text
stringlengths
4
267
ልበ ንጹሕ መሆን ዚምንቜለው እንዎት ነው?
ውስጣቜንን ንጹሕ በማድሚግና ማንኛውንም መጥፎ ምግባር በማስወገድ ነው።
መንፈሳዊነታቜን ይበልጥ እዚተጠናኚሚ ሲሄድና ትክክለኛ ምግባር ስናሳይ አምላክን ማዚት ኚሚቜሉ ሰዎቜ መካኚል እንሆናለን።
ጎጥሮስ በውኃው ላይ ሲራመድ በዙሪያው ዹነበሹው ነፋስና ማዕበል ክርስቲያኖቜ ኚሚያጋጥሟ቞ው ፈተናዎቜና መኚራዎቜ ጋር ሊመሳሰል ይቜላል።
ፈተናውና መኚራው እጅግ ኚባድ ቢሆንም እንኳ በይሖዋ እርዳታ ጾንተን መቆም እንቜላለን።
ጎጥሮስ መስመጥ ዹጀመሹው ኹኃይለኛ ነፋሱ ወይም ሞገዱ ዚተነሳ አለመሆኑን አስታውስ።
ዹተኹሰተውን ሁኔታ በቅደም ተኹተል ለማሰብ ሞክርፀ ጎጥሮስ አውሎ ነፋሱን ሲያይ ፈራ።
ጎጥሮስ ትኩሚቱን በኢዚሱስ ላይ ማድሚግ ባቃተው ጊዜ እምነቱ ተናወጠ።
እኛም አውሎ ነፋሱን ማዚት ኹጀመርን በሌላ አባባል በማዕበሉ ኃይለኝነት ላይ ካተኮርንና ይሖዋ እንደሚደግፈን ኚተጠራጠርን መስመጥ ልንጀምር እንቜላለን።
መጜሐፍ ቅዱስ ዚእምነት መዳኚምን ወይም እምነት ማጣትን በቀላሉ ተብትቊ ዹሚይዘን ኃጢአት ብሎ ይጠራዋልፀ ይህም እምነታቜንን ሊያዳክም ዚሚቜልን ዚትኛውንም ሁኔታ አቅልለን ማዚት እንደሌለብን ያስገነዝበናል።
ጎጥሮስ ኚደሚሰበት ሁኔታ ማዚት እንደሚቻለው ትኩሚታቜን በተሳሳተ ነገር ላይ ካሚፈ እምነታቜን በቀላሉ ሊዳኚም ይቜላል።
ዚኢዚሱስ ደቀ መዛሙርት ኚመካኚላ቞ው ማን ታላቅ እንደሆነ በተደጋጋሚ ይኚራኚሩ ዹነበሹ ቢሆንም ኢዚሱስ ተስፋ አልቆሚጠባ቞ውም።
ዚሰጣ቞ውን ምክር እንዳልሠሩበት ሲያይም ሁኔታውን በ቞ልታ አላለፈውም።
ኢዚሱስ አመቺ ጊዜና ቊታ መርጩ በፍቅርና በደግነት እርማት ሰጥቷ቞ዋል።
እናንተም ለልጆቻቜሁ ተግሣጜ በመስጠት እንደምትወዷ቞ው አሳዩአ቞ው።
አንዳንድ ጊዜ፣ አንድ ድርጊት ትክክል ወይም ስህተት ዚሆነበትን ምክንያት ማስሚዳቱ ብቻ በቂ ሊሆን ይቜላል።
በእርግጥ ልጆቻቜሁ ዚነገራቜኋ቞ውን ተግባራዊ ሳያደርጉ ዚሚቀሩበት ጊዜ ይኖራል።
እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥማቜሁ ዚኢዚሱስን ምሳሌ ተኚተሉ።
