text
stringlengths
4
267
ጥርሶችሽ ገና ተሸልተውናታጥበው እንደወጡ፣ሁሉም መንታ መንታ እንደወለዱ የበግ መንጋ ናቸው፤ደግሞም ከመካከላቸው ግልገሉን ያጣ የለም።
ከንፈሮችሽ እንደ ደማቅ ቀይ ፈትል ናቸው፤ንግግርሽም አስደሳች ነው። በመሸፈኛሽ ውስጥ ያሉት ጉንጮችሽየተከፈለ ሮማን ይመስላሉ።
አንገትሽ አንድ ሺህ ጋሻዎች፣ይኸውም ኃያላን ሰዎች የሚይዟቸው ክብ ጋሻዎች ሁሉ የተንጠለጠሉበትንናበንብርብር ድንጋዮች የተገነባውንየዳዊት ማማ ይመስላል።
ሁለቱ ጡቶችሽበአበቦች መካከል የተሰማሩ፣መንታ የሆኑ ሁለት የሜዳ ፍየል ግልገሎችን ይመስላሉ።”
“የቀኑ ነፋስ መንፈስ ከመጀመሩና ጥላው ከመሸሹ በፊትወደ ከርቤው ተራራናወደ ነጭ ዕጣኑ ኮረብታ እሄዳለሁ።”
“ፍቅሬ ሆይ፣ ሁለንተናሽ ውብ ነው፤እንከንም የለብሽም።
ሙሽራዬ ሆይ፣ ተያይዘን ከሊባኖስ እንሂድ፤አዎ፣ ከሊባኖስ አብረን እንሂድ። ከአማና አናት፣ከሰኒር ጫፍ፣ ከሄርሞን አናት፣ከአንበሳ ዋሻዎች፣ ከነብር ተራሮች ውረጂ።
እህቴ፣ ሙሽራዬ ሆይ፣ ልቤን ማርከሽዋል፤በአንድ አፍታ እይታሽ፣ከሐብልሽ ዶቃዎች በአንዱ ልቤን ማርከሽዋል።
እህቴ፣ ሙሽራዬ ሆይ፣ የፍቅር መግለጫዎችሽ እንዴት ደስ ያሰኛሉ! የፍቅር መግለጫሽ ከወይን ጠጅ፣የሽቶሽም መዓዛ ከየትኛውም ዓይነት ቅመም እጅግ ይበልጣል!
ሙሽራዬ ሆይ፣ ከንፈሮችሽ የማር እንጀራ ወለላ ያንጠባጥባሉ። ከምላስሽ ሥር ማርና ወተት ይፈልቃል፤የልብሶችሽም ጠረን እንደ ሊባኖስ መዓዛ ነው።
እህቴ፣ ሙሽራዬ፣ የተቆለፈ የአትክልት ቦታ፣አዎ የተቆለፈ የአትክልት ቦታ፣ የታሸገም ምንጭ ናት።
ቡቃያሽ ሮማንና ምርጥ ፍራፍሬዎችደግሞም የሂና እና የናርዶስ ተክሎች የበቀሉበት ገነት ነው፤
በተጨማሪም ናርዶስ፣ ሳፍሮን፣ ጠጅ ሣር፣ ቀረፋ፣ነጭ ዕጣን የሚገኝባቸው የተለያዩ ዛፎች፣ ከርቤ፣ እሬትናሁሉም ዓይነት ምርጥ ሽቶዎች ያሉበት ገነት ነው።
አንቺ በአትክልት ቦታ ያለ ምንጭ፣ ንጹሕ ውኃ የሚገኝበት ጉድጓድናከሊባኖስ የሚፈስሱ ጅረቶች ነሽ።
የሰሜን ነፋስ ሆይ፣ ንቃ፤የደቡብ ነፋስ ሆይ፣ ና። በአትክልት ቦታዬ ላይ ንፈስ። መዓዛውም አካባቢውን ያውደው።” “ውዴ ወደ አትክልት ቦታው ይግባናምርጥ የሆኑትን ፍራፍሬዎች ይብላ።”
“ከሴቶች ሁሉ እጅግ የተዋብሽ ሆይ፣ውድሽ የት ሄደ? ለመሆኑ ውድሽ የሄደው በየት በኩል ነው? አብረንሽ እንፈልገው።”
“ውዴ መንጋውን በአትክልት ቦታዎቹ መካከል ለማሰማራትናአበቦችን ለመቅጠፍየቅመማ ቅመም ተክሎች መደብ ወዳለበትወደ አትክልት ቦታው ወርዷል።
እኔ የውዴ ነኝ፤ውዴም የእኔ ነው። እሱ መንጋውን በአበቦች መካከል እየጠበቀ ነው።”
“ፍቅሬ ሆይ፣ አንቺ እንደ ቲርጻ ቆንጆ ነሽ፤እንደ ኢየሩሳሌምም ውብ ነሽ፤በዓርማዎቻቸው ዙሪያ እንደተሰለፉ ወታደሮች እጅግ ታምሪያለሽ።
