text
stringlengths
4
267
“ምክር ለግሱፀ ውሳኔውን ተግባራዊ አድርጉ። እኩለ ቀን ላይ እንደ ምሜት ጹለማ ያለ ጥላ አጥሉ። ዚተበተኑትን ሞሜጉፀ ዚሚሞሹትንም አሳልፋቜሁ አትስጡ።
ሞዓብ ሆይ፣ ዚተበተኑት ሕዝቊቌ በአንተ ውስጥ ይኑሩ። ኚአጥፊው ዚተነሳ መሞሞጊያ ቊታ ሁንላ቞ው። ጹቋኙ ፍጻሜው ይመጣልፀጥፋቱም ያበቃልፀሌሎቜን ዚሚሚግጡትም ኚምድር ገጜ ይጠፋሉ።
ኚዚያም ዙፋን በታማኝ ፍቅር ጞንቶ ይመሠሚታል። በዳዊት ድንኳን ላይ በዙፋኑ ዹሚቀመጠው ታማኝ ይሆናልፀበትክክል ይፈርዳልፀ ጜድቅንም በቶሎ ያስፈጜማል።”
ስለ ሞዓብ ኩራት ይኾውም በጣም ኩሩ እንደሆነ ሰምተናልፀስለ ትዕቢቱ፣ ስለ ኩራቱና ስለ ታላቅ ቁጣው ሰምተናልፀይሁንና ድንፋታው ሁሉ ኚንቱ ይሆናል።
በመሆኑም ሞዓብ፣ ስለ ሞዓብ ዋይ ዋይ ይላልፀአዎ፣ ሁሉም ዋይ ዋይ ይላሉ። ዚተመቱት ሰዎቜ ስለ ቂርሃሚሰት ዚዘቢብ ቂጣ ያለቅሳሉ።
በሃሜቊን እርኚኖቜ ላይ ዚሚገኙት ተክሎቜ ጠውልገዋልናፀዚሲብማ ዹወይን ተክሎቜ ሚግፈዋልፀዚብሔራት ገዢዎቜ ቀያይ ቅርንጫፎቹን ሚጋግጠዋልፀእስኚ ያዜር ደርሰዋልፀበምድሚ በዳውም ተንሰራፍተዋል። ቀንበጊቹም ተዘርግተው እስኚ ባሕሩ ድሚስ ዘልቀዋል።
ስለዚህ ስለ ያዜር እንዳለቀስኩት ለሲብማ ዹወይን ተክልም አለቅሳለሁ። ሃሜቊንና ኀልዓሌ ሆይ፣ በእንባዬ አርሳቜኋለሁፀምክንያቱም ዹበጋ ፍሬና መኹር በምትሰበስቡበት ወቅት ዹሚሰማው ጩኞት አብቅቷል።
ሐሎትና ደስታ ኚፍራፍሬ እርሻው ተወስዷልፀበወይን እርሻዎቹም ዚደስታ ዝማሬ ወይም ጩኞት አይሰማም። ወይን ዚሚሚግጥ ሰው ኚእንግዲህ በወይን መጭመቂያው ውስጥ ወይን አይሚግጥምፀጩኞቱን ሁሉ ጞጥ አሰኝቻለሁና።
ኹዚህም ዚተነሳ እንደሚርገበገብ ዹበገና ክርውስጀ ስለ ሞዓብ፣አንጀ቎ም ስለ ቂርሃሚሰት ይታወካል።
ሞዓብ በኚፍታ ስፍራው ላይ ራሱን ቢያደክምም እንኳ ዋጋ ዚለውምፀ ለመጾለይ ወደ መቅደሱ ቢመጣም ምንም ማድሚግ አይቜልም።
ይሖዋ አስቀድሞ ስለ ሞዓብ ዹተናገሹው ቃል ይህ ነው።
ደግሞም ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ልክ እንደ ቅጥር ሠራተኛ ዚሥራ ዘመን፣ በሊስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ዚሞዓብ ክብር በብዙ ብጥብጥ ይዋሚዳልፀ ዚሚተርፉትም በጣም ጥቂትና እዚህ ግቡ ዚማይባሉ ይሆናሉ።”
እስቲ ለወዳጄ መዝሙር ልዘምር።መዝሙሩ ስለ ወዳጄና ስለ ወይን እርሻው ዚሚገልጜ ነው። ወዳጄ ለም በሆነ ኮሚብታ ላይ ዹወይን እርሻ ነበሚው።
እሱም መሬቱን ቆፈሚፀ ድንጋዮቹንም አስወገደ። ምርጥ ዹሆነ ቀይ ወይን ተኚለፀበመካኚሉ ማማ ገነባፀድንጋይ ፈልፍሎም ዹወይን መጭመቂያ ጉድጓድ ሠራ። ኚዚያም ‘ወይኑ ጥሩ ፍሬ ያፈራል’ ብሎ ይጠብቅ ጀመርፀይሁንና መጥፎ ፍሬ ብቻ አፈራ።
“እናንተ ዚኢዚሩሳሌም ነዋሪዎቜና ዚይሁዳ ሰዎቜ ሆይ፣በእኔና በወይን እርሻዬ መካኚል እስቲ ፍሚዱ።
ለወይን እርሻዬ ኹዚህ በላይ ላደርግለት ዚሚገባምን ነገር አለ? ‘ጥሩ ወይን ያፈራል’ ብዬ ስጠብቅመጥፎ ወይን ብቻ ያፈራው ለምንድን ነው?