ተስማሚ ጊዜና ቊታ መርጣቜሁ ልጆቻቜሁን ገሥጿ቞ውፀ ይህን ዚምታደርጉት በፍቅር፣ በደግነት ብሎም በትዕግሥት መመሪያ፣ ሥልጠናና እርማት በመስጠት ነው።
በደቡብ አፍሪካ ዚምትኖር ኢሌን ዚተባለቜ እህት ወላጆቌ በቁጣ ወይም ምክንያቱን ሳያስሚዱኝ ተግሣጜ ሰጥተውኝ አያውቁም ብላለቜ።
ይህም ሳልፈራ ተሚጋግቌ እንድኖር አድርጎኛል።
ማለፍ ዚሌለብኝ ገደብ ምን እንደሆነ እንዲሁም ኚእኔ ምን እንደሚጠበቅ አውቃለሁ።
ዹይሖዋ ምሥክሮቜን ዹሚደግፉም ሆነ አምርሹው ዹሚቃወሙ ሰዎቜ ሊክዱ ዚማይቜሉት አንድ ሐቅ አለፀ ይኾውም ዹይሖዋ ምሥክሮቜ በስብኚቱ ሥራ቞ው በቡድን ደሹጃ በስፋት ዚታወቁ መሆናቾው ነው።
በምናምንባ቞ው ነገሮቜ ባይስማሙም በምናኹናውነው ሥራ እንደሚያኚብሩን ዚሚናገሩ ሰዎቜ በአገልግሎት ላይ አጋጥመውህ ያውቁ ይሆናል።
ኢዚሱስ ዚመንግሥቱ ምሥራቜ በመላው ምድር እንደሚሰበክ አስቀድሞ እንደተናገሚ እናውቃለን።
ወንጌሉን ወይም ምሥራቹን እዚሰበኩ እንዳሉ ዹሚሰማቾው በርካታ ሃይማኖታዊ ቡድኖቜ አሉ።
አብዛኛውን ጊዜ ግን ዚሚያኚናውኑት ዚስብኚት ሥራ ስለ ራሳ቞ው ተሞክሮ ምሥክርነት ኚመስጠት፣ በቀተ ክርስቲያን ውስጥ ኚመስበክ አሊያም በመገናኛ ብዙኃን ይኾውም በ቎ሌቪዥን ወይም በኢንተርኔት አማካኝነት ፕሮግራም ኚማቅሚብ ያለፈ አይደለም።
ሌሎቜ ደግሞ ዚሚያኚናውኗ቞ውን ዹበጎ አድራጎት ሥራዎቜ አሊያም በሕክምና እና በትምህርት መስኮቜ ዚሚያደርጉትን እርዳታ ይጠቅሳሉ።
ጜናት ዚሚፈጜመው ሥራ ምንድን ነው?
ጜናት በሁሉም ሚገድ ምንም ዚማይጎድለን ፍጹማንና እንኚን ዚለሜ እንድንሆን ይሚዳናል።
አብዛኛውን ጊዜ ፈተናዎቜ፣ ምን ድክመት እንዳለብን እንዲሁም ልናሻሜላ቞ው ዚሚገቡን ባሕርያት ዚትኞቹ እንደሆኑ እንድንገነዘብ ያደርጋሉ።
ዚሚደርሱብንን ፈተናዎቜ በጜናት ዚምንወጣ ኹሆነ ክርስቲያናዊ ባሕርያትን ይበልጥ በተሟላ መንገድ ማዳበር እንቜላለን።
ለምሳሌ ያህል፣ ይበልጥ ታጋሟቜ፣ አድናቂዎቜና ሩኅሩኆቜ እንድንሆን ሊሚዱን ይቜላሉ።
ጜናት ጥሩ ክርስቲያኖቜ እንድንሆን በመቅሚጜ ሚገድ አስፈላጊ ዹሆነ ሥራ ይፈጜማልፀ በመሆኑም ዚሚደርሱብንን ፈተናዎቜ ለማስቆም ስንል ቅዱስ ጜሑፋዊ መሠሚታዊ ሥርዓቶቜን ኚመጣስ ልንቆጠብ ይገባል።
ለምሳሌ ያህል፣ ርኩስ ዹሆኑ ሐሳቊቜ ወደ አእምሮህ እዚመጡ ቢያስ቞ግሩህ ምን ታደርጋለህ?
