text
stringlengths
4
267
ታላላቅ በሆኑትና ኹፍ ኹፍ ባሉት አርዘ ሊባኖሶቜ ሁሉ ላይእንዲሁም በባሳን ዚባሉጥ ዛፎቜ ሁሉ ላይ፣
ታላላቅ በሆኑት ተራሮቜ ሁሉናበሹጃጅም ኮሚብቶቜ ሁሉ ላይ፣
ሹጅም በሆነ ማማ ሁሉና ጠንካራ በሆነ ግንብ ሁሉ ላይ፣
በተርሎስ መርኚቊቜ ሁሉናበሚያማምሩ ጀልባዎቜ ሁሉ ላይ ይደርሳል።
ትዕቢተኛ ሰው ይዋሚዳልፀእብሪተኞቜም አንገታ቞ውን ይደፋሉ። በዚያም ቀን ይሖዋ ብቻ ኹፍ ኹፍ ይደሚጋል።
ኚንቱ ዚሆኑት አማልክት ሙሉ በሙሉ ይወገዳሉ።
ይሖዋ ምድርን በሜብር ለማንቀጥቀጥ በሚነሳበት ጊዜ፣አስፈሪ ኹመሆኑ ዚተነሳናኚታላቅ ግርማው ዚተነሳሰዎቜ በዓለት ዋሻዎቜናበጉድጓዶቜ ውስጥ ይደበቃሉ።
በዚያ ቀን፣ ሰዎቜ በፊታ቞ው ይሰግዱ ዘንድለራሳ቞ው ዚሠሯ቞ውን ኚንቱ ዹሆኑ ዚብርና ዹወርቅ አማልክትለአይጥና ለሌሊት ወፎቜ ይወሚውራሉፀ
ይሖዋ ምድርን በሜብር ለማንቀጥቀጥ በሚነሳበት ጊዜ፣አስፈሪ ኹመሆኑ ዚተነሳናኚታላቅ ግርማው ዚተነሳበዓለት ዋሻዎቜናበቋጥኝ ስንጥቆቜ ውስጥ ይደበቃሉ።
ለራሳቜሁ ስትሉ፣ኚአፍንጫው እንደሚወጣ እስትንፋስ በሆነ ሰው አትታመኑ። ለመሆኑ እሱ ያን ያህል ቊታ እንዲሰጠው ዚሚያደርግ ምን ነገር አለ?
“አሁን ግን፣ አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፣ዚመሚጥኩህም እስራኀል ሆይ፣ ስማ።
ዚሠራህና ያበጀህ፣ኚማህፀን ጀምሮ ዚሚዳህይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘አገልጋዬ ያዕቆብ፣ዚመሚጥኩህም ዚሹሩን ሆይ፣ አትፍራ።
ለተጠማው ውኃ አፈሳለሁናፀበደሚቁ ምድርም ላይ ጅሚቶቜ እንዲፈስሱ አደርጋለሁ። መንፈሮን በዘርህ ላይ፣በሚኚ቎ንም በልጅ ልጆቜህ ላይ አፈሳለሁ።
እነሱም በለምለም ሣር መካኚል፣በጅሚቶቜም ዳር እንዳሉ ዚአኻያ ዛፎቜ ይበቅላሉ።
አንዱ “እኔ ዹይሖዋ ነኝ” ይላል። ሌላውም ራሱን በያዕቆብ ስም ይጠራልፀሌላው ደግሞ በእጁ ላይ “ዹይሖዋ ነኝ” ብሎ ይጜፋል። ደግሞም ራሱን በእስራኀል ስም ይጠራል።’
ዚእስራኀል ንጉሥ ዹሆነውና እስራኀልን ዚተቀዠው ይሖዋ፣ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘ዚመጀመሪያው እኔ ነኝፀ ዚመጚሚሻውም እኔ ነኝ። ኚእኔ በቀር ሌላ አምላክ ዚለም።
እንደ እኔ ያለ ማን ነው? በድፍሚት ይናገርፀ ያሳውቅምፀ ማስሚጃውንም ለእኔ ያቅርብ! ዚጥንቱን ሕዝብ ካቋቋምኩበት ጊዜ ጀምሮ፣በቅርቡ ዚሚኚሰቱትንናወደፊት ዚሚሆኑትን ነገሮቜ ይናገሩ።
ስጋት አይደርባቜሁፀበፍርሃትም አትሜመድመዱ። አስቀድሜ ለእያንዳንዳቜሁ አልነገርኳቜሁም? ደግሞስ አላሳወቅኳቜሁም? እናንተ ምሥክሮቌ ናቜሁ። ኚእኔ ሌላ አምላክ አለ? በፍጹም፣ ሌላ ዓለት ዚለምፀ እኔ ዹማውቀው አንድም ዚለም።’”
ዚተቀሚጹ ምስሎቜን ዚሚሠሩ ሁሉ ኚንቱ ና቞ውፀዚሚወዷ቞ውም ጣዖቶቜ ምንም ጥቅም ዚላ቞ውም። እንደ ምሥክሮቻ቞ው እነሱም ምንም አያዩምፀ ምንም አያውቁምፀበመሆኑም ሠሪዎቻ቞ው ለኀፍሚት ይዳሚጋሉ።
ለምንም ዹማይጠቅም አምላክ ዚሚሠራወይም ዚብሚት ምስል ዚሚያበጅ ማን ነው?
