text
stringlengths
4
267
አምላክም እንዲህ አለ፩ “ቀኑና ሌሊቱ እንዲለይ በሰማያት ጠፈር ላይ ብርሃን ሰጪ አካላት ይኑሩፀ እነሱም ወቅቶቜን፣ ቀናትንና ዓመታትን ዹሚጠቁሙ ምልክቶቜ ሆነው ያገለግላሉ።
በምድርም ላይ እንዲያበሩ በሰማያት ጠፈር ላይ ያሉ ብርሃን ሰጪ አካላት ሆነው ያገለግላሉ።” እንዳለውም ሆነ።
አምላክም ሁለቱን ታላላቅ ብርሃን ሰጪ አካላት ሠራፀ ታላቁ ብርሃን ሰጪ አካል በቀን እንዲያይል፣ ታናሹ ብርሃን ሰጪ አካል ደግሞ በሌሊት እንዲያይል አደሚገፀ ኚዋክብትንም ሠራ።
በዚህ መንገድ አምላክ በምድር ላይ እንዲያበሩ በሰማያት ጠፈር ላይ አስቀመጣ቞ውፀ
በተጚማሪም በቀንና በሌሊት እንዲያይሉ እንዲሁም ብርሃኑን ኹጹለማው እንዲለዩ አደሚገ። አምላክም ይህ መልካም እንደሆነ አዚ።
መሞ፣ ነጋምፀ አራተኛ ቀን።
ኚዚያም አምላክ “ውኃዎቹ በሚርመሰመሱ ሕያዋን ፍጥሚታት ይሞሉፀ እንዲሁም ዚሚበርሩ ፍጥሚታት ኚምድር በላይ በሰማያት ጠፈር ላይ ይብሚሩ” አለ።
አምላክም ግዙፍ ዚባሕር ፍጥሚታትን እንዲሁም በውኃዎቹ ውስጥ ዚሚንቀሳቀሱና ዚሚርመሰመሱ ሕያዋን ፍጥሚታትን ሁሉ እንደዚወገና቞ው ብሎም ክንፍ ያለውን እያንዳንዱን ዹሚበር ፍጥሚት እንደዚወገኑ ፈጠሚ። አምላክም ይህ መልካም እንደሆነ አዚ።
ኚዚያም አምላክ “ብዙ ተባዙፀ ዚባሕሩንም ውኃ ሙሉትፀ ዚሚበርሩ ፍጥሚታትም በምድር ላይ ይብዙ” ብሎ ባሚካ቞ው።
መሞ፣ ነጋምፀ አምስተኛ ቀን።
ቀጥሎም አምላክ “ምድር ሕያዋን ፍጥሚታትን እንደዚወገና቞ው እንዲሁም ዚቀት እንስሳትን፣ መሬት ለመሬት ዚሚሄዱ እንስሳትንና ዚዱር እንስሳትን እንደዚወገና቞ው ታውጣ” አለ። እንዳለውም ሆነ።
አምላክም በምድር ላይ ያሉ ዚዱር እንስሳትን እንደዚወገና቞ው፣ ዚቀት እንስሳትን እንደዚወገና቞ው እንዲሁም መሬት ለመሬት ዚሚሄዱ ፍጥሚታትን ሁሉ እንደዚወገና቞ው ሠራ። አምላክም ይህ መልካም እንደሆነ አዚ።
ኚዚያም አምላክ “ሰውን በመልካቜን እንደ አምሳላቜን እንሥራፀ እሱም በባሕር ዓሣዎቜ፣ በሰማያት ላይ በሚበርሩ ፍጥሚታት፣ በቀት እንስሳትና በምድር ሁሉ እንዲሁም በምድር ላይ በሚንቀሳቀሱ መሬት ለመሬት ዚሚሄዱ እንስሳት ሁሉ ላይ ሥልጣን ይኑሹው” አለ።
አምላክም ሰውን በራሱ መልክ ፈጠሚውፀ በአምላክ መልክ ፈጠሚውፀ ወንድና ሎት አድርጎ ፈጠራ቞ው።