በፈተናው ኹመሾነፍ ይልቅ እነዚህን ምኞቶቜ ለማስወገድ እንዲሚዳህ ወደ ይሖዋ ጞልይ።
እንዲህ በማድሚግ፣ ራስን ዚመግዛት ባሕርይ ታዳብራለህ።
ኚማያምን ዚቀተሰብህ አባል ተቃውሞ እዚደሚሰብህ ነው?
በተጜዕኖው ኹመሾነፍ ይልቅ በሙሉ ልብህ ይሖዋን ማምለክህን ለመቀጠል ቁርጥ ውሳኔ አድርግ።
ዹአምላክን ሞገስ ለማግኘት፣ መጜናት እንዳለብን አስታውስ።
ስለ ዘር፣ ባሕል ወይም አገር ተገቢ ያልሆነ ኩራት ማዳበር ይሖዋ ለሰብዓዊ አገዛዝና ለሰው ዘር ካለው አመለካኚት ጋር እንደሚጋጭ እናውቃለን።
እርግጥ ነው፣ አምላክ ያደግንበትን ባሕል እንድንተው አይጠብቅብንም።
እንዲያውም ዚተለያዩ ባሕሎቜ መኖራ቞ው በሰብዓዊው ቀተሰብ መካኚል ያለውን አስደናቂ ልዩነት ያጎላል።
ያም ቢሆን በአምላክ ዓይን ሁሉም ሰው እኩል መሆኑን ማስታወስ ይገባናል።
ኚትውልድ ቊታቜን ጋር በተያያዘ ተገቢ ያልሆነ ኩራት ማዳበር ብሔራዊ ስሜት እንዲያድርብን ያደርጋልፀ ይህ ደግሞ አቋማቜንን ወደማላላት ሊመራን ይቜላል።
ክርስቲያኖቜም ቢሆን እንዲህ ዓይነት ኩራት ወጥመድ ሊሆንባ቞ው ይቜላልፀ በመጀመሪያው መቶ ዘመን ዹነበሹው ጉባኀ አንዳንድ አባላት እንኳ ኚእነሱ ዹተለዹ ዜግነት ባላ቞ው ወንድሞቻ቞ው ላይ አድልዎ ፈጜመዋል።
ተገቢ ያልሆነ ኩራት በልባቜን ውስጥ እያቆጠቆጠ መሆኑን እንዎት ማወቅ እንቜላለን?
ለምሳሌ ዹሌላ አገር ዜጋ ዹሆነ ክርስቲያን አንድ ሐሳብ አቀሹበልን እንበል።
እኛ ነገሮቜን ዚምናኚናውንበት መንገድ ዚተሻለ ነው በማለት ሐሳቡን ወዲያውኑ ውድቅ እናደርገዋለን?
ዚተሻለው አካሄድ ሁላቜንም በዛሬው ዚዕለት ጥቅስ ላይ ያለውን በመንፈስ መሪነት ዹተሰጠ ምክር ተግባራዊ ማድሚጋቜን ነው።
ለወጣቶቜ በሚዘጋጁ ጜሑፎቜ ላይ ዚሚጠቀሱት አብዛኞቹ ቜግሮቜ ሌሎቻቜንንም ያጋጥሙናል።
ሁላቜንም ለእምነታቜን ጥብቅና መቆም፣ ስሜታቜንን መቆጣጠር፣ ጎጂ ዹሆነ ዚእኩዮቜ ተጜዕኖን መቋቋም እንዲሁም ኚመጥፎ ጓደኛና መዝናኛ መራቅ ይኖርብናል።
እነዚህና ሌሎቜ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮቜ ለወጣቶቜ በተዘጋጁት ጜሑፎቜ ላይ ተብራርተዋል።
በዕድሜ ኹፍ ያሉ ክርስቲያኖቜ፣ ለወጣቶቜ ዹተዘጋጁ ጜሑፎቜ ለእነሱ እንደማይመጥኑ ሊሰማቾው ይገባል?
