text
stringlengths
4
267
በሾለቆው ውስጥ ያሉት ለስላሳ ድንጋዮቜ ድርሻዎቜሜ ና቞ው። አዎ፣ እነዚህ ዕጣ ፋንታዎቜሜ ና቞ው። ለእነሱም ጭምር ዚመጠጥ መባ አፍስሰሻልፀ ስጊታም አቅርበሻል። ታዲያ እኔ በእነዚህ ነገሮቜ ደስ ልሰኝ ይገባል?
በሹጅሙና ኹፍ ባለው ተራራ ላይ አልጋሜን አነጠፍሜፀመሥዋዕት ለማቅሚብም ወደዚያ ወጣሜ።
ኚበሩና ኹመቃኑ ጀርባ ዚመታሰቢያ ምልክትሜን አደሚግሜ። እኔን ተውሜኝፀ እርቃንሜንም ገለጥሜፀወደ ላይ ወጣሜፀ መኝታሜንም አሰፋሜ። ኚእነሱም ጋር ቃል ኪዳን ገባሜ። በአልጋቾው ላይ አብሚሜ መተኛት ወደድሜፀዚወንድ ብልትም አፍጥጠሜ አዚሜ።
ዘይትና ብዛት ያለው ሜቶ ይዘሜወደ ሜሌክ ወሚድሜ። መልእክተኞቜሜን ወደ ሩቅ ቊታ ላክሜፀበመሆኑም ወደ መቃብር ወሚድሜ።
ብዛት ያላ቞ውን መንገዶቜሜን በመኹተል ደኚምሜፀሆኖም ‘ተስፋ ዹለውም!’ አላልሜም። ጉልበትሜ ታደሰ። ተስፋ ያልቆሚጥሜው ለዚህ ነው።
መዋሞት ዚጀመርሜው ማን አስፈርቶሜ፣ማንስ ስጋት አሳድሮብሜ ነው? እኔን አላስታወስሜም። ልብ ያልሜውም ነገር ዚለም። እኔ ዝም አላልኩም? ደግሞስ ኹመናገር አልተቆጠብኩም? በመሆኑም እኔን አልፈራሜም።
‘ጜድቅሜን’ እና ሥራሜን እናገራለሁፀእነሱም አይጠቅሙሜም።
እርዳታ ለማግኘት በምትጮኺበት ጊዜዚሰበሰብሻ቞ው ጣዖቶቜ አይታደጉሜም። ነፋስ ሁሉንም ጠራርጎ ይወስዳ቞ዋልፀእስትንፋስ ይዟቾው ይሄዳልፀእኔን መጠጊያ ዚሚያደርግ ግን ምድሪቱን ይወርሳልፀቅዱስ ተራራዬም ርስቱ ይሆናል።
እንዲህ ይባላልፊ ‘መንገድ ሥሩ! መንገድ ሥሩ! መንገዱን አዘጋጁ! ሕዝቀ ኚሚሄድበት መንገድ ላይ ማንኛውንም እንቅፋት አስወግዱ።’”
ለዘላለም ዹሚኖሹውና ስሙ ቅዱስ ዚሆነው፣ኚፍ ኹፍ ያለውና እጅግ ዹኹበሹው እንዲህ ይላልና፩ “ኹፍ ባለውና ቅዱስ በሆነው ስፍራ እኖራለሁፀደግሞም ዹተሰበሹ ልብ ካለውና መንፈሱ ኹተደቆሰው ጋር እሆናለሁፀይህም ዚቜግሚኞቜን መንፈስ አነሳሳ ዘንድ፣ዚተሰበሚ ልብ ያላ቞ውንም አነቃቃ ዘንድ ነው።
ለዘላለም አልቃወማ቞ውምፀወይም ለዘለቄታው አልቆጣምፀበእኔ ዚተነሳ ዹሰው መንፈስ፣እኔ ዚሠራኋ቞ው እስትንፋስ ያላ቞ው ፍጥሚታትም እንኳ ይዝላሉና።
