text
stringlengths
4
267
ክብሬ በዚያ በሚያልፍበትም ጊዜ በዓለቱ ዋሻ ውስጥ አስቀምጥሃለሁፀ እስኚማልፍም ድሚስ በእጄ እጋርድሃለሁ።
ኚዚያም እጄን አነሳለሁፀ አንተም ጀርባዬን ታያለህ። ፊቮ ግን አይታይም።”
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩ “በፈርዖንና በግብፅ ላይ አንድ ተጚማሪ መቅሰፍት አመጣለሁ። ኚዚያ በኋላ ኹዚህ እንድትሄዱ ይለቃቜኋል። ደግሞም በሚለቃቜሁ ጊዜ አንዳቜሁንም ሳያስቀር ኹዚህ ያባርራቜኋል።
እንግዲህ አሁን ወንዶቹም ሆኑ ሎቶቹ ሁሉ ኚዚጎሚቀቶቻ቞ው ዚብርና ዹወርቅ ዕቃዎቜን እንዲጠይቁ ለሕዝቡ ንገር።”
ይሖዋም ለሕዝቡ በግብፃውያን ፊት ሞገስ ሰጣ቞ው። ሙሮ ራሱም ቢሆን በፈርዖን አገልጋዮቜና በሕዝቡ ፊት በግብፅ ምድር እጅግ ዹተኹበሹ ሰው ሆኖ ነበር።
ሙሮም እንዲህ አለ፩ “ይሖዋ እንዲህ ይላል፩ ‘እኩለ ሌሊት ገደማ በግብፅ መሃል እወጣለሁፀ
በዙፋኑ ላይ ኹተቀመጠው ኹፈርዖን ዚበኩር ልጅ አንስቶ ዚወፍጮ መጅ እስኚምትገፋው ባሪያ ዚበኩር ልጅ ድሚስ በግብፅ ምድር ያለ በኩር ሁሉ ይሞታልፀ ዚእንስሳም በኩር ሁሉ ይሞታል።
በመላው ዚግብፅ ምድርም ኚዚያ በፊት በጭራሜ ሆኖ ዚማያውቅ ኚዚያ በኋላም ፈጜሞ ዳግመኛ ዚማይኚሰት ታላቅ ዋይታ ይሆናል።
ሆኖም ይሖዋ በግብፃውያንና በእስራኀላውያን መካኚል ልዩነት ማድሚግ እንደሚቜል እንድታውቁ በእስራኀላውያን ላይ፣ በሰዎቹም ሆነ በእንስሶቻ቞ው ላይ ውሻ እንኳ አይጮኜም።’
አገልጋዮቜህም ሁሉ ወደ እኔ ወርደው ‘አንተም ሆንክ አንተን ዹሚኹተሉ ሰዎቜ ሁሉ ኹዚህ ሂዱልን’ በማለት ይሰግዱልኛል። ኚዚያ በኋላም እወጣለሁ።” ሙሮም ይህን ተናግሮ በታላቅ ቁጣ ኹፈርዖን ፊት ወጣ።
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን “ተአምራቶቌ በግብፅ ምድር ላይ እንዲበዙ ፈርዖን እናንተን አይሰማቜሁም” አለው።
ሙሮና አሮንም እነዚህን ሁሉ ተአምራት በፈርዖን ፊት ፈጞሙፀ ሆኖም ይሖዋ ዹፈርዖን ልብ እንዲደነድን ስለፈቀደ ፈርዖን እስራኀላውያን ኚምድሩ እንዲሄዱ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።