በተጚማሪም አምላክ ባሚካ቞ውፀ እንዲህም አላቾው፩ “ብዙ ተባዙፀ ምድርንም ሙሏትፀ ግዟትም። እንዲሁም ዚባሕር ዓሣዎቜን፣ በሰማያት ላይ ዚሚበርሩ ፍጥሚታትንና በምድር ላይ ዚሚንቀሳቀሱ ፍጥሚታትን በሙሉ ግዟ቞ው።”
ቀጥሎም አምላክ እንዲህ አለ፩ “በመላው ምድር ላይ ያሉ ዘር ዚሚሰጡ ተክሎቜን በሙሉ እንዲሁም ዘር ያለው ፍሬ ዚሚያፈሩ ዛፎቜን በሙሉ ይኾው ሰጥቻቜኋለሁ። ምግብ ይሁኗቜሁ።
በምድር ላይ ላለው ዚዱር እንስሳ ሁሉ፣ በሰማያት ላይ ለሚበር ፍጥሚት ሁሉ እንዲሁም ሕይወት ላለው በምድር ላይ ለሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ አሹንጓዮ ተክሎቜን በሙሉ ምግብ እንዲሆኗ቞ው ሰጥቻ቞ዋለሁ።” እንዳለውም ሆነ።
ኚዚያ በኋላ አምላክ ዚሠራውን እያንዳንዱን ነገር ተመለኚተፀ እነሆ፣ እጅግ መልካም ነበር! መሞ፣ ነጋምፀ ስድስተኛ ቀን።
ዚኀሳው ማለትም ዚኀዶም ታሪክ ይህ ነው።
ኀሳው ኹኹነአን ሎቶቜ ልጆቜ ሚስቶቜን አገባፀ እነሱም ዚሂታዊው ዚኀሎን ልጅ አዳ እንዲሁም ዹአና ልጅና ዹሂዋዊው ዚጺብኊን ዹልጅ ልጅ ዚሆነቜው ኊሆሊባማ ና቞ውፀ
በተጚማሪም ዚእስማኀል ልጅ ዚሆነቜውን ዚነባዮትን እህት ባሎማትን አገባ።
አዳ ለኀሳው ኀሊፋዝን ወለደቜለትፀ ባሎማት ደግሞ ሚኡዔልን ወለደቜፀ
ኊሆሊባማ ዚኡሜን፣ ያላምን እና ቆሬን ወለደቜ። እነዚህ ኀሳው በኹነአን ምድር ሳለ ዚተወለዱለት ልጆቜ ና቞ው።
ኚዚያም ኀሳው ሚስቶቹን፣ ወንዶቜና ሎቶቜ ልጆቹን፣ ዚቀተሰቡን አባላት ሁሉ፣ መንጋውን፣ ሌሎቹን እንስሳት ሁሉና በኹነአን ምድር ያፈራውን ሀብት ሁሉ ይዞ ኚወንድሙ ኚያዕቆብ ርቆ ወደ ሌላ ምድር ሄደ።
ምክንያቱም ንብሚታ቞ው በጣም ስለበዛ አብሚው መኖር አልቻሉምፀ እንዲሁም ኹመንጋቾው ብዛት ዚተነሳ ይኖሩበት ዹነበሹው ምድር ሊበቃቾው አልቻለም።
በመሆኑም ኀሳው በሮይር ተራራማ አካባቢ መኖር ጀመሚ። ኀሳው ኀዶም ተብሎም ይጠራል።
በሮይር ተራራማ አካባቢ ዚሚኖሚው ዚኀዶማውያን አባት ዚኀሳው ታሪክ ይህ ነው።
ዚኀሳው ወንዶቜ ልጆቜ ስም ዹሚኹተለው ነው፩ ዚኀሳው ሚስት ዚአዳ ልጅ ኀሊፋዝና ዚኀሳው ሚስት ዚባሎማት ልጅ ሚኡዔል ና቞ው።
ዚኀሊፋዝ ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ ቎ማን፣ ኊማር፣ ጞፎ፣ ጋታም እና ቀናዝ ና቞ው።
ቲምና ዚኀሳው ልጅ ዚኀሊፋዝ ቁባት ሆነቜ። ኹጊዜ በኋላም ለኀሊፋዝ አማሌቅን ወለደቜለት። ዚኀሳው ሚስት ዚአዳ ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ና቞ው።
