text
stringlengths
4
267
ታላላቅ በሆኑትና ከፍ ከፍ ባሉት አርዘ ሊባኖሶች ሁሉ ላይእንዲሁም በባሳን የባሉጥ ዛፎች ሁሉ ላይ፣
ታላላቅ በሆኑት ተራሮች ሁሉናበረጃጅም ኮረብቶች ሁሉ ላይ፣
ረጅም በሆነ ማማ ሁሉና ጠንካራ በሆነ ግንብ ሁሉ ላይ፣
በተርሴስ መርከቦች ሁሉናበሚያማምሩ ጀልባዎች ሁሉ ላይ ይደርሳል።
ትዕቢተኛ ሰው ይዋረዳል፤እብሪተኞችም አንገታቸውን ይደፋሉ። በዚያም ቀን ይሖዋ ብቻ ከፍ ከፍ ይደረጋል።
ከንቱ የሆኑት አማልክት ሙሉ በሙሉ ይወገዳሉ።
ይሖዋ ምድርን በሽብር ለማንቀጥቀጥ በሚነሳበት ጊዜ፣አስፈሪ ከመሆኑ የተነሳናከታላቅ ግርማው የተነሳሰዎች በዓለት ዋሻዎችናበጉድጓዶች ውስጥ ይደበቃሉ።
በዚያ ቀን፣ ሰዎች በፊታቸው ይሰግዱ ዘንድለራሳቸው የሠሯቸውን ከንቱ የሆኑ የብርና የወርቅ አማልክትለአይጥና ለሌሊት ወፎች ይወረውራሉ፤
ይሖዋ ምድርን በሽብር ለማንቀጥቀጥ በሚነሳበት ጊዜ፣አስፈሪ ከመሆኑ የተነሳናከታላቅ ግርማው የተነሳበዓለት ዋሻዎችናበቋጥኝ ስንጥቆች ውስጥ ይደበቃሉ።
ለራሳችሁ ስትሉ፣ከአፍንጫው እንደሚወጣ እስትንፋስ በሆነ ሰው አትታመኑ። ለመሆኑ እሱ ያን ያህል ቦታ እንዲሰጠው የሚያደርግ ምን ነገር አለ?
“አሁን ግን፣ አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፣የመረጥኩህም እስራኤል ሆይ፣ ስማ።
የሠራህና ያበጀህ፣ከማህፀን ጀምሮ የረዳህይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘አገልጋዬ ያዕቆብ፣የመረጥኩህም የሹሩን ሆይ፣ አትፍራ።
ለተጠማው ውኃ አፈሳለሁና፤በደረቁ ምድርም ላይ ጅረቶች እንዲፈስሱ አደርጋለሁ። መንፈሴን በዘርህ ላይ፣በረከቴንም በልጅ ልጆችህ ላይ አፈሳለሁ።
እነሱም በለምለም ሣር መካከል፣በጅረቶችም ዳር እንዳሉ የአኻያ ዛፎች ይበቅላሉ።
አንዱ “እኔ የይሖዋ ነኝ” ይላል። ሌላውም ራሱን በያዕቆብ ስም ይጠራል፤ሌላው ደግሞ በእጁ ላይ “የይሖዋ ነኝ” ብሎ ይጽፋል። ደግሞም ራሱን በእስራኤል ስም ይጠራል።’
የእስራኤል ንጉሥ የሆነውና እስራኤልን የተቤዠው ይሖዋ፣የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘የመጀመሪያው እኔ ነኝ፤ የመጨረሻውም እኔ ነኝ። ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም።
እንደ እኔ ያለ ማን ነው? በድፍረት ይናገር፤ ያሳውቅም፤ ማስረጃውንም ለእኔ ያቅርብ! የጥንቱን ሕዝብ ካቋቋምኩበት ጊዜ ጀምሮ፣በቅርቡ የሚከሰቱትንናወደፊት የሚሆኑትን ነገሮች ይናገሩ።
ስጋት አይደርባችሁ፤በፍርሃትም አትሽመድመዱ። አስቀድሜ ለእያንዳንዳችሁ አልነገርኳችሁም? ደግሞስ አላሳወቅኳችሁም? እናንተ ምሥክሮቼ ናችሁ። ከእኔ ሌላ አምላክ አለ? በፍጹም፣ ሌላ ዓለት የለም፤ እኔ የማውቀው አንድም የለም።’”
የተቀረጹ ምስሎችን የሚሠሩ ሁሉ ከንቱ ናቸው፤የሚወዷቸውም ጣዖቶች ምንም ጥቅም የላቸውም። እንደ ምሥክሮቻቸው እነሱም ምንም አያዩም፤ ምንም አያውቁም፤በመሆኑም ሠሪዎቻቸው ለኀፍረት ይዳረጋሉ።
ለምንም የማይጠቅም አምላክ የሚሠራወይም የብረት ምስል የሚያበጅ ማን ነው?
