text
stringlengths
4
267
ክፉ ሰው መንገዱን፣መጥፎ ሰውም ሐሳቡን ይተውፀምሕሚት ወደሚያሳዚው አምላካቜን ወደ ይሖዋ ይመለስፀይቅርታው ብዙ ነውና።
“ሐሳቀ እንደ ሐሳባቜሁ፣መንገዳቜሁም እንደ መንገዮ አይደለምና” ይላል ይሖዋ።
“ሰማያት ኚምድር ኹፍ እንደሚሉመንገዎ ኚመንገዳቜሁ፣ሐሳቀም ኚሐሳባቜሁ ኹፍ ያለ ነው።
ዝናብና በሚዶ ኹሰማይ እንደሚወርድ፣ምድርን በማራስ እንድታበቅልና እንድታፈራ፣ለዘሪው ዘርን፣ ለበላተኛውም ምግብን እንድትሰጥ ሳያደርግ ወደመጣበት እንደማይመለስ ሁሉ፣
ኹአፌ ዚሚወጣውም ቃሌ እንዲሁ ይሆናል። ደስ ዚሚያሰኘኝን ነገር ያደርጋል፣ዚተላኚበትንም ዓላማ በእርግጥ ይፈጜማል እንጂያላንዳቜ ውጀት ወደ እኔ አይመለስም።
በታላቅ ደስታ ትወጣላቜሁናፀበሰላምም ትመለሳላቜሁ። ተራሮቹና ኮሚብቶቹ በደስታ በፊታቜሁ እልል ይላሉፀዚሜዳም ዛፎቜ ሁሉ ያጚበጭባሉ።
በቁጥቋጊ ፋንታ ዚጥድ ዛፍ ይበቅላልፀበሳማም ፋንታ ዚአደስ ዛፍ ይበቅላል። ዹይሖዋ ስም እንዲገን ያደርጋልፀእንዲሁም ፈጜሞ ዹማይጠፋ ዹዘላለም ምልክት ይሆናል።”
በምድሚ በዳው ባሕር ላይ ዹተላለፈ ፍርድፊ ኚደቡብ አቅጣጫ አውሎ ነፋሳት እዚጠራሚጉ እንደሚመጡ፣ኚምድሚ በዳ ይኾውም አስፈሪ ኹሆነው ምድር ዹሆነ ነገር እዚመጣ ነው።
አንድ ዚሚያስጚንቅ ራእይ ተነገሹኝ፩ ኚሃዲው ክህደት ይፈጜማልፀአጥፊውም ያጠፋል። ኀላም ሆይ፣ ተነሺ! ሜዶን ሆይ፣ ክበቢ! እሷ ያስኚተለቜው ሲቃ ሁሉ እንዲያኚትም አደርጋለሁ።
ኹዚህም ዚተነሳ በጣም ተሠቃዚሁ። ልትወልድ እንደተቃሚበቜ ሎት፣ምጥ ያዘኝ። እጅግ ኹመጹነቄ ዚተነሳ መስማት ተሳነኝፀእጅግ ኚመሚበሌም ዚተነሳ ማዚት አቃተኝ።
ልቀ ደኚመፀ በፍርሃት ተንቀጠቀጥኩ። ዹምናፍቀው ዚምሜት ድንግዝግዝታ ሜብር ለቀቀብኝ።
ማዕዱን አሰናዱፀ መቀመጫ ቊታዎቹን አዘጋጁ! ብሉ፣ ጠጡ! እናንተ መኳንንት፣ ተነሱፀ ጋሻውን ዘይት ቀቡ!
