text
stringlengths
4
267
ስለዚህ እናንተ ጉሚኞቜ፣በኢዚሩሳሌም ዹሚኖሹው ሕዝብ ገዢዎቜ፣ ዹይሖዋን ቃል ስሙፊ
እናንተ እንዲህ ብላቜኋልናፊ “ኚሞት ጋር ቃል ኪዳን ገብተናልፀኚመቃብርም ጋር ስምምነት አድርገናል። በድንገት ዚሚያጥለቀልቅ ጎርፍ ሲያልፍእኛን አይነካንምፀውሞትን መጠጊያቜን አድርገናልናፀበሐሰትም ውስጥ ተደብቀናል።”
ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ በጜዮን ዚመሠሚት ድንጋይ ይኾውም ዹተፈተነ ድንጋይ፣አስተማማኝ መሠሚት ሆኖ ዚተጣለ ክቡር ዹማዕዘን ድንጋይ አኖራለሁ። በእሱ ዚሚያምን አይደናገጥም።
እኔም ፍትሕን ዚመለኪያ ገመድ፣ጜድቅንም ውኃ ልክ አደርጋለሁ። ዚውሞት መጠጊያውን፣ በሚዶ ጠራርጎ ይወስደዋልፀውኃዎቹም መደበቂያ ቊታውን ያጥለቀልቁታል።
ኚሞት ጋር ዚገባቜሁት ቃል ኪዳን ይፈርሳልፀኚመቃብርም ጋር ያደሚጋቜሁት ስምምነት አይጞናም። በድንገት ዚሚያጥለቀልቀው ጎርፍ ሲያልፍድምጥማጣቜሁን ያጠፋል።
ጎርፉ ባለፈ ቁጥርጠራርጎ ይወስዳቜኋልፀበዚማለዳው እንዲሁምበቀንና በሌሊት ያልፋልና። ዹተነገሹውን ነገር እንዲሚዱ ዚሚያደርገው ሜብር ብቻ ነው።”
እግር ተዘርግቶ እንዳይተኛ አልጋው አጭር ነውናፀተሞፋፍኖም እንዳይተኛ ጹርቁ በጣም ጠባብ ነው።
ይሖዋ ተግባሩን ይኾውም እንግዳ ዹሆነ ተግባሩን ያኚናውን ዘንድእንዲሁም ሥራውን ይኾውም ያልተለመደ ሥራውን ይሠራ ዘንድበጰራጺም ተራራ እንዳደሚገው ይነሳልናፀበገባኊን አቅራቢያ ባለው ሾለቆ እንዳደሚገውም ራሱን ያነሳሳል።
እንግዲህ ፌዘኞቜ አትሁኑፀአለዚያ እስራቱ ይበልጥ ይጠብቅባቜኋልፀሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋአገሪቱን በሙሉ ለማጥፋት ያስተላለፈውን ፍርድ ሰምቻለሁና።
ጆሯቜሁን አዘንብሉፀ ድምፄንም ስሙፀለምናገሚው ነገር ትኩሚት ስጡፀ በጥሞናም አዳምጡ።
ገበሬ ዘር ኚመዝራቱ በፊት ቀኑን ሙሉ ሲያርስ ይውላል? ደግሞስ ጓሉን ሲኚሰክስና መሬቱን ሲያለሰልስ ይኹርማል?
ኹዚህ ይልቅ መሬቱን ኹደለደለ በኋላጥቁር አዝሙድና ኹሙን አይዘራም?ስንዎውን፣ ማሜላውንና ገብሱንስ በቊታ በቊታ቞ው አይዘራም?ደግሞስ አጃውን ዳር ላይ አይዘራም?
