text stringlengths 4 267 |
|---|
እኔ “በምላሴ ኃጢአት እንዳልፈጽምአካሄዴን እጠብቃለሁ። ክፉ ሰው ከእኔ ጋር እስካለ ድረስአፌን ለመጠበቅ ልጓም አስገባለሁ” አልኩ። |
ዱዳ ሆንኩ፤ ደግሞም ዝም አልኩ፤መልካም ነገር ከመናገር እንኳ ታቀብኩ፤ይሁንና ሥቃዬ ከባድ ነበር። |
ልቤ በውስጤ ነደደ። ሳወጣ ሳወርድ እንደ እሳት ነደድኩ። በዚህ ጊዜ በአንደበቴ እንዲህ አልኩ፦ |
“ይሖዋ ሆይ፣ መጨረሻዬ ምን እንደሚሆን፣የዕድሜዬም ርዝማኔ ምን ያህል እንደሆነ እንዳውቅ እርዳኝ፤ይህም ሕይወቴ ምን ያህል አጭር እንደሆነ አውቅ ዘንድ ነው። |
በእርግጥም ቀኖቼን ጥቂት አደረግካቸው፤የሕይወት ዘመኔም በፊትህ ከምንም አይቆጠርም። አዎ፣ ሰው ሁሉ ምንም ነገር የማይነካው ቢመስልም እንኳ እንደ እስትንፋስ ነው። (ሴላ) |
በእርግጥም ሰው ሁሉ የሚመላለሰው እንደ ጥላ ነው። ላይ ታች የሚለው በከንቱ ነው። ማን እንደሚጠቀምበት ሳያውቅ ንብረት ያከማቻል። |
ይሖዋ ሆይ፣ ታዲያ ተስፋዬ ምንድን ነው? ተስፋዬ አንተ ብቻ ነህ። |
ከፈጸምኩት በደል ሁሉ አድነኝ። ሞኝ ሰው እንዲሳለቅብኝ አትፍቀድ። |
ዱዳ ሆንኩ፤ይህን ያደረግከው አንተ ስለሆንክአፌን መክፈት አልቻልኩም። |
በእኔ ላይ ያመጣኸውን መቅሰፍት ከእኔ አርቅ። እጅህ ስለመታኝ ዛልኩ። |
ሰውን በሠራው ስህተት የተነሳ በመቅጣት ታርመዋለህ፤እንደ ውድ ሀብት የሚመለከታቸውን ነገሮች እንደ ብል ትበላበታለህ። በእርግጥም ሰው ሁሉ እንደ እስትንፋስ ነው። (ሴላ) |
ይሖዋ ሆይ፣ ጸሎቴን ስማ፤ለእርዳታ የማሰማውን ጩኸት አዳምጥ። እንባዬን ችላ አትበል። እኔ በአንተ ዘንድ የባዕድ አገር ሰው ነኝና፤እንደ አባቶቼ አልፌ የምሄድ ተጓዥ ነኝ። |
ከመሞቴና ከሕልውና ውጭ ከመሆኔ በፊት፣ፊቴ እንዲፈካ በክፉ ዓይን አትየኝ።” |
በጭንቀት ቀን ይሖዋ ይስማህ። የያዕቆብ አምላክ ስም ይጠብቅህ። |
ከቅዱሱ ስፍራ እርዳታ ይላክልህ፤ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ። |
በስጦታ የምታቀርበውን መባ ሁሉ ያስብልህ፤የሚቃጠል መባህን በሞገስ ዓይን ይቀበልህ። (ሴላ) |
የልብህን ፍላጎት ያሟላልህ፤ዕቅድህንም ሁሉ ያሳካልህ። |
በማዳን ሥራህ በደስታ እልል እንላለን፤በአምላካችን ስም ዓርማችንን ወደ ላይ ከፍ እናደርጋለን። ይሖዋ የለመንከውን ሁሉ ይፈጽምልህ። |
ይሖዋ የቀባውን እንደሚያድን አሁን አወቅኩ። በቀኝ እጁ በሚያከናውነው ታላቅ የማዳን ሥራ፣ቅዱስ ከሆኑት ሰማያቱ ይመልስለታል። |
አንዳንዶች በሠረገሎች፣ ሌሎች ደግሞ በፈረሶች ይታመናሉ፤እኛ ግን የአምላካችንን የይሖዋን ስም እንጠራለን። |
እነሱ ተዝለፍልፈው ወድቀዋል፤እኛ ግን ተነስተን ቀጥ ብለን ቆመናል። |
ይሖዋ ሆይ፣ ንጉሡን አድን! እርዳታ ለማግኘት በተጣራን ቀን ይመልስልናል። |