ይሖዋ እንዲህ ብሎኛልናፊ “ሂድ፣ ጠባቂ አቁምፀ ዚሚያዚውንም ነገር እንዲናገር አድርግ።”
እሱም በፈሚሶቜ ዚሚጎተቱ ዹጩር ሠሚገሎቜ፣በአህዮቜ ዚሚጎተቱ ዹጩር ሠሚገሎቜ፣በግመሎቜ ዚሚጎተቱ ዹጩር ሠሚገሎቜ አዚ። ዓይኑን ተክሎ በኹፍተኛ ትኩሚት ተመለኚተ።
ኚዚያም እንደ አንበሳ ጮኟ እንዲህ አለ፩ “ይሖዋ ሆይ፣ በዹቀኑ በመጠበቂያው ግንብ ላይ ቆሜአለሁፀበዚሌሊቱም በጥበቃ ቊታዬ ላይ ተሰይሜአለሁ።
እዚመጣ ያለውን ነገር ተመልኚትፊ ሰዎቜ በፈሚሶቜ በሚጎተት ዹጩር ሠሹገላ እዚመጡ ነው!” ኚዚያም ጮክ ብሎ እንዲህ አለ፩ “ወደቀቜ! ባቢሎን ወደቀቜ! ዚተቀሚጹትን ዚአማልክቷን ምስሎቜ በሙሉ መሬት ላይ ጥሎ ሰባበሚ!”
እንደ እህል ዹተወቃኾው ሕዝቀ፣ዚአውድማዬ ውጀት ሆይ፣ኚእስራኀል አምላክ፣ ኚሠራዊት ጌታ ኹይሖዋ ዚሰማሁትን ነግሬሃለሁ።
በዱማ ላይ ዹተላለፈ ፍርድፊ አንዱ ኹሮይር ጠርቶኝ እንዲህ አለኝ፩ “ጠባቂ ሆይ፣ ስለ ሌሊቱ ምን ትላለህ? ጠባቂ ሆይ፣ ስለ ሌሊቱ ምን ትላለህ?”
ጠባቂውም እንዲህ አለ፩ “ሊነጋ ነውፀ ሆኖም ተመልሶ ይመሻል። መጠዹቅ ኚፈለጋቜሁ ጠይቁ። ተመልሳቜሁ ኑ!”
በበሹሃማው ሜዳ ላይ ዹተላለፈ ፍርድፊ እናንተ ዚዎዳን ተጓዥ ነጋዎዎቜ ሆይ፣በበሚሃማው ሜዳ በሚገኘው ዱር ሌሊቱን ታሳልፋላቜሁ።
ዹተጠማውን ለመገናኘት ውኃ ይዛቜሁ ኑፀእናንተ ዹቮማ ነዋሪዎቜ ሆይ፣ለሚሞሞውም ሰው ምግብ አምጡ።
እነሱ ኚሰይፍ፣ ኹተመዘዘ ሰይፍ፣ኚተደገነ ቀስትና ኹተፋፋመ ጊርነት ሞሜተዋልና።
ይሖዋ እንዲህ ብሎኛልፊ “እንደ ቅጥር ሠራተኛ ዚሥራ ዘመን፣ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ዚቄዳር ክብር ሙሉ በሙሉ ይጠፋል።
ኚቄዳር ተዋጊዎቜ ዚሚተርፉት ቀስተኞቜ ጥቂት ይሆናሉፀ ዚእስራኀል አምላክ ይሖዋ ይህን ተናግሯልና።”
እነሆ፣ እውነተኛው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋኢዚሩሳሌምና ይሁዳ ማንኛውም ዓይነት ድጋፍና አቅርቊትይኞውም ዚምግብና ዹውኃ አቅርቊት ሁሉ እንዲቋሚጥባ቞ው ያደርጋልፀ
ኃያሉን ሰውና ተዋጊውን፣ዳኛውንና ነቢዩን፣ ሟርተኛውንና ሜማግሌውን፣
ዚሃምሳ አለቃውን፣ ባለሥልጣኑንና አማካሪውን፣በአስማት ዚተካነውንና በድግምት ዹላቀ ቜሎታ ያለውን ያስወግዳል።
በእነሱ ላይ ልጆቜን መኳንንት አድርጌ እሟማለሁፀያልሰኚነ ሰውም ይገዛ቞ዋል።
ሕዝቡ አንዱ ሌላውን፣እያንዳንዱም ባልንጀራውን ይጚቁናል። ልጅ በሜማግሌ ላይ ጥቃት ይሰነዝራልፀተራው ሰውም ዹተኹበሹውን ይዳፈራል።
እያንዳንዱ ሰው በአባቱ ቀት ዹሚኖሹውን ወንድሙን ይዞ “አንተ ካባ አለህፀ ስለዚህ በእኛ ላይ አዛዥ ሁን። ይህን ዚፍርስራሜ ክምር ግዛ” ይለዋል።
እሱ ግን በዚያ ቀን እንዲህ ሲል ይቃወማል፩ “እኔ ቁስላቜሁን አላክምምፀበቀ቎ ምግብም ሆነ ልብስ ዚለም። በሕዝቡ ላይ አዛዥ አድርጋቜሁ አትሹሙኝ።”
ኢዚሩሳሌም ተሰናክላለቜናፀይሁዳም ወድቃለቜፀምክንያቱም እነሱ በአንደበታ቞ውም ሆነ በሥራ቞ው ይሖዋን ይቃወማሉፀበክብራማው አምላክ ፊት አሻፈሚን ይላሉ።
ዚፊታ቞ው ገጜታ ይመሠክርባ቞ዋልፀደግሞም እንደ ሰዶም ኃጢአታ቞ውን በይፋ ይናገራሉፀኃጢአታ቞ውን ለመደበቅ አይሞክሩም። በራሳ቞ው ላይ ጥፋት ስለሚያመጡ ወዮላ቞ው!