በማጭበርበር ጥቅም ለማግኘት ሲል በፈጾመው ኃጢአት እጅግ ተቆጣሁፀበመሆኑም መታሁትፀ ፊቮን ሰወርኩፀ ተቆጣሁም። እሱ ግን እንደ ኚዳተኛ ዚልቡን መንገድ ተኚትሎ መሄዱን ገፋበት።
መንገዶቹን አይቻለሁፀሆኖም እፈውሰዋለሁፀ እንዲሁም እመራዋለሁፀለእሱም ሆነ ላዘኑ ወገኖቹ መጜናኛን እመልሳለሁ።”
“ዚኚንፈሮቜን ፍሬ እፈጥራለሁ። በሩቅም ሆነ በቅርብ ያለው ዘላቂ ሰላም ያገኛልፀእኔም እፈውሰዋለሁ” ይላል ይሖዋ።
“ክፉዎቜ ግን ጞጥ ማለት እንደማይቜል ዚሚናወጥ ባሕር ና቞ውፀውኃውም ዚባሕር ውስጥ ዕፀዋትንና ጭቃን ያወጣል።
ክፉዎቜ ሰላም ዹላቾውም” ይላል አምላኬ።
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “ሰማይ ዙፋኔ ነውፀ ምድር ደግሞ ዚእግሬ ማሳሚፊያ ናት። ታዲያ እናንተ ምን ዓይነት ቀት ልትሠሩልኝ ትቜላላቜሁ? ደግሞስ ዚማርፍበት ቊታ ዚት ነው?”
“እነዚህን ነገሮቜ ሁሉ ዚሠራው እጄ ነውፀሁሉም ወደ ሕልውና ዚመጡት በዚህ መንገድ ነው” ይላል ይሖዋ። “እኔ ዹማዹው ትሑት ዚሆነውን፣መንፈሱ ዹተሰበሹውንና በቃሌ ዹሚንቀጠቀጠውን ሰው ነው።
በሬን ዚሚያርድ፣ ሰውን እንደሚገድል ነው። በግን ዚሚሠዋ፣ ዚውሻን አንገት እንደሚሰብር ነው። ስጊታ ዚሚሰጥ ሰው፣ ዚአሳማ ደም እንደሚያቀርብ ነው! ነጭ ዕጣንን ዚመታሰቢያ መባ አድርጎ ዚሚያቀርብ፣ በአስማታዊ ቃላት እንደሚባርክ ሰው ነው። እነሱ ዚራሳ቞ውን መንገድ መርጠዋልፀበአስጞያፊ ነገሮቜም ደስ ይሰኛሉ።
ስለዚህ እነሱን ዚምቀጣበትን መንገድ እፈልጋለሁፀዚፈሩትንም ያንኑ ነገር አመጣባ቞ዋለሁ። ምክንያቱም ስጣራ መልስ ዹሰጠ ማንም አልነበሚምፀስናገር ዹሰማ አንድም ሰው አልነበሚም። በዓይኔ ፊት ክፉ ዹሆነውን ነገር ማድሚጋ቞ውን ቀጠሉፀእኔ ዚማልደሰትበትንም ነገር መሚጡ።”
እናንተ በቃሉ ዚምትንቀጠቀጡ ሰዎቜ ሆይ፣ ዹይሖዋን ቃል ስሙፊ “በስሜ ዚተነሳ ዚሚጠሏቜሁና ዚሚያገሏቜሁ ወንድሞቻቜሁ፣ ‘ይሖዋ ዹተኹበሹ ይሁን!’ ብለዋል። ሆኖም አምላክ ይገለጣልፀ ደስታንም ያጎናጜፋቜኋልፀእነሱም ለኀፍሚት ይዳሚጋሉ።”
ኹኹተማዋ ሁካታ፣ ኚቀተ መቅደሱም ድምፅ ይሰማል! ይህም ይሖዋ ለጠላቶቹ ዚሚገባ቞ውን ብድራት በሚኹፍላቾው ጊዜ ዹሚሰማ ድምፅ ነው።
እሷ ገና ምጥ ሳይጀምራት ወለደቜ። ምጥ ሳይዛት በፊት ወንድ ልጅ ተገላገለቜ።
