text
stringlengths
4
267
ምሜት ላይ ተመልሰው ይምጡፀእንደ ውሟቜ እያጉሚመሚሙ በኹተማዋ ዙሪያ ያድቡ።
ምግብ ፍለጋ ወዲያ ወዲህ ይንኚራተቱፀበልተውም አይጥገቡፀ ዚሚያርፉበት ቊታም ይጡ።
እኔ ግን ስለ ብርታትህ እዘምራለሁፀበማለዳ ስለ ታማኝ ፍቅርህ በደስታ እናገራለሁ። አንተ አስተማማኝ መጠጊያዬ፣ደግሞም በጭንቀቮ ቀን መሞሞጊያዬ ነህና።
ብርታ቎ ሆይ፣ ለአንተ ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁፀታማኝ ፍቅር ዚሚያሳዚኝ አምላክ አስተማማኝ መጠጊያዬ ነውና።
ይሖዋ ሆይ፣ ጾሎቮን ስማፀእርዳታ ለማግኘት ዹማሰማው ጩኞት ወደ አንተ ይድሚስ።
ዚሚያስጚንቅ ሁኔታ ባጋጠመኝ ጊዜ ፊትህን ኚእኔ አትሰውር። ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብልፀስጣራ ፈጥነህ መልስልኝ።
ዚሕይወት ዘመኔ እንደ ጭስ እዚበነነ ነውፀአጥንቶቌም እንደ ምድጃ ኚስለዋል።
እህል መብላት ሚስቻለሁናፀልቀ እንደ ሣር ጠውልጓልፀ ደርቋልም።
እጅግ ኹመቃተቮ ዚተነሳአጥንቶቌ ኚቆዳዬ ጋር ተጣበቁ።
ዚምድሚ በዳ ሻላ መሰልኩፀበፍርስራሜ ክምር መካኚል እንዳለቜ ጉጉት ሆንኩ።
እንቅልፍ አጥቌ አድራለሁፀበጣሪያ ላይ እንዳለቜ ብ቞ኛ ወፍ ሆንኩ።
ጠላቶቌ ቀኑን ሙሉ ይሳለቁብኛል። ዚሚያፌዙብኝ ሰዎቜ ስሜን ለእርግማን ይጠቀሙበታል።
አመድን እንደ ምግብ እበላለሁናፀዚምጠጣውም ነገር ኚእንባ ጋር ተቀላቅሏልፀ
ይህም ዹሆነው ኚቁጣህና ኚንዎትህ ዚተነሳ ነውፀእኔን ለመጣል ወደ ላይ አንስተኞኛልና።
ዹሕይወቮ ዘመን ፀሐይ ስትጠልቅ እንደሚጠፋ ጥላ ነውፀእኔም እንደ ሣር ጠወለግኩ።
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን ለዘላለም ትኖራለህፀዝናህም ኚትውልድ እስኚ ትውልድ ይጞናል።
በእርግጥ ትነሳለህፀ ለጜዮንም ምሕሚት ታሳያለህፀለእሷ ሞገስህን ዚምታሳይበት ጊዜ ነውናፀዚተወሰነው ጊዜ ደርሷል።
አገልጋዮቜህ በድንጋዮቿ ደስ ይላ቞ዋልናፀለአፈሯም እንኳ ልዩ ፍቅር አላ቞ው።
ብሔራት ዹይሖዋን ስም፣ዚምድር ነገሥታትም ሁሉ ክብርህን ይፈራሉ።
ይሖዋ ጜዮንን ዳግመኛ ይገነባልናፀበክብሩም ይገለጣል።
ዚድሆቜን ጞሎት በትኩሚት ያዳምጣልፀጞሎታ቞ውን አይንቅም።
ይህ ዚተጻፈው ለመጪው ትውልድ ነውፀበመሆኑም ወደፊት ዚሚመጣው ሕዝብ ያህን ያወድሳል።
ይሖዋ ኹፍ ካለው ቅዱስ ስፍራው ወደ ታቜ ይመለኚታልናፀኚሰማይ ሆኖ ወደ ታቜ ምድርን ያያልፀ
ይህም ዚእስሚኛውን ሲቃ ለመስማት፣ሞት ዚተፈሚደባ቞ውንም ነፃ ለማውጣት ነውፀ
በመሆኑም ዹይሖዋ ስም በጜዮን፣ውዳሎውም በኢዚሩሳሌም ይታወጃልፀ
ይህም ዹሚሆነው ሕዝቊቜና መንግሥታትይሖዋን ለማገልገል አንድ ላይ በሚሰበሰቡበት ጊዜ ነው።
ያለጊዜዬ ኃይል አሳጣኝፀዚሕይወት ዘመኔን አሳጠሚ።
እኔም እንዲህ አልኩፊ“ኚትውልድ እስኚ ትውልድ ዚምትኖሚው አምላኬ ሆይ፣በሕይወት ዘመኔ እኩሌታ አታጥፋኝ።
አንተ ኚብዙ ዘመናት በፊት ዚምድርን መሠሚት ጣልክፀሰማያትም ዚእጆቜህ ሥራ ና቞ው።
እነሱ ይጠፋሉፀ አንተ ግን ትኖራለህፀሁሉም እንደ ልብስ ያሚጃሉ። እንደ ልብስ ትቀይራ቞ዋለህፀ እነሱም ያልፋሉ።
አንተ ግን ያው ነህፀ ዘመንህም ፍጻሜ ዚለውም።
ዚአገልጋዮቜህ ልጆቜ ያለስጋት ይኖራሉፀዘራ቞ውም በፊትህ ጞንቶ ይኖራል።”
ይሖዋ ጥሩ ስለሆነ ምስጋና አቅርቡለትፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራል።
ለአማልክት አምላክ ምስጋና አቅርቡፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ለጌቶቜ ጌታ ምስጋና አቅርቡፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
እሱ ብቻ አስደናቂ ዹሆኑ ታላላቅ ነገሮቜ ይሠራልፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ሰማያትን በጥበብ ሠራፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ምድርን በውኃዎቜ ላይ ዘሚጋፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ታላላቅ ብርሃናትን ሠራፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልናፀ
ፀሐይ በቀን እንዲያይል አደሚገፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልናፀ
ጹሹቃና ኚዋክብት በሌሊት እንዲያይሉ አደሚገፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ዚግብፅን በኩር ቀሰፈፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