ስሜቴን አውከውታልና፣ዓይኖችሽን ከእኔ ላይ አንሺ። ፀጉርሽ ከጊልያድ እየተግተለተለ እንደሚወርድየፍየል መንጋ ነው።
ጥርሶችሽ ታጥበው እንደወጡ፣ሁሉም መንታ መንታ እንደወለዱየበግ መንጋ ናቸው፤ከመካከላቸውም ግልገሉን ያጣ የለም።
በመሸፈኛሽ ውስጥ ያሉት ጉንጮችሽየተከፈለ ሮማን ይመስላሉ።
እርግጥ 60 ንግሥቶች፣80 ቁባቶችናቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ቆነጃጅት ሊኖሩ ይችላሉ።
እንከን የሌለባት ርግቤ ግን አንድ ብቻ ናት። እሷ ለእናቷ ብርቅዬ ልጅ ናት። በወለደቻት ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ናት። ሴቶች ልጆች አይተዋት ‘የታደልሽ ነሽ’ ይሏታል፤ንግሥቶችና ቁባቶችም ያወድሷታል።
‘እንደ ማለዳ ወጋገን የምታበራ፣እንደ ሙሉ ጨረቃ ውብ የሆነች፣እንደ ፀሐይ ብርሃን የጠራች፣በዓርማዎቻቸው ዙሪያ እንደተሰለፉ ወታደሮች እጅግ የምታምረው ይህች ሴት ማን ናት?’”
“በሸለቆው ውስጥ ያቆጠቆጡትን ተክሎች ለማየት፣ደግሞም ወይኑ ለምልሞ፣የሮማን ዛፎቹም አብበው እንደሆነ ለመመልከትየገውዝ ዛፎች ወዳሉበት ወደ አትክልት ቦታው ወረድኩ።
ምንም ሳይታወቀኝምኞቴ የተከበሩ ወገኖቼየያዟቸው ሠረገሎች ወዳሉበት ወሰደኝ።”
“አንቺ ሱላማዊት፣ ተመለሺ፤ ተመለሺ! እናይሽ ዘንድተመለሺ፤ ተመለሺ!” “በሱላማዊቷ ላይ የምታፈጡት ለምንድን ነው?” “እሷ የመሃናይምን ጭፈራ ትመስላለች!”
“ምነው አንተ፣ የእናቴን ጡት እንደጠባ፣እንደ ወንድሜ በሆንክ! እንዲህ ቢሆን ኖሮ ውጭ ሳገኝህ በሳምኩህ ነበር፤ማንም ባልናቀኝ ነበር።
እኔም ወዳስተማረችኝወደ እናቴ ቤት በወሰድኩህናወደዚያ ባስገባሁህ ነበር። ትጠጣው ዘንድ ቅመም የተጨመረበት ወይን ጠጅናየሮማን ጭማቂ በሰጠሁህ ነበር።
ግራ እጁን በተንተራስኩ፣ቀኝ እጁም ባቀፈኝ ነበር።
የኢየሩሳሌም ሴቶች ልጆች ሆይ፣ በራሱ እስኪነሳሳ ድረስ ፍቅርን በውስጤ እንዳትቀሰቅሱ ወይም እንዳታነሳሱ አምላችኋለሁ።”
“ውዷን ደገፍ ብላከምድረ በዳ የምትመጣው ይህች ማን ናት?” “ከፖም ዛፍ ሥር ቀሰቀስኩህ። በዚያ እናትህ አንተን ለመውለድ አማጠች። በዚያም ወላጅ እናትህ ምጥ ይዟት ነበር።
እንደ ማኅተም በልብህ፣እንደ ማኅተም በክንድህ አስቀምጠኝ፤ፍቅር እንደ ሞት የበረታ ነውና፤ታማኝነትም እንደ መቃብር ጽኑ ነው፤ የፍቅር ወላፈን የእሳት ወላፈን ነው፤ የያህም ነበልባል ነው።
ጎርፍ ፍቅርን ሊያጠፋው አይችልም፤ወንዞችም ጠራርገው ሊወስዱት አይችሉም። አንድ ሰው ለፍቅር ሲል የቤቱን ሀብት ሁሉ ለመስጠት ቢያቀርብሰዎች በጣም ይንቁበታል።”
“ገና ጡት ያላወጣችትንሽ እህት አለችን። እሷን በሚጠይቁን ቀንለእህታችን ምን ብናደርግ ይሻላል?”