አምላክ ሰውን በትክክለኛው መንገድ ያስተምሚዋልፀደግሞም ይመራዋል።
ጥቁር አዝሙድ በማሄጃ አይወቃምፀበኚሙንም ላይ ዚመውቂያ መንኮራኩር እንዲሄድ አይደሚግም። ጥቁር አዝሙድ በበትር፣ኚሙንም በዘንግ ይወቃል።
ሰው ዚዳቊ እህል እንዲደቅ ያደርጋል? በጭራሜፀ እስኪደቅ ድሚስ አይወቃውምፀበፈሚሶቹ ዹሚጎተተውን ዚመውቂያ መንኮራኩር በሚያስኬድበት ጊዜ፣እህሉን አያደቀውም።
ይህም ዚተገኘው፣ አስደናቂ ምክር ካለውናታላላቅ ሥራዎቜን ካኚናወነውኚሠራዊት ጌታ ኹይሖዋ ነው።
ስለ ራእይ ሾለቆ ዹተነገሹ ዚፍርድ መልእክትፊ ሁላቜሁም ጣሪያ ላይ ዚወጣቜሁት ምን ሆናቜሁ ነው?
አንቺ ሁኚት ዚነገሠብሜ መዲና፣ ዚፈንጠዝያም ኚተማ፣በትርምስ ተሞልተሻል። ነዋሪዎቜሜ ያለቁት በሰይፍወይም በጊርነት ተገድለው አይደለም።
አምባገነን መሪዎቜሜ ሁሉ በአንድ ላይ ሞሜተዋል። ሆኖም ቀስት መጠቀም ሳያስፈልግ ተማርኚዋል። ወደ ሩቅ ቊታ ሞሜተው ቢሄዱምዚተገኙት ሁሉ ተማርኚዋል።
ስለዚህ እንዲህ አልኩፊ “ዓይናቜሁን ኚእኔ ላይ አንሱፀእኔም አምርሬ አለቅሳለሁ። ዚሕዝቀ ሎት ልጅ ኚደሚሰባት ጥፋት ዚተነሳእኔን ለማጜናናት አትድኚሙ።
ኹሉዓላዊው ጌታ፣ ኚሠራዊት ጌታ ኹይሖዋ ዘንድበራእይ ሞለቆግራ ዚመጋባት፣ ዚሜንፈትና ዚመደናገጥ ቀን ሆኗልና። ቅጥሩ ይፈርሳልፀወደ ተራራውም ይጮኻሉ።
ኀላም ሰዎቜን ባሳፈሩ ሠሚገሎቜና በፈሚሶቜ ላይዚፍላጻ ኮሮጆዋን ይዛለቜፀቂርም ዚጋሻውን ልባስ አወለቀቜ።
ምርጥ ዚሆኑት ሞለቆዎቜሜበጊር ሠሚገሎቜ ይሞላሉፀፈሚሶቹም ዹኹተማዋ በር ላይ ይቆማሉፀ
ዚይሁዳም መኚለያ ይወገዳል። “አንተም በዚያ ቀን ዹደኑን ዹጩር መሣሪያ ግምጃ ቀት ትመለኚታለህፀ
እናንተም በዳዊት ኹተማ ቅጥር ላይ ያሉትን በርካታ ክፍተቶቜ ትመለኚታላቜሁ። በታቜኛውም ኩሬ ውኃ ታጠራቅማላቜሁ።
ዚኢዚሩሳሌምን ቀቶቜ ትቆጥራላቜሁፀ ቅጥሩንም ለማጠናኹር ቀቶቹን ታፈርሳላቜሁ።
በሁለቱ ቅጥሮቜ መካኚል በድሮው ኩሬ ላለው ውኃ ዹሚሆን ማጠራቀሚያ ትሠራላቜሁፀ ይሁንና ይህን ወዳደሚገው ታላቅ አምላክ አትመለኚቱምፀ ኚዘመናት በፊት ወደሠራውም አምላክ አታዩም።
በዚያም ቀን ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋእንድታለቅሱና እንድታዝኑ፣ፀጉራቜሁን እንድትላጩና ማቅ እንድትለብሱ ይጠራቜኋል።
ይሁን እንጂ ድግስና ፈንጠዝያ፣ፍሪዳ መጣልና ሙክት ማሚድ፣ሥጋ መብላትና ዹወይን ጠጅ መጠጣት ሆኗል። ‘ነገ ስለምንሞት እንብላ፣ እንጠጣ’ ትላላቜሁ።”