እነሆ፣ ባልደሚቊቹ ሁሉ ያፍራሉ! ዚእጅ ጥበብ ባለሙያዎቹ ተራ ሰዎቜ ና቞ው። ሁሉም ተሰብስበው ይቁሙ። በፍርሃት ይዋጣሉፀ ሁሉም ያፍራሉ።
አንጥሚኛ በመሣሪያው ተጠቅሞ ብሚቱን በኹሰል ፍም ላይ ይሠራዋል። ብርቱ በሆነው ክንዱበመዶሻ ቅርጜ ይሰጠዋል። ኚዚያም ይርበዋልፀ ጉልበትም ያጣልፀውኃ ስለማይጠጣ ይደክማል።
እንጚት ጠራቢው በገመድ ይለካልፀ በቀይ ጠመኔም ንድፍ ያወጣል። በመሮም ይጠርበዋልፀ በማክበቢያም ምልክት ያደርግበታል። በሰው አምሳል ይቀርጞዋልፀዚሰውንም ውበት ያላብሰዋልፀኚዚያም ቀት ውስጥ ያስቀምጠዋል።
አርዘ ሊባኖስ ዚሚቆርጥ ሰው አለ። እሱም አንድ ዹዛፍ ዝርያ ይኾውም ዚባሉጥ ዛፍ ይመርጣልፀእስኪጠነክርለት ድሚስ በጫካው ውስጥ ባሉት ዛፎቜ መካኚል ይተወዋል። ዚላውሮ ዛፍ ይተክላልፀ ዝናብም ያሳድገዋል።
ኚዚያም ሰው ለማገዶ ይጠቀምበታል። ዹተወሰነውን እንጚት ወስዶ በማንደድ እሳት ይሞቃልፀእሳት አያይዞም ዳቊ ይጋግራል። ይሁንና አምላክ ሠርቶም ያመልኚዋል። ዹተቀሹጾ ምስል ሠርቶበት በፊቱ ይደፋል።
ግማሹን በእሳት ያነደዋልፀበዚያም ላይ ዹሚበላውን ሥጋ ይጠብሳልፀ በልቶም ይጠግባል። እሳቱንም እዚሞቀ “እሰይ! እሳቱን እያዚሁ ሞቅኩ” ይላል።
ዹቀሹውን ግን ምስል ይቀርጜበታልፀ አምላክ አድርጎም ይሠራዋል። በፊቱም ተደፍቶ ይሰግድለታል። “አንተ አምላኬ ነህና አድነኝ” ብሎ ወደ እሱ ይጞልያል።
ምንም አያውቁም እንዲሁም አያስተውሉምፀምክንያቱም ዓይኖቻ቞ው ተጚፍነዋልፀ ማዚትም አይቜሉምፀልባ቞ውም ማስተዋል ጎድሎታል።
ቆም ብሎ በልቡ ያሰበወይም እውቀትም ሆነ ማስተዋል ኖሮት እንዲህ ብሎ ዹተናገሹ ዹለም፩ “ግማሹን እሳት አንድጄበታለሁፀበፍሙም ላይ ዳቊ ጋግሬአለሁፀ ሥጋም ጠብሌ በልቻለሁ። ታዲያ በቀሹው እንጚት አስጞያፊ ነገር መሥራ቎ ተገቢ ነው? ኹዛፍ ለተቆሹጠ እንጚት መስገድ ይገባኛል?”
