text
stringlengths
4
267
ቅኖቜ ይህን አይተው ሐሎት ያደርጋሉፀዓመፀኞቜ ሁሉ ግን አፋቾውን ይዘጋሉ።
ጥበበኛ ዹሆነ ሁሉ እነዚህን ነገሮቜ ልብ ይላልፀደግሞም ይሖዋ በታማኝ ፍቅር ያኚናወና቞ውን ነገሮቜ በትኩሚት ይመለኚታል።
ይሖዋ ዚጜዮንን ምርኮኞቜ መልሶ በሰበሰበ ጊዜ፣ሕልም ዹምናይ መስሎን ነበር።
በዚያን ጊዜ አፋቜን በሳቅ፣አንደበታቜንም በእልልታ ተሞላ። ያን ጊዜ ብሔራት እንዲህ አሉ፩ “ይሖዋ ታላላቅ ነገሮቜ አደሚገላ቞ው።”
ይሖዋ ታላላቅ ነገሮቜ አደሚገልንፀእኛም እጅግ ተደሰትን።
ይሖዋ ሆይ፣ በኔጌብ እንዳሉ ጅሚቶቜ፣ዚተማሚኩብንን ሰዎቜ መልሰህ ሰብስብ።
በእንባ ዚሚዘሩ፣በእልልታ ያጭዳሉ።
ዘር ቋጥሮ ዚወጣው ሰው፣ዚሄደው እያለቀሰ ቢሆንም እንኳነዶውን ተሞክሞእልል እያለ ይመለሳል።
አምላክ በመለኮታዊ ጉባኀ መካኚል ይሰዚማልፀበአማልክት መካኚል ይፈርዳልፊ
“ፍትሕ ዚምታዛቡት እስኚ መቌ ነው?ለክፉዎቜስ ዚምታዳሉት እስኚ መቌ ነው? (ሮላ)
ለቜግሚኛውና አባት ለሌለው ተሟገቱ። ሚዳት ዹሌለውና ምስኪኑ ፍትሕ እንዲያገኝ አድርጉ።
ቜግሚኛውንና ድሃውን ታደጉፀኚክፉዎቜም እጅ አድኗ቞ው።”
ፈራጆቹ ምንም አያውቁምፀ ደግሞም አያስተውሉምፀበጚለማ ውስጥ ይመላለሳሉፀዚምድር መሠሚቶቜ ሁሉ ተናግተዋል።
“እኔም እንዲህ አልኩፊ ‘እናንተ አማልክት ናቜሁፀሁላቜሁም ዹልዑሉ አምላክ ልጆቜ ናቜሁ።
ይሁንና እናንተም ሰው እንደሚሞተው ትሞታላቜሁፀደግሞም እንደ ማንኛውም ገዢ ትወድቃላቜሁ!’”
አምላክ ሆይ፣ ተነስፀ በምድርም ላይ ፍሚድፀብሔራት ሁሉ ዹአንተ ና቞ውና።
ይሖዋ ሆይ፣ ቃሌን አዳምጥፀመቃተ቎ን ልብ በል።
ንጉሀና አምላኬ ሆይ፣ ወደ አንተ እጞልያለሁና፣ለእርዳታ ዹማሰማውን ጩኞት በትኩሚት አዳምጥ።
ይሖዋ ሆይ፣ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህፀያሳሰበኝን ነገር በማለዳ ለአንተ እናገራለሁፀ በተስፋም እጠባበቃለሁ።
አንተ በክፋት ዚምትደሰት አምላክ አይደለህምናፀክፉ ሰው ኹአንተ ጋር አይቀመጥም።
እብሪተኛ ሰው በፊትህ አይቆምም። መጥፎ ምግባር ያላ቞ውን ሁሉ ትጠላለህፀ
ውሞት ዚሚናገሩትን ታጠፋለህ። ይሖዋ ዓመፀኞቜንና አታላዮቜን ይጞዚፋል።
እኔ ግን ታላቅ ኹሆነው ታማኝ ፍቅርህ ዚተነሳ ወደ ቀትህ እገባለሁፀአንተን በመፍራት ቅዱስ ወደሆነው ቀተ መቅደስህ እሰግዳለሁ።
ይሖዋ ሆይ፣ ጠላቶቌ በዙሪያዬ ስላሉ በጜድቅህ ምራኝፀኚመንገድህ ላይ እንቅፋቶቜን አስወግድልኝ።
ዚሚሉት ነገር ሁሉ ሊታመን አይቜልምፀውስጣ቞ው በተንኮል ዹተሞላ ነው።ጉሮሯ቞ው ዹተኹፈተ መቃብር ነውፀበምላሳ቞ው ይሞነግላሉ።