ኚዚያም ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ በጆሮዬ ይህን ገለጠልኝ፩ “‘እናንተ እስክትሞቱ ድሚስ ይህ በደል አይሰሚይላቜሁም’ ይላል ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ።”
ሉዓላዊው ጌታ፣ ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “በቀቱ ላይ ወደተሟመው ወደ መጋቢው ወደ ሞብና ሄደህ እንዲህ በለው፩
‘በዚህ ለራስህ ዚመቃብር ቊታ ዚወቀርኚው፣ ዹአንተ ዹሆነ ምን ነገር ቢኖርህ ነው? በዚህስ ዹአንተ ዹሆነ ማን አለ? በኚፍታ ቊታ ዚራሱን መቃብር ወቅሯልፀ ቋጥኝ ጠርቩ ለራሱ ማሚፊያ ስፍራ አዘጋጅቷል።
‘አንተ ሰው፣ እነሆ፣ ይሖዋ በኃይል አሜቀንጥሮ ይጥልሃልፀ ጚምድዶም ይይዝሃል።
ጠቅልሎና አጡዞ እንደ ኳስ ወደ ሰፊ ምድር ይወሚውርሃል። በዚያ ትሞታለህፀ ያማሩ ሠሚገሎቜህም በዚያ ለጌታህ ቀት ውርደት ይሆናሉ።
እኔም ኚሹመትህ እሜርሃለሁፀ ኚኃላፊነትህም አባርርሃለሁ።
“‘በዚያም ቀን አገልጋዬን ዚኬልቅያስን ልጅ ኀልያቄምን እጠራለሁፀ
ቀሚስህን አለብሰዋለሁፀ መታጠቂያህንም በደንብ አስታጥቀዋለሁፀ ሥልጣንህንም በእጁ አሳልፌ እሰጠዋለሁ። እሱም ለኢዚሩሳሌም ነዋሪዎቜና ለይሁዳ ቀት አባት ይሆናል።
ዚዳዊትንም ቀት ቁልፍ በትኚሻው ላይ አደርጋለሁ። እሱ ዹሚኹፍተውን ማንም አይዘጋምፀ እሱ ዹሚዘጋውንም ማንም አይኚፍትም።
በአስተማማኝ ቊታ ላይ እንደ ማንጠልጠያ እተክለዋለሁፀ ለአባቱም ቀት እንደ ክብር ዙፋን ይሆናል።
በእሱም ላይ ዚአባቱን ቀት ክብር በሙሉ፣ ልጆቹንና ዘሮቹን ይኾውም ትናንሟቹን ዕቃዎቜ በሙሉ፣ ጎድጓዳ ሳህኖቹንና ትላልቆቹን እንስራዎቜ ሁሉ ይሰቅሉበታል።
“‘በዚያም ቀን’ ይላል ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ፣ ‘በአስተማማኝ ቊታ ላይ ዹተተኹለው ማንጠልጠያ ይነቀላልፀ ተቆርጩም ይወድቃልፀ በላዩ ላይ ዹተንጠለጠለው ሾክምም ወድቆ ይኚሰኚሳልፀ ይሖዋ ራሱ ተናግሯልና።’”
በሞዓብ ላይ ዹተላለፈ ፍርድፊ ዚሞዓብ ኀር በሌሊት ስለወደመቜጞጥ ሹጭ ብላለቜ። ዚሞዓብ ቂር በሌሊት ስለወደመቜጞጥ ሹጭ ብላለቜ።
ወደ ቀቱ፣ ወደ ዲቊን፣ወደ ኚፍታ ቊታዎቹም ለማልቀስ ወጥቷል። ሞዓብ ስለ ነቩና ስለ መደባ ዋይ ዋይ ይላል። ራስ ሁሉ ተመልጧልፀ ጢምም ሁሉ ተላጭቷል።