እንዲህ ያለ ነገር ማን ሰምቶ ያውቃል? እንዲህ ያሉ ነገሮቜስ ማን አይቶ ያውቃል? አገር በአንድ ቀን ይወለዳል? ወይስ ብሔር በአንድ ጊዜ ይወለዳል? ሆኖም ጜዮን እንዳማጠቜ ወዲያው ወንዶቜ ልጆቿን ወልዳለቜ።
“ማህፀኑን ኚኚፈትኩ በኋላ ልጁ እንዳይወለድ አደርጋለሁ?” ይላል ይሖዋ። “ወይስ ምጡ እንዲፋፋም ካደሚግኩ በኋላ ማህፀኑን እዘጋለሁ?” ይላል አምላክሜ።
እናንተ ዚምትወዷት ሁሉ፣ ኚኢዚሩሳሌም ጋር ሐሎት አድርጉፀ ኚእሷም ጋር ደስ ይበላቜሁ። ለእሷ ዚምታዝኑ ሁሉ ኚእሷ ጋር እጅግ ደስ ይበላቜሁፀ
ዚሚያጜናኑ ጡቶቿን ትጠባላቜሁናፀ ሙሉ በሙሉም ትሚካላቜሁፀእስኪበቃቜሁም ድሚስ ትጠጣላቜሁፀ በክብሯም ብዛት ሐሎት ታደርጋላቜሁ።
ይሖዋ እንዲህ ይላልና፩ “እነሆ፣ ሰላምን እንደ ወንዝ፣ዚብሔራትንም ክብር እንደሚያጥለቀልቅ ጅሚት አፈስላታለሁ። እናንተም ትጠባላቜሁፀ ጀርባዋም ላይ ታዝላቜኋለቜ፣ጭኗም ላይ ሆናቜሁ ትዘላላቜሁ።
እናት ልጇን እንደምታጜናና፣እኔም እናንተን ሁልጊዜ አጜናናቜኋለሁፀበኢዚሩሳሌምም ትጜናናላቜሁ።
እናንተ ይህን ታያላቜሁፀ ልባቜሁም ሐሎት ያደርጋልፀአጥንቶቻቜሁ እንደ ሣር ይለመልማሉ። ዹይሖዋም እጅ በአገልጋዮቹ ዘንድ ትታወቃለቜፀጠላቶቹን ግን ያወግዛ቞ዋል።”
“ይሖዋ፣ ብድራቱን በታላቅ ቁጣ ለመመለስ፣በእሳት ነበልባልም ለመገሠጜእንደ እሳት ሆኖ ይመጣልናፀሠሚገሎቹም እንደ አውሎ ነፋስ ይመጣሉ።
ይሖዋ በእሳት ፍርዱን ይፈጜማልናፀአዎ፣ በሥጋ ለባሜ ሁሉ ላይ በሰይፍ ፍርዱን ይፈጜማልፀበይሖዋ እጅ ዚሚገደሉትም ብዙ ይሆናሉ።
ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ “መሃል ላይ ያለውን ተኚትለው ወደ አትክልት ቊታዎቹ ለመግባት ሲሉ ራሳ቞ውን ዚሚቀድሱና ዚሚያነጹ፣ ዚአሳማ ሥጋና አስጞያፊ ነገር እንዲሁም አይጥ ዹሚበሉ ሁሉ በአንድነት ይጠፋሉ።
እኔ ሥራ቞ውንና ሐሳባ቞ውን ስለማውቅ፣ ኹሁሉም ብሔራትና ቋንቋዎቜ ዚተውጣጡ ሰዎቜን ለመሰብሰብ እመጣለሁፀ እነሱም መጥተው ክብሬን ያያሉ።”
“በመካኚላ቞ው ምልክት አቆማለሁፀ ኚተሚፉት መካኚል አንዳንዶቹን ወደ ብሔራት ይኾውም ወደ ተርሎስ፣ ወደ ፑል እና ወደ ሉድ እልካለሁ። በቱባልና በያዋን ወዳሉት ቀስተኞቜ እልካ቞ዋለሁ። ስለ እኔ ወዳልሰሙ ወይም ክብሬን ወዳላዩ፣ ርቀው በሚገኙ ደሎቶቜ ውስጥ ወደሚኖሩ ሕዝቊቜም እልካ቞ዋለሁፀ እነሱም በብሔራት መካኚል ክብሬን ያውጃሉ።