“እሷ ቅጥር ብትሆንበላይዋ ላይ የብር ጉልላት እንሠራለን፤በር ብትሆን ግንከአርዘ ሊባኖስ በተሠራ ሳንቃ እናሽጋታለን።”
“እኔ ቅጥር ነኝ፤ጡቶቼም እንደ ማማ ናቸው። በእሱም ፊትሰላም እንዳገኘች ሴት ሆንኩ።
ሰለሞን በበዓልሃሞን የወይን እርሻ ነበረው። እሱም የወይን እርሻውን ለጠባቂዎች በአደራ ሰጠ። እያንዳንዳቸውም ለሚያገኙት ፍሬ አንድ ሺህ የብር ሰቅል ያመጡ ነበር።
የራሴ የሆነ የወይን እርሻ አለኝ። ሰለሞን ሆይ፣ አንድ ሺው የብር ሰቅል የአንተ ነው፤ሁለት መቶው ደግሞ ፍሬውን ለሚጠብቁት ነው።”
“አንቺ በአትክልት ቦታዎቹ የምትኖሪ ሆይ፣ጓደኞቼ ድምፅሽን ያዳምጣሉ። እስቲ እኔም ልስማው።”
“ውዴ ሆይ፣ ቶሎ ና፤እንደ ሜዳ ፍየልወይም የቅመም ተክሎች በሚበቅሉባቸው ተራሮች ላይ እንዳለየአጋዘን ግልገል ፍጠን።”
አሁን ግን፣ ያዕቆብ ሆይ ፈጣሪህ፣እስራኤልም ሆይ የሠራህ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “እኔ ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ። በስምህ ጠርቼሃለሁ። አንተ የእኔ ነህ።
በውኃዎች መካከል ስታልፍ እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤በወንዞችም መካከል ስትሻገር አያሰምጡህም። በእሳት መካከል ስትሄድ አትቃጠልም፤ነበልባሉም አይፈጅህም።
እኔ ይሖዋ አምላክህ፣የእስራኤል ቅዱስ፣ አዳኝህ ነኝና። ግብፅን ለአንተ ቤዛ አድርጌ ሰጥቻለሁ፤ኢትዮጵያንና ሴባን በአንተ ምትክ ሰጥቻለሁ።
አንተ በዓይኔ ፊት ውድ ሆነሃልና፤የተከበርክም ነህ፤ እኔም ወድጄሃለሁ። ስለዚህ በአንተ ምትክ ሰዎችን፣በሕይወትህም ምትክ ብሔራትን እሰጣለሁ።
እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ። ዘርህን ከምሥራቅ አመጣለሁ፤ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ።
ሰሜንን ‘ልቀቃቸው!’ እለዋለሁ፤ ደቡብንም እንዲህ እለዋለሁ፦ ‘አታግታቸው። ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ፣ ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ አምጣ፤
በስሜ የተጠራውን፣ለክብሬም የፈጠርኩትን፣የሠራሁትንና ያበጀሁትን ሁሉ አምጣ።’
ዓይን ቢኖራቸውም ዕውር የሆኑትን፣ጆሮ ቢኖራቸውም ደንቆሮ የሆኑትን ሰዎች አውጣ።
ብሔራት ሁሉ አንድ ቦታ ይሰብሰቡ፤ሕዝቦችም በአንድነት ይሰብሰቡ። ከመካከላቸው ይህን ሊናገር የሚችል ማን አለ? ወይስ የመጀመሪያዎቹን ነገሮች ሊነግሩን ይችላሉ? ትክክል መሆናቸውን እንዲያረጋግጡ ምሥክሮቻቸውን ያቅርቡ፤ወይም ሰምተው ‘ይህ እውነት ነው!’ ይበሉ።”