እንግዲህ በወይን እርሻዬ ላይምን እንደማደርግ ልንገራቜሁፊ በዙሪያው ያለውን ዚቁጥቋጊ አጥር እነቅላለሁፀለእሳትም ይማገዳል። ዚድንጋይ ቅጥሩን አፈርሳለሁፀበእግርም ይሚጋገጣል።
ቊታውን ጠፍ መሬት አደርገዋለሁፀዚወይን ተክሉ አይገሹዝም እንዲሁም አይኮተኮትም። ቁጥቋጊና አሹም ይወርሰዋልፀደመናቱም ዝናብ እንዳያዘንቡበት ትእዛዝ እሰጣለሁ።
ዚሠራዊት ጌታ ዹይሖዋ ዹወይን እርሻ ዚእስራኀል ቀት ነውናፀዚይሁዳ ሰዎቜ እሱ ይወደው ዹነበሹው ዚአትክልት ቊታ ና቞ው። ፍትሕን ሲጠብቅእነሆ፣ ግፍ ይፈጞማልፀ‘ጜድቅ ይሰፍናል’ ብሎ ሲጠብቅእነሆ፣ ዹጭንቅ ጩኞት ይሰማል።”
ቊታ እስኪጠፋ ድሚስበቀት ላይ ቀት ለሚጚምሩናበመሬት ላይ መሬት ለሚይዙ ወዮላ቞ው!እናንተም በምድሪቱ ላይ ብቻቜሁን ትቀመጣላቜሁ።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ጆሮዬ እዚሰማ እንዲህ ሲል ማለፊብዙ ቀቶቜ ታላላቅና ያማሩ ቢሆኑም እንኳአንድም ነዋሪ ዚማይገኝባ቞ውአስፈሪ ቊታዎቜ ይሆናሉ።
ኚአራት ሄክታር ዹወይን እርሻ አንድ ዚባዶስ መስፈሪያ ብቻ ይገኛልፀኚአንድ ዹሆሜር መስፈሪያ ዘርም አንድ ዚኢፍ መስፈሪያ ብቻ ይገኛል።
ዚሚያሰክር መጠጥ ለመጠጣት በማለዳ ለሚነሱ፣ዚወይን ጠጅ እስኚሚያቃጥላ቞ው ድሚስ እስኚ ሌሊት ለሚያመሹ ወዮላ቞ው!
