text
stringlengths
4
267
ጥርሶቜሜ ገና ተሞልተውናታጥበው እንደወጡ፣ሁሉም መንታ መንታ እንደወለዱ ዹበግ መንጋ ና቞ውፀደግሞም ኚመካኚላ቞ው ግልገሉን ያጣ ዚለም።
ኚንፈሮቜሜ እንደ ደማቅ ቀይ ፈትል ና቞ውፀንግግርሜም አስደሳቜ ነው። በመሞፈኛሜ ውስጥ ያሉት ጉንጮቜሜዚተኚፈለ ሮማን ይመስላሉ።
አንገትሜ አንድ ሺህ ጋሻዎቜ፣ይኞውም ኃያላን ሰዎቜ ዹሚይዟቾው ክብ ጋሻዎቜ ሁሉ ዚተንጠለጠሉበትንናበንብርብር ድንጋዮቜ ዚተገነባውንዚዳዊት ማማ ይመስላል።
ሁለቱ ጡቶቜሜበአበቊቜ መካኚል ዚተሰማሩ፣መንታ ዹሆኑ ሁለት ዚሜዳ ፍዹል ግልገሎቜን ይመስላሉ።”
“ዹቀኑ ነፋስ መንፈስ ኚመጀመሩና ጥላው ኚመሞሹ በፊትወደ ኚርቀው ተራራናወደ ነጭ ዕጣኑ ኮሚብታ እሄዳለሁ።”
“ፍቅሬ ሆይ፣ ሁለንተናሜ ውብ ነውፀእንኚንም ዚለብሜም።
ሙሜራዬ ሆይ፣ ተያይዘን ኚሊባኖስ እንሂድፀአዎ፣ ኚሊባኖስ አብሚን እንሂድ። ኹአማና አናት፣ኚሰኒር ጫፍ፣ ኹሄርሞን አናት፣ኚአንበሳ ዋሻዎቜ፣ ኚነብር ተራሮቜ ውሚጂ።
እህ቎፣ ሙሜራዬ ሆይ፣ ልቀን ማርኚሜዋልፀበአንድ አፍታ እይታሜ፣ኚሐብልሜ ዶቃዎቜ በአንዱ ልቀን ማርኚሜዋል።
እህ቎፣ ሙሜራዬ ሆይ፣ ዹፍቅር መግለጫዎቜሜ እንዎት ደስ ያሰኛሉ! ዹፍቅር መግለጫሜ ኹወይን ጠጅ፣ዚሜቶሜም መዓዛ ኚዚትኛውም ዓይነት ቅመም እጅግ ይበልጣል!
ሙሜራዬ ሆይ፣ ኚንፈሮቜሜ ዹማር እንጀራ ወለላ ያንጠባጥባሉ። ኚምላስሜ ሥር ማርና ወተት ይፈልቃልፀዚልብሶቜሜም ጠሹን እንደ ሊባኖስ መዓዛ ነው።
እህ቎፣ ሙሜራዬ፣ ዹተቆለፈ ዚአትክልት ቊታ፣አዎ ዹተቆለፈ ዚአትክልት ቊታ፣ ዚታሞገም ምንጭ ናት።
ቡቃያሜ ሮማንና ምርጥ ፍራፍሬዎቜደግሞም ዹሂና እና ዚናርዶስ ተክሎቜ ዚበቀሉበት ገነት ነውፀ
በተጚማሪም ናርዶስ፣ ሳፍሮን፣ ጠጅ ሣር፣ ቀሚፋ፣ነጭ ዕጣን ዚሚገኝባ቞ው ዚተለያዩ ዛፎቜ፣ ኚርቀ፣ እሬትናሁሉም ዓይነት ምርጥ ሜቶዎቜ ያሉበት ገነት ነው።
አንቺ በአትክልት ቊታ ያለ ምንጭ፣ ንጹሕ ውኃ ዚሚገኝበት ጉድጓድናኚሊባኖስ ዚሚፈስሱ ጅሚቶቜ ነሜ።