ለጻድቃን መልካም እንደሚሆንላ቞ው ንገሯ቞ውፀለሥራ቞ው ወሮታ ይኚፈላ቞ዋል።
ለክፉ ሰው ወዮለት! ጥፋት ይደርስበታልፀበሌሎቜ ላይ ሲያደርግ ዹነበሹው በራሱ ላይ ይደርሳልና!
ዚሕዝቀ አሠሪዎቜ ጚቋኞቜ ና቞ውፀሎቶቜም ይገዟ቞ዋል። ሕዝቀ ሆይ፣ ዚሚመሯቜሁ ሰዎቜ እንድትባዝኑናበዚትኛው መንገድ እንደምትሄዱ ግራ እንድትጋቡ እያደሚጓቜሁ ነው።
ይሖዋ ለመክሰስ ተሰይሟልፀበሕዝቊቜ ላይ ብያኔውን ለማሰማት ተነስቷል።
ይሖዋ ዚሕዝቡን ሜማግሌዎቜና አለቆቜ ይፋሚዳል። “ዹወይኑን እርሻ አቃጥላቜኋልፀኚድሃው ዚዘሚፋቜሁት ንብሚትም በቀታቜሁ ይገኛል።
ሕዝቀን ዚምታደቁት፣ ዚድሆቜንም ፊት መሬት ላይ ዚምትፈጩትእንዎት ብትዳፈሩ ነው?” ይላል ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ።
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ዚጜዮን ሎቶቜ ልጆቜ ትዕቢተኛ ስለሆኑ፣ራሳ቞ውን ቀና አድርገው ስለሚራመዱ፣በዓይና቞ው እዚተጣቀሱና እዚተውሚገሚጉ በመሄድእግራ቞ው ላይ ያደሚጉትን አልቩ ስለሚያቃጭሉ፣
ይሖዋ ዚጜዮንን ሎቶቜ አናት በቁስል ይመታልፀደግሞም ይሖዋ ግንባራ቞ውን ይገልጣል።
በዚያ ቀን ይሖዋ ጌጊቻ቞ውን ሁሉ ይነጥቃልፊአልቊውን፣ ዹፀጉር ጌጡን፣ ዹጹሹቃ ቅርጜ ያለውን ጌጥ፣
ዚጆሮ ጉትቻውን፣ አምባሩን፣ መኚናነቢያውን፣
ዚራስ መሞፈኛውን፣ ዚሰንሰለት አልቊውን፣ ጌጠኛውን መቀነት፣ዚሜቶ ዕቃውን፣ ክታቡን፣
ዚጣት ቀለበቱን፣ ዚአፍንጫ ቀለበቱን፣
ዚክት ልብሱን፣ መደሚቢያውን፣ ካባውን፣ ዚእጅ ቊርሳውን፣
ዚእጅ መስተዋቱን፣ ዚበፍታ ልብሶቹን፣ጥምጥሙንና መኚናነቢያውን ይወስድባ቞ዋል።
በበለሳን ዘይት መዓዛ ፋንታ ዚጠነባ ሜታ፣በመታጠቂያ ፋንታ ገመድ፣አምሮ በተሠራ ፀጉር ፋንታ መላጣነት፣ባማሚ ልብስ ፋንታ ማቅ፣በውበትም ፋንታ ጠባሳ ይሆናል።
ወንዶቜሜ በሰይፍ፣ኃያላኖቜሜም በውጊያ ይወድቃሉ።
ዹኹተማዋም መግቢያዎቜ ያዝናሉ፣ ያለቅሳሉምፀእሷም ባዶዋን ቀርታ በሐዘን መሬት ላይ ትቀመጣለቜ።”
“ግትር ለሆኑ ልጆቜ ወዮላ቞ው” ይላል ይሖዋፀ“በኃጢአት ላይ ኃጢአት ለመጚመርዚእኔን ሳይሆን ዚራሳ቞ውን ዕቅድ ይፈጜማሉፀደግሞም ኅብሚት ይፈጥራሉፀ ይህን ዚሚያደርጉት ግን በመንፈሮ አይደለም።
