text stringlengths 4 267 |
|---|
ይልቁንም በዚያ ከነበሩት ብሔራት ጋር ተቀላቀሉ፤የእነሱንም መንገድ ተከተሉ። |
ጣዖቶቻቸውን አመለኩ፤እነሱም ወጥመድ ሆኑባቸው። |
ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውንለአጋንንት መሥዋዕት አድርገው ያቀርቡ ነበር። |
ንጹሕ ደም፣ይኸውም ለከነአን ጣዖቶች የሠዉአቸውንየገዛ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን ደም አፈሰሱ፤ምድሪቱም በደም ተበከለች። |
በሥራቸው ረከሱ፤በድርጊታቸውም መንፈሳዊ ምንዝር ፈጸሙ። |
በመሆኑም የይሖዋ ቁጣ በሕዝቡ ላይ ነደደ፤ርስቱንም ተጸየፈ። |
በተደጋጋሚ ጊዜያት በብሔራት እጅ አሳልፎ ሰጣቸው፤ይህም የሚጠሏቸው ሰዎች እንዲገዟቸው ነው። |
ጠላቶቻቸው ጨቆኗቸው፤ለእነሱም ሥልጣን ተገዢ ሆኑ። |
ብዙ ጊዜ ታደጋቸው፤እነሱ ግን ያምፁና ለመታዘዝ አሻፈረኝ ይሉ ነበር፤ከሠሩት ጥፋት የተነሳም ተዋረዱ። |
እሱ ግን ጭንቀታቸውን ይመለከት፣እርዳታ ለማግኘት የሚያሰሙትንም ጩኸት ይሰማ ነበር። |
ለእነሱ ሲል ቃል ኪዳኑን ያስታውስ ነበር፤ታላቅ በሆነው ታማኝ ፍቅሩ ተገፋፍቶ ያዝንላቸው ነበር። |
የማረኳቸው ሰዎች ሁሉበሐዘኔታ እንዲይዟቸው ያደርግ ነበር። |
ይሖዋ አምላካችን ሆይ፣ አድነን፤ደግሞም ለቅዱስ ስምህ ምስጋና እንድናቀርብ፣አንተንም በማወደስ ሐሴት እንድናደርግ፣ከብሔራት ሰብስበን። |
የእስራኤል አምላክ ይሖዋከዘላለም እስከ ዘላለም ይወደስ፤ ሕዝቦችም ሁሉ “አሜን!” ይበሉ። ያህን አወድሱ! |
ከታማኝ ፍቅርህና ከታማኝነትህ የተነሳለእኛ ሳይሆን፣ ይሖዋ ሆይ፣ ለእኛ ሳይሆን፣ለስምህ ክብር ስጥ። |
ብሔራት “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ? |
አምላካችን ያለው በሰማያት ነው፤እሱ የወደደውን ሁሉ ያደርጋል። |
የእነሱ ጣዖቶች ከብርና ከወርቅ የተሠሩ፣የሰው እጅ ሥራ ናቸው። |
አፍ አላቸው፤ መናገር ግን አይችሉም፤ዓይን አላቸው፤ ማየት ግን አይችሉም፤ |
ጆሮ አላቸው፤ መስማት ግን አይችሉም፤አፍንጫ አላቸው፤ ማሽተት ግን አይችሉም፤ |
እጅ አላቸው፤ መዳሰስ ግን አይችሉም፤እግር አላቸው፤ መራመድ ግን አይችሉም፤በጉሮሯቸው የሚያሰሙት ድምፅ የለም። |
የሚሠሯቸውም ሆኑ የሚታመኑባቸው ሁሉ፣እንደ እነሱ ይሆናሉ። |
እስራኤል ሆይ፣ በይሖዋ ታመኑ፤እሱ ረዳታቸውና ጋሻቸው ነው። |
የአሮን ቤት ሆይ፣ በይሖዋ ታመኑ፤እሱ ረዳታቸውና ጋሻቸው ነው። |
እናንተ ይሖዋን የምትፈሩ፣ በይሖዋ ታመኑ፤እሱ ረዳታቸውና ጋሻቸው ነው። |
ይሖዋ ያስታውሰናል፤ ደግሞም ይባርከናል፤የእስራኤልን ቤት ይባርካል፤የአሮንን ቤት ይባርካል። |