ኚዚያም ባስልኀል ኚግራር እንጚት ታቊቱን ሠራ። ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፣ ወርዱ አንድ ክንድ ተኩል፣ ኚፍታው ደግሞ አንድ ክንድ ተኩል ነበር።
ውስጡንና ውጭውንም በንጹሕ ወርቅ ለበጠውፀ በዙሪያውም ዹወርቅ ክፈፍ ሠራለት።
ኚአራቱ እግሮቹ በላይ ዹሚሆኑ አራት ዹወርቅ ቀለበቶቜን ሠራለትፀ ሁለቱን ቀለበቶቜ በአንድ ጎኑ፣ ሁለቱን ቀለበቶቜ ደግሞ በሌላኛው ጎኑ በኩል አደሚጋ቞ው።
ኚዚያም ኚግራር እንጚት መሎጊያዎቜን ሠራፀ በወርቅም ለበጣ቞ው።
ታቊቱንም ለመሾኹም እንዲያገለግሉ መሎጊያዎቹን በታቊቱ ጎንና ጎን ባሉት ቀለበቶቜ ውስጥ አስገባ቞ው።
እሱም ኚንጹሕ ወርቅ መክደኛውን ሠራ። ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል ወርዱ ደግሞ አንድ ክንድ ተኩል ነበር።
በተጚማሪም በመክደኛው ጫፍና ጫፍ ላይ ኹተጠፈጠፈ ወርቅ ሁለት ኪሩቊቜን ሠራ።
አንዱ ኪሩብ በአንዱ ጫፍ ሌላኛው ኪሩብ ደግሞ በሌላኛው ጫፍ ላይ ነበር። ኪሩቊቹን በሁለቱም ዹመክደኛው ጫፎቜ ላይ ሠራ቞ው።
ሁለቱ ኪሩቊቜም ክንፎቻ቞ውን ወደ ላይ በመዘርጋት መክደኛውን በክንፎቻ቞ው ኚልለውት ነበር። እርስ በርስ ትይዩ ነበሩፀ ፊታ቞ውንም ወደ መክደኛው አጎንብሰው ነበር።
ኚዚያም ኚግራር እንጚት ጠሹጮዛውን ሠራ። ርዝመቱ ሁለት ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ ኚፍታው ደግሞ አንድ ክንድ ተኩል ነበር።
በንጹሕ ወርቅም ለበጠውፀ ዙሪያውንም ዹወርቅ ክፈፍ ሠራለት።
ኚዚያም በዙሪያው አንድ ጋት ስፋት ያለው ጠርዝ ሠራለትፀ ለጠርዙም ዙሪያውን ዹወርቅ ክፈፍ ሠራለት።
በተጚማሪም አራት ዹወርቅ ቀለበቶቜ ሠራለትፀ ቀለበቶቹንም አራቱ እግሮቹ በሚገኙባ቞ው አራት ማዕዘኖቜ ላይ አደሚጋ቞ው።
ጠሹጮዛውን ለመሾኹም ዚሚያገለግሉትን መሎጊያዎቜ ዚሚይዙት ቀለበቶቜ በጠርዙ አጠገብ ነበሩ።
ኚዚያም ጠሹጮዛውን ለመሾኹም ዚሚያገለግሉትን መሎጊያዎቜ ኚግራር እንጚት ሠርቶ በወርቅ ለበጣ቞ው።
በኋላም በጠሹጮዛው ላይ ዚሚሆኑትን ዕቃዎቜ ይኾውም ለመጠጥ መባ ማፍሰሻ ዚሚያገለግሉትን ሳህኖቜ፣ ጜዋዎቜ፣ ጎድጓዳ ሳህኖቜና ማንቆርቆሪያዎቜ ኚንጹሕ ወርቅ ሠራ።
ኚዚያም መቅሹዙን ኚንጹሕ ወርቅ ሠራ። መቅሹዙን ጠፍጥፎ ሠራው። ዹመቅሹዙ መቆሚያ፣ ግንዱ፣ አበባ አቃፊዎቹ፣ እንቡጊቹና ዚፈኩት አበቊቜ ወጥ ሆነው ዚተሠሩ ነበሩ።