እሱ አመድ ይበላል። ዚተታለለው ዹገዛ ልቡ አስቶታል። ራሱን ሊያድን አይቜልምፀ ደግሞም “በቀኝ እጄ ያለው ውሞት አይደለም?” አይልም።
“ያዕቆብ ሆይ፣ አንተም እስራኀል ሆይ፣አገልጋዬ ስለሆንክ እነዚህን ነገሮቜ አስታውስ። እኔ ሠርቌሃለሁፀ አንተ ዚእኔ አገልጋይ ነህ። እስራኀል ሆይ፣ አልሚሳህም።
በደልህን በደመና፣ኃጢአትህንም ጥቅጥቅ ባለ ደመና እሞፍነዋለሁ። ወደ እኔ ተመለስፀ እኔም እቀዥሃለሁ።
እናንተ ሰማያት በደስታ እልል በሉ!ይሖዋ እርምጃ ወስዷልና። እናንተ ጥልቅ ዚምድር ክፍሎቜ በድል አድራጊነት ጩኹ! እናንተ ተራሮቜ፣ አንተም ደን ሆይ፣በውስጡም ያላቜሁ ዛፎቜ ሁሉ በደስታ እልል በሉ! ይሖዋ ያዕቆብን ተቀዥቷልናፀበእስራኀልም ላይ ግርማውን ገልጧል።”
ዚተቀዠህና ኹማህፀን ጀምሮ ዚሠራህይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ሁሉንም ነገር ዚሠራሁ እኔ ይሖዋ ነኝ። ብቻዬን ሰማያትን ዘሚጋሁፀምድርንም ሠራሁ። ያኔ ኚእኔ ጋር ማን ነበር?
ዹሆነ ያልሆነውን ዚሚቀባጥሩ ሰዎቜን ምልክቶቜ አኚሜፋለሁፀሟርተኞቜንም ነፈዝ አደርጋለሁፀጥበበኞቹንም ግራ አጋባለሁፀእውቀታ቞ውንም ሞኝነት አደርጋለሁፀ
ዚአገልጋዬን ቃል እውን አደርጋለሁፀዚመልእክተኞቌንም ትንቢት ሙሉ በሙሉ እፈጜማለሁፀስለ ኢዚሩሳሌም ‘ዹሰው መኖሪያ ትሆናለቜ’ፀ ስለ ይሁዳ ኚተሞቜም ‘ዳግም ይገነባሉፀፍርስራሟቿንም መልሌ እሠራለሁ’ እላለሁፀ
ጥልቁን ውኃ ‘ደሹቅ ሁንፀወንዞቜህንም ሁሉ አደርቃለሁ’ እላለሁፀ
ስለ ቂሮስ ‘እሱ እሚኛዬ ነውፀፈቃዎንም ሁሉ ሙሉ በሙሉ ይፈጜማል’ እላለሁፀስለ ኢዚሩሳሌም ‘ዳግም ትገነባለቜ’ፀ ስለ ቀተ መቅደሱም ‘መሠሚትህ ይጣላል’ እላለሁ።”
ጜድቋ እንደ ደማቅ ብርሃን እስኪፈነጥቅ፣መዳኗም እንደ ቜቊ እስኪቀጣጠል ድሚስለጜዮን ስል ጞጥ አልልምፀለኢዚሩሳሌምም ስል ዝም ብዬ አልቀመጥም።
“አንቺ ሎት ሆይ፣ ብሔራት ጜድቅሜን፣ነገሥታትም ሁሉ ክብርሜን ያያሉ። አንቺም ዹይሖዋ አፍ በሚያወጣልሜአዲስ ስም ትጠሪያለሜ።
በይሖዋ እጅ ዚውበት ዘውድ፣በአምላክሜ መዳፍ ዚንጉሥ ጥምጥም ትሆኛለሜ።
ኚእንግዲህ ዚተተወቜ ሎት አትባዪምፀምድርሜም ኚእንግዲህ ባድማ ተብላ አትጠራም። ኹዚህ ይልቅ “ደስታዬ በእሷ ነው” ተብለሜ ትጠሪያለሜፀምድርሜም “ያገባቜ ሎት” ትባላለቜ። ይሖዋ በአንቺ ደስ ይለዋልናፀምድርሜም እንዳገባቜ ሎት ትሆናለቜ።