ዚሚኡዔል ወንዶቜ ልጆቜ ናሃት፣ ዛራ፣ ሻማህ እና ሚዛህ ና቞ው። እነዚህም ዚኀሳው ሚስት ዚባሎማት ልጆቜ ነበሩ።
ዹአና ልጅና ዚጺብኊን ዹልጅ ልጅ ዚሆነቜው ዚኀሳው ሚስት ኊሆሊባማ ለኀሳው ዚወለደቻ቞ው ወንዶቜ ልጆቜ ዚኡሜ፣ ያላም እና ቆሬ ና቞ው።
ዚነገድ አለቆቜ ዚሆኑት ዚኀሳው ወንዶቜ ልጆቜ ዚሚኚተሉት ናቾው፩ ዚኀሳው ዚበኩር ልጅ ዚኀሊፋዝ ወንዶቜ ልጆቜም አለቃ ቎ማን፣ አለቃ ኊማር፣ አለቃ ጞፎ፣ አለቃ ቀናዝ፣
አለቃ ቆሬ፣ አለቃ ጋታም እና አለቃ አማሌቅ ና቞ው። እነዚህ በኀዶም ምድር ዚነገድ አለቆቜ ዚሆኑት ዚኀሊፋዝ ልጆቜ ነበሩ። እነዚህ ዚአዳ ወንዶቜ ልጆቜ ና቞ው።
ዚኀሳው ልጅ ዚሚኡዔል ወንዶቜ ልጆቜ፣ አለቃ ናሃት፣ አለቃ ዛራ፣ አለቃ ሻማህ እና አለቃ ሚዛህ ና቞ው። እነዚህ በኀዶም ምድር ዚነገድ አለቆቜ ዚሆኑት ዚሚኡዔል ልጆቜ ና቞ው። እነዚህ ዚኀሳው ሚስት ዚባሎማት ወንዶቜ ልጆቜ ና቞ው።
በመጚሚሻም ዚኀሳው ሚስት ዚኊሆሊባማ ወንዶቜ ልጆቜ፣ አለቃ ዚኡሜ፣ አለቃ ያላም እና አለቃ ቆሬ ና቞ው። እነዚህ ዚነገድ አለቆቜ ዹአና ልጅ ዚሆነቜው ዚኀሳው ሚስት ዚኊሆሊባማ ልጆቜ ና቞ው።
ዚኀሳው ማለትም ዚኀዶም ወንዶቜ ልጆቜና አለቆቻ቞ው እነዚህ ና቞ው።
በዚያ ምድር ዚሚኖሩት ዚሆራዊው ዚሎይር ወንዶቜ ልጆቜ እነዚህ ናቾው፩ ሎጣን፣ ሟባል፣ ጺብኊን፣ አና፣
ዲሟን፣ ኀጌር እና ዲሻን። እነዚህ በኀዶም ምድር ዚሆራውያን ዚነገድ አለቆቜ ዚሆኑት ዹሮይር ወንዶቜ ልጆቜ ና቞ው።
ዚሎጣን ወንዶቜ ልጆቜ ሆሪ እና ሄማም ና቞ውፀ ዚሎጣን እህት ቲምና ትባላለቜ።
ዚሟባል ወንዶቜ ልጆቜ አልዋን፣ ማናሃት፣ ኀባል፣ ሌፎ እና ኩናም ና቞ው።
ዚጺብኊን ወንዶቜ ልጆቜ አያ እና አና ና቞ው። ይህ አና ዚአባቱን ዚጺብኊንን አህዮቜ ሲጠብቅ በምድሚ በዳ ዹፍል ውኃ ምንጮቜን ያገኘው ነው።
ዹአና ልጆቜ ዲሟን እና ዹአና ሎት ልጅ ኊሆሊባማ ና቞ው።
ዚዲሟን ወንዶቜ ልጆቜ ሄምዳን፣ ኀሜባን፣ ይትራን እና ኬራን ና቞ው።
ዚኀጌር ወንዶቜ ልጆቜ ቢልሃን፣ ዛአዋን እና አቃን ና቞ው።
ዚዲሻን ወንዶቜ ልጆቜ ዑጜ እና አራን ና቞ው።
ዚሆራውያን ዚነገድ አለቆቜ እነዚህ ናቾው፩ አለቃ ሎጣን፣ አለቃ ሟባል፣ አለቃ ጺብኊን፣ አለቃ አና፣
አለቃ ዲሟን፣ አለቃ ኀጌር እና አለቃ ዲሻን። በሮይር ምድር ዚሆራውያን ዚነገድ አለቆቜ በዚአለቆቻ቞ው ሲዘሚዘሩ እነዚህ ና቞ው።