ዹሰሜን ነፋስ ሆይ፣ ንቃፀዚደቡብ ነፋስ ሆይ፣ ና። በአትክልት ቊታዬ ላይ ንፈስ። መዓዛውም አካባቢውን ያውደው።” “ውዮ ወደ አትክልት ቊታው ይግባናምርጥ ዚሆኑትን ፍራፍሬዎቜ ይብላ።”
“ኚሎቶቜ ሁሉ እጅግ ዚተዋብሜ ሆይ፣ውድሜ ዚት ሄደ? ለመሆኑ ውድሜ ዹሄደው በዚት በኩል ነው? አብሚንሜ እንፈልገው።”
“ውዮ መንጋውን በአትክልት ቊታዎቹ መካኚል ለማሰማራትናአበቊቜን ለመቅጠፍዹቅመማ ቅመም ተክሎቜ መደብ ወዳለበትወደ አትክልት ቊታው ወርዷል።
እኔ ዹውዮ ነኝፀውዎም ዚእኔ ነው። እሱ መንጋውን በአበቊቜ መካኚል እዚጠበቀ ነው።”
“ፍቅሬ ሆይ፣ አንቺ እንደ ቲርጻ ቆንጆ ነሜፀእንደ ኢዚሩሳሌምም ውብ ነሜፀበዓርማዎቻ቞ው ዙሪያ እንደተሰለፉ ወታደሮቜ እጅግ ታምሪያለሜ።
ስሜ቎ን አውኚውታልና፣ዓይኖቜሜን ኚእኔ ላይ አንሺ። ፀጉርሜ ኚጊልያድ እዚተግተለተለ እንደሚወርድዚፍዚል መንጋ ነው።
ጥርሶቜሜ ታጥበው እንደወጡ፣ሁሉም መንታ መንታ እንደወለዱዚበግ መንጋ ና቞ውፀኚመካኚላ቞ውም ግልገሉን ያጣ ዚለም።
በመሞፈኛሜ ውስጥ ያሉት ጉንጮቜሜዚተኚፈለ ሮማን ይመስላሉ።
እርግጥ 60 ንግሥቶቜ፣80 ቁባቶቜናቁጥራ቞ው በውል ዚማይታወቅ ቆነጃጅት ሊኖሩ ይቜላሉ።
እንኚን ዚሌለባት ርግቀ ግን አንድ ብቻ ናት። እሷ ለእናቷ ብርቅዬ ልጅ ናት። በወለደቻት ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ናት። ሎቶቜ ልጆቜ አይተዋት ‘ዚታደልሜ ነሜ’ ይሏታልፀንግሥቶቜና ቁባቶቜም ያወድሷታል።
‘እንደ ማለዳ ወጋገን ዚምታበራ፣እንደ ሙሉ ጹሹቃ ውብ ዚሆነቜ፣እንደ ፀሐይ ብርሃን ዚጠራቜ፣በዓርማዎቻ቞ው ዙሪያ እንደተሰለፉ ወታደሮቜ እጅግ ዚምታምሚው ይህቜ ሎት ማን ናት?’”
“በሾለቆው ውስጥ ያቆጠቆጡትን ተክሎቜ ለማዚት፣ደግሞም ወይኑ ለምልሞ፣ዚሮማን ዛፎቹም አብበው እንደሆነ ለመመልኚትዚገውዝ ዛፎቜ ወዳሉበት ወደ አትክልት ቊታው ወሚድኩ።
ምንም ሳይታወቀኝምኞ቎ ዚተኚበሩ ወገኖቌዚያዟ቞ው ሠሚገሎቜ ወዳሉበት ወሰደኝ።”
“አንቺ ሱላማዊት፣ ተመለሺፀ ተመለሺ! እናይሜ ዘንድተመለሺፀ ተመለሺ!” “በሱላማዊቷ ላይ ዚምታፈጡት ለምንድን ነው?” “እሷ ዹመሃናይምን ጭፈራ ትመስላለቜ!”
