖዋ፣ ለባቢሎን አምላክ እንደተገዛ ሆኖ እንዲሰማው ለማድረግ ፈልጎ ሊሆን ይችላል።
|
ዳንኤል የንጉሡ ምርጥ ምግብ ቢቀርብለትም በዚህ ምግብ ላለመርከስ በልቡ ቁርጥ ውሳኔ አድርጓል።
|
ዳንኤል ቅዱሳን መጻሕፍትን በአፍ መፍቻ ቋንቋው ያጠና ስለነበር በሌላ አገር ቢኖርም መንፈሳዊነቱን ሊጠብቅ ችሏል።
|
ግርጌ በመሆኑም ወደ ባቢሎን ከተወሰደ ከ70 ዓመታት ገደማ በኋላም እንኳ የሚታወቀው በዕብራይስጥ ስሙ ነበር።
|
ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ምሥራቹን ለመስበክ የትኞቹን ዘዴዎች ተጠቅመዋል?
|
ምሥራቹን ለማድረስ፣ ሰዎች በብዛት ወደሚገኙባቸው ቦታዎችና ከቤት ወደ ቤት ሄደዋል።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.