በፈርዖን ጥበቃ ሥር ለመሞሞግናበግብፅ ጥላ ሥር ለመጠለልእኔን ሳያማክሩ ወደ ግብፅ ይወርዳሉ!
ይሁንና ፈርዖን ዚሚያደርግላቜሁ ጥበቃ ለኀፍሚት፣በግብፅ ጥላ ሥር መጠለልም ለውርደት ይዳርጋቜኋል።
መኳንንቱ በጟዓን ና቞ውናፀመልእክተኞቹም ሃኔስ ደርሰዋል።
ምንም ሊጠቅማቾው በማይቜል፣እርዳታ በማይሰጥና ጥቅም በማያስገኝ፣ይልቁንም ለውርደትና ለነቀፋ በሚዳርግ ሕዝብሁሉም ኀፍሚት ይኚናነባሉ።”
በደቡብ እንስሳት ላይ ዹተላለፈ ፍርድፊ አንበሳ፣ አዎ ዚሚያገሳ አንበሳ ባለበት፣እፉኝት እንዲሁም ዹሚበርና ዚሚያቃጥል እባብ በሚገኙበት፣አስጚናቂና አስ቞ጋሪ ሁኔታዎቜ በሞሉበት ምድርሀብታ቞ውን በአህያ ላይ፣ቁሳቁሳ቞ውንም በግመል ሻኛ ላይ ጭነው ይሄዳሉ። ሆኖም እነዚህ ነገሮቜ ለሕዝቡ ምንም ጥቅም አያስገኙለትም።
ግብፅ ዚምትሰጠው እርዳታ ምንም እርባና ዚለውምና። ስለዚህ እሷን “ሚዓብ፣ ሥራ ፈታ ዚምትጎለት” ብዬ ጠርቻታለሁ።
“በል ሂድፀ ለመጪዎቹ ዘመናት፣ቋሚ ምሥክር እንዲሆንእነሱ ባሉበት በጜላት ላይ ጻፈውፀበመጜሐፍም ላይ ክተበው።
እነሱ ዓመፀኛ ሕዝብ፣ አታላይ ልጆቜናዚይሖዋን ሕግ ለመስማት እንቢተኛ ዹሆኑ ልጆቜ ና቞ውና።
ባለ ራእዮቜን ‘ኚእንግዲህ ራእይ አትዩ’ ይላሉፀ ነቢያትንም እንዲህ ይላሉ፩ ‘እውነተኛ ራእይ አትንገሩን። ዚሚጥም ነገር ንገሩንፀ አሳሳቜ ዹሆነ ሕልም አልሙልን።
ኚመንገዱ ዞር በሉፀ ጎዳናውንም ልቀቁ። ዚእስራኀልን ቅዱስ በፊታቜን አታድርጉ።’”
ስለዚህ ዚእስራኀል ቅዱስ እንዲህ ይላል፩ “ይህን ቃል ስለናቃቜሁ፣በማጭበርበርና በማታለል ስለታመናቜሁ፣በዚያም ላይ ስለተደገፋቜሁ፣
ይህ በደል እንደተሰነጠቀ ቅጥር፣ሊወድቅ እንደተቃሚበ ያዘመመ ሹጅም ቅጥር ይሆንባቜኋል። ሳይታሰብ በድንገት ይፈርሳል።
ሾክላ ሠሪ እንደሠራው ትልቅ እንስራ ይሰባበራልፀእንክትክቱ ኚመውጣቱ ዚተነሳ ኚምድጃ ፍም ለመውሰድወይም ኹሹግሹጋማ ቊታ ውኃ ለመጹለፍ ዚሚያስቜልአንድም ገል አይገኝም።”
ዚእስራኀል ቅዱስ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላልና፩ “ወደ እኔ በመመለስና በማሹፍ ትድናላቜሁፀሳትሚበሹ፣ ተማምናቜሁ በመኖር ብርቱ መሆናቜሁን ታሳያላቜሁ።” እናንተ ግን ፈቃደኞቜ አልሆናቜሁም።