ይሖዋ እሱን የሚፈሩትን፣ታናናሾችንም ሆነ ታላላቆችን ይባርካል። |
ይሖዋ እናንተን፣አዎ፣ እናንተንና ልጆቻችሁን ያበዛል። |
ሰማይንና ምድርን የሠራውይሖዋ ይባርካችሁ። |
ሰማያት የይሖዋ ናቸው፤ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት። |
ሙታንም ሆኑ ወደ ዝምታው ዓለም የሚወርዱ ሁሉ፣ያህን አያወድሱም። |
እኛ ግን ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣ያህን እናወድሳለን። ያህን አወድሱ! |
ብርታታችን ለሆነው አምላክ እልል በሉ። ለያዕቆብ አምላክ በድል አድራጊነት ስሜት ጩኹ። |
ሙዚቃውን መጫወት ጀምሩ፤ አታሞም ምቱ፤ደስ የሚያሰኘውን በገና ከባለ አውታር መሣሪያ ጋር ተጫወቱ። |
አዲስ ጨረቃ በምትታይበት፣ሙሉ ጨረቃም ወጥታ በዓል በምናከብርበት ዕለት ቀንደ መለከት ንፉ። |
ይህ ለእስራኤል የተሰጠ ድንጋጌ፣የያዕቆብም አምላክ ያስተላለፈው ውሳኔ ነውና። |
በግብፅ ምድር ላይ ባለፈ ጊዜ፣ይህን ለዮሴፍ ማሳሰቢያ አድርጎ ሰጠው። እኔም የማላውቀውን ድምፅ ሰማሁ፦ |
“ሸክሙን ከትከሻው ላይ አነሳሁለት፤እጆቹ ቅርጫት ከመያዝ አረፉ። |
በጨነቀህ ጊዜ ጠራኸኝ፤ እኔም ታደግኩህ፤ከነጎድጓዳማው ደመና መለስኩልህ። የመሪባ ውኃዎች ባሉበት ስፍራ ፈተንኩህ። (ሴላ) |
ሕዝቤ ሆይ፣ ስማኝ፤ እኔም እመሠክርብሃለሁ። እስራኤል ሆይ፣ ምነው ብታዳምጠኝ! |
በመካከልህ እንግዳ አምላክ አይኖርም፤ለባዕድ አምላክም አትሰግድም። |
ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ፣እኔ ይሖዋ አምላክህ ነኝ። አፍህን በሰፊው ክፈት፤ እኔም በምግብ እሞላዋለሁ። |
ሕዝቤ ግን ድምፄን አልሰማም፤እስራኤል ለእኔ አይገዛም። |
በመሆኑም እልኸኛ ልባቸውን እንዲከተሉ ተውኳቸው፤ትክክል መስሎ የታያቸውን አደረጉ። |
ምነው ሕዝቤ ቢያዳምጠኝ ኖሮ!ምነው እስራኤል በመንገዴ ቢመላለስ ኖሮ! |
ጠላቶቻቸውን ወዲያውኑ ባንበረከክኋቸው፣እጄን በባላጋራዎቻቸው ላይ በሰነዘርኩ ነበር። |
ይሖዋን የሚጠሉ በፊቱ ይሸማቀቃሉ፤የሚደርስባቸውም ነገር ዘላለማዊ ነው። |
እሱ ግን ምርጡን ስንዴ ይመግባችኋል፤ከዓለት በሚገኝ ማርም ያጠግባችኋል።” |
አምላክ ሆይ፣ አንተን መጠጊያ አድርጌአለሁና ጠብቀኝ። |
ይሖዋን እንዲህ አልኩት፦ “አንተ ይሖዋ ነህ፤ ለእኔ የጥሩ ነገሮች ምንጭ አንተ ነህ። |
ደግሞም በምድር ላይ ያሉት ቅዱሳን፣ክብር የተላበሱት አገልጋዮች እጅግ ደስ ያሰኙኛል።” |
ሌሎች አማልክትን የሚከተሉ ሐዘናቸውን ያበዛሉ። እንደ እነሱ ደምን የመጠጥ መባ አድርጌ አላቀርብም፤በከንፈሬም ስማቸውን አላነሳም። |