በጎዳናዎቹ ላይ ማቅ ለብሰው ይታያሉ። ሁሉም በጣሪያዎቻ቞ውና በአደባባዮቻ቞ው ላይ ዋይ ዋይ ይላሉፀእያለቀሱም ይወርዳሉ።
ሃሜቊንና ኀልዓሌ ያለቅሳሉፀድምፃ቞ው እስኚ ያሃጜ ድሚስ ተሰምቷል። ኹዚህም ዚተነሳ ዚሞዓብ ተዋጊዎቜ ይጮኻሉ። እሱም ይንቀጠቀጣል።
ልቀ ስለ ሞዓብ ያለቅሳል። ዚሚሞሹት ዚሞዓብ ሰዎቜ እስኚ ዞአርና እስኚ ኀግላት ሞሊሺያ ድሚስ ተሰደዱ። እያለቀሱ ዚሉሂትን ዳገት ይወጣሉፀበደሚሰባ቞ው ድንገተኛ ጥፋት ዚተነሳ ወደ ሆሮናይም በሚወስደው መንገድ ላይ ሲሄዱ ይጮኻሉ።
ዚኒምሪም ውኃዎቜ ደርቀዋልናፀለምለሙ ዚግጊሜ መስክ ደርቋልፀሣሩ ጠፍቷልፀ አንድም ዹለመለመ ነገር አይታይም።
በመሆኑም ካኚማቹት ንብሚት ውስጥ ዹተሹፈውን እንዲሁም ሀብታ቞ውን ተሞክመውዚአኻያ ዛፎቜ ዚሚገኙበትን ሾለቆ ይሻገራሉ።
ጩኞታ቞ው እስኚ ሞዓብ ወሰን ድሚስ አስተጋብቷል። ዋይታ቞ው እስኚ ኀግላይም፣እስኚ በኀርዔሊም ድሚስም ተሰምቷል።
ዚዲሞን ውኃዎቜ በደም ተሞልተዋልናፀበዲሞንም ላይ ተጚማሪ ነገሮቜ አመጣለሁፊ በሚሞሹት ሞዓባውያንናበምድሪቱ ላይ በሚቀሩት ሰዎቜ ላይ አንበሶቜ እሰዳለሁ።
እናንተ ደሎቶቜ ስሙኝፀእናንተም በሩቅ ያላቜሁ ብሔራት በጥሞና አዳምጡ። ይሖዋ ኹመወለዮ በፊት ጠርቶኛል። በእና቎ ማህፀን ኚነበርኩበት ጊዜ አንስቶ ስሜን ጠርቷል።
አፌን እንደተሳለ ሰይፍ አደሚገውፀበእጁ ጥላ ሥር ሰወሚኝ። ዚሟለ ፍላጻ አደሚገኝፀበኮሮጆው ውስጥ ሞሞገኝ።
እሱም “እስራኀል ሆይ፣ አንተ ግርማዬን ዚምገልጥብህአገልጋዬ ነህ” አለኝ።
እኔ ግን “ዚደኚምኩት በኚንቱ ነው። ጉልበቮንም ያፈሰስኩት ኚንቱ ለሆነና ምንም ፋይዳ ለሌለው ነገር ነው። ሆኖም ዚሚዳኘኝ ይሖዋ ነውፀደሞዜንም ዹሚኹፍለኝ አምላኬ ነው” አልኩ።
ዚእሱ አገልጋይ እንድሆን ኹማህፀን ጀምሮ ዚሠራኝ ይሖዋ፣እስራኀል ወደ እሱ ይሰበሰብ ዘንድያዕቆብን ወደ እሱ እንድመልስ አዞኛል። በይሖዋ ፊት እኚብራለሁፀአምላኬም ብርታ቎ ይሆናል።
እንዲህም አለ፩ “ዚያዕቆብን ነገዶቜ ዳግመኛ ለማቋቋምናጥበቃ ያገኙትን እስራኀላውያን መልሰህ ለማምጣትአገልጋዬ መሆንህ በቂ አይደለም። ዚማዳን ሥራዬ እስኚ ምድር ዳርቻ ይደርስ ዘንድለብሔራት ብርሃን አድርጌ ሰጥቌሃለሁ።”
እስራኀልን ዚሚቀዠው፣ ዚእስራኀል ቅዱስ ዹሆነው ይሖዋ፣ እጅግ ለተናቀውና በሕዝብ ለተጠላው ዚገዢዎቜ አገልጋይ እንዲህ ይላል፩ “ታማኝ በሆነው በይሖዋ፣አንተንም በመሹጠህ በእስራኀል ቅዱስ ዚተነሳነገሥታት አይተው ይነሳሉፀመኳንንትም ይሰግዳሉ።”