አምላክ ግን ይፈርድባ቞ዋልፀዚገዛ ራሳ቞ው ዕቅድ ለጥፋት ይዳርጋ቞ዋል። ኹበደላቾው ብዛት ዚተነሳ ይባሚሩፀበአንተ ላይ ዓምፀዋልና።
አንተን መጠጊያ ዚሚያደርጉ ሁሉ ግን ሐሎት ያደርጋሉፀምንጊዜም በደስታ እልል ይላሉ። ሊጎዷ቞ው ኹሚፈልጉ ሰዎቜ ትጠብቃ቞ዋለህፀስምህን ዚሚወዱም በአንተ ሐሎት ያደርጋሉ።
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ጻድቅ ዹሆነውን ሁሉ ትባርካለህናፀሞገስህ እንደ ትልቅ ጋሻ ይሆንላ቞ዋል።
አምላክ መጠጊያቜንና ብርታታቜን፣በጭንቅ ጊዜ ፈጥኖ ዚሚደርስልን ሚዳታቜን ነው።
በመሆኑም በምድር ላይ ነውጥ ቢኚሰት፣ተራሮቜ ተንደው ወደ ጥልቁ ባሕር ቢሰምጡ አንፈራምፀ
ውኃዎቹ ቢያስገመግሙና አሹፋ ቢደፍቁ፣ተራሮቜም ኚውኃዎቹ ነውጥ ዚተነሳ ቢንቀጠቀጡ አንሞበርም። (ሮላ)
ዹአምላክን ኹተማ ደስ ዚሚያሰኙ ጅሚቶቜ ያሉት ወንዝ አለፀኚተማዋም ዹልዑሉ አምላክ ዹተቀደሰ ታላቅ ማደሪያ ነቜ።
አምላክ በኹተማዋ ውስጥ ነውፀ እሷም አትንኮታኮትም። ጎህ ሲቀድ አምላክ ይደርስላታል።
ብሔራት ሁኚት ፈጠሩፀ መንግሥታት ተገለበጡፀእሱ ድምፁን ኹፍ አድርጎ አሰማፀ ምድርም ቀለጠቜ።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ኚእኛ ጋር ነውፀዚያዕቆብ አምላክ አስተማማኝ መጠጊያቜን ነው። (ሮላ)
ኑና ዹይሖዋን ሥራዎቜ እዩፀበምድርም ላይ አስደናቂ ነገሮቜን እንዎት እንዳኚናወነ ተመልኚቱ።
ጊርነትን ኹመላው ምድር ላይ ያስወግዳል። ቀስትን ይሰባብራልፀ ጩርንም ያነክታልፀዚጊር ሠሚገሎቜን በእሳት ያቃጥላል።
“አርፋቜሁ ተቀመጡፀ እኔ አምላክ እንደሆንኩም እወቁ። በብሔራት መካኚል ኹፍ ኹፍ እላለሁፀበምድርም ላይ ኹፍ ኹፍ እላለሁ።”
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ኚእኛ ጋር ነውፀዚያዕቆብ አምላክ አስተማማኝ መጠጊያቜን ነው። (ሮላ)
አምላክ ሆይ፣ ብሔራት ርስትህን ወሚውታልፀቅዱስ መቅደስህንም አርክሰዋልፀኢዚሩሳሌምን ዚፍርስራሜ ክምር አድርገዋታል።
ዚአገልጋዮቜህን ሬሳ ለሰማይ ወፎቜ፣ዚታማኝ አገልጋዮቜህንም ሥጋ ለምድር አራዊት ምግብ አድርገው ሰጥተዋል።
ደማቾውን በኢዚሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውኃ አፈሰሱፀእነሱንም ዚሚቀብር አንድም ሰው አልተሚፈም።
በጎሚቀቶቻቜን ዘንድ መሳለቂያ ሆንንፀበዙሪያቜን ያሉትም ያፌዙብናልፀ ደግሞም ይዘብቱብናል።
ይሖዋ ሆይ፣ ዚምትቆጣው እስኚ መቌ ነው? ለዘላለም? ቁጣህስ እንደ እሳት ዹሚነደው እስኚ መቌ ነው?