ይሖዋ ድርሻዬ፣ ዕጣ ፋንታዬና ጽዋዬ ነው። ርስቴን ትጠብቅልኛለህ። |
ለእኔ ርስት አድርገህ ለመስጠት የለካኸው ቦታ ያማረ ነው። አዎ፣ ባገኘሁት ርስት ረክቻለሁ። |
ምክር የሰጠኝን ይሖዋን አወድሳለሁ። በሌሊትም እንኳ በውስጤ ያለው ሐሳብ ያርመኛል። |
ይሖዋን ሁልጊዜ በፊቴ አደርገዋለሁ። እሱ በቀኜ ስላለ ፈጽሞ አልናወጥም። |
ስለዚህ ልቤ ሐሴት ያደርጋል፤ ሁለንተናዬ ደስ ይለዋል። ያለ ስጋትም እኖራለሁ። |
መቃብር ውስጥ አትተወኝምና። ታማኝ አገልጋይህ ጉድጓድ እንዲያይ አትፈቅድም። |
የሕይወትን መንገድ አሳወቅከኝ። በፊትህ ብዙ ደስታ አለ፤በቀኝህ ለዘላለም ደስታ አለ። |
ይሖዋ ጥሩ ስለሆነ ምስጋና አቅርቡለት፤ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል። |
ይሖዋ የዋጃቸው፣አዎ፣ ከጠላት እጅ የዋጃቸው ይህን ይበሉ፤ |
ከምሥራቅና ከምዕራብ፣ከሰሜንና ከደቡብ፣ከየአገሩ አንድ ላይ የሰበሰባቸው ይህን ይናገሩ። |
በምድረ በዳ፣ በበረሃም ተቅበዘበዙ፤ሊኖሩ ወደሚችሉበት ከተማ የሚወስድ መንገድ አላገኙም። |
ተርበውና ተጠምተው ነበር፤ኃይላቸው ከመሟጠጡ የተነሳ ተዝለፈለፉ። |
በተጨነቁ ጊዜ ወደ ይሖዋ ይጮኹ ነበር፤እሱም ከደረሰባቸው መከራ ታደጋቸው። |
መኖር ወደሚችሉበት ከተማ እንዲደርሱበትክክለኛው መንገድ መራቸው። |
ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩናለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት። |
እሱ የተጠማውን አርክቷልና፤የተራበውንም በመልካም ነገሮች አጥግቧል። |
አንዳንዶች በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የሚኖሩ፣በመከራ ውስጥ ያሉና በሰንሰለት የተጠፈሩ እስረኞች ነበሩ። |
በአምላክ ቃል ላይ ዓምፀዋልና፤የልዑሉን አምላክ ምክር ንቀዋል። |
ስለዚህ በደረሰባቸው መከራ ልባቸው እንዲለሰልስ አደረገ፤ተሰናከሉ፤ የሚረዳቸውም አንዳች ሰው አልነበረም። |
በተጨነቁ ጊዜ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ተጣሩ፤እሱም ከደረሰባቸው መከራ አዳናቸው። |
ከድቅድቅ ጨለማ አወጣቸው፤የታሰሩበትንም ሰንሰለት በጠሰ። |
ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩናለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት። |
እሱ የመዳብ በሮችን ሰብሯልና፤የብረት መወርወሪያዎችንም ቆርጧል። |
ከጥፋታቸውና ከበደላቸው የተነሳሞኝ ሆኑ፤ ለመከራም ተዳረጉ። |