ይልቁንም “አይሆንም፣ በፈሚሶቜ እንሞሻለን!” አላቜሁ። ደግሞም ትሞሻላቜሁ። “በፈጣን ፈሚሶቜም እንጋልባለን!” አላቜሁ። ስለሆነም ዚሚያሳድዷቜሁ ሰዎቜ ፈጣኖቜ ይሆናሉ።
አንድ ሰው ኹሚሰነዝሹው ዛቻ ዚተነሳ ሺዎቜ ይሞበራሉፀበተራራ አናት ላይ እንደተተኚለ ምሰሶናበኮሚብታ ላይ እንደቆመ ለምልክት ዚሚያገለግል ግንድ ሆናቜሁ እስክትቀሩ ድሚስ፣አምስት ሰዎቜ ኚሚሰነዝሩት ዛቻ ዚተነሳ ትሞሻላቜሁ።
ይሁንና ይሖዋ ሞገስ ሊያሳያቜሁ በትዕግሥት ይጠባበቃልፀምሕሚት ሊያሳያቜሁም ይነሳል። ይሖዋ ዚፍትሕ አምላክ ነውና። እሱን በተስፋ ዚሚጠባበቁ ሁሉ ደስተኞቜ ና቞ው።
ሕዝቡ በጜዮን ይኾውም በኢዚሩሳሌም በሚኖርበት ጊዜ ፈጜሞ አታለቅሱም። እርዳታ ለማግኘት በምትጮኹበት ጊዜ በእርግጥ ሞገስ ያሳያቜኋልፀ ጩኞታቜሁን እንደሰማም ይመልስላቜኋል።
ይሖዋ ዚጭንቀትን ምግብና ዹጭቆናን ውኃ ቢሰጥህም እንኳ ታላቁ አስተማሪህ ኚእንግዲህ ራሱን አይሰውርምፀ በገዛ ዓይኖቜህም ታላቁን አስተማሪህን ታያለህ።
ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ዞር ብትል ጆሮህ ኹኋላህ “መንገዱ ይህ ነው። በእሱ ሂድ” ዹሚል ድምፅ ይሰማል።
ዚተቀሚጹ ምስሎቜህ ዚተለበጡበትን ብርና ኚብሚት ዚተሠሩ ሐውልቶቜህ ዚተለበጡበትን ወርቅ ታሚክሳለህ። እንደ ወር አበባ ጹርቅ “ኹዚህ ጥፉ!” በማለት አሜቀንጥሚህ ትጥላ቞ዋለህ።
እሱም መሬት ላይ ለምትዘራው ዘር ዝናብ ይሰጥሃልፀ ምድሪቱም ዚምታፈራው እህል ዚተትሚፈሚፈና ምርጥ ይሆናል። በዚያም ቀን ኚብቶቜህ ሰፊ በሆነ ዚግጊሜ መስክ ይሰማራሉ።
መሬቱንም ዚሚያርሱ ኚብቶቜና አህዮቜ በእንቧጮ ዹተቀመመ እንዲሁም በላይዳና በመንሜ ዹተለዹ ገፈራ ይበላሉ።
ብዙ እልቂት በሚደርስበትና ግንቊቜ በሚፈርሱበት ቀን፣ በሹጅም ተራራና ኹፍ ባለ ኮሚብታ ሁሉ ላይ ጅሚቶቜ ይፈስሳሉፀ ዹውኃ መውሹጃ ቊዮቜም ይኖራሉ።
ዹሙሉ ጹሹቃ ብርሃንም እንደ ፀሐይ ብርሃን ይሆናልፀ ይሖዋ ዚሕዝቡን ስብራት በሚጠግንበትና በእሱ ምት ዚተነሳ ዚደሚሰባ቞ውን ኚባድ ቁስል በሚፈውስበት ቀን ዹፀሐይ ብርሃን፣ እንደ ሰባት ቀን ብርሃን ሰባት እጥፍ ይደምቃል።