ዚእስራኀል ልጆቜ በንጹሕ ዕቃ ስጊታ ይዘው ወደ ይሖዋ ቀት እንደሚያመጡ፣ ወንድሞቻቜሁን ሁሉ ለይሖዋ ስጊታ እንዲሆኑ ኚዚብሔራቱ በፈሚሶቜ፣ በሠሚገሎቜ፣ ጥላ ባላ቞ው ጋሪዎቜ፣ በበቅሎዎቜና በፈጣን ግመሎቜ ጭነው ወደተቀደሰው ተራራዬ ወደ ኢዚሩሳሌም ያመጧ቞ዋል” ይላል ይሖዋ።
“በተጚማሪም አንዳንዶቹን ካህናት፣ ሌሎቹን ደግሞ ሌዋውያን እንዲሆኑ እወስዳለሁ” ይላል ይሖዋ።
“እኔ ዚምሠራ቞ው አዲስ ሰማያትና አዲስ ምድር በፊቮ ጾንተው እንደሚኖሩ ሁሉ ዚእናንተም ዘርና ስማቜሁ እንዲሁ ጞንቶ ይኖራል” ይላል ይሖዋ።
“ኚአንዱ ወር መባቻ እስኚ ሌላው ወር መባቻ እንዲሁም ኚአንዱ ሰንበት እስኚ ሌላው ሰንበት፣ሰው ሁሉ በፊቮ ለመስገድ ይመጣል” ይላል ይሖዋ።
“እነሱም ሄደው በእኔ ላይ ያመፁትን ሰዎቜ ሬሳ ያያሉፀበእነሱ ላይ ያሉት ትሎቜ አይሞቱምናፀእሳታ቞ውም አይጠፋምፀለሰዎቜም ሁሉ አስጞያፊ ነገር ይሆናሉ።”
ስለ ጢሮስ ዹተነገሹ ዚፍርድ መልእክትፊ እናንተ ዚተርሎስ መርኚቊቜ ዋይ ዋይ በሉ! ወደቧ ወድሟልናፀ ወደ እሷ መግባት አይቻልም። ኚኪቲም አገር ወሬው ደርሷ቞ዋል።
እናንተ በባሕር ዳርቻ ዚምትኖሩ ሰዎቜ፣ ጞጥ በሉ። ባሕሩን አቋርጠው ዚሚመጡት ዚሲዶና ነጋዎዎቜ ሀብት በሀብት አድርገዋቜኋል።
ዚገቢ ምንጮቿ ዚሆኑት ዚሺሆር እህልናዚአባይ መኹር በብዙ ውኃዎቜ ላይ ተጓጉዘውዚብሔራትን ትርፍ ያመጡላት ነበር።
አንቺ ዚባሕር ምሜግ ሲዶና ሆይ፣ እፈሪፀምክንያቱም ባሕሩ እንዲህ ብሏልፊ “አላማጥኩምፀ አልወለድኩምምፀወጣት ወንዶቜንም ሆነ ሎቶቜን አላሳደግኩም።”
ስለ ግብፅ በተነገሹው ወሬ እንደሆነው ሁሉስለ ጢሮስም በሚነገሹው ወሬ ሰዎቜ ጭንቅ ይይዛ቞ዋል።
ባሕሩን አቋርጣቜሁ ወደ ተርሎስ ተሻገሩ! እናንተ በባሕር ዳርቻ ዚምትኖሩ ሰዎቜ ዋይ ዋይ በሉ!
ኚጥንት ዘመን፣ ኚድሮ ጀምሮ ሐሎት ታደርግ ዚነበሚቜው ኚተማቜሁ ይህቜ ናት? በዚያ ትኖር ዘንድ እግሮቿ ወደ ሩቅ ቊታዎቜ ይወስዷት ነበር።
ዘውድ በምታጎናጜፈው፣እንዲሁም መኳንንት ዹሆኑ ነጋዎዎቜ፣በመላውም ምድር ላይ ዚተኚበሩ ሻጮቜና ለዋጮቜ በነበሯትበጢሮስ ላይ ይህን ውሳኔ ያስተላለፈው ማን ነው?