“እናንተ ምሥክሮቼ ናችሁ” ይላል ይሖዋ፤“አዎ፣ የመረጥኩት አገልጋዬ ናችሁ፤ይህም ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድደግሞም እኔ ምንጊዜም ያው እንደሆንኩ ታስተውሉ ዘንድ ነው። ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም፤ከእኔም በኋላ የለም።
እኔ፣ አዎ እኔ ይሖዋ ነኝ፤ ከእኔ በቀር አዳኝ የለም።”
“በመካከላችሁ ባዕድ አምላክ ባልነበረበት ጊዜየተናገርኩት፣ ያዳንኩትና ያሳወቅኩት እኔ ነኝ። ስለዚህ እናንተ ምሥክሮቼ ናችሁ” ይላል ይሖዋ፤ “እኔም አምላክ ነኝ።
ደግሞም እኔ ምንጊዜም ያው ነኝ፤ከእጄም አንዳች ነገር ሊነጥቅ የሚችል የለም። እርምጃ በምወስድበት ጊዜ ሊያግድ የሚችል ማን ነው?”
እናንተን የሚቤዠው የእስራኤል ቅዱስ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ለእናንተ ስል ወደ ባቢሎን እሰዳለሁ፤ የበሮቹንም መቀርቀርያዎች ሁሉ እጥላለሁ፤በመርከቦቻቸው ላይ ያሉት ከለዳውያንም በጭንቀት ይጮኻሉ።
እኔ ይሖዋ የእናንተ ቅዱስ፣ የእስራኤል ፈጣሪ፣ ንጉሣችሁ ነኝ።”
ይሖዋ ይኸውምበባሕር መካከል መንገድ የሚያበጀው፣በሚናወጡ ውኃዎችም መካከል ጎዳና የሚዘረጋው፣
የጦር ሠረገላውንና ፈረሱን፣ሠራዊቱንና ኃያላን ተዋጊዎቹን በአንድነት የሚያወጣው አምላክ እንዲህ ይላል፦ “ይተኛሉ፤ አይነሱምም። እንደሚነድ የጧፍ ክር ተዳፍነው ይጠፋሉ።”
“የቀድሞዎቹን ነገሮች አታስታውሱ፤ያለፈውንም ነገር አታውጠንጥኑ።
እነሆ፣ አዲስ ነገር አደርጋለሁ፤አሁንም እንኳ መከናወን ጀምሯል። ይህን አታስተውሉም? በምድረ በዳ መንገድ አዘጋጃለሁ፤በበረሃም ወንዞችን አፈልቃለሁ።
የዱር አውሬ፣ ቀበሮዎችናሰጎኖች ያከብሩኛል፤በምድረ በዳ ውኃ፣በበረሃም ወንዞችን እሰጣለሁና፤ይህን የማደርገው የመረጥኩት ሕዝቤ እንዲጠጣ፣
ለራሴ የሠራሁትም ሕዝብ እንዲጎነጭ ነው፤ሕዝቤ ውዳሴዬን እንዲያውጅ ይህን አደርጋለሁ።
እስራኤል ሆይ፣ አንተ ግን የእኔ ነገር ስለታከተህ፣ያዕቆብ ሆይ፣ አልጠራኸኝም።
ሙሉ በሙሉ የሚቃጠል መባ ለማቅረብ በግ አላመጣህልኝም፤ወይም መሥዋዕቶች በማቅረብ አላከበርከኝም። ስጦታ እንድታመጣልኝ አላስገደድኩህም፤ነጭ ዕጣን አቅርብልኝ ብዬም አላሰለቸሁህም።
በገንዘብህ ጠጅ ሣር አልገዛህልኝም፤በመሥዋዕቶችህም ስብ አላጠገብከኝም። ከዚህ ይልቅ ኃጢአትህን አሸክመኸኛል፤በምትፈጽማቸውም በደሎች አሰልችተኸኛል።
ስለ ራሴ ስል በደልህን እኔ ራሴ እደመስሰዋለሁ፤ኃጢአትህንም አላስታውስም።