እነሆ፣ ባልደረቦቹ ሁሉ ያፍራሉ! የእጅ ጥበብ ባለሙያዎቹ ተራ ሰዎች ናቸው። ሁሉም ተሰብስበው ይቁሙ። በፍርሃት ይዋጣሉ፤ ሁሉም ያፍራሉ።
አንጥረኛ በመሣሪያው ተጠቅሞ ብረቱን በከሰል ፍም ላይ ይሠራዋል። ብርቱ በሆነው ክንዱበመዶሻ ቅርጽ ይሰጠዋል። ከዚያም ይርበዋል፤ ጉልበትም ያጣል፤ውኃ ስለማይጠጣ ይደክማል።
እንጨት ጠራቢው በገመድ ይለካል፤ በቀይ ጠመኔም ንድፍ ያወጣል። በመሮም ይጠርበዋል፤ በማክበቢያም ምልክት ያደርግበታል። በሰው አምሳል ይቀርጸዋል፤የሰውንም ውበት ያላብሰዋል፤ከዚያም ቤት ውስጥ ያስቀምጠዋል።
አርዘ ሊባኖስ የሚቆርጥ ሰው አለ። እሱም አንድ የዛፍ ዝርያ ይኸውም የባሉጥ ዛፍ ይመርጣል፤እስኪጠነክርለት ድረስ በጫካው ውስጥ ባሉት ዛፎች መካከል ይተወዋል። የላውሮ ዛፍ ይተክላል፤ ዝናብም ያሳድገዋል።
ከዚያም ሰው ለማገዶ ይጠቀምበታል። የተወሰነውን እንጨት ወስዶ በማንደድ እሳት ይሞቃል፤እሳት አያይዞም ዳቦ ይጋግራል። ይሁንና አምላክ ሠርቶም ያመልከዋል። የተቀረጸ ምስል ሠርቶበት በፊቱ ይደፋል።
ግማሹን በእሳት ያነደዋል፤በዚያም ላይ የሚበላውን ሥጋ ይጠብሳል፤ በልቶም ይጠግባል። እሳቱንም እየሞቀ “እሰይ! እሳቱን እያየሁ ሞቅኩ” ይላል።
የቀረውን ግን ምስል ይቀርጽበታል፤ አምላክ አድርጎም ይሠራዋል። በፊቱም ተደፍቶ ይሰግድለታል። “አንተ አምላኬ ነህና አድነኝ” ብሎ ወደ እሱ ይጸልያል።
ምንም አያውቁም እንዲሁም አያስተውሉም፤ምክንያቱም ዓይኖቻቸው ተጨፍነዋል፤ ማየትም አይችሉም፤ልባቸውም ማስተዋል ጎድሎታል።
ቆም ብሎ በልቡ ያሰበወይም እውቀትም ሆነ ማስተዋል ኖሮት እንዲህ ብሎ የተናገረ የለም፦ “ግማሹን እሳት አንድጄበታለሁ፤በፍሙም ላይ ዳቦ ጋግሬአለሁ፤ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ። ታዲያ በቀረው እንጨት አስጸያፊ ነገር መሥራቴ ተገቢ ነው? ከዛፍ ለተቆረጠ እንጨት መስገድ ይገባኛል?”