የምግብ ፍላጎታቸው ሙሉ በሙሉ ጠፋ፤ወደ ሞት ደጆች ቀረቡ። |
በተጨነቁ ጊዜ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ይጣሩ ነበር፤እሱም ከደረሰባቸው መከራ ያድናቸው ነበር። |
ቃሉን ልኮ ይፈውሳቸው፣ከተያዙበትም ጉድጓድ ይታደጋቸው ነበር። |
ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩናለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት። |
የምስጋና መሥዋዕት ያቅርቡ፤በእልልታም ሥራዎቹን ያስታውቁ። |
በባሕር ላይ በመርከቦች የሚጓዙ፣በሰፋፊ ውኃዎች ላይ ንግድ የሚያካሂዱ፣ |
እነሱ የይሖዋን ሥራዎች፣በጥልቁም ውስጥ ያከናወናቸውን አስደናቂ ነገሮች ተመልክተዋል፤ |
እሱ በቃሉ አውሎ ነፋስ ሲያስነሳ፣የባሕሩንም ማዕበል ሲያናውጥ አይተዋል። |
ወደ ሰማይ ይወጣሉ፣ወደ ጥልቆችም ይወርዳሉ። እየመጣባቸው ካለው መከራ የተነሳ ሐሞታቸው ፈሰሰ። |
እንደሰከረ ሰው ይንገዳገዳሉ፤ ደግሞም ይወላገዳሉ፤ችሎታቸውም ሁሉ የፈየደላቸው ነገር የለም። |
በዚህ ጊዜ ከጭንቀታቸው የተነሳ ወደ ይሖዋ ይጮኻሉ፤እሱም ከደረሰባቸው መከራ ይታደጋቸዋል። |
አውሎ ነፋሱ እንዲቆም ያደርጋል፤የባሕሩም ሞገዶች ጸጥ ይላሉ። |
ሞገዶቹ ጸጥ ሲሉ ሰዎቹ ሐሴት ያደርጋሉ፤እሱም ወዳሰቡት ወደብ ይመራቸዋል። |
ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩናለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት። |
በሕዝብ ጉባኤ መካከል ከፍ ከፍ ያድርጉት፤በሽማግሌዎችም ሸንጎ ያወድሱት። |
እሱ ወንዞችን ወደ በረሃ፣የውኃ ምንጮችንም ወደ ደረቅ መሬት ይለውጣል፤ |
ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሳፍሬያማዋን አገር ጨዋማ የሆነ ጠፍ ምድር ያደርጋታል። |
በረሃውን ቄጠማ የሞላበት ኩሬ፣ደረቁንም ምድር የውኃ ምንጭ ያደርጋል። |
ሊኖሩ የሚችሉበትን ከተማ እንዲመሠርቱ፣የተራቡ ሰዎችን በዚያ ያኖራል። |
መሬት ላይ ዘሩ፤ ወይንም ተከሉ፤መሬቱም ብዙ ምርት ሰጠ። |
እሱ ይባርካቸዋል፤ እነሱም እጅግ ይበዛሉ፤የከብቶቻቸው ብዛት እንዲያንስ አያደርግም። |
ሆኖም ከደረሰባቸው ጭቆና፣ መከራና ሐዘን የተነሳዳግመኛ ቁጥራቸው ተመናመነ፤ ተዋረዱም። |
በታላላቅ ሰዎች ላይ የውርደት መዓት ያዘንባል፤መንገድ በሌለበት ጠፍ መሬትም እንዲቅበዘበዙ ያደርጋል። |
ድሆችን ግን ከጭቆና ይጠብቃል፤ቤተሰባቸውንም እንደ መንጋ ያበዛል። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.