አንተን በማያውቁ ብሔራት፣ስምህንም በማይጠሩ መንግሥታት ላይ ቁጣህን አፍስስ።
ያዕቆብን በልተውታልናፀዚትውልድ አገሩንም አውድመዋል።
አባቶቻቜን በሠሩት ስህተት እኛን ተጠያቂ አታድርገን። ፈጥነህ ምሕሚት አድርግልንፀበጭንቀት ተውጠናልና።
አዳኛቜን ዹሆንክ አምላክ ሆይ፣ለታላቁ ስምህ ስትል እርዳንፀለስምህም ስትል ታደገንፀ ኃጢአታቜንንም ይቅር በለን።
ብሔራት “አምላካ቞ው ዚት አለ?” ለምን ይበሉ? በፈሰሰው ዚአገልጋዮቜህ ደም ዚተነሳ ዚሚወሰድባ቞ውን ዹበቀል እርምጃ፣ዓይናቜን እያዚ ብሔራት ይወቁት።
እስሚኛው ዚሚያሰማውን ሲቃ ስማ። ሞት ዚተፈሚደባ቞ውን በታላቅ ኃይልህ አድና቞ው።
ይሖዋ ሆይ፣ ጎሚቀቶቻቜን በአንተ ላይ በመሳለቃ቞ውሰባት እጥፍ አድርገህ ብድራታ቞ውን ክፈላ቞ው።
በዚህ ጊዜ እኛ ሕዝቊቜህ፣ በመስክህ ያሰማራኞን መንጋ፣ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለንፀኚትውልድ እስኚ ትውልድም ውዳሎህን እናሰማለን።
ይሖዋ ሆይ፣ ኹክፉ ሰዎቜ ታደገኝፀኚጚካኞቜም ጠብቀኝፀ
እነሱ በልባ቞ው ክፉ ነገር ይጠነስሳሉፀደግሞም ቀኑን ሙሉ ጠብ ይጭራሉ።
እንደ እባብ ምላሳ቞ውን ያሟላሉፀኚኚንፈራ቞ው ኋላ ዚእፉኝት መርዝ አለ። (ሮላ)
ይሖዋ ሆይ፣ ኚክፉዎቜ እጅ አድነኝፀእኔን ጠልፈው ለመጣል ኚሚያሎሩጚካኝ ሰዎቜ ጠብቀኝ።
ትዕቢተኞቜ በስውር ወጥመድ አስቀመጡብኝፀኚመንገዱ አጠገብ ዚመሚባ቞ውን ገመድ ዘሚጉብኝ። አሜክላም አስቀመጡብኝ። (ሮላ)
ይሖዋን እንዲህ እለዋለሁፊ “አንተ አምላኬ ነህ። ይሖዋ ሆይ፣ እርዳታ ለማግኘት ዹማቀርበውን ልመና ስማ።”
ኃያል አዳኜ ዹሆንኹው ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣በጊርነት ቀን ራሎን ትኚልላለህ።
ይሖዋ ሆይ፣ ዚክፉዎቜ ምኞት እንዲሳካ አታድርግ። ራሳ቞ውን ኹፍ ኹፍ እንዳያደርጉ፣ ሎራ቞ው እንዲሰምር አትፍቀድ። (ሮላ)
ዙሪያዬን ዚኚበቡኝን ሰዎቜ ራስ፣ዚገዛ ኚንፈራ቞ው ዹተናገሹው ክፋት ይሞፍነው።
ዚእሳት ፍም በላያ቞ው ይውሚድ። መነሳት እንዳይቜሉ ወደ እሳት፣ወደ ጥልቅ ጉድጓዶቜ ይወርወሩ።
ስም አጥፊ በምድር ላይ አንዳቜ ቊታ አያግኝ። ጚካኞቜን ክፋት አሳዶ ይምታ቞ው።
ይሖዋ ለቜግሚኛው እንደሚሟገትናለድሃው ፍትሕ እንደሚያሰፍን አውቃለሁ።
በእርግጥ ጻድቃን ለስምህ ምስጋና ያቀርባሉፀቅኖቜም በፊትህ ይኖራሉ።
ሞኝ ሰው በልቡ “ይሖዋ ዹለም” ይላል። ሥራ቞ው ብልሹ ነውፀ ተግባራ቞ውም አስጞያፊ ነውፀመልካም ዚሚሠራ ማንም ዚለም።
ሆኖም ጥልቅ ማስተዋል ያለውና ይሖዋን ዹሚፈልግ ሰው ይኖር እንደሆነ ለማዚት፣ይሖዋ ኹሰማይ ሆኖ ወደ ሰው ልጆቜ ይመለኚታል።
ሁሉም መንገድ ስተዋልፀሁሉም ብልሹ ና቞ው። መልካም ዚሚሠራ ማንም ዚለምፀአንድ እንኳ ዚለም።
ኹክፉ አድራጊዎቹ መካኚል አንዳ቞ውም አያስተውሉም? ምግብ እንደሚበሉ ሕዝቀን ይውጣሉ። ይሖዋን አይጠሩም።