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ሞገስ በማሳይበት ዘመን መልስ ሰጥቌሃለሁፀበመዳንም ቀን ሚድቌሃለሁፀለሰዎቜ ቃል ኪዳን አድርጌ እሰጥህ ዘንድ ጠብቄሃለሁፀይህም ምድሪቱን ዳግመኛ እንድታቋቁም፣ዚወደመውን ርስታ቞ውን መልሰህ እንድታወርሳ቞ው፣
እስሚኞቹን ‘ኑ ውጡ!’ በጹለማ ያሉትንም ‘ራሳቜሁን ግለጡ!’ እንድትል ነው። በዚመንገዱ ዳር ይመገባሉፀበተበላሹ መንገዶቜም ሁሉ አጠገብ መሰማሪያ ያገኛሉ።
አይራቡምፀ አይጠሙምፀሐሩርም ሆነ ፀሐይ አያቃጥላ቞ውም። ምሕሚት ዚሚያደርግላ቞ው ይመራ቞ዋልናፀዚውኃ ምንጮቜ ወዳሉበትም ይወስዳ቞ዋል።
ተራሮቌን ሁሉ መንገድ አደርጋለሁፀአውራ ጎዳናዎቌም ኹፍ ያሉ ይሆናሉ።
እነሆ፣ እነዚህ ኚሩቅ ይመጣሉፀእነሆም፣ እነዚህ ኹሰሜንና ኚምዕራብ፣እነዚህ ደግሞ ኚሲኒም ምድር ይመጣሉ።”
እናንተ ሰማያት፣ እልል በሉፀ አንቺም ምድር፣ ሐሎት አድርጊ። ተራሮቜ በደስታ እልል ይበሉ። ይሖዋ ሕዝቡን አጜናንቷልናፀለተጎሳቆሉት ሕዝቊቹም ምሕሚት ያሳያል።
ጜዮን ግን “ይሖዋ ትቶኛልፀ ይሖዋም ሚስቶኛል” ትላለቜ።
እናት ዚምታጠባውን ልጇን ልትሚሳ ትቜላለቜ?ኹማህፀኗ ለወጣውስ ልጅ አትራራም? እነዚህ ሎቶቜ ቢሚሱ እንኳ እኔ ፈጜሞ አልሚሳሜም።
እነሆ፣ በእጄ መዳፍ ላይ ቀርጬሻለሁ። ግንቊቜሜ ምንጊዜም በፊቮ ና቞ው።
ወንዶቜ ልጆቜሜ ፈጥነው ይመለሳሉ። ያፈራሚሱሜና ያወደሙሜ አንቺን ለቀው ይሄዳሉ።
ዓይንሜን አንስተሜ ዙሪያሜን ተመልኚቺ። ሁሉም በአንድነት እዚተሰበሰቡ ነው። ወደ አንቺም እዚመጡ ነው። “በሕያውነ቎ እምላለሁ” ይላል ይሖዋ፣“አንቺም ሁሉንም እንደ ጌጥ ትለብሻ቞ዋለሜፀእንደ ሙሜራም ትጎናጞፊያ቞ዋለሜ።
ስፍራዎቜሜ ባድማና ወና፣ ምድርሜም ዹወደመ ቢሆንምአሁን በዚያ ዚሚኖሩ ሰዎቜ ቊታው በጣም ይጠባ቞ዋልፀዚዋጡሜም ኚአንቺ ይርቃሉ።
ዚወላድ መሃን ኚሆንሜ በኋላ ዚተወለዱት ወንዶቜ ልጆቜ፣ጆሮሜ እዚሰማ ‘ይህ ቊታ በጣም ጠቊናል። ዚምንኖርበት በቂ ስፍራ ስጪን’ ይላሉ።
አንቺም በልብሜ እንዲህ ትያለሜፊ‘እኔ ልጆቌን በሞት ያጣሁና መሃንእንዲሁም በምርኮ ዚተወሰድኩና እስሚኛ ዚሆንኩ ሎት ሆኜ ሳለእነዚህን ልጆቜ ዹወለደልኝ ማን ነው? ያሳደጋ቞ውስ ማን ነው? እነሆ፣ እኔ ብቻዬን ቀርቌ ነበርፀታዲያ እነዚህ ኚዚት መጡ?’”
ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “እነሆ፣ እጄን ለብሔራት አነሳለሁፀምልክ቎ንም ለሕዝቊቜ ኹፍ አደርጋለሁ። ወንዶቜ ልጆቜሜን በክንዳ቞ው ይዘው ያመጧ቞ዋልፀሎቶቜ ልጆቜሜንም በትኚሻ቞ው ይሞኚሟ቞ዋል።
ነገሥታት ይንኚባኚቡሻልፀልዕልቶቻ቞ውም ሞግዚቶቜሜ ይሆናሉ። በግንባራ቞ው ተደፍተው ይሰግዱልሻልፀዚእግርሜንም አቧራ ይልሳሉፀአንቺም እኔ ይሖዋ እንደሆንኩ ታውቂያለሜፀእኔን ተስፋ ዚሚያደርጉ አያፍሩም።”
በምርኮ ዚተያዙ ሰዎቜ ኚኃያል ሰው እጅ ሊወሰዱ ይቜላሉ?ወይስ በጹቋኝ እጅ ዹወደቁ ምርኮኞቜን ዚሚታደጋ቞ው ይኖራል?
ይሖዋ ግን እንዲህ ይላል፩ “በኃያል ሰው ዚተማሚኩ ሰዎቜም እንኳ ኚእጁ ላይ ይወሰዳሉፀበጚቋኝ እጅ ዹወደቁ ሰዎቜንም ዚሚታደጋ቞ው ይኖራል። አንቺን ዚሚቃወሙትን እቃወማለሁፀወንዶቜ ልጆቜሜንም አድና቞ዋለሁ።
በደል ዚሚፈጜሙብሜን ዹገዛ ሥጋ቞ውን እንዲበሉ አደርጋ቞ዋለሁፀልክ እንደ ጣፋጭ ወይን ጠጅ ዹገዛ ደማቾውን ጠጥተው ይሰክራሉ። ሰውም ሁሉ እኔ ይሖዋአዳኝሜና ዚምቀዥሜ፣ዚያዕቆብም ኃያል አምላክ እንደሆንኩ ያውቃል።”
እነሆ፣ ንጉሥ ለጜድቅ ይነግሣልፀመኳንንትም ፍትሕ ለማስፈን ይገዛሉ።
እያንዳንዱም ኚነፋስ እንደ መኚለያ፣ኚውሜንፍር እንደ መሞሞጊያ፣ውኃ በሌለበት ምድር እንደ ጅሚት፣በደሚቅ ምድርም እንደ ትልቅ ቋጥኝ ጥላ ይሆናል።
በዚያ ጊዜ፣ ዚሚያዩ ሰዎቜ ዓይኖቜ አይጚፈኑምፀዚሚሰሙ ሰዎቜም ጆሮዎቜ በትኩሚት ያዳምጣሉ።
ዚቜኩሎቜ ልብ እውቀትን ያሰላስላልፀዚሚንተባተብ ምላስም አቀላጥፎና አጥርቶ ይናገራል።
ዹማመዛዘን ቜሎታ ዹጎደለው ሰው ኚእንግዲህ ለጋስ አይባልምፀሥርዓት ዹሌለው ሰውም ትልቅ ሰው አይባልምፀ
ዹማመዛዘን ቜሎታ ዹጎደለው ሰው ዚማይሚባ ነገር ይናገራልናፀደግሞም በይሖዋ ላይ ክህደት ለመፈጾምና ዚውሞት ቃል ለመናገር፣እንዲሁም ዚተራበ ሰው ዹሚበላ ነገር እንዳያገኝናዚተጠማ ሰው ዚሚጠጣ ነገር እንዳያገኝ ለማድሚግልቡ ክፋትን ያውጠነጥናል።
ሥርዓት ዹሌለው ሰው ዚሚጠቀምባ቞ው ዘዎዎቜ መጥፎ ና቞ውፀድሃው ትክክል ዹሆነውን ነገር በሚናገርበት ጊዜም እንኳዚተጎሳቆለውን ሰው በውሞት ቃል ለማጥፋትአሳፋሪ ለሆነ ምግባር ድጋፍ ይሰጣል።
ለጋስ ሰው ግን ስለ ልግስና ያስባልፀዘወትር ዚልግስና ተግባር ለመፈጾም ይተጋል።
“እናንተ ደንታ ቢስ ሎቶቜ፣ ተነሱፀ ድምፄንም ስሙ! እናንተ ግድዚለሜ ሎቶቜ ልጆቜ፣ ዹምናገሹውን ነገር በትኩሚት አዳምጡ!