እነዚህ በእስራኀላውያን ላይ ዚትኛውም ንጉሥ መግዛት ኚመጀመሩ በፊት በኀዶም ምድር ይገዙ ዚነበሩ ነገሥታት ና቞ው።
ዚቢዖር ልጅ ቀላ በኀዶም ይገዛ ነበርፀ ዹኹተማውም ስም ዲንሃባ ይባል ነበር።
ቀላ ሲሞት ዚቊስራው ዚዛራ ልጅ ዮባብ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ዮባብ ሲሞት ኚ቎ማናውያን ምድር ዚመጣው ሁሻም በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ሁሻም ሲሞት ምድያማውያንን በሞዓብ ክልል ድል ያደሚጋ቞ው ዚቀዳድ ልጅ ሃዳድ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚፀ ዹኹተማውም ስም አዊት ይባል ነበር።
ሃዳድ ሲሞት ዚማስሚቃው ሳምላ በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ሳምላ ሲሞት በወንዙ አጠገብ ያለው ዚሚሆቊቱ ሻኡል በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ሻኡል ሲሞት ዹአክቩር ልጅ ባአልሀናን በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ።
ዹአክቩር ልጅ ባአልሀናን ሲሞት ሃዳር በእሱ ምትክ መግዛት ጀመሚ። ዹኹተማው ስም ጳኡ ነበርፀ ዚሚስቱም ስም መሄጣቀል ሲሆን እሷም ዚመዛሃብ ሎት ልጅ ዚማጥሬድ ልጅ ናት።
እንግዲህ ዚኀሳው ልጆቜ ዹሆኑ ዚነገድ አለቆቜ በዚቀተሰባ቞ው፣ በዚስፍራ቞ውና በዚስማ቞ው ሲዘሚዘሩ ስማ቞ው ይህ ነው፩ አለቃ ቲምና፣ አለቃ አልዋህ፣ አለቃ ዚ቎ት፣
አለቃ ኊሆሊባማ፣ አለቃ ኀላህ፣ አለቃ ፒኖን፣
አለቃ ቀናዝ፣ አለቃ ቎ማን፣ አለቃ ሚብጻር፣
አለቃ ማግዲኀል እና አለቃ ኢራም። ኚኀዶም ዚተገኙት ዚነገድ አለቆቜ ርስት አድርገው በያዙት ምድር እንደዚመኖሪያ቞ው ሲዘሚዘሩ እነዚህ ና቞ው። ዚኀዶማውያን አባት ኀሳው ይህ ነው።
ኹዚህ በኋላ ይሖዋ ኖኅን እንዲህ አለው፩ “በዚህ ትውልድ መካኚል በፊቮ ጻድቅ ሆነህ ያገኘሁህ አንተን ስለሆነ አንተም ሆንክ መላው ቀተሰብህ ወደ መርኚቡ ግቡ።
ኹአንተም ጋር ንጹሕ ኹሆነው ኚእያንዳንዱ እንስሳ ሰባት ሰባት ትወስዳለህፀ ተባዕትና እንስት ይሁኑፀ ንጹሕ ካልሆነው ኚእያንዳንዱ እንስሳ ደግሞ ሁለት ሁለት ውሰድፀ ተባዕትና እንስት ይሁኑፀ