እስቲ አስታውሰኝ፤ ጉዳያችንን አቅርበን እንሟገት፤ትክክለኛ መሆንህን ለማረጋገጥ በበኩልህ ጉዳይህን ተናገር።
የመጀመሪያው አባትህ ኃጢአት ሠርቷል፤የገዛ ቃል አቀባዮችህም በእኔ ላይ ዓምፀዋል።
ስለዚህ በቅዱሱ ስፍራ የሚገኙትን መኳንንት አረክሳለሁ፤ያዕቆብንም ለጥፋት አሳልፌ እሰጠዋለሁ፤እስራኤልንም ለስድብ እዳርገዋለሁ።
እነሆ፣ ደግፌ የያዝኩት፣ ደስ የምሰኝበትና የመረጥኩት አገልጋዬ! መንፈሴን በእሱ ላይ አድርጌአለሁ፤እሱ ለብሔራት ፍትሕን ያመጣል።
አይጮኽም ወይም ድምፁን ከፍ አያደርግም፤ድምፁንም በጎዳና ላይ አያሰማም።
የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፤የሚጨስንም የጧፍ ክር አያጠፋም። ፍትሕን በታማኝነት ያመጣል።
እሱ ፍትሕን በምድር ላይ እስኪያሰፍን ድረስ አይሰበርም ወይም ብርሃኑ አይደክምም፤ደሴቶችም ሕጉን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
ሰማያትን የፈጠረውና የዘረጋው፣ምድርንና በውስጧ ያሉትን ነገሮች ሁሉ የሠራው፣በላይዋም ለሚኖሩ ሰዎች እስትንፋስን፣በእሷም ላይ ለሚመላለሱ መንፈስን የሰጠውእውነተኛው አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦
“እኔ ይሖዋ በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፤እጅህን ይዣለሁ። እጠብቅሃለሁ፤ እንዲሁም ለሰዎች ቃል ኪዳን፣ለብሔራትም ብርሃን አድርጌ እሰጥሃለሁ፤
አንተም የዓይነ ስውራንን ዓይን ታበራለህ፤እስረኛውን ከወህኒ ቤት፣በጨለማ ውስጥ የተቀመጡትንም ከእስር ቤት ታወጣለህ።
እኔ ይሖዋ ነኝ። ስሜ ይህ ነው፤ክብሬን ለሌላ፣ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም።
እነሆ፣ የቀደሙት ነገሮች ተፈጽመዋል፤አሁን ደግሞ አዳዲስ ነገሮችን እናገራለሁ። ገና ከመከሰታቸው በፊት ስለ እነሱ እነግራችኋለሁ።”
እናንተ በባሕር ላይና በውስጡ ባሉት ፍጥረታት መካከል የምትጓዙ፣እናንተ ደሴቶችና በእነሱ ላይ የምትኖሩ ሁሉ፣ለይሖዋ አዲስ መዝሙር ዘምሩ፤ከምድር ዳርቻም ውዳሴውን አሰሙ።
ምድረ በዳውና በዚያ ያሉ ከተሞች፣ቄዳር ያለችባቸውም ሰፈሮች ድምፃቸውን ከፍ ያድርጉ። ዓለታማ በሆኑ ቦታዎች የሚኖሩ ሰዎች በደስታ እልል ይበሉ፤በተራሮችም አናት ላይ ሆነው ይጩኹ።
ለይሖዋ ክብር ይስጡ፤በደሴቶችም ላይ ውዳሴውን ያውጁ።
ይሖዋ እንደ ኃያል ሰው ይወጣል። እንደ ተዋጊ ቅንዓቱን ይቀሰቅሳል። ይጮኻል፤ አዎ፣ ቀረርቶ ያሰማል፤ከጠላቶቹ ይበልጥ ኃያል መሆኑን ያሳያል።