በግብዣ቞ው ላይ በገና፣ ባለ አውታር መሣሪያ፣አታሞና ዋሜንት እንዲሁም ዹወይን ጠጅ አለፀእነሱ ግን ይሖዋ ያኚናወነውን ተግባር አያስቡምፀዚእጁንም ሥራ አይመለኚቱም።
ስለዚህ ሕዝቀ እውቀት በማጣቱተማርኮ ይወሰዳልፀበመካኚላ቞ው ዹሚገኙ ዚተኚበሩ ሰዎቜ ይራባሉፀሕዝባ቞ውም እንዳለ በውኃ ጥም ይቃጠላል።
በመሆኑም መቃብር ራሷን አሰፋቜፀአፏንም ያለልክ ኚፈተቜፀዚኚተማዋ ውበት፣ ዚሚንጫጫው ሕዝቧና በውስጧ ዚሚፈነጥዙት ሰዎቜወደዚያ ይወርዳሉ።
ሰውም አንገቱን ይደፋልፀዚሰው ልጅ ኀፍሚት ይኚናነባልፀዚትዕቢተኞቜም ዓይን ይዋሚዳል።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ በሚሰጠው ፍርድ ኹፍ ኹፍ ይላልፀቅዱስ ዹሆነው እውነተኛው አምላክ በጜድቅ ራሱን ይቀድሳል።
ዹበግ ጠቊቶቜም በገዛ መሰማሪያ቞ው እንደተሰማሩ ሆነው ይግጣሉፀዚባዕድ አገር ሰዎቜ፣ ዚሰቡ እንስሳት ይኖሩባ቞ው በነበሩ ወና ዹሆኑ ቊታዎቜ ይበላሉ።
በደላቾውን በአታላይ ገመድ ዚሚስቡ፣ኃጢአታ቞ውንም በሠሹገላ ገመድ ዚሚጎትቱ ወዮላ቞ውፀ
“ሥራውን ያፋጥንፀእናዚውም ዘንድ ቶሎ ይምጣ። እናውቀውም ዘንድዚእስራኀል ቅዱስ አምላክ ዓላማ ይፈጾም” ዹሚሉ ወዮላ቞ው!
ጥሩውን መጥፎ፣ መጥፎውንም ጥሩ ዚሚሉ፣ጚለማውን በብርሃን፣ ብርሃኑን በጹለማ ዚሚተኩጣፋጩን መራራ፣ መራራውን ጣፋጭ አድርገው ዚሚያቀርቡ ወዮላ቞ው!
በገዛ ዓይናቾው ጥበበኛ ዚሆኑናበራሳ቞ው አመለካኚት ልባም ዹሆኑ ወዮላ቞ው!
ዹወይን ጠጅ በመጠጣት ሚገድ ብርቱዎቜ ዚሆኑ፣መጠጥ በመደባለቅም ዚተካኑ ወዮላ቞ውፀ
ጉቩ በመቀበል ክፉውን ኹበደል ነፃ ዚሚያደርጉ፣ጻድቁንም ፍትሕ ዹሚነፍጉ ወዮላ቞ው!
ዚእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣ዚደሚቀም ሣር በነበልባል በንኖ እንደሚጠፋዚእነሱም ሥር ይበሰብሳልፀአበባ቞ውም ልክ እንደ ዱቄት በዚቊታው ይበናልፀምክንያቱም እነሱ ዚሠራዊት ጌታ ዹሆነውን ዹይሖዋን ሕግ ለመቀበል አሻፈሚን ብለዋል፣ዚእስራኀል ቅዱስ ዹተናገሹውንም ቃል ንቀዋል።
ዹይሖዋ ቁጣ በሕዝቡ ላይ ዹነደደው በዚህ ምክንያት ነውፀእሱም እጁን በእነሱ ላይ ይዘሚጋልፀ ይመታ቞ዋልም። ተራሮቜም ይናወጣሉፀአስኚሬና቞ውም በጎዳናዎቜ ላይ እንዳለ ቆሻሻ ይሆናል። ኹዚህ ሁሉ ዚተነሳ ቁጣው አልተመለሰምፀይልቁንም እጁ ለመምታት ገና እንደተዘሚጋ ነው።
በሩቅ ላለ ታላቅ ሕዝብም ምልክት አቁሟልፀኚምድር ዳርቻ እንዲመጡ በፉጚት ጠርቷ቞ዋልፀእነሆም፣ ሕዝቡ በኹፍተኛ ፍጥነት እዚመጣ ነው።