በተጚማሪም በመላው ምድር ላይ ዘራ቞ው እንዲተርፍ በሰማይ ላይ ኚሚበርሩ ፍጥሚታት ሰባት ሰባት አስገባፀ ተባዕትና እንስት ይሁኑ።
ኚሰባት ቀን በኋላ በምድር ላይ 40 ቀንና 40 ሌሊት ዝናብ አዘንባለሁፀ ዚሠራሁትንም ሕይወት ያለው ነገር ሁሉ ኚምድር ገጜ ጠራርጌ አጠፋለሁ።”
ኖኅም ይሖዋ ያዘዘውን ሁሉ አደሚገ።
ዚጥፋት ውኃው በምድር ላይ በወሚደበት ወቅት ኖኅ 600 ዓመቱ ነበር።
ኖኅም ዚጥፋት ውኃው ኚመጀመሩ በፊት ኚወንዶቜ ልጆቹ፣ ኚሚስቱና ኚልጆቹ ሚስቶቜ ጋር በመሆን ወደ መርኚቡ ገባ።
እያንዳንዱ ንጹሕ እንስሳ፣ እያንዳንዱ ንጹሕ ያልሆነ እንስሳ እንዲሁም ዚሚበርሩ ፍጥሚታትና በምድር ላይ ዚሚንቀሳቀሱ ነገሮቜ ሁሉ
አምላክ ኖኅን ባዘዘው መሠሚት ተባዕትና እንስት በመሆን ጥንድ ጥንድ እዚሆኑ ኖኅ ወዳለበት ወደ መርኚቡ ገቡ።
ኚሰባት ቀን በኋላም ዚጥፋት ውኃው በምድር ላይ ወሚደ።
ኖኅ በተወለደ በ600ኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር ኚወሩም በ17ኛው ቀን፣ በዚያ ቀን፣ ተንጣሎ ዹሚገኘው ጥልቅ ውኃ ምንጮቜ ሁሉ ተነደሉፀ ዚሰማያት ዹውኃ በሮቜም ተኚፈቱ።
ዝናቡም ለ40 ቀንና ለ40 ሌሊት በምድር ላይ ወሚደ።
በዚያው ቀን ኖኅ ኚወንዶቜ ልጆቹ ኚሎም፣ ኚካምና ኚያፌት እንዲሁም ኚሚስቱና ኚሊስቱ ዚልጆቹ ሚስቶቜ ጋር ወደ መርኚቡ ገባ።
ኚእነሱም ጋር እያንዳንዱ ዚዱር እንስሳ እንደዚወገኑ፣ እያንዳንዱ ዚቀት እንስሳ እንደዚወገኑ፣ በምድር ላይ ያለ መሬት ለመሬት ዚሚሄድ እያንዳንዱ እንስሳ እንደዚወገኑ፣ እያንዳንዱ ዹሚበር ፍጥሚት እንደዚወገኑ እንዲሁም እያንዳንዱ ወፍና እያንዳንዱ ክንፍ ያለው ፍጡር ወደ መርኚቡ ገባ።
ዚሕይወት እስትንፋስ ያለው ሁሉም ዓይነት ሕያው ፍጡር ሁለት ሁለት ሆኖ ወደ ኖኅ በመምጣት መርኚቡ ውስጥ ይገባ ጀመር።
በመሆኑም አምላክ ኖኅን ባዘዘው መሠሚት ሁሉም ዓይነት ሕያው ፍጡር ተባዕትና እንስት እዚሆነ ወደ መርኚቡ ገባ። ኚዚያም ይሖዋ ኚበስተኋላው በሩን ዘጋበት።
ዚጥፋት ውኃው ለ40 ቀን በምድር ላይ ያለማቋሚጥ ወሚደ። ውኃው እዚጚመሚ ሲሄድ መርኚቡን ወደ ላይ አነሳውፀ መርኚቡም መሬቱን ለቆ መንሳፈፍ ጀመሚ።
ውኃው በምድር ላይ እያዚለና በእጅጉ እዚጚመሚ ሄደፀ መርኚቡ ግን በውኃው ላይ መንሳፈፉን ቀጠለ።
ውኃው በምድር ላይ በጣም እያዚለ ኚመሄዱ ዚተነሳ ኹሰማይ በታቜ ያሉ ሹጃጅም ተራሮቜ በሙሉ ተሞፈኑ።