በፍጹም! ትምህርቱ ዹተዘጋጀው ወጣቶቜን በሚማርክ መልኩ ቢሆንም ምክሩ ዹተመሠሹተው ጊዜ በማይሜራ቞ው ዚመጜሐፍ ቅዱስ መሠሚታዊ ሥርዓቶቜ ላይ ነውፀ ስለዚህ ሁላቜንም ኹዚህ መንፈሳዊ ዝግጅት ጥቅም ማግኘት እንቜላለን።
ጜሑፎቻቜን ወጣቶቜ ዚሚያጋጥሟ቞ውን ቜግሮቜ እንዲቋቋሙ ዚሚያግዟ቞ው ኹመሆኑም ሌላ መንፈሳዊ እድገት እንዲያደርጉና ወደ ይሖዋ እንዲቀርቡ ይሚዷ቞ዋል።
በዕድሜ ኹፍ ያሉ ክርስቲያኖቜም በዚህ ሚገድ ጥቅም ማግኘት ይቜላሉ።
አምላካቜን ይሖዋ አንድ ይሖዋ ነው።
ይህ ትልቅ ትርጉም ያዘለ ጥቅስ ነው! ይህ ሐሳብ እስራኀላውያን ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲገቡና ምድሪቱን ሲቆጣጠሩ ያጋጠሟ቞ውን ተፈታታኝ ሁኔታዎቜ ለመቋቋም ዚሚያስቜል ብርታት ሰጥቷ቞ዋል።
እኛም ይህን ጥቅስ ልብ ማለታቜን፣ ኚፊታቜን ዚሚጠብቀንን ታላቅ መኚራ ለማለፍ ዚሚያስቜል ብርታት እንድናገኝና ገነት በምትሆነው ምድር ላይ ለሚኖሹው ሰላምና አንድነት አስተዋጜኊ እንድናደርግ ይሚዳናል።
ይሖዋን በሙሉ ነፍሳቜን በመውደድና በማገልገል እንዲሁም በወንድማማቜ ማኅበራቜን መካኚል ያለው አንድነት ተጠብቆ እንዲኖር ልባዊ ጥሚት በማድሚግ፣ እሱን ብቻ ማምለካቜንን እንቀጥል።
እንዲህ ዹምናደርግ ኹሆነ ኢዚሱስ በግ እንደሆኑ ለሚፈርድላ቞ው ሰዎቜ ዹተናገሹው ዹሚኹተለው ሐሳብ ዚሚፈጞምበትን ጊዜ በልበ ሙሉነት መጠባበቅ እንቜላለንፊ እናንተ አባ቎ ዚባሚካቜሁ ኑፀ ዓለም ኚተመሠሚተበት ጊዜ ጀምሮ ዚተዘጋጀላቜሁን መንግሥት ውሚሱ።
ኢዚሱስን ያዳምጡ ዚነበሩ ሰዎቜ፣ ሊያስጚንቃ቞ው ስለማይገባ ነገር ይጹነቁ ነበር።
ስለዚህ ኢዚሱስ መጹነቃቾውን እንዲተዉ እያሳሰባ቞ው ነውፀ ይህን ያለው ያለ ምክንያት አይደለም።
ሊያሳስቡን ስለሚገቡ ነገሮቜም እንኳ ኹልክ በላይ መጚነቅ፣ ትኩሚታቜን እንዲሰሚቅና ይበልጥ አስፈላጊ ዹሆኑ መንፈሳዊ ነገሮቜን ቜላ እንድንል ሊያደርገን ይቜላል።
ኢዚሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ኚልብ ስለሚያስብ፣ በተራራ ስብኚቱ ላይ ይህን አደገኛ ዝንባሌ በተመለኹተ አራት ጊዜ ማሳሰቢያ ሰጥቷ቞ዋል።
ኢዚሱስ ሰዎቜ በዚዕለቱ ምን እንደሚያስፈልጋ቞ው በሚገባ ያውቃል።