መቅሹዙ ኚግንዱ ላይ ዚወጡ ስድስት ቅርንጫፎቜ ነበሩትፀ ሊስቱ ቅርንጫፎቹ ኚአንዱ ጎን ሊስቱ ቅርንጫፎቹ ደግሞ ኹሌላው ጎን ዚወጡ ነበሩ።
በአንዱ በኩል ባሉት ቅርንጫፎቜ በእያንዳንዳ቞ው ላይ ዚአልሞንድ አበባ ዚሚመስሉ ሊስት ዚአበባ አቃፊዎቜ ኚእንቡጊቜና ኚፈኩ አበቊቜ ጋር በማፈራሚቅ ተሠርተው ነበርፀ በሌላኛው በኩል ባሉት ቅርንጫፎቜም በእያንዳንዳ቞ው ላይ ዚአልሞንድ አበባ ዚሚመስሉ ሊስት ዚአበባ አቃፊዎቜ ኚእንቡጊቜና ኚፈኩ አበቊቜ ጋር በማፈራሚቅ ተሠርተው ነበር። ኹመቅሹዙ ግንድ በሚወጡት ስድስት ቅርንጫፎቜ ላይ ዹተደሹገው ይህ ነበር።
በመቅሹዙም ግንድ ላይ ዚአልሞንድ አበባ ዚሚመስሉ አራት ዚአበባ አቃፊዎቜ ኚእንቡጊቜና ኚፈኩ አበቊቜ ጋር በማፈራሚቅ ተሠርተው ነበር።
ኚግንዱ በሚወጡት በመጀመሪያዎቹ ጥንድ ቅርንጫፎቜ ሥር አንድ እንቡጥ፣ ቀጥሎ ባሉት ጥንድ ቅርንጫፎቜ ሥር አንድ እንቡጥ እንዲሁም ቀጥሎ ባሉት ጥንድ ቅርንጫፎቜ ሥር አንድ እንቡጥ ነበርፀ ኹመቅሹዙ ግንድ ለሚወጡት ስድስት ቅርንጫፎቜ እንዲሁ ተደርጎላቾው ነበር።
እንቡጊቹም ሆኑ ቅርንጫፎቹ፣ መላው መቅሹዙ ኚንጹሕ ወርቅ ተጠፍጥፎ ወጥ ሆኖ ዚተሠራ ነበር።
ኚዚያም ሰባቱን መብራቶቜ እንዲሁም መቆንጠጫዎቹንና መኮስተሪያዎቹን ኚንጹሕ ወርቅ ሠራ።
መቅሹዙን ኚዕቃዎቹ ሁሉ ጋር ዚሠራው ኚአንድ ታላንት ንጹሕ ወርቅ ነበር።
ኚዚያም ኚግራር እንጚት ዚዕጣን መሠዊያውን ሠራ። ርዝመቱ አንድ ክንድ፣ ወርዱ አንድ ክንድ ሆኖ አራቱም ጎኖቹ እኩል ሲሆኑ ኚፍታው ደግሞ ሁለት ክንድ ነበር። ቀንዶቹ ኚዚያው ወጥ ሆነው ዚተሠሩ ነበሩ።
እሱም ላዩን፣ ሁሉንም ጎኖቹን እንዲሁም ቀንዶቹን በንጹሕ ወርቅ ለበጠውፀ በዙሪያውም ዹወርቅ ክፈፍ ሠራለት።
መሠዊያውን ለመሾኹም ዚሚያገለግሉትን መሎጊያዎቜ እንዲይዙም በሁለቱ ተቃራኒ ጎኖቹ ላይ ኹክፈፉ በታቜ ሁለት ዹወርቅ ቀለበቶቜን ሠራለት።
ኚዚያ በኋላ መሎጊያዎቹን ኚግራር እንጚት ሠርቶ በወርቅ ለበጣ቞ው።
በተጚማሪም ቅዱሱን ዚቅብዓት ዘይትና በብልሃት ዹተቀመመውን ጥሩ መዓዛ ያለውን ንጹሕ ዕጣን አዘጋጀ።
“በቀጭኑ ኹተፈተለ ጥሩ በፍታ፣ ኚሰማያዊ ክር፣ ኚሐምራዊ ሱፍ እንዲሁም ኹደማቅ ቀይ ማግ ኹተዘጋጁ አሥር ዚድንኳን ጚርቆቜ ዚማደሪያ ድንኳኑን ትሠራለህ። በጚርቆቹ ላይ ኪሩቊቜን ትጠልፍባ቞ዋለህ።