እነሆ፣ ዹይሖዋ ስም በቁጣው እዚነደደጥቅጥቅ ካለ ደመና ጋር ኚሩቅ ይመጣል። ኚንፈሮቹ በቁጣ ተሞልተዋልፀምላሱም እንደሚባላ እሳት ነው።
መንፈሱ እስኚ አንገት ድሚስ እንደሚደርስ ዚሚያጥለቀልቅ ወንዝ ነውፀብሔራትን በጥፋት ወንፊት ይነፋ቞ዋልፀበሕዝቊቜ መንጋጋም መንገድ እንዲስቱ ዚሚያደርግ ልጓም ይገባል።
እናንተ ግን፣ ለበዓል በምትዘጋጁበት ጊዜበሌሊት እንደሚዘመሚው ያለ መዝሙር ትዘምራላቜሁፀደግሞም ወደ እስራኀል ዓለት፣ ወደ ይሖዋ ተራራ ሲጓዝዋሜንት ይዞ እንደሚሄድ ሰውልባቜሁ ሐሎት ያደርጋል።
ይሖዋ ግርማ ዹተላበሰ ድምፁ እንዲሰማ ያደርጋልፀዚክንዱንም ብርታት ይገልጣልፀይህን ዚሚያደርገው በሚነድ ቁጣ፣ በሚባላ ዚእሳት ነበልባል፣ሳይታሰብ በሚወርድ ዶፍ፣ ነጎድጓድ በቀላቀለ ውሜንፍርና በበሚዶ ድንጋይ ታጅቊ ክንዱ ጥቃት ለመሰንዘር ወደ ታቜ በሚወርድበት ጊዜ ነው።
ኹይሖዋ ድምፅ ዚተነሳ አሩር በሜብር ይናጣልናፀበበትርም ይመታዋል።
ይሖዋ በጊርነት ክንዱን በእነሱ ላይ በሚያነሳበት ጊዜበአሩር ላይ ዚሚያወርደውዚቅጣት በትር ሁሉበአታሞና በበገና ዚታጀበ ይሆናል።
ቶፌቱ ኚወዲሁ ተዘጋጅቷልናፀለንጉሡም ተዘጋጅቶለታል። ዚእንጚት ክምሩ ጥልቀትና ስፋት ያለው እንዲሆን አድርጓልፀብዙ እሳትና እንጚትም አለ። ዹይሖዋ እስትንፋስ ልክ እንደ ድኝ ጅሚትበእሳት ያያይዘዋል።
ይሁን እንጂ ፅልማሞቱ ምድሪቱ በተጚነቀቜበት ጊዜ እንደነበሚው ይኾውም ዚዛብሎን ምድርና ዚንፍታሌም ምድር በተዋሚዱበት ወቅት እንደነበሚው እንደቀድሞው ዘመን አይሆንም። በኋለኛው ዘመን ግን ምድሩ ማለትም በባሕሩ አጠገብ ዚሚያልፈው መንገድ፣ በዮርዳኖስ ክልል ዹሚገኘው ዚአሕዛብ ገሊላ እንዲኚበር ያደርጋል።
በጹለማ ውስጥ ይሄዱ ዚነበሩ ሰዎቜታላቅ ብርሃን አዩ። ድቅድቅ ጹለማ ባጠላበት ምድር ዚሚኖሩ ሰዎቜምብርሃን ወጣላ቞ው።
ሕዝቡን አብዝተሃልፀታላቅ ደስታ እንዲያገኝ አድርገሃል። መኹር በሚሰበሰብበት ጊዜ ሐሎት እንደሚያደርጉ፣ምርኮንም ሲኚፋፈሉ እንደሚደሰቱ ሰዎቜበፊትህ ደስ ይሰኛሉ።
ምድያም ድል በተደሚገበት ጊዜ እንደሆነው ሁሉዹሾክማቾውን ቀንበር፣ በትኚሻ቞ው ላይ ያለውን በትር፣ዚተቆጣጣሪያ቞ውንም ዘንግ ሰባብሚሃልና።