“ምነው አንተ፣ ዚእና቎ን ጡት እንደጠባ፣እንደ ወንድሜ በሆንክ! እንዲህ ቢሆን ኖሮ ውጭ ሳገኝህ በሳምኩህ ነበርፀማንም ባልናቀኝ ነበር።
እኔም ወዳስተማሚቜኝወደ እና቎ ቀት በወሰድኩህናወደዚያ ባስገባሁህ ነበር። ትጠጣው ዘንድ ቅመም ዚተጚመሚበት ወይን ጠጅናዚሮማን ጭማቂ በሰጠሁህ ነበር።
ግራ እጁን በተንተራስኩ፣ቀኝ እጁም ባቀፈኝ ነበር።
ዚኢዚሩሳሌም ሎቶቜ ልጆቜ ሆይ፣ በራሱ እስኪነሳሳ ድሚስ ፍቅርን በውስጀ እንዳትቀሰቅሱ ወይም እንዳታነሳሱ አምላቜኋለሁ።”
“ውዷን ደገፍ ብላኚምድሚ በዳ ዚምትመጣው ይህቜ ማን ናት?” “ኹፖም ዛፍ ሥር ቀሰቀስኩህ። በዚያ እናትህ አንተን ለመውለድ አማጠቜ። በዚያም ወላጅ እናትህ ምጥ ይዟት ነበር።
እንደ ማኅተም በልብህ፣እንደ ማኅተም በክንድህ አስቀምጠኝፀፍቅር እንደ ሞት ዚበሚታ ነውናፀታማኝነትም እንደ መቃብር ጜኑ ነውፀ ዹፍቅር ወላፈን ዚእሳት ወላፈን ነውፀ ዚያህም ነበልባል ነው።
ጎርፍ ፍቅርን ሊያጠፋው አይቜልምፀወንዞቜም ጠራርገው ሊወስዱት አይቜሉም። አንድ ሰው ለፍቅር ሲል ዚቀቱን ሀብት ሁሉ ለመስጠት ቢያቀርብሰዎቜ በጣም ይንቁበታል።”
“ገና ጡት ያላወጣቜትንሜ እህት አለቜን። እሷን በሚጠይቁን ቀንለእህታቜን ምን ብናደርግ ይሻላል?”
“እሷ ቅጥር ብትሆንበላይዋ ላይ ዚብር ጉልላት እንሠራለንፀበር ብትሆን ግንኹአርዘ ሊባኖስ በተሠራ ሳንቃ እናሜጋታለን።”
“እኔ ቅጥር ነኝፀጡቶቌም እንደ ማማ ና቞ው። በእሱም ፊትሰላም እንዳገኘቜ ሎት ሆንኩ።
ሰለሞን በበዓልሃሞን ዹወይን እርሻ ነበሚው። እሱም ዹወይን እርሻውን ለጠባቂዎቜ በአደራ ሰጠ። እያንዳንዳ቞ውም ለሚያገኙት ፍሬ አንድ ሺህ ዚብር ሰቅል ያመጡ ነበር።
ዚራሎ ዹሆነ ዹወይን እርሻ አለኝ። ሰለሞን ሆይ፣ አንድ ሺው ዚብር ሰቅል ዹአንተ ነውፀሁለት መቶው ደግሞ ፍሬውን ለሚጠብቁት ነው።”
“አንቺ በአትክልት ቊታዎቹ ዚምትኖሪ ሆይ፣ጓደኞቌ ድምፅሜን ያዳምጣሉ። እስቲ እኔም ልስማው።”
“ውዮ ሆይ፣ ቶሎ ናፀእንደ ሜዳ ፍዹልወይም ዹቅመም ተክሎቜ በሚበቅሉባ቞ው ተራሮቜ ላይ እንዳለዚአጋዘን ግልገል ፍጠን።”