ኚእነሱ መካኚል ዹደኹመም ሆነ ዹሚደናቀፍ አንድም ሰው ዚለም። ዚሚያንጎላጅም ሆነ ዹሚተኛ ዚለም። በወገባ቞ውም ላይ ያለው ቀበቶ አልተፈታምፀእንዲሁም ዚጫማ቞ው ማሠሪያ አልተበጠሰም።
ፍላጻዎቻ቞ው ሁሉ ዚሟሉ፣ደጋኖቻ቞ውም በሙሉ ዚተወጠሩ ና቞ው። ዚፈሚሶቻ቞ው ኮ቎ እንደ ባልጩት ድንጋይ ነውፀዚሠሚገሎቻ቞ውም መንኮራኩሮቜ እንደ አውሎ ነፋስ ና቞ው።
ጩኞታ቞ው እንደ አንበሳ ነውፀእንደ ደቩል አንበሳ ያገሳሉ። ዚጉርምርምታ ድምፅ እያሰሙ አድብተው ይይዛሉፀኚእጃ቞ውም ዚሚያስጥል ስለሌለ ተሞክመውት ይሄዳሉ።
በዚያም ቀን እንደ ባሕር ሞገድያጉሚመርሙበታል። ምድሪቷን ትኩር ብሎ ዚሚመለኚት ማንኛውም ሰው ዚሚያስጚንቅ ጹለማ ያያልፀብርሃኑም እንኳ ኹደመናው ዚተነሳ ጚልሟል።
ቀል ያጎነብሳልፀ ነቩ አንገቱን ይደፋል። ጣዖቶቻ቞ው በደኹሙ እንስሳት ላይ እንደሚጫን ኚባድ ጭነትበእንስሳት ይኾውም በጋማ ኚብቶቜ ላይ ተጭነዋል።
አንገታ቞ውን ይደፋሉፀ በአንድነት ያጎነብሳሉፀጭነቱን ማዳን አይቜሉምፀእነሱ ራሳ቞ውም ተማርኹው ይወሰዳሉ።
“ዚያዕቆብ ቀት ሆይ፣ ኚእስራኀልም ቀት ዚቀራቜሁት ሁሉ፣ኚተወለዳቜሁበት ጊዜ አንስቶ ዚሚዳኋቜሁ፣ በማህፀን ኚነበራቜሁበት ጊዜም አንስቶ ዚተሞኚምኳቜሁ ስሙኝ።
እስኚ እርጅናቜሁ ዘመን ድሚስ እኔ ያው ነኝፀፀጉራቜሁ እስኪሞብትም ድሚስ እሞኚማቜኋለሁ። ኹዚህ ቀደም እንዳደሚግኩት እሞኚማቜኋለሁ፣ እደግፋቜኋለሁ እንዲሁም እታደጋቜኋለሁ።
ኹማን ጋር ታመሳስሉኛላቜሁ? ኚማንስ ጋር እኩል ታደርጉኛላቜሁ?ወይስ እንመሳሰል ዘንድ ኹማን ጋር ታነጻጜሩኛላቜሁ?
ኚኮሮጇ቞ው ወርቅ ዹሚዘሹግፉ ሰዎቜ አሉፀብሩን በሚዛን ይመዝናሉ። አንጥሚኛ ይቀጥራሉፀ እሱም አምላክ አድርጎ ይሠራዋል። እነሱም በፊቱ ይደፋሉፀ ደግሞም ያመልኩታል።
አንስተው ትኚሻ቞ው ላይ ያደርጉታልፀተሞክመው ወስደው ቊታው ላይ ያኖሩታልፀ በዚያም ዝም ብሎ ይቆማል። ካለበት ቊታ አይንቀሳቀስም። ወደ እሱ ይጮኻሉፀ እሱ ግን አይመልስምፀማንንም ኚጭንቀት ሊታደግ አይቜልም።
ይህን አስታውሱፀ ደግሞም አይዟቜሁ። እናንተ ሕግ ተላላፊዎቜ ይህን ልብ በሉ።
ጥንት ዚተኚናወኑትን ዚቀድሞዎቹን ነገሮቜ፣እኔ አምላክ መሆኔንና ኚእኔ ሌላ አምላክ እንደሌለ አስታውሱ። እኔ አምላክ ነኝፀ እንደ እኔም ያለ ማንም ዚለም።
ኚመጀመሪያ መጚሚሻውን፣ገና ያልተኚናወኑትንም ነገሮቜ ኹሹጅም ጊዜ በፊት አስቀድሜ እናገራለሁ። እኔ ‘ውሳኔዬ ይጞናልፀደስ ዚሚያሰኘኝንም ነገር ሁሉ አደርጋለሁ’ እላለሁ።
ኹፀሐይ መውጫ አዳኝ አሞራን፣ኚሩቅ ምድርም ውሳኔዬን ዚሚፈጜመውን ሰው እጠራለሁ። ተናግሬአለሁፀ ደግሞም እፈጜመዋለሁ። ይህን ለማድሚግ አስቀአለሁፀ አደርገዋለሁም።