እሱ አመድ ይበላል። የተታለለው የገዛ ልቡ አስቶታል። ራሱን ሊያድን አይችልም፤ ደግሞም “በቀኝ እጄ ያለው ውሸት አይደለም?” አይልም።
“ያዕቆብ ሆይ፣ አንተም እስራኤል ሆይ፣አገልጋዬ ስለሆንክ እነዚህን ነገሮች አስታውስ። እኔ ሠርቼሃለሁ፤ አንተ የእኔ አገልጋይ ነህ። እስራኤል ሆይ፣ አልረሳህም።
በደልህን በደመና፣ኃጢአትህንም ጥቅጥቅ ባለ ደመና እሸፍነዋለሁ። ወደ እኔ ተመለስ፤ እኔም እቤዥሃለሁ።
እናንተ ሰማያት በደስታ እልል በሉ!ይሖዋ እርምጃ ወስዷልና። እናንተ ጥልቅ የምድር ክፍሎች በድል አድራጊነት ጩኹ! እናንተ ተራሮች፣ አንተም ደን ሆይ፣በውስጡም ያላችሁ ዛፎች ሁሉ በደስታ እልል በሉ! ይሖዋ ያዕቆብን ተቤዥቷልና፤በእስራኤልም ላይ ግርማውን ገልጧል።”
የተቤዠህና ከማህፀን ጀምሮ የሠራህይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ሁሉንም ነገር የሠራሁ እኔ ይሖዋ ነኝ። ብቻዬን ሰማያትን ዘረጋሁ፤ምድርንም ሠራሁ። ያኔ ከእኔ ጋር ማን ነበር?
የሆነ ያልሆነውን የሚቀባጥሩ ሰዎችን ምልክቶች አከሽፋለሁ፤ሟርተኞችንም ነፈዝ አደርጋለሁ፤ጥበበኞቹንም ግራ አጋባለሁ፤እውቀታቸውንም ሞኝነት አደርጋለሁ፤
የአገልጋዬን ቃል እውን አደርጋለሁ፤የመልእክተኞቼንም ትንቢት ሙሉ በሙሉ እፈጽማለሁ፤ስለ ኢየሩሳሌም ‘የሰው መኖሪያ ትሆናለች’፤ ስለ ይሁዳ ከተሞችም ‘ዳግም ይገነባሉ፤ፍርስራሾቿንም መልሼ እሠራለሁ’ እላለሁ፤
ጥልቁን ውኃ ‘ደረቅ ሁን፤ወንዞችህንም ሁሉ አደርቃለሁ’ እላለሁ፤
ስለ ቂሮስ ‘እሱ እረኛዬ ነው፤ፈቃዴንም ሁሉ ሙሉ በሙሉ ይፈጽማል’ እላለሁ፤ስለ ኢየሩሳሌም ‘ዳግም ትገነባለች’፤ ስለ ቤተ መቅደሱም ‘መሠረትህ ይጣላል’ እላለሁ።”
ጽድቋ እንደ ደማቅ ብርሃን እስኪፈነጥቅ፣መዳኗም እንደ ችቦ እስኪቀጣጠል ድረስለጽዮን ስል ጸጥ አልልም፤ለኢየሩሳሌምም ስል ዝም ብዬ አልቀመጥም።
“አንቺ ሴት ሆይ፣ ብሔራት ጽድቅሽን፣ነገሥታትም ሁሉ ክብርሽን ያያሉ። አንቺም የይሖዋ አፍ በሚያወጣልሽአዲስ ስም ትጠሪያለሽ።
በይሖዋ እጅ የውበት ዘውድ፣በአምላክሽ መዳፍ የንጉሥ ጥምጥም ትሆኛለሽ።
ከእንግዲህ የተተወች ሴት አትባዪም፤ምድርሽም ከእንግዲህ ባድማ ተብላ አትጠራም። ከዚህ ይልቅ “ደስታዬ በእሷ ነው” ተብለሽ ትጠሪያለሽ፤ምድርሽም “ያገባች ሴት” ትባላለች። ይሖዋ በአንቺ ደስ ይለዋልና፤ምድርሽም እንዳገባች ሴት ትሆናለች።