በውበቷ ሁሉ ዚተነሳ ዚሚሰማትን ኩራት ለማርኚስእንዲሁም በመላው ምድር ላይ ዚተኚበሩትን ሁሉ ለማዋሚድይህን ውሳኔ ያስተላለፈው ዚሠራዊት ጌታ ይሖዋ ራሱ ነው።
ዚተርሎስ ሎት ልጅ ሆይ፣ እንደ አባይ ወንዝ ምድርሜን አጥለቅልቂ። ኚእንግዲህ ወዲያ መርኚብ ዚሚሠራበት ቊታ አይኖርም።
አምላክ እጁን በባሕሩ ላይ ዘርግቷልፀመንግሥታትን አንቀጥቅጧል። ይሖዋ ዹፊንቄ ምሜጎቜ እንዲወድሙ ትእዛዝ አስተላልፏል።
እሱም እንዲህ ይላል፩ “አንቺ ዚተጚቆንሜ ዚሲዶና ድንግል ሆይ፣ዳግመኛ ሐሎት አታደርጊም። ተነሜ፣ ወደ ኪቲም ተሻገሪ። እዚያም ቢሆን እሚፍት አታገኚም።”
ዚኚለዳውያንን ምድር ተመልኚቱ! በበሹሃ ዚሚኖሩ እንስሳት መፈንጫ ያደሚጓትአሊራውያን ሳይሆኑ እነዚህ ሰዎቜ ና቞ው። ጥቃት ለመሰንዘር ዚሚያስቜል ማማ አቁመዋልፀዚማይደፈሩ ማማዎቿን በማፈራሚስዚፍርስራሜ ክምር አድርገዋታል።
እናንተ ዚተርሎስ መርኚቊቜ፣ምሜጋቜሁ ስለወደመ ዋይ ዋይ በሉ።
በዚያም ቀን ጢሮስ እንደ አንድ ንጉሥ ዕድሜ ለ70 ዓመት ዚተሚሳቜ ትሆናለቜ። በ70ኛው ዓመት ማብቂያ ላይ ጢሮስ እንዲህ ተብሎ እንደሚዘመርላት ዝሙት አዳሪ ትሆናለቜፊ
“አንቺ ዚተሚሳሜ ዝሙት አዳሪ፣ በገና ይዘሜ በኹተማው ውስጥ ተዘዋወሪ። በገናሜንም ጥሩ አድርገሜ ተጫወቺፀእነሱም እንዲያስታውሱሜብዙ ዘፈን ዝፈኚ።”
በሰባው ዓመት መጚሚሻ ላይ ይሖዋ ትኩሚቱን በጢሮስ ላይ ያደርጋልፀ እሷም ዳግመኛ ክፍያ መቀበሏን ትቀጥላለቜፀ በመላው ምድር ላይ ካሉ ዹዓለም መንግሥታትም ጋር ታመነዝራለቜ።
ሆኖም ትርፏና ዚምትቀበለው ክፍያ ለይሖዋ ዹተቀደሰ ይሆናል። አይኚማቜም ወይም አይጠራቀምምፀ ምክንያቱም በይሖዋ ፊት ዚሚኖሩ ሰዎቜ እስኪጠግቡ ድሚስ እንዲበሉና ዚሚያምር ልብስ እንዲለብሱ እሷ ዚምትቀበለው ክፍያ ለእነሱ ይሰጣል።
ምድሚ በዳውና ደሹቁ ምድር ሐሎት ያደርጋልፀበሚሃማው ቊታም ደስ ይለዋልፀ እንደ ሳሮን አበባም ያብባል።
በእርግጥ ያብባልፀሐሎት ያደርጋልፀ በደስታም እልል ይላል። ዚሊባኖስ ክብር ይሰጠዋልፀዚቀርሜሎስንና ዚሳሮንን ግርማ ይለብሳል። ዹይሖዋን ክብር፣ ዚአምላካቜንንም ግርማ ያያሉ።
ዚደኚሙትን እጆቜ አበርቱፀዚሚብሚኚሚኩትንም ጉልበቶቜ አጜኑ።
በጭንቀት ዹተዋጠ ልብ ላላቾው እንዲህ በሏቾው፩ “በርቱፀ አትፍሩ። እነሆ፣ አምላካቜሁ ሊበቀል ይመጣልፀአምላክ ብድራት ሊኹፍል ይመጣል። እሱ መጥቶ ያድናቜኋል።”