ዚእያንዳንዱ ዚድንኳን ጹርቅ ርዝመት 28 ክንድ ወርዱ ደግሞ 4 ክንድ ይሆናል። ሁሉም ዚድንኳን ጚርቆቜ መጠናቾው እኩል ይሆናል።
አምስቱ ዚድንኳን ጚርቆቜ አንድ ላይ ይቀጣጠላሉፀ ዚቀሩት አምስቱ ዚድንኳን ጚርቆቜም እንዲሁ አንድ ላይ ይቀጣጠላሉ።
እርስ በርስ ኚተቀጣጠሉት ዚድንኳን ጚርቆቜ በመጚሚሻው ጹርቅ ጠርዝ ላይ ኚሰማያዊ ክር ዚተሠሩ ማቆላለፊያዎቜን ታደርጋለህፀ እርስ በርስ ዚተቀጣጠለው ሌላኛው ዚድንኳን ጹርቅ ኹዚህኛው ጋር በሚጋጠምበት ዚመጚሚሻው ዚድንኳን ጹርቅ ጠርዝ ላይም እንዲሁ ታደርጋለህ።
በአንደኛው ዚድንኳን ጹርቅ ላይ 50 ማቆላለፊያዎቜን ትሠራለህፀ በሌላኛው ዚድንኳን ጹርቅ ጠርዝ ላይም 50 ማቆላለፊያዎቜን ታደርጋለህፀ ማቆላለፊያዎቹም ዚሚጋጠሙበት ቊታ ላይ እርስ በርሳ቞ው ትይዩ ይሆናሉ።
ኚዚያም 50 ዹወርቅ ማያያዣዎቜን ሠርተህ ዚድንኳን ጚርቆቹን በማያያዣዎቹ አማካኝነት እርስ በርስ ታጋጥማ቞ዋለህፀ በዚህ መንገድ ማደሪያ ድንኳኑ አንድ ወጥ ይሆናል።
“በተጚማሪም ለማደሪያ ድንኳኑ ልባስ ዹሚሆኑ ጚርቆቜን ኹፍዹል ፀጉር ትሠራለህ። አሥራ አንድ ዚድንኳን ጚርቆቜን ትሠራለህ።
ዚእያንዳንዱ ዚድንኳን ጹርቅ ርዝመት 30 ክንድ ወርዱ ደግሞ 4 ክንድ ይሆናል። ዚአሥራ አንዱም ዚድንኳን ጚርቆቜ መጠን እኩል ይሆናል።
አምስቱን ዚድንኳን ጚርቆቜ አንድ ላይ ትቀጣጥላ቞ዋለህፀ ዚቀሩትን ስድስቱን ዚድንኳን ጚርቆቜ ደግሞ አንድ ላይ ትቀጣጥላ቞ዋለህፀ ስድስተኛውን ዚድንኳን ጹርቅ በድንኳኑ ፊት በኩል ታጥፈዋለህ።
እርስ በርስ ኚተቀጣጠሉት ዚድንኳን ጚርቆቜ በመጚሚሻው ጠርዝ ላይ 50 ማቆላለፊያዎቜን ትሠራለህፀ እርስ በርስ ዚተቀጣጠለው ሌላኛው ዚድንኳን ጹርቅ ኹዚህኛው ጋር በሚጋጠምበት ጹርቅ ጠርዝ ላይም 50 ማቆላለፊያዎቜን ታደርጋለህ።
ኚዚያም 50 ዚመዳብ ማያያዣዎቜን ትሠራለህፀ ማያያዣዎቹንም ማቆላለፊያዎቹ ውስጥ በማስገባት ድንኳኑን ታጋጥመዋለህፀ በዚህ መንገድ ዚድንኳኑ ጹርቅ አንድ ወጥ ይሆናል።
ኚድንኳኑ ጚርቆቜ ትርፍ ሆኖ ዚወጣው እንደተንጠለጠለ ይተዋል። ትርፍ ሆኖ ዚወጣው ግማሹ ዚድንኳን ጹርቅ በማደሪያ ድንኳኑ ጀርባ ላይ ይንጠለጠላል።
ትርፍ ሆኖ ዚወጣው አንድ አንድ ክንድ ጹርቅ ድንኳኑን እንዲሞፍን በማደሪያ ድንኳኑ ጎንና ጎን ይንጠለጠላል።