እናንተ ግድዚለሟቜ፣ ኚአንድ ዓመት ብዙም ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ትሞበራላቜሁፀምክንያቱም ዹወይን ፍሬ ዚምትለቅሙበት ጊዜ ሲያልፍ ዹተሰበሰበ ፍሬ አይኖርም።
እናንተ ደንታ ቢስ ሎቶቜ፣ ተንቀጥቀጡ! እናንተ ግድዚለሟቜ፣ ተሞበሩ! ልብሳቜሁን በሙሉ አውልቁፀበወገባቜሁም ላይ ማቅ ታጠቁ።
ስለ መልካሙ እርሻና ፍሬያማ ስለሆነው ወይንበሐዘን ደሚታቜሁን ምቱ።
ዚሕዝቀን ምድር እሟህና አሜኬላ ይወርሱታልናፀበደስታ ተሞልተው ዚነበሩትን ቀቶቜ ሁሉ፣አዎ፣ በሐሎት ተሞልታ ዚነበሚቜውን ኹተማ ይሞፍናሉ።
ዹማይደፈሹው ማማ ባዶ ሆኗልናፀሁካታ ዚነበሚበት ኹተማ ወና ቀርቷል። ኩፌልና መጠበቂያ ግንቡ ለዘለቄታው ጠፍ ሆነዋልፀዚዱር አህዮቜ መፈንጫናዚመንጎቜ መሰማሪያ ሆነዋልፀ
ይህም ዹሚሆነው መንፈስ ኹላይ እስኪፈስብን፣ምድሚ በዳውም ዚፍራፍሬ እርሻ እስኚሚሆን፣ዚፍራፍሬ እርሻውም እንደ ጫካ እስኚሚቆጠር ድሚስ ነው።
ኚዚያም በምድሚ በዳ ፍትሕ ይሰፍናልፀበፍራፍሬ እርሻም ጜድቅ ይኖራል።
ዚእውነተኛ ጜድቅ ውጀት ሰላም፣ዚእውነተኛ ጜድቅ ፍሬም ዘላቂ ጞጥታና ደህንነት ይሆናል።
ሕዝቀ ሰላማዊ በሆነ ዚመኖሪያ ስፍራ፣አስተማማኝ በሆነ መኖሪያና ጞጥታ በሰፈነበት ዚማሚፊያ ቊታ ይኖራል።
ሆኖም በሚዶው ጫካውን ያወድማልፀኚተማዋም ሙሉ በሙሉ ትፈራርሳለቜ።
እናንተ በውኃዎቜ ሁሉ ዳር ዘር ዚምትዘሩ፣በሬውንና አህያውንም ዚምትለቁ ደስተኞቜ ናቜሁ።”
በዚያን ቀን ሰባት ሎቶቜ አንድን ወንድ ይዘው እንዲህ ይሉታልፊ “ዚራሳቜንን ምግብ እንበላለንፀዚራሳቜንንም ልብስ እንለብሳለንፀብቻ በእኛ ላይ ዹደሹሰው ውርደት እንዲወገድበአንተ ስም እንድንጠራ ፍቀድልን።”
በዚያን ቀን፣ ይሖዋ እንዲያቆጠቁጥ ያደሚገው ተክል ያማሚና ክብር ዹተላበሰ ይሆናልፀ ዚምድሪቱም ፍሬ ኚጥፋት ለተሚፉት እስራኀላውያን ዚኩራት ምንጭና ውበት ይሆንላ቞ዋል።
በጜዮን ዚቀሩትና በኢዚሩሳሌም ዚተሚፉት ሁሉ ይኾውም በኢዚሩሳሌም እንዲኖሩ ዚተመዘገቡት በጠቅላላ ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ።
ይሖዋ በፍርድ መንፈስና በሚነድ መንፈስ ዚጜዮንን ሎቶቜ ልጆቜ ቆሻሻ አጥቊ ያስወግዳልፀ ዚኢዚሩሳሌምንም ዹደም ዕዳ ኚመካኚሏ አጥቊ ያነጻልፀ