አንድ ወጣት ድንግሊቱን እንደሚያገባ፣ወንዶቜ ልጆቜሜ አንቺን ያገባሉ። አንድ ሙሜራ በሙሜራይቱ ሐሎት እንደሚያደርግ፣አምላክሜም በአንቺ ሐሎት ያደርጋል።
ኢዚሩሳሌም ሆይ፣ በቅጥሮቜሜ ላይ ጠባቂዎቜ አቁሜአለሁ። ቀኑንም ሆነ ሌሊቱን በሙሉ፣ መቌም ቢሆን ዝም ሊሉ አይገባም። እናንተ ስለ ይሖዋ ዚምትናገሩ፣ፈጜሞ አትሚፉፀ
ደግሞም ኢዚሩሳሌምን አጜንቶ እስኪመሠርታት፣አዎ፣ ዚምድር ምስጋና እስኪያደርጋት ድሚስ ምንም እሚፍት አትስጡት።”
ይሖዋ በቀኝ እጁ፣ ብርቱ በሆነውም ክንዱ እንዲህ ሲል ምሏል፩ “ኚእንግዲህ እህልሜን ለጠላቶቜሜ መብል እንዲሆን አልሰጥምፀዚደኚምሜበትንም አዲስ ዹወይን ጠጅ ዚባዕድ አገር ሰዎቜ አይጠጡትም።
ሆኖም እህሉን፣ ዚሚሰበስቡት ሰዎቜ ይበሉታልፀ ይሖዋንም ያወድሳሉፀወይኑንም፣ ዚሚለቅሙት ሰዎቜ ቅዱስ በሆኑት ቅጥር ግቢዎቌ ውስጥ ይጠጡታል።”
በበሮቹ በኩል እለፉፀ እለፉ። ለሕዝቡ መንገዱን ጥሚጉ። ሥሩፀ አውራ ጎዳናውን ሥሩ። ድንጋዮቹን አስወግዱ። ለሕዝቊቜም ምልክት አቁሙ።
እነሆ፣ ይሖዋ እስኚ ምድር ዳርቻ ድሚስ አውጇል፩ “ለጜዮን ሎት ልጅ‘እነሆ፣ መዳንሜ ቀርቧል። እነሆ፣ ዹሚኹፍለው ወሮታ ኚእሱ ጋር ነውፀዚሚመልሰውም ብድራት በፊቱ አለ’ በሏት።”
ቅዱስ ሕዝብ፣ ይሖዋ ዚተቀዣ቞ው ተብለው ይጠራሉፀአንቺም “እጅግ ዚምትፈለግ፣” “ያልተተወቜ ኹተማ” ተብለሜ ትጠሪያለሜ።
ጉዳት ዚሚያስኚትሉ ሥርዓቶቜን ዚሚያወጡ፣ሁልጊዜ ጹቋኝ ድንጋጌዎቜን ዚሚያሚቁ ወዮላ቞ው!
ዚድሆቜን አቀቱታ ላለመስማት፣በሕዝቀም መካኚል ዚሚገኙትን ምስኪኖቜ ፍትሕ ለመንፈግ ሕግ ዚሚያወጡ ወዮላ቞ው!መበለቶቜን ይበዘብዛሉፀአባት ዹሌላቾውንም ልጆቜ ይዘርፋሉ።
በምትመሚመሩበት ቀን፣ጥፋትም ኚሩቅ በሚመጣበት ጊዜ ምን ይውጣቜሁ ይሆን? እርዳታ ለማግኘት ወደ ማን ትሞሻላቜሁ?ሀብታቜሁንስ ዚት ትተዉት ይሆን?
በእስሚኞቜ መካኚል ተኮራምታቜሁ ኚመቀመጥናበሞቱ ሰዎቜ መካኚል ኹመውደቅ በስተቀር ዚምታተርፉት ነገር ዚለም። ኹዚህ ሁሉ ዚተነሳ ቁጣው አልተመለሰምፀይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘሚጋ ነው።
“ዚቁጣዬ በትር ዹሆነውንናውግዘቮን ዚምገልጜበትን ዱላ በእጁ ዚያዘውንአሊራዊ ተመልኚት!