ለይሖዋ አዲስ መዝሙር ዘምሩ። መላዋ ምድር ለይሖዋ ትዘምር! |
ለይሖዋ ዘምሩ፤ ስሙንም አወድሱ። የማዳኑን ምሥራች በየቀኑ አውጁ። |
ክብሩን በብሔራት፣አስደናቂ ሥራዎቹንም በሕዝቦች ሁሉ መካከል አስታውቁ። |
ይሖዋ ታላቅ ነው፤ ደግሞም እጅግ ሊወደስ ይገባዋል። ከሌሎች አማልክት ሁሉ በላይ እጅግ የሚፈራ ነው። |
የሌሎች ሕዝቦች አማልክት ሁሉ ከንቱ ናቸው፤ይሖዋ ግን ሰማያትን የሠራ አምላክ ነው። |
ሞገስና ግርማ በፊቱ ናቸው፤ብርታትና ውበት በመቅደሱ ውስጥ አሉ። |
እናንተ የሕዝብ ነገዶች፣ ለይሖዋ የሚገባውን ስጡ፤ከክብሩና ከብርታቱ የተነሳ ለይሖዋ የሚገባውን ስጡ። |
ለስሙ የሚገባውን ክብር ለይሖዋ ስጡ፤ስጦታ ይዛችሁ ወደ ቅጥር ግቢዎቹ ግቡ። |
ያጌጠ የቅድስና ልብስ ለብሳችሁ ለይሖዋ ስገዱ፤ምድር ሁሉ በፊቱ ተንቀጥቀጪ! |
በብሔራት መካከል እንዲህ ብላችሁ አስታውቁ፦ “ይሖዋ ነገሠ! ምድር በጽኑ ተመሥርታለች፤ ከቦታዋ ልትንቀሳቀስ አትችልም። እሱ ለሕዝቦች በትክክል ይፈርዳል።” |
ሰማያት ሐሴት ያድርጉ፤ ምድርም ደስ ይበላት፤ባሕሩና በውስጡ ያለው ነገር ሁሉ የነጎድጓድ ድምፅ ያሰማ፤ |
መስኩና በላዩ ላይ ያለው ሁሉ ሐሴት ያድርግ። የዱር ዛፎችም ሁሉ በይሖዋ ፊት እልል ይበሉ። |
እሱ እየመጣ ነውና፤በምድር ላይ ለመፍረድ እየመጣ ነው። በዓለም ላይ በጽድቅ፣በሕዝቦችም ላይ በታማኝነት ይፈርዳል። |
ይሖዋ ሆይ፣ አንድም ታማኝ ሰው ስለሌለ አድነኝ፤ከሰው ልጆች መካከል ታማኞች ጠፍተዋል። |
እርስ በርሳቸው ውሸት ይነጋገራሉ፤በከንፈራቸው ይሸነግላሉ፤ አታላይ በሆነ ልብም ይናገራሉ። |
ይሖዋ የሚሸነግልን ከንፈር ሁሉ፣ጉራ የሚነዛውንም ምላስ ይቆርጣል፤ |
እነሱ “በምላሳችን እንረታለን። አንደበታችንን እንዳሻን እንጠቀምበታለን፤በእኛ ላይ ጌታ ሊሆን የሚችል ማን ነው?” ይላሉ። |
“የተጎሳቆሉት ሰዎች በመጨቆናቸው፣ድሆችም በመቃተታቸው፣እርምጃ ለመውሰድ እነሳለሁ” ይላል ይሖዋ። “በንቀት ዓይን ከሚመለከቷቸው ሁሉ እታደጋቸዋለሁ።” |
የይሖዋ ቃል የጠራ ነው፤ከሸክላ በተሠራ ምድጃ እንደተጣራ ብር ሰባት ጊዜ የነጠረ ነው። |
ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ትጋርዳቸዋለህ፤እያንዳንዳቸውን ከዚህ ትውልድ ለዘላለም ትጠብቃቸዋለህ። |
የሰው ልጆች ብልሹ ምግባርን ስለሚያስፋፉ፣ክፉዎች እንዳሻቸው ይፈነጫሉ። |
ሞኝ ሰው በልቡ “ይሖዋ የለም” ይላል። የዓመፅ ድርጊታቸው ብልሹና አስጸያፊ ነው፤መልካም የሚሠራ ማንም የለም። |
ሆኖም ጥልቅ ማስተዋል ያለውና ይሖዋን የሚፈልግ ሰው ይኖር እንደሆነ ለማየትአምላክ ከሰማይ ሆኖ ወደ ሰው ልጆች ይመለከታል። |
ሁሉም ወደ ሌላ ዞር ብለዋል፤ሁሉም ብልሹ ናቸው። መልካም የሚሠራ ማንም የለም፤አንድ እንኳ የለም። |