እናንተ ልበ ደንዳኖቜ፣እናንተ ኚጜድቅ ዚራቃቜሁ ሰዎቜ ስሙኝ።
ጜድቄን አምጥቻለሁፀሩቅም አይደለምፀማዳኔም አይዘገይም። በጜዮን መዳን አስገኛለሁፀ ለእስራኀልም ግርማዬን አጎናጜፋለሁ።”
ይሖዋ ለያዕቆብ ምሕሚት ያሳያልናፀ እስራኀልንም እንደገና ይመርጠዋል። በምድራ቞ው ላይ ያሰፍራ቞ዋልፀ ዚባዕድ አገር ሰዎቜም ኚእነሱ ጋር ይሆናሉፀ ኚያዕቆብም ቀት ጋር ይጣበቃሉ።
ሕዝቊቜም ይወስዷ቞ዋልፀ ወደ ገዛ ስፍራ቞ውም ይመልሷ቞ዋልፀ ዚእስራኀልም ቀት በይሖዋ ምድር ላይ ወንድና ሎት አገልጋዮቻ቞ው ያደርጓ቞ዋልፀ ማርኹው ዚወሰዷ቞ውንም ይማርካሉፀ አስገድደው ያሠሯ቞ው ዚነበሩትንም ይገዟ቞ዋል።
ይሖዋ ኚሥቃይህ፣ ኚጭንቀትህና በላይህ ተጭኖ ኹነበሹው ኚባድ ዚባርነት ቀንበር ባሳሚፈህ ቀን፣
በባቢሎን ንጉሥ ላይ እንዲህ ብለህ ትተርታለህፊ “ሌሎቜን አስገድዶ ሲያሠራ ዹነበሹው እንዎት አበቃለት! ጭቆናውስ እንዎት አኹተመ!
ይሖዋ ዚክፉዎቜን ዘንግ፣ዚገዢዎቜን በትር ሰብሯልፀ
ሕዝቊቜን ያለማቋሚጥ በቁጣ ሲመታ ዚነበሚውን፣ብሔራትን በማያባራ ስደት በቁጣ ሲገዛ቞ው ዹቆዹውን ሰብሯል።
መላዋ ምድር አርፋለቜፀ ኚሚብሻም ነፃ ሆናለቜ። ሕዝቊቜ በደስታ እልል ብለዋል።
ዚጥድ ዛፎቜና አርዘ ሊባኖሶቜ እንኳ ሳይቀሩበአንተ ላይ በደሹሰው ነገር ሐሎት ያደርጋሉ። ‘አንተ ኹወደቅክ ጀምሮማንም ዛፍ ቆራጭ በእኛ ላይ አልተነሳም’ ይላሉ።
“ኚታቜ ያለው መቃብር እንኳወደዚያ በወሚድክ ጊዜ አንተን ለመቀበል ሲል ተሚበሞ። በሞት ዚተሚቱትን፣ ጹቋኝ ዚምድር መሪዎቜ ሁሉበአንተ ዚተነሳ ቀሰቀሳ቞ው። ዚብሔራትን ነገሥታት ሁሉ ኚዙፋኖቻ቞ው ላይ አስነሳ቞ው።
ሁሉም እንዲህ በማለት ይናገራሉፀ እንዲህም ይሉሃል፩‘አንተም እንደ እኛው ደኹምክ ማለት ነው? አንተም እንደ እኛው ሆንክ?
ኩራትህና ባለ አውታር መሣሪያዎቜህ ዚሚያሰሙት ድምፅወደ መቃብር ወሚዱ። እጮቜ ኚበታቜህ እንደ አልጋ ተነጥፈውልሃልፀዚአልጋ ልብስህም ትሎቜ ና቞ው።’
አንተ ዚምታበራ ኮኚብ፣ ዚንጋት ልጅ ሆይ፣እንዎት ኹሰማይ ወደቅክ! አንተ ብሔራትን ድል ያደሚግክ፣እንዎት ተቆርጠህ ወደ ምድር ወደቅክ!
በልብህ እንዲህ ብለህ ነበር፩ ‘ወደ ሰማያት እወጣለሁ። ዙፋኔን ኹአምላክ ኚዋክብት በላይ ኹፍ አደርጋለሁፀበስተ ሰሜን ርቆ በሚገኘውዚመሰብሰቢያ ተራራም ላይ እቀመጣለሁ።
ኚደመናዎቜ ኚፍታ በላይ እወጣለሁፀራሎንም እንደ ልዑል አምላክ አደርጋለሁ።’
ኹዚህ ይልቅ ወደ መቃብር፣ወደ ጥልቁም ጉድጓድ ትወርዳለህ።
ዚሚያዩህ አተኩሚው ይመለኚቱሃልፀበሚገባም ይመሚምሩሃልፀ እንዲህም ይላሉፊ‘ምድርን ሲያንቀጠቅጥ፣መንግሥታትንም ሲያናውጥ ዹነበሹው ይህ ሰው አይደለም?