አንድ ወጣት ድንግሊቱን እንደሚያገባ፣ወንዶች ልጆችሽ አንቺን ያገባሉ። አንድ ሙሽራ በሙሽራይቱ ሐሴት እንደሚያደርግ፣አምላክሽም በአንቺ ሐሴት ያደርጋል።
ኢየሩሳሌም ሆይ፣ በቅጥሮችሽ ላይ ጠባቂዎች አቁሜአለሁ። ቀኑንም ሆነ ሌሊቱን በሙሉ፣ መቼም ቢሆን ዝም ሊሉ አይገባም። እናንተ ስለ ይሖዋ የምትናገሩ፣ፈጽሞ አትረፉ፤
ደግሞም ኢየሩሳሌምን አጽንቶ እስኪመሠርታት፣አዎ፣ የምድር ምስጋና እስኪያደርጋት ድረስ ምንም እረፍት አትስጡት።”
ይሖዋ በቀኝ እጁ፣ ብርቱ በሆነውም ክንዱ እንዲህ ሲል ምሏል፦ “ከእንግዲህ እህልሽን ለጠላቶችሽ መብል እንዲሆን አልሰጥም፤የደከምሽበትንም አዲስ የወይን ጠጅ የባዕድ አገር ሰዎች አይጠጡትም።
ሆኖም እህሉን፣ የሚሰበስቡት ሰዎች ይበሉታል፤ ይሖዋንም ያወድሳሉ፤ወይኑንም፣ የሚለቅሙት ሰዎች ቅዱስ በሆኑት ቅጥር ግቢዎቼ ውስጥ ይጠጡታል።”
በበሮቹ በኩል እለፉ፤ እለፉ። ለሕዝቡ መንገዱን ጥረጉ። ሥሩ፤ አውራ ጎዳናውን ሥሩ። ድንጋዮቹን አስወግዱ። ለሕዝቦችም ምልክት አቁሙ።
እነሆ፣ ይሖዋ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ አውጇል፦ “ለጽዮን ሴት ልጅ‘እነሆ፣ መዳንሽ ቀርቧል። እነሆ፣ የሚከፍለው ወሮታ ከእሱ ጋር ነው፤የሚመልሰውም ብድራት በፊቱ አለ’ በሏት።”
ቅዱስ ሕዝብ፣ ይሖዋ የተቤዣቸው ተብለው ይጠራሉ፤አንቺም “እጅግ የምትፈለግ፣” “ያልተተወች ከተማ” ተብለሽ ትጠሪያለሽ።
ጉዳት የሚያስከትሉ ሥርዓቶችን የሚያወጡ፣ሁልጊዜ ጨቋኝ ድንጋጌዎችን የሚያረቁ ወዮላቸው!
የድሆችን አቤቱታ ላለመስማት፣በሕዝቤም መካከል የሚገኙትን ምስኪኖች ፍትሕ ለመንፈግ ሕግ የሚያወጡ ወዮላቸው!መበለቶችን ይበዘብዛሉ፤አባት የሌላቸውንም ልጆች ይዘርፋሉ።
በምትመረመሩበት ቀን፣ጥፋትም ከሩቅ በሚመጣበት ጊዜ ምን ይውጣችሁ ይሆን? እርዳታ ለማግኘት ወደ ማን ትሸሻላችሁ?ሀብታችሁንስ የት ትተዉት ይሆን?
በእስረኞች መካከል ተኮራምታችሁ ከመቀመጥናበሞቱ ሰዎች መካከል ከመውደቅ በስተቀር የምታተርፉት ነገር የለም። ከዚህ ሁሉ የተነሳ ቁጣው አልተመለሰም፤ይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘረጋ ነው።
“የቁጣዬ በትር የሆነውንናውግዘቴን የምገልጽበትን ዱላ በእጁ የያዘውንአሦራዊ ተመልከት!