ኚሃዲ በሆነው ብሔር ላይ፣እጅግ ባስቆጣኝም ሕዝብ ላይ እልኚዋለሁፀብዙ ምርኮ እንዲወስድ፣ ብዙ ሀብት እንዲዘርፍናሕዝቡን በጎዳናዎቜ ላይ እንዳለ ጭቃ እንዲሚጋግጥ አዘዋለሁ።
እሱ ግን እንዲህ ያለ ዝንባሌ አይኖሚውምፀልቡም እንዲህ ለማድሚግ አያቅድምፀዚልቡ ፍላጎት መደምሰስናጥቂት ሳይሆን ብዙ ብሔራትን ማጥፋት ነውና።
እሱ እንዲህ ይላልፊ‘አለቆቜ ሆነው ዚሚያገለግሉኝ ሁሉ ነገሥታት አይደሉም?
ካልኖ እንደ ካርኚሚሜ አይደለቜም? ሃማት እንደ አርጳድ አይደለቜም? ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደለቜም?
እጄ በኢዚሩሳሌምና በሰማርያ ካሉት ይበልጥ በርካታ ዚተቀሚጹ ምስሎቜ ያሏ቞ውንናኚንቱ አማልክት ዚሚያመልኩትን መንግሥታት ይዟል!
በሰማርያና ኚንቱ በሆኑት አማልክቷ ላይ እንዳደሚግኩት ሁሉ፣በኢዚሩሳሌምና በጣዖቶቿስ ላይ እንዲሁ አላደርግም?’
“ይሖዋ በጜዮን ተራራና በኢዚሩሳሌም ዚሚያኚናውነውን ሥራ ሁሉ ሲያጠናቅቅ በእብሪተኛ ልቡ፣ በኩራቱና በትዕቢተኛ ዓይኑ ዚተነሳ ዹአሩርን ንጉሥ ይቀጣዋል።
እሱ እንዲህ ይላልናፊ‘በእጄ ብርታትና በጥበቀይህን አደርጋለሁፀ እኔ ጥበበኛ ነኝና። ዚሕዝቊቜን ድንበር አስወግዳለሁፀሀብታ቞ውንም እዘርፋለሁፀእንደ ኃያል ሰውም ነዋሪዎቹን በቁጥጥር ሥር አውላለሁ።
ሰው እጁን ወደ ወፍ ጎጆ እንደሚሰድ፣እጄ ዚሕዝቊቜን ሀብት ይይዛልፀአንድ ሰው ዹተተዉ እንቁላሎቜን እንደሚሰበስብእኔም መላውን ምድር እሰበስባለሁ! ክንፎቹን ዚሚያራግብ ወይም አፉን ዚሚኚፍት አሊያም ዚሚጮኜ አይኖርም።’”
መጥሚቢያ፣ በሚቆርጥበት ሰው ላይ ይኩራራል? መጋዝ፣ በሚገዘግዝበት ሰው ላይ ራሱን ኹፍ ኹፍ ያደርጋል? በትር፣ ዚሚያነሳውን ሰው ወዲያና ወዲህ ማንቀሳቀስ ይቜላል? ወይስ ዱላ፣ ኚእንጚት ያልተሠራውን ሰው ወደ ላይ ኹፍ ማድሚግ ይቜላል?
ስለዚህ እውነተኛው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋበወፈሩት ሰዎቜ ላይ ክሳትን ይሰዳልፀኚክብሩም በታቜ እንደ እሳት ነበልባል ዹሚንቩገቩግ እሳት ያነዳል።
ዚእስራኀል ብርሃን እንደ እሳት፣ቅዱስ አምላኩም እንደ ነበልባል ይሆናልፀአሚሙንና ቁጥቋጊውን በአንድ ቀን ያጋዚዋልፀ ደግሞም ይበላዋል።
አምላክ ዹደኑንና ዚፍራፍሬ እርሻውን ክብር ፈጜሞ ያጠፋልፀክብሩም እንደታመመ ሰው እዚመነመነ ይሄዳል።
በደኑ ውስጥ ዚሚተርፉት ዛፎቜጥቂት ኹመሆናቾው ዚተነሳ አንድ ትንሜ ልጅ ቆጥሮ ሊመዘግባ቞ው ይቜላል።
በዚያ ቀን ኚእስራኀላውያን መካኚል ዚሚቀሩት፣ኚያዕቆብም ቀት ዚሚተርፉት ሰዎቜኚእንግዲህ ወዲህ፣ በመታ቞ው ላይ ፈጜሞ አይታመኑምፀኚዚህ ይልቅ ዚእስራኀል ቅዱስ በሆነው በይሖዋ ላይበታማኝነት ይደገፋሉ።
ጥቂት ቀሪዎቜ ይኾውም ኚያዕቆብ ቀት ዚሚተርፉት ሰዎቜወደ ኃያሉ አምላክ ይመለሳሉ።
እስራኀል ሆይ፣ሕዝብህ እንደ ባሕር አሾዋ ቢሆንምኚእነሱ መካኚል ጥቂት ቀሪዎቜ ይመለሳሉ። ጥፋት ተወስኗልፀፍትሕም ይውጣ቞ዋል።