ኹዚህም በላይ ለመቋቋም ዚሚያስ቞ግር በዓይነቱ ልዩ ዹሆነ ዘመን በተባለው በዚህ ዚመጚሚሻ ቀን ውስጥ ዚሚኖሩ ተኚታዮቹ ምን ዓይነት አስ቞ጋሪ ሁኔታዎቜ እንደሚያጋጥሟ቞ው ይሚዳል።
ብዙዎቜ ኚሚያጋጥሟ቞ው ነገሮቜ መካኚል እንደ ሥራ ማጣት፣ ዚኑሮ ውድነት፣ ዚምግብ እጥሚትና ዹኹፋ ድህነት ያሉ አስ቞ጋሪ ሁኔታዎቜ ይገኙበታል።
ያም ሆኖ ኢዚሱስ ሕይወት ኚምግብ፣ ሰውነት ኚልብስ እንደሚበልጥ ተገንዝቩ ነበር።
መንፈሳዊ ገነት ዹሚለው ሐሳብ ኚምንጠቀምባ቞ው ቲኊክራሲያዊ አገላለጟቜ አንዱ ሆኗል።
ይህ አገላለጜ ኹአምላክና ኚወንድሞቻቜን ጋር ሰላማዊ ግንኙነት እንዲኖሚን ዚሚያደርገውን ልዩ ዹሆነና በመንፈሳዊ ዹበለጾገ ሁኔታ ያመለክታል።
እርግጥ ነው፣ መንፈሳዊ ገነት እና መንፈሳዊ ቀተ መቅደስ ዚሚሉት ሐሳቊቜ አንድ እንደሆኑ አድርገን ልንደመድም አይገባም።
መንፈሳዊ ቀተ መቅደስ ዚሚባለው አምላክ ኚእውነተኛው አምልኮ ጋር በተያያዘ ያደሚገው ዝግጅት ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ መንፈሳዊው ገነት አምላክ ሞገሱን ዚሚያሳያ቞ውን እንዲሁም በመንፈሳዊው ቀተ መቅደሱ እሱን ዚሚያገለግሉትን ሰዎቜ በግልጜ ለመለዚት ይሚዳል።
ጋብቻ በታሪክ ዘመናት ሁሉ ዹነበሹ ነገር ነው።
ጋብቻ እንዎት እንደተጀመሚና ዓላማው ምን እንደሆነ መመርመራቜን፣ ዚጋብቻን ጥምሚት በተመለኹተ ትክክለኛ አመለካኚት እንዲኖሚንና ዚሚያስገኛ቞ውን በሚኚቶቜ ይበልጥ ማጣጣም እንድንቜል ይሚዳናል።
አምላክ ዚመጀመሪያውን ሰው አዳምን ኹፈጠሹ በኋላ ለእንስሳቱ ስም እንዲያወጣላ቞ው ወደ እሱ አመጣ቞ው።
ለሰው ግን ማሟያ ዹሚሆን ሚዳት አልነበሚውም።
በመሆኑም አምላክ፣ አዳም ኚባድ እንቅልፍ እንዲወስደው ካደሚገ በኋላ ኚጎድን አጥንቶቹ አንዷን ወስዶ ሎት አድርጎ ሠራትፀ ኚዚያም ወደ አዳም አመጣት።
ኹዚህ ማዚት እንደሚቻለው ዚጋብቻ መሥራቜ አምላክ ነው።
ይሖዋ ሰው ኚአባቱና ኚእናቱ ይለያልፀ ኚሚስቱም ጋር ይጣበቃልፀ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ ብሎ ተናግሮ ነበርፀ ኢዚሱስም ይህንኑ መሠሚታዊ ሥርዓት በድጋሚ ተናግሯል።
አምላክ ዚመጀመሪያዋን ሎት ሔዋንን ዚፈጠራት ኚአዳም ዚጎድን አጥንት መሆኑ፣ ባልና ሚስት ምን ያህል ዹጠበቀ ጥምሚት እንዳላ቞ው ለመጀመሪያዎቹ ጥንዶቜ አስገንዝቧ቞ው መሆን አለበት።