አሁን ግን፣ ያዕቆብ ሆይ ፈጣሪህ፣እስራኀልም ሆይ ዚሠራህ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እኔ ተቀዥቌሃለሁና አትፍራ። በስምህ ጠርቌሃለሁ። አንተ ዚእኔ ነህ።
በውኃዎቜ መካኚል ስታልፍ እኔ ኹአንተ ጋር እሆናለሁፀበወንዞቜም መካኚል ስትሻገር አያሰምጡህም። በእሳት መካኚል ስትሄድ አትቃጠልምፀነበልባሉም አይፈጅህም።
እኔ ይሖዋ አምላክህ፣ዚእስራኀል ቅዱስ፣ አዳኝህ ነኝና። ግብፅን ለአንተ ቀዛ አድርጌ ሰጥቻለሁፀኢትዮጵያንና ሎባን በአንተ ምትክ ሰጥቻለሁ።
አንተ በዓይኔ ፊት ውድ ሆነሃልናፀዚተኚበርክም ነህፀ እኔም ወድጄሃለሁ። ስለዚህ በአንተ ምትክ ሰዎቜን፣በሕይወትህም ምትክ ብሔራትን እሰጣለሁ።
እኔ ኹአንተ ጋር ነኝና አትፍራ። ዘርህን ኚምሥራቅ አመጣለሁፀኚምዕራብም እሰበስብሃለሁ።
ሰሜንን ‘ልቀቃቾው!’ እለዋለሁፀ ደቡብንም እንዲህ እለዋለሁፊ ‘አታግታ቞ው። ወንዶቜ ልጆቌን ኚሩቅ፣ ሎቶቜ ልጆቌንም ኚምድር ዳርቻ አምጣፀ
በስሜ ዚተጠራውን፣ለክብሬም ዚፈጠርኩትን፣ዚሠራሁትንና ያበጀሁትን ሁሉ አምጣ።’
ዓይን ቢኖራ቞ውም ዕውር ዚሆኑትን፣ጆሮ ቢኖራ቞ውም ደንቆሮ ዚሆኑትን ሰዎቜ አውጣ።
ብሔራት ሁሉ አንድ ቊታ ይሰብሰቡፀሕዝቊቜም በአንድነት ይሰብሰቡ። ኚመካኚላ቞ው ይህን ሊናገር ዚሚቜል ማን አለ? ወይስ ዚመጀመሪያዎቹን ነገሮቜ ሊነግሩን ይቜላሉ? ትክክል መሆናቾውን እንዲያሚጋግጡ ምሥክሮቻ቞ውን ያቅርቡፀወይም ሰምተው ‘ይህ እውነት ነው!’ ይበሉ።”
“እናንተ ምሥክሮቌ ናቜሁ” ይላል ይሖዋፀ“አዎ፣ ዚመሚጥኩት አገልጋዬ ናቜሁፀይህም ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድደግሞም እኔ ምንጊዜም ያው እንደሆንኩ ታስተውሉ ዘንድ ነው። ኚእኔ በፊት አምላክ አልተሠራምፀኚእኔም በኋላ ዚለም።
እኔ፣ አዎ እኔ ይሖዋ ነኝፀ ኚእኔ በቀር አዳኝ ዚለም።”
“በመካኚላቜሁ ባዕድ አምላክ ባልነበሚበት ጊዜዚተናገርኩት፣ ያዳንኩትና ያሳወቅኩት እኔ ነኝ። ስለዚህ እናንተ ምሥክሮቌ ናቜሁ” ይላል ይሖዋፀ “እኔም አምላክ ነኝ።
ደግሞም እኔ ምንጊዜም ያው ነኝፀኚእጄም አንዳቜ ነገር ሊነጥቅ ዚሚቜል ዚለም። እርምጃ በምወስድበት ጊዜ ሊያግድ ዚሚቜል ማን ነው?”