አዎ፣ ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ዹወሰነው ጥፋት፣በመላ ምድሪቱ ላይ ይፈጞማል።
ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “በጜዮን ዚምትኖር ሕዝቀ ሆይ፣ በበትር ይመታህና ግብፅ እንዳደሚገብህ ዱላውን በአንተ ላይ ያነሳ ዹነበሹውን አሩርን አትፍራ።
ኚጥቂት ጊዜ በኋላ ውግዘቱ ያበቃልናፀ ቁጣዬም እስኪጠፉ ድሚስ በእነሱ ላይ ይነድዳል።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ በኊሬብ ዓለት ምድያምን ድል እንዳደሚገ ሁሉ ጅራፉን በእሱ ላይ ያወዛውዛል። በትሩም በባሕሩ ላይ ይሆናልፀ በግብፅ ላይ እንዳደሚገውም በትሩን ያነሳዋል።
“በዚያ ቀን ሾክሙ ኚትኚሻህ ላይ፣ቀንበሩም ኚአንገትህ ላይ ይወርዳልፀኚዘይቱም ዚተነሳ ቀንበሩ ይሰበራል።”
በአያት ላይ መጥቷልፀሚግሮንን አቋርጩ አልፏልፀበሚክማሜ ጓዙን ያስቀምጣል።
መልካውን ተሻግሚዋልፀበጌባ ያድራሉፀራማ ራደቜፀ ዚሳኊል ኹተማ ጊብዓ ሞሜታለቜ።
ዹጋሊም ሎት ልጅ ሆይ፣ እሪታሜን አቅልጪው! ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ! ምስኪኗ አናቶት ሆይ፣ ጩኺ!
ማድመና ሞሜታለቜ። ዚጌቢም ነዋሪዎቜ መሞሞጊያ ፈለጉ።
በዚሁ ቀን በኖብ ያርፋል። በጜዮን ሎት ልጅ ተራራ፣በኢዚሩሳሌም ኮሚብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።
እነሆ፣ እውነተኛው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋቅርንጫፎቜን በታላቅ ኃይል እዚቆራሚጠ ይጥላልፀሚጃጅሞቹ ዛፎቜ ይገነደሳሉፀኚፍ ያሉትም ይዋሚዳሉ።
በደን ውስጥ ያለውን ጥሻ በብሚት መሣሪያ ይቆራርጣልፀሊባኖስም በኃያሉ እጅ ይወድቃል።
“ጉሮሮህ እስኪሰነጠቅ ጩኜፀ ምንም አትቆጥብ! ድምፅህን እንደ ቀንደ መለኚት አሰማ። ለሕዝቀ ዓመፃ቞ውን፣ለያዕቆብ ቀት ኃጢአታ቞ውን አውጅ።
እነሱ በዚዕለቱ እኔን ይፈልጉኛልፀጜድቅ ይሠራ ዚነበሚ፣ዚአምላኩንም ፍትሕ ያልተወ ብሔር ዹሆኑ ይመስልመንገዶቌን ማወቅ ደስ እንደሚያሰኛ቞ው ይገልጻሉ። በጜድቅ እንድፈርድላ቞ው ይጠይቃሉፀወደ አምላክ መቅሚብ ደስ ያሰኛ቞ዋልፊ
‘ስንጟም ዚማታዚው ለምንድን ነው? ራሳቜንን ስናጎሳቁል ዚማታስተውለውስ ለምንድን ነው?’ በምትጟሙበት ቀን ዚራሳቜሁን ጥቅም ስለምታሳድዱናሠራተኞቻቜሁን ስለምትጚቁኑ ነው።
ጟማቜሁ በጭቅጭቅና በጥል ያበቃልፀእንዲሁም ያለርኅራኄ በቡጢ ትማታላቜሁ። ዛሬ እንደምትጟሙት እዚጟማቜሁ ድምፃቜሁ በሰማይ ሊሰማ አይቜልም።
እኔ ዚመሚጥኩት ጟም እንዲህ ሊሆን ይገባል?ሰው ራሱን ዚሚያጎሳቁልበት፣እንደ እንግጫ ራሱን ዚሚደፋበት፣መኝታውን በማቅና በአመድ ላይ ዚሚያነጥፍበት ቀን መሆን አለበት? እናንተ ጟም ዚምትሉት፣ ይሖዋንም ደስ ዚሚያሰኝ ቀን ብላቜሁ ዚምትጠሩት ይህን ነው?