“ለረጅም ጊዜ ዝም አልኩ። ጸጥ ብዬ ቆየሁ፤ ራሴንም ገታሁ። ምጥ እንደያዛት ሴትእቃትታለሁ፣ አለከልካለሁ እንዲሁም ቁና ቁና እተነፍሳለሁ።
ተራሮችንና ኮረብቶችን አወድማለሁ፤ደግሞም በላያቸው ላይ ያለውን ተክል ሁሉ አደርቃለሁ። ወንዞችን ደሴቶች አደርጋለሁ፤ቄጠማ የሞላባቸውንም ኩሬዎች አደርቃለሁ።
ዓይነ ስውራንን በማያውቁት መንገድ እመራቸዋለሁ፤ባልለመዱት ጎዳናም እንዲሄዱ አደርጋቸዋለሁ። ጨለማውን በፊታቸው ብርሃን፣ወጣ ገባ የሆነውንም ምድር ደልዳላ ሜዳ አደርጋለሁ። ይህን አደርግላቸዋለሁ፤ ደግሞም አልተዋቸውም።”
በተቀረጸ ምስል የሚታመኑ፣ከብረት የተሠሩትን ሐውልቶች “እናንተ አምላኮቻችን ናችሁ” የሚሉወደ ኋላ ይመለሳሉ፤ እጅግም ያፍራሉ።
እናንተ ደንቆሮዎች፣ ስሙ፤እናንተ ዕውሮች እዩ፤ ተመልከቱም።
ከአገልጋዬ በቀር የታወረ፣እንደምልከው መልእክተኛዬም ደንቆሮ የሆነ ማን አለ? ብድራት እንደተከፈለው ሰው ዕውር የሆነወይም እንደ ይሖዋ አገልጋይ የታወረ ማን ነው?
ብዙ ነገሮች ብታዩም ልብ የምትሉት ነገር የለም። ጆሮዎቻችሁን ብትከፍቱም ምንም አትሰሙም።
ይሖዋ ለጽድቁ ሲልሕጉን ታላቅና ክብራማ በማድረግ ደስ ተሰኝቷል።
ይህ ሕዝብ ግን የተበዘበዘና የተዘረፈ ነው፤ሁሉም ጉድጓድ ውስጥ ተይዘዋል፤ በእስር ቤትም ተሰውረዋል። የሚታደጋቸው በሌለበት ተበዝብዘዋል፤“መልሷቸው!” የሚል በሌለበትም ተዘርፈዋል።
ከእናንተ መካከል ይህን የሚሰማ ማን ነው? በትኩረት የሚያዳምጥና ለወደፊቱ ጊዜ ትምህርት የሚወስድ ማን ነው?
ያዕቆብን ለዘረፋ፣እስራኤልንም ለበዝባዦች አሳልፎ የሰጠ ማን ነው? በእሱ ላይ ኃጢአት በመፈጸም የበደልነው ይሖዋ አይደለም? እነሱ በመንገዱ ለመሄድ አልፈለጉም፤ሕጉንም አይታዘዙም።
ስለዚህ ንዴቱን፣ ቁጣውንና የጦርነቱን መዓትበእስራኤል ላይ አፈሰሰ። የጦርነቱም እሳት በዙሪያው ያለውን ሁሉ በላው፤ እሱ ግን አላስተዋለም። አቃጠለው፤ እሱ ግን ጨርሶ ልብ አላለም።
“እናንተ ደሴቶች፣ ዝም ብላችሁ አዳምጡኝ፤ብሔራትም ኃይላቸውን ያድሱ። በመጀመሪያ ይቅረቡ፤ ከዚያም ይናገሩ። ለፍርድ አንድ ላይ እንሰብሰብ።
ብሔራትን አሳልፎ ይሰጠውናነገሥታትን ድል ይነሳ ዘንድከፀሐይ መውጫ አንዱን ያስነሳው፣በጽድቅ ወደ እግሩ የጠራው ማን ነው? በሰይፉ ፊት አቧራ የሚያደርጋቸው፣በቀስቱ ፊት በነፋስ እንደተወሰደ ገለባ የሚያደርጋቸው ማን ነው?
እግሩ ባልረገጠው መንገድ በመጓዝምንም ነገር ሳያግደው እነሱን ያሳድዳል።
ይህን የሠራና ያደረገ፣ትውልዶቹንም ከመጀመሪያ አንስቶ የጠራ ማን ነው? እኔ ይሖዋ የመጀመሪያው ነኝ፤ከመጨረሻዎቹም ጋር እኔ ያው ነኝ።”
ደሴቶች አይተው ፈሩ። የምድር ዳርቻዎች ተንቀጠቀጡ። ቀረቡ፤ ወደ ፊትም መጡ።