መሬቱ እስኪንቀጠቀጥ ድሚስ በኃይል ዚሚሚግጡ ሰልፈኞቜ ጫማ ሁሉእንዲሁም በደም ዹተጹማለቀ ልብስ በሙሉለእሳት ማገዶ ይሆናል።
ልጅ ተወልዶልናልናፀወንድ ልጅም ተሰጥቶናልፀገዢነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል። ስሙ ድንቅ መካሪ፣ ኃያል አምላክ፣ ዹዘላለም አባትና ዹሰላም መስፍን ይባላል።
በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ ይቀመጣልፀእዚተጠናኚሚ ዹሚሄደው አገዛዙም ሆነሰላሙ ፍጻሜ አይኖሚውም። ኹአሁን ጀምሮ ለዘላለምበማይናወጥ ሁኔታ ይመሠሚታልፀበፍትሕና በጜድቅም ጞንቶ ይኖራል። ዚሠራዊት ጌታ ዹይሖዋ ቅንዓት ይህን ያደርጋል።
ይሖዋ በያዕቆብ ላይ ቃል ላኚፀቃሉም በእስራኀል ላይ ደሚሰ።
ሕዝቡም ሁሉ ይኾውም ዚኀፍሬምና ዚሰማርያ ነዋሪዎቜይህን ያውቃሉፀበትዕቢታ቞ውና በልባ቞ው እብሪት ዚተነሳ እንዲህ ይላሉ፩
“ጡቊቹ ወድቀዋልፀእኛ ግን በጥርብ ድንጋይ እንገነባለን። ዚሟላ ዛፎቹ ተቆርጠዋልፀእኛ ግን በአርዘ ሊባኖስ እንተካ቞ዋለን።”
ይሖዋ ዚሚጺንን ባላጋራዎቜ በእሱ ላይ ያስነሳልፀጠላቶቹንም እርምጃ እንዲወስዱ ይቀሰቅሳ቞ዋልፀ
ሶርያን ኚምሥራቅ፣ ፍልስጀማውያንን ደግሞ ኚምዕራብ ያመጣበታልፀእነሱም አፋቾውን ኹፍተው እስራኀልን ይውጡታል። ኹዚህ ሁሉ ዚተነሳ ቁጣው አልተመለሰምፀይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘሚጋ ነው።
ሕዝቡ ወደመታ቞ው አልተመለሱምናፀዚሠራዊት ጌታ ይሖዋን አልፈለጉም።
ይሖዋ ራስንና ጅራትን፣ ቀንበጥንና እንግጫንኚእስራኀል በአንድ ቀን ይቆርጣል።
ሜማግሌውና ዹተኹበሹው ሰው ራስ ነውፀዚሐሰት መመሪያ ዹሚሰጠው ነቢይ ደግሞ ጅራት ነው።
ይህን ሕዝብ ዚሚመሩት ሰዎቜ እንዲባዝን ያደርጉታልፀበእነሱ ዚሚመራውም ሕዝብ ግራ ይጋባል።
ይሖዋ በወጣቶቻ቞ው ዹማይደሰተው ለዚህ ነውፀበመካኚላ቞ው ላሉት አባት ዹሌላቾው ልጆቜና መበለቶቜ ምሕሚት አያሳይምፀምክንያቱም ሁሉም ኚሃዲዎቜና ክፉ አድራጊዎቜ ና቞ውፀዚሁሉም አፍ ዚማይሚባ ነገር ይናገራል። ኹዚህ ሁሉ ዚተነሳ ቁጣው አልተመለሰምፀይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘሚጋ ነው።