ከሃዲ በሆነው ብሔር ላይ፣እጅግ ባስቆጣኝም ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፤ብዙ ምርኮ እንዲወስድ፣ ብዙ ሀብት እንዲዘርፍናሕዝቡን በጎዳናዎች ላይ እንዳለ ጭቃ እንዲረጋግጥ አዘዋለሁ።
እሱ ግን እንዲህ ያለ ዝንባሌ አይኖረውም፤ልቡም እንዲህ ለማድረግ አያቅድም፤የልቡ ፍላጎት መደምሰስናጥቂት ሳይሆን ብዙ ብሔራትን ማጥፋት ነውና።
እሱ እንዲህ ይላል፦‘አለቆች ሆነው የሚያገለግሉኝ ሁሉ ነገሥታት አይደሉም?
ካልኖ እንደ ካርከሚሽ አይደለችም? ሃማት እንደ አርጳድ አይደለችም? ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደለችም?
እጄ በኢየሩሳሌምና በሰማርያ ካሉት ይበልጥ በርካታ የተቀረጹ ምስሎች ያሏቸውንናከንቱ አማልክት የሚያመልኩትን መንግሥታት ይዟል!
በሰማርያና ከንቱ በሆኑት አማልክቷ ላይ እንዳደረግኩት ሁሉ፣በኢየሩሳሌምና በጣዖቶቿስ ላይ እንዲሁ አላደርግም?’
“ይሖዋ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም የሚያከናውነውን ሥራ ሁሉ ሲያጠናቅቅ በእብሪተኛ ልቡ፣ በኩራቱና በትዕቢተኛ ዓይኑ የተነሳ የአሦርን ንጉሥ ይቀጣዋል።
እሱ እንዲህ ይላልና፦‘በእጄ ብርታትና በጥበቤይህን አደርጋለሁ፤ እኔ ጥበበኛ ነኝና። የሕዝቦችን ድንበር አስወግዳለሁ፤ሀብታቸውንም እዘርፋለሁ፤እንደ ኃያል ሰውም ነዋሪዎቹን በቁጥጥር ሥር አውላለሁ።
ሰው እጁን ወደ ወፍ ጎጆ እንደሚሰድ፣እጄ የሕዝቦችን ሀብት ይይዛል፤አንድ ሰው የተተዉ እንቁላሎችን እንደሚሰበስብእኔም መላውን ምድር እሰበስባለሁ! ክንፎቹን የሚያራግብ ወይም አፉን የሚከፍት አሊያም የሚጮኽ አይኖርም።’”
መጥረቢያ፣ በሚቆርጥበት ሰው ላይ ይኩራራል? መጋዝ፣ በሚገዘግዝበት ሰው ላይ ራሱን ከፍ ከፍ ያደርጋል? በትር፣ የሚያነሳውን ሰው ወዲያና ወዲህ ማንቀሳቀስ ይችላል? ወይስ ዱላ፣ ከእንጨት ያልተሠራውን ሰው ወደ ላይ ከፍ ማድረግ ይችላል?
ስለዚህ እውነተኛው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋበወፈሩት ሰዎች ላይ ክሳትን ይሰዳል፤ከክብሩም በታች እንደ እሳት ነበልባል የሚንቦገቦግ እሳት ያነዳል።
የእስራኤል ብርሃን እንደ እሳት፣ቅዱስ አምላኩም እንደ ነበልባል ይሆናል፤አረሙንና ቁጥቋጦውን በአንድ ቀን ያጋየዋል፤ ደግሞም ይበላዋል።
አምላክ የደኑንና የፍራፍሬ እርሻውን ክብር ፈጽሞ ያጠፋል፤ክብሩም እንደታመመ ሰው እየመነመነ ይሄዳል።
በደኑ ውስጥ የሚተርፉት ዛፎችጥቂት ከመሆናቸው የተነሳ አንድ ትንሽ ልጅ ቆጥሮ ሊመዘግባቸው ይችላል።
በዚያ ቀን ከእስራኤላውያን መካከል የሚቀሩት፣ከያዕቆብም ቤት የሚተርፉት ሰዎችከእንግዲህ ወዲህ፣ በመታቸው ላይ ፈጽሞ አይታመኑም፤ከዚህ ይልቅ የእስራኤል ቅዱስ በሆነው በይሖዋ ላይበታማኝነት ይደገፋሉ።
ጥቂት ቀሪዎች ይኸውም ከያዕቆብ ቤት የሚተርፉት ሰዎችወደ ኃያሉ አምላክ ይመለሳሉ።
እስራኤል ሆይ፣ሕዝብህ እንደ ባሕር አሸዋ ቢሆንምከእነሱ መካከል ጥቂት ቀሪዎች ይመለሳሉ። ጥፋት ተወስኗል፤ፍትሕም ይውጣቸዋል።