ከክፉ አድራጊዎቹ መካከል አንዳቸውም አያስተውሉም? ምግብ እንደሚበሉ ሕዝቤን ይውጣሉ። ይሖዋን አይጠሩም። |
ይሁንና በታላቅ ሽብር፣ከዚህ በፊት ተሰምቷቸው በማያውቅ ታላቅ ፍርሃት ይዋጣሉ፤በአንተ ላይ ጥቃት የሚሰነዝሩትን ሰዎች አጥንት አምላክ ይበታትነዋልና። ይሖዋ ስላልተቀበላቸው አንተ ታዋርዳቸዋለህ። |
የእስራኤል መዳን ምነው ከጽዮን በመጣ! ይሖዋ የተማረከውን ሕዝቡን በሚመልስበት ጊዜ፣ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤል ሐሴት ያድርግ። |
ይሖዋ ታላቅ ነው፤በአምላካችን ከተማ፣ በቅዱስ ተራራው እጅግ ሊወደስ ይገባዋል። |
በከፍታ ቦታ ላይ ተውባ የምትታየው፣ የምድር ሁሉ ደስታ፣በስተ ሰሜን ርቃ የምትገኘው የጽዮን ተራራ ነች፤ደግሞም የታላቁ ንጉሥ ከተማ ነች። |
አምላክ በማይደፈሩ ማማዎቿ ውስጥአስተማማኝ መጠጊያ መሆኑን አስመሥክሯል። |
እነሆ፣ ነገሥታት ተሰብስበዋልና፤አንድ ላይ ሆነው ገሰገሱ። |
ከተማዋን ባዩአት ጊዜ ተገረሙ። ደንግጠውም ፈረጠጡ። |
በዚያም በፍርሃት ተንቀጠቀጡ፤እንደምትወልድ ሴት ጭንቅ ያዛቸው። |
የተርሴስን መርከቦች በምሥራቅ ነፋስ ሰባበርክ። |
የሰማነውን ነገር፣ በሠራዊት ጌታ በይሖዋ ከተማይኸውም በአምላካችን ከተማ አሁን በገዛ ዓይናችን አይተናል። አምላክ ለዘላለም ያጸናታል። (ሴላ) |
አምላክ ሆይ፣ በቤተ መቅደስህ ውስጥ ሆነንስለ ታማኝ ፍቅርህ እናሰላስላለን። |
አምላክ ሆይ፣ እንደ ስምህ ሁሉ ውዳሴህምእስከ ምድር ዳርቻ ይደርሳል። ቀኝ እጅህ በጽድቅ ተሞልቷል። |
ከፍርድህ የተነሳ የጽዮን ተራራ ደስ ይበላት፤የይሁዳ ከተሞችም ሐሴት ያድርጉ። |
በጽዮን ዙሪያ ሂዱ፤ በዙሪያዋም ተጓዙ፤ማማዎቿን ቁጠሩ። |
የመከላከያ ግንቦቿን ልብ ብላችሁ ተመልከቱ። ለመጪዎቹ ትውልዶች መናገር ትችሉ ዘንድ፣የማይደፈሩ ማማዎቿን በሚገባ አጢኑ። |
ይህ አምላክ፣ ለዘላለም አምላካችን ነውና። እስከ ወዲያኛው ይመራናል። |
ብርታቴ ይሖዋ ሆይ፣ እወድሃለሁ። |
ይሖዋ ቋጥኜ፣ ምሽጌና ታዳጊዬ ነው። አምላኬ የምሸሸግበት ዓለቴ ነው፤ጋሻዬ፣ የመዳኔ ቀንድና አስተማማኝ መጠጊያዬ ነው። |
ውዳሴ የሚገባውን ይሖዋን እጠራለሁ፤ከጠላቶቼም እድናለሁ። |
የሞት ገመዶች ተተበተቡብኝ፤የማይረቡ ሰዎች የለቀቁት ድንገተኛ ጎርፍ አሸበረኝ። |
የመቃብር ገመድ ተጠመጠመብኝ፤የሞት ወጥመድ ተጋረጠብኝ። |
በጭንቅ ውስጥ ሳለሁ ይሖዋን ጠራሁት፤እርዳታ ለማግኘት አምላኬን አጥብቄ ተማጸንኩት። በመቅደሱ ሆኖ ድምፄን ሰማ፤እርዳታ ለማግኘት የማሰማውም ጩኸት ወደ ጆሮው ደረሰ። |
ምድርም ትንቀጠቀጥና ትናወጥ ጀመር፤የተራሮች መሠረቶች ተንቀጠቀጡ፤እሱ ስለተቆጣም ራዱ። |
ከአፍንጫው ጭስ ወጣ፤የሚባላም እሳት ከአፉ ወጣ፤ፍምም ከእሱ ፈለቀ። |
ወደ ታች ሲወርድ ሰማያት እንዲያጎነብሱ አደረገ፤ከእግሮቹም በታች ጥቅጥቅ ያለ ደመና ነበር። |