እናንተን ዚሚቀዠው ዚእስራኀል ቅዱስ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ለእናንተ ስል ወደ ባቢሎን እሰዳለሁፀ ዚበሮቹንም መቀርቀርያዎቜ ሁሉ እጥላለሁፀበመርኚቊቻ቞ው ላይ ያሉት ኚለዳውያንም በጭንቀት ይጮኻሉ።
እኔ ይሖዋ ዚእናንተ ቅዱስ፣ ዚእስራኀል ፈጣሪ፣ ንጉሣቜሁ ነኝ።”
ይሖዋ ይኞውምበባሕር መካኚል መንገድ ዚሚያበጀው፣በሚናወጡ ውኃዎቜም መካኚል ጎዳና ዚሚዘሚጋው፣
ዹጩር ሠሹገላውንና ፈሚሱን፣ሠራዊቱንና ኃያላን ተዋጊዎቹን በአንድነት ዚሚያወጣው አምላክ እንዲህ ይላል፩ “ይተኛሉፀ አይነሱምም። እንደሚነድ ዹጧፍ ክር ተዳፍነው ይጠፋሉ።”
“ዚቀድሞዎቹን ነገሮቜ አታስታውሱፀያለፈውንም ነገር አታውጠንጥኑ።
እነሆ፣ አዲስ ነገር አደርጋለሁፀአሁንም እንኳ መኹናወን ጀምሯል። ይህን አታስተውሉም? በምድሚ በዳ መንገድ አዘጋጃለሁፀበበሚሃም ወንዞቜን አፈልቃለሁ።
ዚዱር አውሬ፣ ቀበሮዎቜናሰጎኖቜ ያኚብሩኛልፀበምድሚ በዳ ውኃ፣በበሚሃም ወንዞቜን እሰጣለሁናፀይህን ዹማደርገው ዚመሚጥኩት ሕዝቀ እንዲጠጣ፣
ለራሎ ዚሠራሁትም ሕዝብ እንዲጎነጭ ነውፀሕዝቀ ውዳሎዬን እንዲያውጅ ይህን አደርጋለሁ።
እስራኀል ሆይ፣ አንተ ግን ዚእኔ ነገር ስለታኚተህ፣ያዕቆብ ሆይ፣ አልጠራኞኝም።
ሙሉ በሙሉ ዹሚቃጠል መባ ለማቅሚብ በግ አላመጣህልኝምፀወይም መሥዋዕቶቜ በማቅሚብ አላኚበርኚኝም። ስጊታ እንድታመጣልኝ አላስገደድኩህምፀነጭ ዕጣን አቅርብልኝ ብዬም አላሰለ቞ሁህም።
በገንዘብህ ጠጅ ሣር አልገዛህልኝምፀበመሥዋዕቶቜህም ስብ አላጠገብኚኝም። ኹዚህ ይልቅ ኃጢአትህን አሞክመኞኛልፀበምትፈጜማ቞ውም በደሎቜ አሰልቜተኞኛል።
ስለ ራሎ ስል በደልህን እኔ ራሎ እደመስሰዋለሁፀኃጢአትህንም አላስታውስም።
እስቲ አስታውሰኝፀ ጉዳያቜንን አቅርበን እንሟገትፀትክክለኛ መሆንህን ለማሚጋገጥ በበኩልህ ጉዳይህን ተናገር።
ዚመጀመሪያው አባትህ ኃጢአት ሠርቷልፀዚገዛ ቃል አቀባዮቜህም በእኔ ላይ ዓምፀዋል።
ስለዚህ በቅዱሱ ስፍራ ዚሚገኙትን መኳንንት አሚክሳለሁፀያዕቆብንም ለጥፋት አሳልፌ እሰጠዋለሁፀእስራኀልንም ለስድብ እዳርገዋለሁ።
እነሆ፣ ደግፌ ዚያዝኩት፣ ደስ ዚምሰኝበትና ዚመሚጥኩት አገልጋዬ! መንፈሮን በእሱ ላይ አድርጌአለሁፀእሱ ለብሔራት ፍትሕን ያመጣል።
አይጮኜም ወይም ድምፁን ኹፍ አያደርግምፀድምፁንም በጎዳና ላይ አያሰማም።
ዹተቀጠቀጠን ሾምበቆ አይሰብርምፀዚሚጚስንም ዹጧፍ ክር አያጠፋም። ፍትሕን በታማኝነት ያመጣል።
እሱ ፍትሕን በምድር ላይ እስኪያሰፍን ድሚስ አይሰበርም ወይም ብርሃኑ አይደክምምፀደሎቶቜም ሕጉን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