አዎ፣ ሉዓላዊው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ የወሰነው ጥፋት፣በመላ ምድሪቱ ላይ ይፈጸማል።
ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “በጽዮን የምትኖር ሕዝቤ ሆይ፣ በበትር ይመታህና ግብፅ እንዳደረገብህ ዱላውን በአንተ ላይ ያነሳ የነበረውን አሦርን አትፍራ።
ከጥቂት ጊዜ በኋላ ውግዘቱ ያበቃልና፤ ቁጣዬም እስኪጠፉ ድረስ በእነሱ ላይ ይነድዳል።
የሠራዊት ጌታ ይሖዋ በኦሬብ ዓለት ምድያምን ድል እንዳደረገ ሁሉ ጅራፉን በእሱ ላይ ያወዛውዛል። በትሩም በባሕሩ ላይ ይሆናል፤ በግብፅ ላይ እንዳደረገውም በትሩን ያነሳዋል።
“በዚያ ቀን ሸክሙ ከትከሻህ ላይ፣ቀንበሩም ከአንገትህ ላይ ይወርዳል፤ከዘይቱም የተነሳ ቀንበሩ ይሰበራል።”
በአያት ላይ መጥቷል፤ሚግሮንን አቋርጦ አልፏል፤በሚክማሽ ጓዙን ያስቀምጣል።
መልካውን ተሻግረዋል፤በጌባ ያድራሉ፤ራማ ራደች፤ የሳኦል ከተማ ጊብዓ ሸሽታለች።
የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፣ እሪታሽን አቅልጪው! ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ! ምስኪኗ አናቶት ሆይ፣ ጩኺ!
ማድመና ሸሽታለች። የጌቢም ነዋሪዎች መሸሸጊያ ፈለጉ።
በዚሁ ቀን በኖብ ያርፋል። በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ፣በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።
እነሆ፣ እውነተኛው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋቅርንጫፎችን በታላቅ ኃይል እየቆራረጠ ይጥላል፤ረጃጅሞቹ ዛፎች ይገነደሳሉ፤ከፍ ያሉትም ይዋረዳሉ።
በደን ውስጥ ያለውን ጥሻ በብረት መሣሪያ ይቆራርጣል፤ሊባኖስም በኃያሉ እጅ ይወድቃል።
“ጉሮሮህ እስኪሰነጠቅ ጩኽ፤ ምንም አትቆጥብ! ድምፅህን እንደ ቀንደ መለከት አሰማ። ለሕዝቤ ዓመፃቸውን፣ለያዕቆብ ቤት ኃጢአታቸውን አውጅ።
እነሱ በየዕለቱ እኔን ይፈልጉኛል፤ጽድቅ ይሠራ የነበረ፣የአምላኩንም ፍትሕ ያልተወ ብሔር የሆኑ ይመስልመንገዶቼን ማወቅ ደስ እንደሚያሰኛቸው ይገልጻሉ። በጽድቅ እንድፈርድላቸው ይጠይቃሉ፤ወደ አምላክ መቅረብ ደስ ያሰኛቸዋል፦
‘ስንጾም የማታየው ለምንድን ነው? ራሳችንን ስናጎሳቁል የማታስተውለውስ ለምንድን ነው?’ በምትጾሙበት ቀን የራሳችሁን ጥቅም ስለምታሳድዱናሠራተኞቻችሁን ስለምትጨቁኑ ነው።
ጾማችሁ በጭቅጭቅና በጥል ያበቃል፤እንዲሁም ያለርኅራኄ በቡጢ ትማታላችሁ። ዛሬ እንደምትጾሙት እየጾማችሁ ድምፃችሁ በሰማይ ሊሰማ አይችልም።
እኔ የመረጥኩት ጾም እንዲህ ሊሆን ይገባል?ሰው ራሱን የሚያጎሳቁልበት፣እንደ እንግጫ ራሱን የሚደፋበት፣መኝታውን በማቅና በአመድ ላይ የሚያነጥፍበት ቀን መሆን አለበት? እናንተ ጾም የምትሉት፣ ይሖዋንም ደስ የሚያሰኝ ቀን ብላችሁ የምትጠሩት ይህን ነው?