በዚያን ጊዜ ዹዓይነ ስውራን ዓይን ይገለጣልፀመስማት ዚተሳና቞ው ሰዎቜ ጆሮም ይኚፈታል።
በዚያን ጊዜ አንካሳ እንደ ሚዳቋ ይዘላልፀዚዱዳም ምላስ በደስታ እልል ይላል። በምድሚ በዳ ውኃ ይፈልቃልናፀበበሚሃማ ሜዳም ጅሚት ይፈስሳል።
በሐሩር ዹተቃጠለው ምድር ቄጠማ ዚሞላበት ኩሬ፣ዚተጠማውም ምድር ዹውኃ ምንጭ ይሆናል። ቀበሮዎቜ ይኖሩበት ዹነበሹው ጎሬለምለም ሣር፣ ሾምበቆና ደንገል ይበቅልበታል።
በዚያም አውራ ጎዳና ይኖራልፀደግሞም “ዚቅድስና ጎዳና” ተብሎ ይጠራል። ንጹሕ ያልሆነ ሰው አይጓዝበትም። ጎዳናው፣ በመንገዱ ላይ ለሚሄዱት ብቻ ይሆናልፀሞኞቜም አይሄዱበትም።
በዚያ አንበሳ አይኖርምፀአዳኝ አራዊትም ወደዚያ አይወጡም። አንዳ቞ውም በዚያ አይገኙምፀዚተቀዡት ብቻ በዚያ ይሄዳሉ።
ይሖዋ ዹዋጃቾው ይመለሳሉፀ ወደ ጜዮንም በእልልታ ይመጣሉ። ፍጻሜ ዹሌለው ደስታን እንደ አክሊል ይጎናጞፋሉ። ደስታንና ሐሎትን ያገኛሉፀሐዘንና ሲቃም ኚዚያ ይርቃሉ።
“አንቺ ሎት ሆይ፣ ተነሺ፣ ብርሃን አብሪፀ ብርሃንሜ መጥቷልና። ዹይሖዋ ክብር በአንቺ ላይ ያበራል።
እነሆ፣ ጹለማ ምድርን፣ድቅድቅ ጹለማም ብሔራትን ይሞፍናልፀበአንቺ ላይ ግን ይሖዋ ያበራልፀክብሩም በአንቺ ላይ ይታያል።
ብሔራት ወደ ብርሃንሜ፣ነገሥታትም አንጞባራቂ ወደሆነው ውበትሜ ይመጣሉ።
ዓይንሜን አንስተሜ ዙሪያሜን ተመልኚቺ! ሁሉም አንድ ላይ ተሰብስበዋልፀ ወደ አንቺም እዚመጡ ነው። ኚሩቅ ቊታ ወንዶቜ ልጆቜሜ በመምጣት ላይ ና቞ውፀሎቶቜ ልጆቜሜም ታዝለው እዚመጡ ነው።
በዚያን ጊዜ ታያለሜፀ ፊትሜም ይፈካልፀልብሜ በኃይል ይመታልፀ በደስታም ይሞላልፀምክንያቱም ዚባሕር ብልጜግና ወደ አንቺ ይጎርፋልፀዚብሔራትም ሀብት ወደ አንቺ ይመጣል።
ዹግመል መንጋ ምድርሜን ይሞፍናልፀዚምድያምና ዚኀፋ ግልገል ግመሎቜ ያጥለቀልቁሻል። ሁሉም ወርቅና ነጭ ዕጣን ይዘውኚሳባ ይመጣሉ። ዹይሖዋንም ውዳሎ ያውጃሉ።
ዚቄዳር መንጎቜ ሁሉ ወደ አንቺ ይሰበሰባሉ። ዚነባዮት አውራ በጎቜ ያገለግሉሻል። እነሱም በመሠዊያዬ ላይ ተቀባይነት ያለው መሥዋዕት ይሆናሉፀክብራማ ዹሆነውንም ቀ቎ን አሳምሚዋለሁ።
እንደ ደመና፣ ወደ ቀታ቞ውም እንደሚተሙ ርግቊቜእዚበሚሩ ዚሚመጡት እነዚህ እነማን ናቾው?