እስራኀልን ኚመካኚላ቞ው አወጣፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልናፀ
በኃያል እጅና በተዘሹጋ ክንድ ይህን አድርጓልፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ቀይ ባሕርን ለሁለት ኚፈለፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
እስራኀል በመካኚሉ እንዲያልፍ አደሚገፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ፈርዖንንና ሠራዊቱን ቀይ ባሕር ውስጥ ወሚወሚፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ሕዝቡን በምድሚ በዳ መራፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ታላላቅ ነገሥታትን መታፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ኃያላን ነገሥታትን ገደለፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልናፀ
ዚአሞራውያንን ንጉሥ ሲሖንን ገደለፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልናፀ
ዚባሳንንም ንጉሥ ኩግን ገደለፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ምድራ቞ውን ርስት አድርጎ ሰጠፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልናፀ
ለአገልጋዩ ለእስራኀል ርስት አድርጎ አወሚሰፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
መንፈሳቜን ተደቁሶ በነበሚበት ጊዜ አስታወሰንፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ኚጠላቶቻቜን እጅ ይታደገን ነበርፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ሕይወት ላለው ሁሉ ምግብ ይሰጣልፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
ለሰማያት አምላክ ምስጋና አቅርቡፀታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጞንቶ ይኖራልና።
አምላክ ሆይ፣ እርዳታ ለማግኘት ዹማሰማውን ጩኞት ስማ። ጾሎቮን በትኩሚት አዳምጥ።
ልቀ ተስፋ በቆሹጠ ጊዜኚምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጮኻለሁ። ኚእኔ ይልቅ ኹፍ ወዳለ ዓለት ምራኝ።
አንተ መጠጊያዬ ነህናፀኚጠላት ዚምትጠብቀኝ ጜኑ ግንብ ነህ።
በድንኳንህ ለዘላለም በእንግድነት እቀመጣለሁፀበክንፎቜህ ጥላ ሥር እጠለላለሁ። (ሮላ)
አምላክ ሆይ፣ ስእለ቎ን ሰምተሃልና። ስምህን ዚሚፈሩትን ሰዎቜ ርስት ሰጥተኞኛል።
ዚንጉሡን ሕይወት ታሚዝምለታለህፀዕድሜውም ኚትውልድ እስኚ ትውልድ ድሚስ ይሆናል።
በአምላክ ፊት ለዘላለም ይነግሣልፀታማኝ ፍቅርና ታማኝነት እንዲጠብቁት እዘዝ።
እኔም ስእለ቎ን በዹቀኑ ስፈጜም፣ለስምህ ለዘላለም ዚውዳሎ መዝሙር እዘምራለሁ።
ድምፄን አውጥቌ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ እጣራለሁፀሞገስ እንዲያሳዚኝ ይሖዋን እማጞናለሁ።
ዚሚያሳስበኝን ነገር በፊቱ አፈስሳለሁፀዚውስጀን ጭንቀት በፊቱ እናገራለሁፀ
መንፈሮ በውስጀ ሲዝል፣ እሱን እማጞናለሁ። በዚህ ጊዜ ጎዳናዬን ትመለኚታለህ። በምሄድበት መንገድ ላይበስውር ወጥመድ ዘሚጉብኝ።
ቀኝ እጄን ተመልኚትፀስለ እኔ ግድ ዹሚሰጠው ሰው እንደሌለ እይ። ሞሜቌ ማምለጥ ዚምቜልበት ቊታ ዚለምፀስለ እኔ ዚሚያስብ ማንም ዚለም።
ይሖዋ ሆይ፣ እርዳታ ለማግኘት ወደ አንተ እጣራለሁ። ደግሞም “አንተ መጠጊያዬ ነህፀበሕያዋን ምድር ያለኞኝ አንተ ብቻ ነህ” እላለሁ።
መንፈሮ እጅግ ተደቁሷልና፣እርዳታ ለማግኘት ዹማቀርበውን ልመና ስማ። ኚእኔ ይልቅ ብርቱ ስለሆኑኚሚያሳድዱኝ ሰዎቜ ታደገኝ።
ስምህን አወድስ ዘንድኚእስር ቀት አውጣኝ። ደግነት ስለምታሳዚኝጻድቃን በዙሪያዬ ይሰብሰቡ።
ዮሎፍን እንደ መንጋ ዚምትመራዚእስራኀል እሚኛ ሆይ፣ አዳምጥ። ኚኪሩቀል በላይ በዙፋን ዚምትቀመጥ ሆይ፣ብርሃን አብራ።
በኀፍሬም፣ በቢንያምና በምናሮ ፊትኃያልነትህን አሳይፀመጥተህም አድነን።
አምላክ ሆይ፣ ወደ ቀድሞው ሁኔታቜን መልሰንፀእንድንም ዘንድ ፊትህን በእኛ ላይ አብራ።
ዚሠራዊት አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ ሕዝቊቜህ ዚሚያቀርቡትን ጞሎት ዚምትጠላው እስኚ መቌ ነው?