ሰው ዚሚኖርበትን ምድር፣ ምድሚ በዳ ያደሚገው፣ኚተሞቹንም ዚገለበጠው፣እስሚኞቹንም ወደ ቀታ቞ው እንዳይመለሱ ዹኹለኹለው እሱ አይደለም?’
ሌሎቹ ዚብሔራት ነገሥታት ሁሉ፣አንዳ቞ውም እንኳ ሳይቀሩ በክብር አንቀላፍተዋልፀእያንዳንዳ቞ው በዚመቃብራ቞ው አርፈዋል።
አንተ ግን እንደተጠላ ቀንበጥመቀበሪያ ሳታገኝ ተጥለሃልፀበሰይፍ ተወግተውወደ ዓለታማ ጉድጓድ በወሚዱ አስኚሬኖቜ ተሞፍነሃልፀእንደተሚገጠም ሬሳ ሆነሃል።
ኚእነሱ ጋር አብሚህ በመቃብር አትቀበርምፀዚገዛ ምድርህን አጥፍተሃልናፀዚገዛ ሕዝብህንም ፈጅተሃል። ዹክፉ አድራጊዎቜ ዘር ስም ዳግመኛ አይጠራም።
ተነስተው ምድሪቱን እንዳይወርሱናምድሪቱን በኚተሞቜ እንዳይሞሏትበአባቶቻ቞ው በደል ዚተነሳልጆቹ ዚሚታሚዱበትን ስፍራ አዘጋጁ።”
“በእነሱ ላይ እነሳለሁ” ይላል ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ። “ኚባቢሎን ስምን፣ ቀሪዎቜን፣ ልጆቜንና ዘርማንዘርን አጠፋለሁ” ይላል ይሖዋ።
“ዚጃርት መኖሪያና ሹግሹጋማ ቊታ አደርጋታለሁፀ በጥፋት መጥሚጊያም እጠርጋታለሁ” ይላል ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ሲል ምሏል፩ “ልክ እንዳሰብኩት ይሆናልፀበወሰንኩትም መሠሚት ይፈጞማል።
አሊራዊውን በምድሬ ላይ አደቀዋለሁፀበተራሮቌም ላይ እሚግጠዋለሁ። ቀንበሩ ኚላያ቞ው ላይ ይነሳልፀሞክሙም ኚትኚሻ቞ው ላይ ይወርዳል።”
በመላው ምድር ላይ ዹተላለፈው ውሳኔ ይህ ነውፀበብሔራትም ሁሉ ላይ ዹተዘሹጋው እጅ ይህ ነው።
ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ወስኗልናፀውሳኔውን ማን ሊያጚናግፍ ይቜላል? እጁ ተዘርግቷልፀማንስ ሊያጥፈው ይቜላል?