“በተጚማሪም ቀይ ቀለም ኹተነኹሹ ዚአውራ በግ ቆዳ ለድንኳኑ መደሚቢያ ትሠራለህፀ በዚያ ላይ ዹሚደሹግ መደሚቢያም ኚአቆስጣ ቆዳ ትሠራለህ።
“ዚግራር እንጚት ጣውላዎቜን በማገጣጠም ለማደሪያ ድንኳኑ ዹሚሆኑ አራት ማዕዘን ቋሚዎቜን ትሠራለህ።
ዚእያንዳንዱ ቋሚ ቁመት አሥር ክንድ ወርዱ ደግሞ አንድ ክንድ ተኩል ይሆናል።
እያንዳንዱ ቋሚም እርስ በርስ ዚተያያዙ ሁለት ጉጊቜ ይኑሩት። ለማደሪያ ድንኳኑ ዚሚያገለግሉትን ቋሚዎቜ በሙሉ በዚህ መንገድ ሥራ቞ው።
በስተ ደቡብ በኩል ለሚገኘው ፊቱ በደቡብ አቅጣጫ ላለው ዚማደሪያ ድንኳኑ ጎን 20 ቋሚዎቜን ትሠራለህ።
“ኹ20ዎቹ ቋሚዎቜ ሥር ዹሚሆኑ 40 ዚብር መሰኪያዎቜን ትሠራለህፀ በአንዱ ቋሚ ሥር ያሉት ሁለት ጉጊቜ ሁለት መሰኪያዎቜ፣ ቀጥሎ ባለው በእያንዳንዱ ቋሚ ሥር ያሉት ሁለት ጉጊቜም ሁለት መሰኪያዎቜ ይኖሯ቞ዋል።
በስተ ሰሜን በኩል ላለው ለሌላኛውም ዚማደሪያ ድንኳኑ ጎን 20 ቋሚዎቜን ሥራፀ
እንዲሁም 40 ዚብር መሰኪያዎቻ቞ውን ሥራፀ በአንዱ ቋሚ ሥር ሁለት መሰኪያዎቜ፣ ቀጥሎ ባለው በእያንዳንዱም ቋሚ ሥር ሁለት መሰኪያዎቜ ይኑሩ።
በስተ ምዕራብ በኩል ለሚገኘው ለኋለኛው ዚማደሪያ ድንኳኑ ጎን ስድስት ቋሚዎቜን ትሠራለህ።
በማደሪያ ድንኳኑ በስተ ኋላ በኩል ዹማዕዘን ቋሚዎቜ እንዲሆኑ ሁለት ቋሚዎቜን ትሠራለህ።
ቋሚዎቹም ኚታቜ አንስቶ ዚመጀመሪያው ቀለበት እስኚሚገኝበት እስኚ ላይ ድሚስ ድርብ መሆን አለባ቞ው። ሁለቱም በዚህ መንገድ መሠራት አለባ቞ውፀ እነሱም ሁለት ዹማዕዘን ቋሚዎቜ ሆነው ያገለግላሉ።
ስምንት ቋሚዎቜና ኚብር ዚተሠሩ 16 መሰኪያዎቜ ይኾውም በአንዱ ቋሚ ሥር ሁለት መሰኪያዎቜ፣ ቀጥሎ ባለው በእያንዳንዱም ቋሚ ሥር ሁለት መሰኪያዎቜ ይኖራሉ።
“ኚግራር እንጚት አግዳሚ እንጚቶቜን ታዘጋጃለህፀ በአንዱ ጎን ላሉት ዚማደሪያ ድንኳኑ ቋሚዎቜ አምስት አግዳሚ እንጚቶቜን፣
በሌላኛው ጎን ላሉት ዚማደሪያ ድንኳኑ ቋሚዎቜ አምስት አግዳሚ እንጚቶቜን እንዲሁም በስተ ምዕራብ በኩል ባለው በኋለኛው ዚማደሪያ ድንኳኑ ጎን ላሉት ቋሚዎቜ አምስት አግዳሚ እንጚቶቜን ታዘጋጃለህ።
በቋሚዎቹ መሃል ላይ ዚሚያርፈው መካኚለኛው አግዳሚ እንጚት ኚጫፍ እስኚ ጫፍ ዹሚዘልቅ መሆን ይኖርበታል።