እንባን እንደ ምግብ ትመግባ቞ዋለህፀደግሞም እንባ ትግታ቞ዋለህ።
ለጎሚቀቶቻቜን ዚጠብ ምክንያት አደሚግኚንፀጠላቶቻቜን እንዳሻ቞ው ያላግጡብናል።
ዚሠራዊት አምላክ ሆይ፣ ወደ ቀድሞው ሁኔታቜን መልሰንፀእንድንም ዘንድ ፊትህን በእኛ ላይ አብራ።
ዹወይን ተክል ኚግብፅ እንድትወጣ አደሚግክ። ብሔራትን አባሚህ እሷን ተኚልክ።
መሬቱን መነጠርክላትፀእሷም ሥር ሰዳ በምድሪቱ ላይ ተንሰራፋቜ።
ተራሮቜ በጥላዋ፣ዚአምላክ አርዘ ሊባኖሶቜም በቅርንጫፎቿ ተሞፈኑ።
ቅርንጫፎቿ እስኚ ባሕሩ፣ቀንበጊቿም እስኚ ወንዙ ድሚስ ተዘሚጉ።
በዚያ ዚሚያልፉ ሁሉ ፍሬዋን እንዲቀጥፉ፣ዚወይን እርሻዋን ዚድንጋይ ቅጥሮቜ ያፈሚስኚው ለምንድን ነው?
ኚጫካ ዚወጡ ዚዱር አሳማዎቜ ያወድሟታልፀበሜዳ ያሉ ዚዱር አራዊትም ይበሏታል።
ዚሠራዊት አምላክ ሆይ፣ እባክህ ተመለስ። ኹሰማይ ወደ ታቜ እይፀ ተመልኚትም! ይህቜን ዹወይን ተክል ተንኚባኚባትፀ
ቀኝ እጅህ ዚተኚላትን ግንድ በእንክብካቀ ያዛትፀለራስህ ስትል ያጠነኚርኚውንም ልጅ ተመልኚት።
እሷ ተቆርጣ በእሳት ተቃጥላለቜ። ሕዝቡ ኚተግሣጜህ ዚተነሳ ይጠፋል።
እጅህ በቀኝህ ላለው ሰው፣ለራስህም ስትል ብርቱ ላደሹግኹው ዹሰው ልጅ ድጋፍ ትስጥ።
እኛም ኹአንተ አንርቅም። ስምህን መጥራት እንድንቜል በሕይወት አኑሚን።
ዚሠራዊት አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ ወደ ቀድሞው ሁኔታቜን መልሰንፀእንድንም ዘንድ ፊትህን በእኛ ላይ አብራ።
እስራኀል ኚግብፅ ሲወጣ፣ዚያዕቆብ ቀት ባዕድ ቋንቋ ኹሚናገር ሕዝብ ተለይቶ ሲሄድ፣
ይሁዳ መቅደሱ፣እስራኀልም ግዛቱ ሆነ።
ባሕሩ ይህን አይቶ ሞሞፀዮርዳኖስ ወደ ኋላ ተመለሰ።
ተራሮቜ እንደ አውራ በግ፣ኮሚብቶቜ እንደ ጠቊት ፈነጩ።
አንተ ባሕር ሆይ፣ ዹሾሾኾው ምን ሆነህ ነው? ዮርዳኖስ ሆይ፣ ወደ ኋላ ዚተመለስኚው ለምንድን ነው?
ተራሮቜ ሆይ፣ እንደ አውራ በግ ዚዘለላቜሁት፣እናንተ ኮሚብቶቜ፣ እንደ ጠቊት ዚፈነጫቜሁት ለምንድን ነው?
ምድር ሆይ፣ ኚጌታ ዚተነሳ፣ኚያዕቆብም አምላክ ዚተነሳ ተንቀጥቀጪፀ
እሱ ዓለቱን ቄጠማ ወደሞላበት ኩሬ፣ጠንካራውንም ዓለት ወደ ውኃ ምንጮቜ ይለውጣል።