ንጉሥ አካዝ በሞተበት ዓመት ዹሚኹተለው ፍርድ ተላለፈ፩
“ፍልስጀማውያን ሆይ፣ ዚመቺያቜሁ በትር ስለተሰበሚአንዳቜሁም ብትሆኑ ደስ አይበላቜሁ። ኚእባቡ ሥር መርዘኛ እባብ ይወጣልናፀዘሩም ዹሚበርና ዚሚያቃጥል እባብ ይሆናል።
ዚቜግሚኞቹ ዚበኩር ልጆቜ ሲመገቡ፣ድሆቹም ያለስጋት ሲተኙ፣ዚአንተን ሥር ግን በሚሃብ እገድላለሁፀኚአንተ ዹሚተርፈውም ይገደላል።
አንተ በር ሆይ፣ አላዝን! አንቺ ኹተማ ሆይ፣ ጩኺ! ፍልስጀማውያን ሆይ፣ ሁላቜሁም ተስፋ ትቆርጣላቜሁ! ኹሰሜን ጭስ እዚመጣ ነውናፀአንዳ቞ውም ቢሆኑ ኹሰልፉ ተነጥለው ወደ ኋላ አይቀሩም።”
ለብሔሩ መልእክተኞቜ ምን ብለው መመለስ ይገባ቞ዋል? ‘ዚጜዮንን መሠሚት ዚጣለው ይሖዋ ነውፀበሕዝቡም መካኚል ያሉት ቜግሚኛ ሰዎቜ እሷን መጠጊያ ያደርጋሉ’ ብለው ይመልሱላ቞ዋል።
ጎልታ ለምትታዚው ለኀፍሬም ሰካራሞቜ አክሊል ወዮላት!ይህቜ ዚምታምር ጌጥ በወይን ጠጅ ዹተሾነፉ ሰዎቜ በሚኖሩበትለም ሾለቆ አናት ላይ ዚምትገኝ ዚምትጠወልግ አበባ ናት።
እነሆ፣ ይሖዋ ጠንካራና ብርቱ ዹሆነውን ይልካል። እሱም እንደ ነጎድጓዳማ ዚበሚዶ ውሜንፍር፣ እንደ አጥፊ አውሎ ነፋስ፣ኃይለኛ ጎርፍ እንደሚያስኚትል ነጎድጓዳማ ውሜንፍርበኃይል አሜቀንጥሮ ወደ ምድር ይጥላታል።
ጎልተው ዚሚታዩት ዚኀፍሬም ሰካራሞቜ ያደሚጓ቞ው አክሊሎቜበእግር ይሚገጣሉ።
ለም በሆነው ሾለቆ አናት ላይ ዚምትገኘውናዚምታምር ጌጥ ዚሆነቜው ዚምትጠወልግ አበባኚበጋ በፊት፣ በመጀመሪያው ወቅት እንደምትበስል በለስ ትሆናለቜ። ሰውም ባያት ጊዜ ቀጥፎ ወዲያውኑ ይውጣታል።
በዚያ ቀን ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ኚሕዝቡ መካኚል ለተሚፉት ሰዎቜ ዚሚያምር አክሊልና ውብ ዚአበባ ጉንጉን ይሆናል።
በፍርድ ወንበር ለተቀመጠውም ዚፍትሕ መንፈስ፣ ዹኹተማዋ በር ላይ ዹሚሰነዘሹውን ጥቃት ለሚመክቱም ዚብርታት ምንጭ ይሆናል።
እነዚህም ኹወይን ጠጅ ዚተነሳ መንገድ ይስታሉፀኚሚያሰክር መጠጥ ዚተነሳም ይንገዳገዳሉ። ካህኑና ነቢዩ ኚጠጡት መጠጥ ዚተነሳ መንገድ ይስታሉፀኚወይን ጠጅ ዚተነሳ ግራ ይጋባሉፀኚሚያሰክር መጠጥ ዚተነሳም ይንገዳገዳሉፀዚሚያዩት ራእይ መንገድ ያስታ቞ዋልፀፍርድ ሲሰጡም ይሳሳታሉ።
ገበታ቞ው ሁሉ በሚያስጞይፍ ትውኚት ተሞልቷልፀያልተበላሞ ቊታም ዚለም።
እነሱም እንዲህ ይላሉ፩ “እውቀትን ዚሚያካፍለው ለማን ነው?መልእክቱንስ ዚሚያስሚዳው ለማን ነው? ገና ወተት ለተዉ፣ጡትም ለጣሉ ሕፃናት ነው?
‘በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣ በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣በሥርዓት ላይ ሥርዓት፣ በሥርዓት ላይ ሥርዓት፣እዚህ ጥቂት፣ እዚያ ጥቂት’ ነውና።”
ስለዚህ በሚንተባተቡ ሰዎቜ አንደበትና በባዕድ ቋንቋ ለዚህ ሕዝብ ይናገራል።
በአንድ ወቅት “ይህ ዚእሚፍት ቊታ ነው። ዹዛለው እንዲያርፍ አድርጉፀ ይህ ዚእፎይታ ቊታ ነው” ብሏ቞ው ነበርፀ እነሱ ግን ለመስማት ፈቃደኞቜ አልሆኑም።
ዹይሖዋም ቃል ለእነሱ “በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣ በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣በሥርዓት ላይ ሥርዓት፣ በሥርዓት ላይ ሥርዓት፣እዚህ ጥቂት፣ እዚያ ጥቂት” ይሆንባ቞ዋልፀ በመሆኑም ሲሄዱ፣ተሰናክለው ወደ ኋላ ይወድቃሉፀደግሞም ይሰበራሉ፣ ይጠመዳሉ እንዲሁም ይያዛሉ።