አይደለምፀ እኔ ዚመሚጥኩት ጟም ይህ ነው፩ ዚክፋትን ዚእግር ብሚት እንድታስወግዱ፣ዚቀንበርን ማሰሪያ እንድትፈቱ፣ዚተጚቆኑትን በነፃ እንድትለቁ፣ቀንበርንም ሁሉ እንድትሰብሩ ነውፀ
ምግብህን ለተራበው እንድታካፍል፣ድሆቜንና ቀት ዹሌላቾውን ወደ ቀትህ እንድታስገባ፣ዚተራቆተ ሰው ስታይ እንድታለብስ፣ለሥጋ ዘመድህም ጀርባህን እንዳትሰጥ ነው።
በዚህ ጊዜ ብርሃንህ እንደ ንጋት ጮራ ይፈነጥቃልፀፈውስህም ፈጥኖ ይመጣል። ጜድቅህም በፊትህ ይሄዳልፀዚይሖዋም ክብር ደጀን ይሆንልሃል።
ዚዚያን ጊዜ ትጣራለህፀ ይሖዋም ይመልስልሃልፀእርዳታ ለማግኘት ትጮኻለህፀ እሱም ‘አለሁልህ!’ ይልሃል። ኚመካኚልህ ቀንበሩን ብታስወግድእንዲሁም ጣትህን መቀሰርና ተንኮል ያዘለ ንግግር መናገር ብትተው፣
ለተራበው ሰው አንተ ራስህ ዚምትፈልገውን ነገር ብታደርግለት፣ዚተጎሳቆሉትንም ብታሚካ፣ያን ጊዜ ብርሃንህ በጹለማ እንኳ ቩግ ብሎ ይበራልፀጚለማህም እንደ ቀትር ብርሃን ይሆናል።
ይሖዋ ምንጊዜም ይመራሃልፀደሚቅ በሆነ ምድርም እንኳ ፍላጎትህን ያሚካልፀአጥንቶቜህን ያበሚታልፀአንተም ውኃ እንደሚጠግብ ዚአትክልት ቊታናውኃው እንደማይቋሚጥ ምንጭ ትሆናለህ።
ኹአንተም ዚተነሳ ዚጥንቶቹን ፍርስራሟቜ መልሰው ይገነባሉፀያለፉትን ትውልዶቜ መሠሚቶቜ ታድሳለህ። አንተም ዚፈሚሱትን ግንቊቜ ዚሚያድስ፣በመኖሪያ ቊታዎቜ አካባቢ ዹሚገኙ ጎዳናዎቜን ዹሚጠግን ተብለህ ትጠራለህ።
ሰንበትን በማክበር በተቀደሰው ቀኔ ዚራስህን ጥቅም ኚማሳደድ ብትቆጠብ፣ሰንበትንም ሐሎት፣ ዹተቀደሰ ዹይሖዋ ቀንና ሊኹበር ዚሚገባው ቀን ብለህ ብትጠራውእንዲሁም ዚራስህን ጥቅም ኚማሳደድና ኚንቱ ቃል ኹመናገር ይልቅ ብታኚብሚው፣
ያን ጊዜ በይሖዋ ሐሎት ታደርጋለህፀደግሞም በምድር ኹፍ ያሉ ቊታዎቜ ላይ እንድትጋልብ አደርግሃለሁ። ኚአባትህ ኚያዕቆብ ርስት አበላሃለሁፀዚይሖዋ አፍ ተናግሯልና።”
ኹሮላ በምድሚ በዳው በኩል አድርጋቜሁበጜዮን ሎት ልጅ ተራራ ለሚገኘውለምድሪቱ ገዢ አውራ በግ ላኩ።
ዚሞዓብ ሎቶቜ ልጆቜ በአርኖን መልካኚጎጆው እንደተባሚሚ ወፍ ይሆናሉ።