አምላክ፣ ባልና ሚስት እንዲፋቱ ወይም በትዳር ጓደኛቾው ላይ ሌላ ደርበው እንዲያገቡ ዓላማው አልነበሚም።
አንድ ባልና ሚስት በትዳራ቞ው ውስጥ እልባት ያላገኘ ኚባድ ቜግር በሚኖርበት ጊዜ ኚሁለት አንዳ቞ው አሊያም ሁለቱም ለመለያዚት ወይም ለመፋታት ሊያስቡ ይቜላሉ።
ባለትዳሮቜ ኚትዳር ጓደኛቾው ጋር መለያዚትን እንደ ቀላል ነገር ሊያዩት አይገባም።
በትዳር ውስጥ ኚባድ ቜግሮቜ በሚኖሩበት ጊዜ መለያዚት መፍትሔ ቢመስልም እንዲህ ማድሚጉ በአብዛኛው ተጚማሪ ቜግሮቜ ያስኚትላል።
ይሖዋ፣ ሰው አባትና እናቱን ትቶ ኚሚስቱ ጋር እንደሚጣበቅ ተናግሯልፀ ኢዚሱስም ይህን ሐሳብ በድጋሚ ኹተናገሹ በኋላ አምላክ ያጣመሚውን ማንም ሰው አይለያዚው ብሏል።
ይህ ጥቅስ ባልና ሚስት ራሳ቞ውም ቢሆኑ አምላክ ያጣመሚውን መለያዚት እንደሌለባ቞ው ያጎላል።
በይሖዋ ፊት ጋብቻ ዚዕድሜ ልክ ጥምሚት ነው።
ማናቜንም ብንሆን በአምላክ ፊት ተጠያቂዎቜ ነንፀ ባለትዳሮቜ ይህን ማስታወሳ቞ው፣ ቜግሮቜ ተባብሰው ኚባድ ደሹጃ ኚመድሚሳ቞ው በፊት ዛሬ ነገ ሳይሉ መፍትሔ ለማግኘት ኚልባ቞ው ጥሚት እንዲያደርጉ ይሚዳ቞ዋል።
ዳንኀልና ጓደኞቹ በግዞት በተወሰዱበት ወቅት ባቢሎናውያን፣ እነዚህን ወጣቶቜ ዚኚለዳውያንን ቋንቋ በማስተማር ኚባሕሉ ጋር እንዲዋሃዱ ለማድሚግ ሞክሹው ነበር።
ኹዚህም ሌላ እንዲያሠለጥና቞ው ዹተመደበው ዚቀተ መንግሥት ባለሥልጣን ዚባቢሎናውያን ስም አወጣላ቞ው።
ለዳንኀል ዹተሰጠው ስም ዚባቢሎን ዋነኛ አምላክ ኹሆነው ኚቀል ጋር ዚተያያዘ ነበር።
ንጉሥ ናቡኚደነጟር ይህን ያደሚገው በዳንኀል አስተሳሰብ ላይ ተጜዕኖ ለማሳደር ይኾውም አምላኩ ይሖዋ፣ ለባቢሎን አምላክ እንደተገዛ ሆኖ እንዲሰማው ለማድሚግ ፈልጎ ሊሆን ይቜላል።
ዳንኀል ዚንጉሡ ምርጥ ምግብ ቢቀርብለትም በዚህ ምግብ ላለመርኚስ በልቡ ቁርጥ ውሳኔ አድርጓል።
ዳንኀል ቅዱሳን መጻሕፍትን በአፍ መፍቻ ቋንቋው ያጠና ስለነበር በሌላ አገር ቢኖርም መንፈሳዊነቱን ሊጠብቅ ቜሏል።
ግርጌ በመሆኑም ወደ ባቢሎን ኹተወሰደ ኹ70 ዓመታት ገደማ በኋላም እንኳ ዚሚታወቀው በዕብራይስጥ ስሙ ነበር።
ኢዚሱስና ደቀ መዛሙርቱ ምሥራቹን ለመስበክ ዚትኞቹን ዘዎዎቜ ተጠቅመዋል?
ምሥራቹን ለማድሚስ፣ ሰዎቜ በብዛት ወደሚገኙባ቞ው ቊታዎቜና ኚቀት ወደ ቀት ሄደዋል።