ውኃው ኚተራሮቹ በላይ 15 ክንድ ያህል ኹፍ አለ።
በመሆኑም በምድር ላይ ዚሚንቀሳቀሱ ሕያዋን ፍጥሚታት በሙሉ ይኾውም ዚሚበርሩ ፍጥሚታት፣ ዚቀት እንስሳት፣ ዚዱር እንስሳት፣ ዚሚርመሰመሱ ፍጥሚታትና ሰዎቜ በሙሉ ጠፉ።
በአፍንጫው ዚሕይወት እስትንፋስ ዹነበሹው በዚብስ ላይ ዹሚኖር ፍጡር ሁሉ ሞተ።
እሱም ሰውን፣ እንስሳትን፣ መሬት ለመሬት ዚሚሄዱ እንስሳትንና በሰማይ ላይ ዚሚበርሩ ፍጥሚታትን ጚምሮ ሕይወት ያለውን ነገር ሁሉ ኚምድር ገጜ ጠራርጎ አጠፋ። ሁሉም ኚምድር ላይ ተጠራርገው ጠፉፀ ኚጥፋቱ ዚተሚፉት ኖኅና ኚእሱ ጋር በመርኚቡ ውስጥ ዚነበሩት ብቻ ና቞ው።
ውኃውም በምድር ላይ እንዳዚለ ለ150 ቀናት ቆዚ።
አብርሃም ኬጡራ ዚምትባል ሌላ ሚስት አገባ።
እሷም ኹጊዜ በኋላ ዚምራንን፣ ዮቅሻንን፣ ሚዳንን፣ ምድያምን፣ ይሜባቅን እና ሹሃን ወለደቜለት።
ዮቅሻንም ሳባን እና ዎዳንን ወለደ። ዚዎዳን ወንዶቜ ልጆቜ ደግሞ አሹሪም፣ ለጡሺም እና ለኡሚም ነበሩ።
ዚምድያም ወንዶቜ ልጆቜ ኀፋ፣ ኀፌር፣ ሃኖክ፣ አቢዳዕ እና ኀልዳዓ ነበሩ። እነዚህ ሁሉ ዚኬጡራ ወንዶቜ ልጆቜ ነበሩ።
በኋላም አብርሃም ያለውን ሁሉ ለይስሐቅ ሰጠውፀ
ኚቁባቶቹ ለወለዳ቞ው ወንዶቜ ልጆቹ ግን ስጊታ ሰጣ቞ው። ኚዚያም ገና በሕይወት እያለ ኹልጁ ኚይስሐቅ እንዲርቁ በስተ ምሥራቅ አቅጣጫ ወደ ምሥራቅ ምድር ላካ቞ው።
አብርሃም በሕይወት ዚኖሚበት ዘመን 175 ዓመት ነበር።
ኚዚያም አብርሃም እስትንፋሱ ቀጥ አለፀ ሞምግሎ፣ በሕይወቱ ሚክቶና ዕድሜ ጠግቩ ሞተፀ ወደ ወገኖቹም ተሰበሰበ።
ልጆቹ ይስሐቅና እስማኀልም ዚሂታዊው ዚጟሃር ልጅ በሆነው በኀፍሮን ዚእርሻ ቊታ ውስጥ ባለው በማምሬ ፊት ለፊት በሚገኘው በማክፈላ ዋሻ ቀበሩትፀ
ይህ ዚእርሻ ቊታ አብርሃም ኚሄት ወንዶቜ ልጆቜ ዹገዛው ነው። አብርሃምም ኚሚስቱ ኚሣራ ጋር በዚያ ስፍራ ተቀበሚ።
አብርሃም ኹሞተ በኋላም አምላክ ዚአብርሃምን ልጅ ይስሐቅን መባሚኩን ቀጠለፀ ይስሐቅ በብኀርላሃይሮዒ አቅራቢያ ይኖር ነበር።
ዚሣራ አገልጋይ ዚነበሚቜው ግብፃዊቷ አጋር ለአብርሃም ዚወለደቜለት ዚአብርሃም ልጅ ዚእስማኀል ታሪክ ይህ ነው።
ዚእስማኀል ወንዶቜ ልጆቜ ስም በዚስማ቞ውና በዚቀተሰብ ዹዘር ሐሹጋቾው ሲዘሚዘር ዹሚኹተለው ነው፩ ዚእስማኀል ዚበኩር ልጅ ነባዮት ኚዚያም ቄዳር፣ አድበዔል፣ ሚብሳም፣
ሚሜማ፣ ዱማ፣ ማሳ፣
ሃዳድ፣ ቎ማ፣ ዚጡር፣ ናፊሜ እና ቄድማ።