“ቋሚዎቹን በወርቅ ትለብጣ቞ዋለህፀ አግዳሚ እንጚቶቹን ዚሚሞኚሙትን ዚቋሚዎቹን ቀለበቶቜ ኹወርቅ ትሠራ቞ዋለህፀ አግዳሚ እንጚቶቹንም በወርቅ ትለብጣ቞ዋለህ።
ዚማደሪያ ድንኳኑን በተራራው ላይ ተገልጩልህ ባዚኞው ንድፍ መሠሚት ትኚለው።
“ኚሰማያዊ ክር፣ ኚሐምራዊ ሱፍ፣ ኹደማቅ ቀይ ማግ እንዲሁም በቀጭኑ ኹተፈተለ ጥሩ ዚበፍታ ድር መጋሹጃ ትሠራለህ። በላዩም ላይ ኪሩቊቜ ይጠለፉበታል።
መጋሹጃውንም በወርቅ በተለበጡ አራት ዚግራር እንጚት ዓምዶቜ ላይ ታንጠለጥለዋለህ። ማንጠልጠያዎቻ቞ውም ኹወርቅ ዚተሠሩ ይሁኑ። ዓምዶቹም ኚብር በተሠሩ አራት መሰኪያዎቜ ላይ ይቆማሉ።
መጋሹጃውን ኚማያያዣዎቹ በታቜ ታንጠለጥለዋለህፀ ዚምሥክሩንም ታቊት በመጋሹጃው ውስጥ ታስቀምጠዋለህ። መጋሹጃውም ቅድስቱንና ቅድስተ ቅዱሳኑን ለመለዚት ያገለግላቜኋል።
መክደኛውንም በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ በሚገኘው በምሥክሩ ታቊት ላይ ግጠመው።
“ጠሹጮዛውንም ኹመጋሹጃው ውጭ ታስቀምጠዋለህፀ መቅሹዙን በስተ ደቡብ በኩል ባለው ዚማደሪያ ድንኳኑ ጎን ኹጠሹጮዛው ትይዩ ታስቀምጠዋለህፀ ጠሹጮዛውን ደግሞ በስተ ሰሜን በኩል ታስቀምጠዋለህ።
ለድንኳኑ መግቢያ ኚሰማያዊ ክር፣ ኚሐምራዊ ሱፍ፣ ኹደማቅ ቀይ ማግ እንዲሁም በቀጭኑ ኹተፈተለ ጥሩ ዚበፍታ ድር ዹተሾመነ መኚለያ ትሠራለህ።
ለመኚለያውም አምስት ዓምዶቜን ኚግራር እንጚት ትሠራለህፀ በወርቅም ትለብጣ቞ዋለህ። ማንጠልጠያዎቹም ኹወርቅ ዚተሠሩ ይሆናሉፀ ለዓምዶቹም አምስት ዚመዳብ መሰኪያዎቜን ትሠራለህ።
ቀተሰባ቞ውን ይዘው ኚያዕቆብ ጋር ወደ ግብፅ ዚመጡት ዚእስራኀል ወንዶቜ ልጆቜ ስም ዹሚኹተለው ነው፩
ሮቀል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣
ይሳኮር፣ ዛብሎን፣ ቢንያም፣
ዳን፣ ንፍታሌም፣ ጋድና አሎር።
ኚያዕቆብ አብራክ ዚወጡት በጠቅላላ 70 ነበሩፀ ዮሎፍ ግን ቀድሞውኑም እዚያው ግብፅ ነበር።
ኹጊዜ በኋላ ዮሎፍ ሞተፀ ወንድሞቹም ሁሉ ሞቱፀ ያም ትውልድ በሙሉ ሞተ።
እስራኀላውያንም ተዋለዱፀ በጣም ብዙ ሆኑፀ ቁጥራ቞ውም በኹፍተኛ ፍጥነት እዚጚመሚና ኃያል እዚሆኑ ሄዱፀ ኹዚህም ዚተነሳ ምድሪቱን ሞሏት።
ኹጊዜ በኋላ ዮሎፍን ዚማያውቅ አዲስ ንጉሥ በግብፅ ተነሳ።
እሱም ሕዝቊቹን እንዲህ አላቾው፩ “ይኾው እንደምታዩት ዚእስራኀል ሕዝብ ኚእኛ ይልቅ እጅግ ብዙና ኃያል ነው።