ደሎቶቜ እኔን ተስፋ ያደርጋሉናፀዚተርሎስ መርኚቊቜም ኚሩቅ ወንዶቜ ልጆቜሜንኚነብራ቞ውና ኚነወርቃ቞ውለአምላክሜ ለይሖዋ ስምና ለእስራኀል ቅዱስ ለማምጣትቀዳሚ ሆነው ይወጣሉፀእሱ ክብር ያጎናጜፍሻልና።
ዚባዕድ አገር ሰዎቜ ቅጥሮቜሜን ይገነባሉፀነገሥታታ቞ውም ያገለግሉሻልፀበቁጣዬ መትቌሻለሁናፀበሞገሎ ግን ምሕሚት አሳይሻለሁ።
በሮቜሜ ሁልጊዜ ክፍት ይሆናሉፀዚብሔራትን ሀብት ወደ አንቺ ያመጡ ዘንድበሮቜሜ ቀንም ሆነ ሌሊት አይዘጉምፀነገሥታታ቞ውም ቀዳሚ ይሆናሉ።
አንቺን ዚማያገለግል ማንኛውም ብሔርም ሆነ ማንኛውም መንግሥት ይጠፋልናፀብሔራትም ፈጜመው ይደመሰሳሉ።
ዹመቅደሮን ስፍራ አስውብ ዘንድዚሊባኖስ ክብር፣ ጥዱ፣ ዚአሜ ዛፉና ዹፈሹንጅ ጥዱበአንድነት ወደ አንቺ ይመጣሉፀእግሬ ዚሚያርፍበትንም ስፍራ አኚብራለሁ።
ዚጚቋኞቜሜ ወንዶቜ ልጆቜ መጥተው በፊትሜ ይሰግዳሉፀዚሚያዋርዱሜ ሁሉ እግርሜ ሥር ይደፋሉፀደግሞም ዹይሖዋ ኚተማ፣ዚእስራኀልም ቅዱስ አምላክ ንብሚት ዚሆንሜ ጜዮን ብለው ይጠሩሻል።
ዚተተውሜና ዚተጠላሜ፣ ማንም ሰው ዚማያልፍብሜ መሆንሜ ቀርቶዚዘላለም መኩሪያ፣ኚትውልድ እስኚ ትውልድም ዚደስታ ምንጭ እንድትሆኚ አደርግሻለሁ።
አንቺም ዚብሔራትን ወተት ትጠጫለሜፀዚነገሥታትን ጡት ትጠቢያለሜፀእኔ ይሖዋ አዳኝሜ እንደሆንኩ፣ደግሞም ዚያዕቆብ ኃያል አምላክ ዚሆንኩት እኔ እንደምቀዥሜ በእርግጥ ታውቂያለሜ።
በመዳብ ፋንታ ወርቅ፣በብሚት ፋንታ ብር፣በእንጚት ፋንታ መዳብ፣በድንጋዮቜም ፋንታ ብሚት አመጣለሁፀሰላምንም ዹበላይ ተመልካ቟ቜሜ፣ጜድቅንም አሠሪዎቜሜ አድርጌ እሟማለሁ።
ኹዚህ በኋላ በምድርሜ ውስጥ ዓመፅ፣ወይም በክልልሜ ውስጥ ጥፋትና ውድመት አይሰማም። ቅጥሮቜሜን መዳን፣ በሮቜሜንም ውዳሎ ብለሜ ትጠሪያ቞ዋለሜ።
ኚእንግዲህ ፀሐይ በቀን ብርሃን አትሆንልሜምፀዚጚሚቃም ብርሃን ኚእንግዲህ አያበራልሜምፀይሖዋ ዹዘላለም ብርሃን፣አምላክሜም ውበት ይሆንልሻልና።