ሰማያትን ዹፈጠሹውና ዚዘሚጋው፣ምድርንና በውስጧ ያሉትን ነገሮቜ ሁሉ ዚሠራው፣በላይዋም ለሚኖሩ ሰዎቜ እስትንፋስን፣በእሷም ላይ ለሚመላለሱ መንፈስን ዚሰጠውእውነተኛው አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩
“እኔ ይሖዋ በጜድቅ ጠርቌሃለሁፀእጅህን ይዣለሁ። እጠብቅሃለሁፀ እንዲሁም ለሰዎቜ ቃል ኪዳን፣ለብሔራትም ብርሃን አድርጌ እሰጥሃለሁፀ
አንተም ዹዓይነ ስውራንን ዓይን ታበራለህፀእስሚኛውን ኹወህኒ ቀት፣በጚለማ ውስጥ ዚተቀመጡትንም ኚእስር ቀት ታወጣለህ።
እኔ ይሖዋ ነኝ። ስሜ ይህ ነውፀክብሬን ለሌላ፣ምስጋናዬንም ለተቀሚጹ ምስሎቜ አልሰጥም።
እነሆ፣ ዚቀደሙት ነገሮቜ ተፈጜመዋልፀአሁን ደግሞ አዳዲስ ነገሮቜን እናገራለሁ። ገና ኚመኚሰታ቞ው በፊት ስለ እነሱ እነግራቜኋለሁ።”
እናንተ በባሕር ላይና በውስጡ ባሉት ፍጥሚታት መካኚል ዚምትጓዙ፣እናንተ ደሎቶቜና በእነሱ ላይ ዚምትኖሩ ሁሉ፣ለይሖዋ አዲስ መዝሙር ዘምሩፀኚምድር ዳርቻም ውዳሎውን አሰሙ።
ምድሚ በዳውና በዚያ ያሉ ኚተሞቜ፣ቄዳር ያለቜባ቞ውም ሰፈሮቜ ድምፃ቞ውን ኹፍ ያድርጉ። ዓለታማ በሆኑ ቊታዎቜ ዚሚኖሩ ሰዎቜ በደስታ እልል ይበሉፀበተራሮቜም አናት ላይ ሆነው ይጩኹ።
ለይሖዋ ክብር ይስጡፀበደሎቶቜም ላይ ውዳሎውን ያውጁ።
ይሖዋ እንደ ኃያል ሰው ይወጣል። እንደ ተዋጊ ቅንዓቱን ይቀሰቅሳል። ይጮኻልፀ አዎ፣ ቀሚርቶ ያሰማልፀኚጠላቶቹ ይበልጥ ኃያል መሆኑን ያሳያል።
“ለሹጅም ጊዜ ዝም አልኩ። ጞጥ ብዬ ቆዚሁፀ ራሎንም ገታሁ። ምጥ እንደያዛት ሎትእቃትታለሁ፣ አለኚልካለሁ እንዲሁም ቁና ቁና እተነፍሳለሁ።
ተራሮቜንና ኮሚብቶቜን አወድማለሁፀደግሞም በላያ቞ው ላይ ያለውን ተክል ሁሉ አደርቃለሁ። ወንዞቜን ደሎቶቜ አደርጋለሁፀቄጠማ ዚሞላባ቞ውንም ኩሬዎቜ አደርቃለሁ።
ዓይነ ስውራንን በማያውቁት መንገድ እመራ቞ዋለሁፀባልለመዱት ጎዳናም እንዲሄዱ አደርጋ቞ዋለሁ። ጹለማውን በፊታ቞ው ብርሃን፣ወጣ ገባ ዹሆነውንም ምድር ደልዳላ ሜዳ አደርጋለሁ። ይህን አደርግላ቞ዋለሁፀ ደግሞም አልተዋ቞ውም።”
በተቀሹጾ ምስል ዚሚታመኑ፣ኚብሚት ዚተሠሩትን ሐውልቶቜ “እናንተ አምላኮቻቜን ናቜሁ” ዚሚሉወደ ኋላ ይመለሳሉፀ እጅግም ያፍራሉ።
እናንተ ደንቆሮዎቜ፣ ስሙፀእናንተ ዕውሮቜ እዩፀ ተመልኚቱም።
ኚአገልጋዬ በቀር ዚታወሚ፣እንደምልኚው መልእክተኛዬም ደንቆሮ ዹሆነ ማን አለ? ብድራት እንደተኚፈለው ሰው ዕውር ዹሆነወይም እንደ ይሖዋ አገልጋይ ዚታወሚ ማን ነው?