በኪሩብ ላይ ተቀምጦ እየበረረ መጣ። በመንፈስ ክንፎች በፍጥነት ወረደ። |
ከዚያም በጨለማ ራሱን ሸፈነ፤ጥቁር ውኃና ጥቅጥቅ ያለ ደመናእንደ መጠለያ በዙሪያው ነበር። |
በፊቱ ካለው ብርሃን፣ከደመናቱ መካከል በረዶና ፍም ወጣ። |
ከዚያም ይሖዋ በሰማያት ያንጎደጉድ ጀመር፤ልዑሉ አምላክ ድምፁን አሰማ፤ደግሞም በረዶና ፍም ነበር። |
ፍላጻዎቹን አስፈንጥሮ በታተናቸው፤መብረቁን አዥጎድጉዶ ግራ አጋባቸው። |
ይሖዋ ሆይ፣ ከተግሣጽህ፣ ከአፍንጫህም ከሚወጣው ኃይለኛ እስትንፋስ የተነሳየጅረቶች ወለል ታየ፤የምድር መሠረቶችም ተገለጡ። |
ከላይ ሆኖ እጁን ሰደደ፤ከጥልቅ ውኃ ውስጥም አወጣኝ። |
ከብርቱ ጠላቴ አዳነኝ፤ከእኔ ይበልጥ ብርቱዎች ከሆኑት፣ ከሚጠሉኝ ሰዎች ታደገኝ። |
ችግር ላይ በወደቅኩበት ቀን ተነሱብኝ፤ይሖዋ ግን ድጋፍ ሆነልኝ። |
ከዚያም ደህንነት ወደማገኝበት ስፍራ አመጣኝ፤በእኔ ስለተደሰተ ታደገኝ። |
ይሖዋ እንደ ጽድቄ ወሮታ ይከፍለኛል፤እንደ እጄ ንጽሕና ብድራት ይመልስልኛል። |
የይሖዋን መንገድ ጠብቄአለሁና፤አምላኬን በመተው ክፉ ድርጊት አልፈጸምኩም። |
ፍርዱ ሁሉ በፊቴ ነው፤ደንቦቹን ቸል አልልም። |
በፊቱ እንከን የለሽ ሆኜ እኖራለሁ፤ራሴንም ከስህተት እጠብቃለሁ። |
ይሖዋ እንደ ጽድቄ፣በፊቱ ንጹሕ እንደሆኑት እጆቼ ብድራት ይመልስልኝ። |
ታማኝ ለሆነ ሰው ታማኝ ትሆናለህ፤እንከን የለሽ ለሆነ ሰው እንከን የለሽ ትሆናለህ፤ |
ከንጹሕ ሰው ጋር ንጹሕ ሆነህ ትገኛለህ፤ጠማማ ለሆነ ሰው ግን ብልህ መሆንህን ታሳያለህ። |
ችግረኞችን ታድናለህና፤ትዕቢተኛውን ግን ታዋርዳለህ። |
ይሖዋ ሆይ፣ መብራቴን የምታበራው አንተ ነህና፤አምላኬ ሆይ፣ ጨለማዬን ብርሃን የምታደርገው አንተ ነህ። |
በአንተ እርዳታ ወራሪውን ቡድን መጋፈጥ እችላለሁ፤በአምላክ ኃይል ቅጥር መውጣት እችላለሁ። |
የእውነተኛው አምላክ መንገድ ፍጹም ነው፤የይሖዋ ቃል የነጠረ ነው። እሱ መጠጊያ ለሚያደርጉት ሁሉ ጋሻቸው ነው። |
ደግሞስ ከይሖዋ ሌላ አምላክ ማን ነው? ከአምላካችንስ ሌላ ዓለት ማን ነው? |
ብርታትን የሚያስታጥቀኝ እውነተኛው አምላክ ነው፤መንገዴንም ፍጹም ያደርግልኛል። |
እግሮቼን እንደ ዋልያ እግሮች ያደርጋል፤በከፍታ ቦታዎች ላይ ያቆመኛል። |
እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናል፤ክንዶቼ የመዳብ ደጋን ማጠፍ ይችላሉ። |
የመዳን ጋሻህን ትሰጠኛለህ፤ቀኝ እጅህ ይደግፈኛል፤ትሕትናህም ታላቅ ያደርገኛል። |
ለእርምጃዬ መንገዱን ታሰፋልኛለህ፤እግሮቼ አያዳልጣቸውም። |
ጠላቶቼን አሳድጄ እደርስባቸዋለሁ፤ተጠራርገው እስኪጠፉ ድረስ ወደ ኋላ አልመለስም። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.