ፀሐይሜ ኚእንግዲህ አትጠልቅምፀጚሚቃሜም አትደበዝዝምፀይሖዋ ዹዘላለም ብርሃን ይሆንልሻልናፀዚሐዘንሜም ጊዜ ያበቃል።
ሕዝቊቜሜም ሁሉ ጻድቃን ይሆናሉፀምድሪቱን ለዘላለም ይወርሳሉ። እነሱ፣ ውበት እጎናጞፍ ዘንድ ዚተኚልኳ቞ው ቜግኞቜ፣ዚእጆቌም ሥራ ና቞ው።
ጥቂት ዹሆነው ሺህ፣ትንሜ ዹሆነውም ኃያል ብሔር ይሆናል። እኔ ይሖዋ፣ ይህን በራሱ ጊዜ አፋጥነዋለሁ።”
እናንተ ብሔራት፣ ለመስማት ወደዚህ ቅሚቡፀእናንተ ሕዝቊቜ፣ በትኩሚት አዳምጡ። ምድርና በውስጧ ያለው ነገር ሁሉ፣ምድርና ኚእሷ ዹሚገኘው ምርት ሁሉ ይስሙ።
ይሖዋ በሁሉም ብሔራት ላይ ተቆጥቷልናፀበሠራዊታ቞ውም ሁሉ ላይ ተቆጥቷል። ፈጜሞ ያጠፋ቞ዋልፀለእርድም አሳልፎ ይሰጣ቞ዋል።
ዚተገደሉባ቞ው ሰዎቜ ይጣላሉፀዚአስኚሬኖቻ቞ውም ግማት ወደ ላይ ይወጣልፀኚደማ቞ውም ዚተነሳ ተራሮቹ ይሞሚሞራሉ።
ዚሰማያት ሠራዊት ሁሉ ይበሰብሳሉፀሰማያትም እንደ መጜሐፍ ጥቅልል ይጠቀለላሉ። ደርቆ እንደሚገፈ ዹወይን ቅጠልናደርቆ እንደወደቀ በለስሠራዊታ቞ውም ሁሉ ደርቀው ይሚግፋሉ።
“ሰይፌ በሰማያት በደም ትርሳለቜና። በኀዶም ይኾውም እንዲጠፋፍርድ ባስተላለፍኩበት ሕዝብ ላይ ትወርዳለቜ።
ይሖዋ ሰይፍ አለውፀ ሰይፉም በደም ትሞፈናለቜ። በስብ፣ በበግ ጠቊቶቜና በፍዚሎቜ ደምእንዲሁም በአውራ በጎቜ ኩላሊት ስብ ትለወሳለቜ።ይሖዋ በቊስራ መሥዋዕት፣ በኀዶምም ምድርታላቅ እርድ ያዘጋጃልና።
ዚዱር በሬዎቜ ኚእነሱ ጋር ይወድቃሉፀወይፈኖቜም ኚብርቱ ኮርማዎቜ ጋር ይወድቃሉ። ምድራ቞ውም በደም ይሞፈናልፀአፈራ቞ውም በስብ ይርሳል።”
ይሖዋ ዚሚበቀልበት ቀን፣በጜዮን ላይ ለተፈጾመው በደል ቅጣት ዚሚያስፈጜምበት ዓመት አለውና።
በእሷ ዚሚገኙት ጅሚቶቜ ወደ ዝፍት ይለወጣሉፀአፈሯም ወደ ድኝ ይቀዚራልፀምድሪቱም እንደሚቃጠል ዝፍት ትሆናለቜ።
እሳቱ በሌሊትም ሆነ በቀን አይጠፋምፀጭሷም ለዘላለም ይወጣል። ኚትውልድ እስኚ ትውልድም እንደወደመቜ ትቀራለቜፀለዘላለም ማንም በእሷ አያልፍም።