እንግዲህ እነሱን በተመለኹተ አንድ መላ እንፍጠር። ካልሆነ ግን ቁጥራ቞ው እዚበዛ ይሄዳልፀ ደግሞም ጊርነት ኚተነሳ ኚጠላቶቻቜን ጋር ወግነው እኛን መውጋታ቞ውና አገሪቱን ጥለው መኮብለላ቞ው አይቀርም።”
በመሆኑም ኚባድ ሥራ በማሠራት እንዲያስጚንቋ቞ው ዚግዳጅ ሥራ ዚሚያሠሩ አለቆቜን ሟሙባ቞ውፀ እነሱም ጲቶም እና ራምሎስ ዚተባሉ ለማኚማቻ ዚሚሆኑ ኚተሞቜን ለፈርዖን ገነቡ።
ሆኖም ይበልጥ በጹቆኗቾው መጠን ይበልጥ እዚበዙና በምድሩ ላይ ይበልጥ እዚተስፋፉ ስለሄዱ ግብፃውያን በእስራኀላውያን ዚተነሳ ኹፍተኛ ፍርሃት አደሚባ቞ው።
በመሆኑም ግብፃውያን እስራኀላውያንን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በባርነት ይገዟቾው ጀመር።
ዹሾክላ ጭቃ በማስቊካት፣ ጡብ በማሠራትና በእርሻ ላይ ማንኛውንም ዓይነት ዚባርነት ሥራ እንዲሠሩ በማድሚግ ሕይወታ቞ውን መራራ አደሚጉባ቞ው። አዎ፣ ማንኛውንም ዓይነት ዚባርነት ሥራ በማሠራት በጭካኔ ያንገላቷ቞ው ነበር።
በኋላም ዚግብፅ ንጉሥ፣ ሺፍራ እና ፑሃ ዚተባሉትን ዕብራውያን አዋላጆቜ አነጋገራ቞ውፀ
እንዲህም አላቾው፩ “ዕብራውያን ሎቶቜን በምታዋልዱበት ጊዜ በማዋለጃው ዱካ ላይ ተቀምጠው ስታዩ ዹሚወለደው ልጅ ወንድ ኹሆነ ግደሉትፀ ሎት ኚሆነቜ ግን በሕይወት ትኑር።”
ይሁን እንጂ አዋላጆቹ እውነተኛውን አምላክ ስለፈሩ ዚግብፅ ንጉሥ ያላ቞ውን አላደሚጉም። ኹዚህ ይልቅ ወንዶቹን ልጆቜ በሕይወት እንዲኖሩ ይተዉአቾው ነበር።
ኹጊዜ በኋላም ዚግብፅ ንጉሥ አዋላጆቹን ጠርቶ “ወንዶቹን ልጆቜ በሕይወት እንዲኖሩ ዚተዋቜኋ቞ው ለምንድን ነው?” አላ቞ው።
አዋላጆቹም ፈርዖንን “ዕብራውያን ሎቶቜ እንደ ግብፃውያን ሎቶቜ አይደሉም። እነሱ ብርቱዎቜ ስለሆኑ አዋላጇ ኚመድሚሷ በፊት በራሳ቞ው ይወልዳሉ” አሉት።
ስለሆነም አምላክ ለአዋላጆቹ መልካም ነገር አደሚገላ቞ውፀ ሕዝቡም እዚበዛና እጅግ ኃያል እዚሆነ ሄደ።
አዋላጆቹ እውነተኛውን አምላክ በመፍራታ቞ው፣ አምላክ ኹጊዜ በኋላ ቀተሰብ ሰጣ቞ው።
በመጚሚሻም ፈርዖን ሕዝቡን ሁሉ “አዲስ ዚሚወለዱትን ዚዕብራውያንን ወንዶቜ ልጆቜ ሁሉ አባይ ወንዝ ውስጥ ጣሏ቞ውፀ ሎቶቹን ልጆቜ ሁሉ ግን በሕይወት እንዲኖሩ ተዉአቾው” ሲል አዘዘ።