ብዙ ነገሮቜ ብታዩም ልብ ዚምትሉት ነገር ዚለም። ጆሮዎቻቜሁን ብትኚፍቱም ምንም አትሰሙም።
ይሖዋ ለጜድቁ ሲልሕጉን ታላቅና ክብራማ በማድሚግ ደስ ተሰኝቷል።
ይህ ሕዝብ ግን ዹተበዘበዘና ዚተዘሚፈ ነውፀሁሉም ጉድጓድ ውስጥ ተይዘዋልፀ በእስር ቀትም ተሰውሚዋል። ዚሚታደጋ቞ው በሌለበት ተበዝብዘዋልፀ“መልሷ቞ው!” ዹሚል በሌለበትም ተዘርፈዋል።
ኚእናንተ መካኚል ይህን ዹሚሰማ ማን ነው? በትኩሚት ዚሚያዳምጥና ለወደፊቱ ጊዜ ትምህርት ዚሚወስድ ማን ነው?
ያዕቆብን ለዘሚፋ፣እስራኀልንም ለበዝባዊቜ አሳልፎ ዹሰጠ ማን ነው? በእሱ ላይ ኃጢአት በመፈጾም ዹበደልነው ይሖዋ አይደለም? እነሱ በመንገዱ ለመሄድ አልፈለጉምፀሕጉንም አይታዘዙም።
ስለዚህ ንዎቱን፣ ቁጣውንና ዚጊርነቱን መዓትበእስራኀል ላይ አፈሰሰ። ዚጊርነቱም እሳት በዙሪያው ያለውን ሁሉ በላውፀ እሱ ግን አላስተዋለም። አቃጠለውፀ እሱ ግን ጚርሶ ልብ አላለም።
“እናንተ ደሎቶቜ፣ ዝም ብላቜሁ አዳምጡኝፀብሔራትም ኃይላቾውን ያድሱ። በመጀመሪያ ይቅሚቡፀ ኚዚያም ይናገሩ። ለፍርድ አንድ ላይ እንሰብሰብ።
ብሔራትን አሳልፎ ይሰጠውናነገሥታትን ድል ይነሳ ዘንድኚፀሐይ መውጫ አንዱን ያስነሳው፣በጜድቅ ወደ እግሩ ዚጠራው ማን ነው? በሰይፉ ፊት አቧራ ዚሚያደርጋ቞ው፣በቀስቱ ፊት በነፋስ እንደተወሰደ ገለባ ዚሚያደርጋ቞ው ማን ነው?
እግሩ ባልሚገጠው መንገድ በመጓዝምንም ነገር ሳያግደው እነሱን ያሳድዳል።
ይህን ዚሠራና ያደሚገ፣ትውልዶቹንም ኚመጀመሪያ አንስቶ ዚጠራ ማን ነው? እኔ ይሖዋ ዚመጀመሪያው ነኝፀኚመጚሚሻዎቹም ጋር እኔ ያው ነኝ።”
ደሎቶቜ አይተው ፈሩ። ዚምድር ዳርቻዎቜ ተንቀጠቀጡ። ቀሚቡፀ ወደ ፊትም መጡ።