ይሁንና በታላቅ ሜብር ይዋጣሉፀይሖዋ ኚጻድቅ ትውልድ ጋር ነውና።
እናንተ ክፉ አድራጊዎቜ ዚቜግሚኛውን ሰው ዕቅድ ለማጹናገፍ ትሞክራላቜሁፀይሖዋ ግን መጠጊያው ነው።
ዚእስራኀል መዳን ምነው ኚጜዮን በመጣ! ይሖዋ ዹተማሹኹውን ሕዝቡን በሚመልስበት ጊዜ፣ያዕቆብ ደስ ይበለውፀ እስራኀል ሐሎት ያድርግ።
ያህን አወድሱ! ለአምላካቜን ዚውዳሎ መዝሙር መዘመር ጥሩ ነውፀእሱን ማወደስ ደስ ያሰኛልፀ ደግሞም ተገቢ ነው።
ይሖዋ ኢዚሩሳሌምን ይገነባልፀዚተበተኑትን ዚእስራኀል ነዋሪዎቜ ይሰበስባል።
ዹተሰበሹ ልብ ያላ቞ውን ይጠግናልፀቁስላ቞ውን ይፈውሳል።
ዚኚዋክብትን ብዛት ይቆጥራልፀሁሉንም በዚስማ቞ው ይጠራ቞ዋል።
ጌታቜን ታላቅ ነውፀ ደግሞም እጅግ ኃያል ነውፀማስተዋሉም ወሰን ዚለውም።
ይሖዋ ዚዋሆቜን ያነሳልፀክፉዎቜን ግን መሬት ላይ ይጥላል።
ለይሖዋ በምስጋና ዘምሩፀለአምላካቜን በበገና ዚውዳሎ መዝሙር ዘምሩፀ
እሱ ሰማያትን በደመናት ይሞፍናልፀለምድር ዝናብ ይሰጣልፀበተራሮቜ ላይ ሣር እንዲበቅል ያደርጋል።
ለእንስሳት እንዲሁም ዚሚበሉትን ለማግኘት ለሚጮኹ ዚቁራ ጫጩቶቜምግብ ይሰጣል።
በፈሚስ ጉልበት አይደሰትምፀዚሰው እግር ጥንካሬም አያስደንቀውም።
ኹዚህ ይልቅ ይሖዋ እሱን በሚፈሩ፣ታማኝ ፍቅሩን በሚጠባበቁ ሰዎቜ ይደሰታል።
ኢዚሩሳሌም ሆይ፣ ይሖዋን ኹፍ ኹፍ አድርጊ። ጜዮን ሆይ፣ አምላክሜን አወድሺ።
እሱ ዚኚተማሜን በሮቜ መወርወሪያዎቜ አጠናክሯልፀበውስጥሜ ያሉትን ወንዶቜ ልጆቜ ይባርካል።
በክልልሜ ውስጥ ሰላም ያሰፍናልፀምርጥ በሆነ ስንዎ ያጠግብሻል።
ትእዛዙን ወደ ምድር ይልካልፀቃሉም በፍጥነት ይሮጣል።
በሚዶን እንደ ሱፍ ይልካልፀአመዳዩን እንደ አመድ ይበትናል።
ዚበሚዶውን ድንጋይ እንደ ዳቊ ፍርፋሪ ይወሚውራል። እሱ ዹሚልኹውን ቅዝቃዜ ማን ሊቋቋም ይቜላል?
ቃሉን ይልካልፀ እነሱም ይቀልጣሉ። ነፋሱ እንዲነፍስ ያደርጋልፀ ውኃውም ይፈስሳል።
ቃሉን ለያዕቆብ፣ሥርዓቱንና ፍርዶቹን ለእስራኀል ያስታውቃል።
ይህን ለሌላ ለማንም ብሔር አላደሚገምፀእነሱ ስለ ፍርዶቹ ምንም ዚሚያውቁት ነገር ዚለም። ያህን አወድሱ!
በሌሊት በይሖዋ ቀት ዚምታገለግሉ፣እናንተ ዹይሖዋ አገልጋዮቜ ሁሉ፣ይሖዋን አወድሱ።
እጆቻቜሁን በቅድስና ወደ ላይ አንሱፀይሖዋንም አወድሱ።
ሰማይንና ምድርን ዚሠራው ይሖዋ፣ኚጜዮን ይባርክህ።
አምላክ ሆይ፣ ልቀ ጜኑ ነው። በሁለንተናዬ እዘምራለሁፀ ደግሞም አዜማለሁ።
ባለ አውታር መሣሪያ ሆይ፣ አንተም በገና ሆይ፣ ተነሱ። እኔም በማለዳ እነሳለሁ።
ይሖዋ ሆይ፣ በሕዝቊቜ መካኚል አወድስሃለሁፀበብሔራትም መካኚል ዚውዳሎ መዝሙር እዘምርልሃለሁ።
ታማኝ ፍቅርህ ታላቅ ነውናፀ እንደ ሰማያት ኹፍ ያለ ነውፀታማኝነትህም እስኚ ደመናት ድሚስ ነው።
አምላክ ሆይ፣ ኚሰማያት በላይ ኹፍ ኹፍ በልፀክብርህ በምድር ሁሉ ላይ ይሁን።