አይደለም፤ እኔ የመረጥኩት ጾም ይህ ነው፦ የክፋትን የእግር ብረት እንድታስወግዱ፣የቀንበርን ማሰሪያ እንድትፈቱ፣የተጨቆኑትን በነፃ እንድትለቁ፣ቀንበርንም ሁሉ እንድትሰብሩ ነው፤
ምግብህን ለተራበው እንድታካፍል፣ድሆችንና ቤት የሌላቸውን ወደ ቤትህ እንድታስገባ፣የተራቆተ ሰው ስታይ እንድታለብስ፣ለሥጋ ዘመድህም ጀርባህን እንዳትሰጥ ነው።
በዚህ ጊዜ ብርሃንህ እንደ ንጋት ጮራ ይፈነጥቃል፤ፈውስህም ፈጥኖ ይመጣል። ጽድቅህም በፊትህ ይሄዳል፤የይሖዋም ክብር ደጀን ይሆንልሃል።
የዚያን ጊዜ ትጣራለህ፤ ይሖዋም ይመልስልሃል፤እርዳታ ለማግኘት ትጮኻለህ፤ እሱም ‘አለሁልህ!’ ይልሃል። ከመካከልህ ቀንበሩን ብታስወግድእንዲሁም ጣትህን መቀሰርና ተንኮል ያዘለ ንግግር መናገር ብትተው፣
ለተራበው ሰው አንተ ራስህ የምትፈልገውን ነገር ብታደርግለት፣የተጎሳቆሉትንም ብታረካ፣ያን ጊዜ ብርሃንህ በጨለማ እንኳ ቦግ ብሎ ይበራል፤ጨለማህም እንደ ቀትር ብርሃን ይሆናል።
ይሖዋ ምንጊዜም ይመራሃል፤ደረቅ በሆነ ምድርም እንኳ ፍላጎትህን ያረካል፤አጥንቶችህን ያበረታል፤አንተም ውኃ እንደሚጠግብ የአትክልት ቦታናውኃው እንደማይቋረጥ ምንጭ ትሆናለህ።
ከአንተም የተነሳ የጥንቶቹን ፍርስራሾች መልሰው ይገነባሉ፤ያለፉትን ትውልዶች መሠረቶች ታድሳለህ። አንተም የፈረሱትን ግንቦች የሚያድስ፣በመኖሪያ ቦታዎች አካባቢ የሚገኙ ጎዳናዎችን የሚጠግን ተብለህ ትጠራለህ።
ሰንበትን በማክበር በተቀደሰው ቀኔ የራስህን ጥቅም ከማሳደድ ብትቆጠብ፣ሰንበትንም ሐሴት፣ የተቀደሰ የይሖዋ ቀንና ሊከበር የሚገባው ቀን ብለህ ብትጠራውእንዲሁም የራስህን ጥቅም ከማሳደድና ከንቱ ቃል ከመናገር ይልቅ ብታከብረው፣
ያን ጊዜ በይሖዋ ሐሴት ታደርጋለህ፤ደግሞም በምድር ከፍ ያሉ ቦታዎች ላይ እንድትጋልብ አደርግሃለሁ። ከአባትህ ከያዕቆብ ርስት አበላሃለሁ፤የይሖዋ አፍ ተናግሯልና።”
ከሴላ በምድረ በዳው በኩል አድርጋችሁበጽዮን ሴት ልጅ ተራራ ለሚገኘውለምድሪቱ ገዢ አውራ በግ ላኩ።
የሞዓብ ሴቶች ልጆች በአርኖን መልካከጎጆው እንደተባረረ ወፍ ይሆናሉ።