text
stringlengths
4
267
ለእናንተም ሆነ ኚእናንተ ጋር ለሚኖር ዚባዕድ አገር ሰው አንድ ዓይነት ሕግና አንድ ዓይነት ድንጋጌ ይኑር።’”
ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“እስራኀላውያንን አናግራ቞ውፀ እንዲህም በላቾው፩ ‘ወደማመጣቜሁ ምድር በምትገቡበትና
ኚምድሪቱ ማንኛውንም ምግብ በምትበሉበት ጊዜ ለይሖዋ መዋጮ ማድሚግ አለባቜሁ።
ኹተፈጹው ዚእህላቜሁ በኩር ላይ ዚቀለበት ቅርጜ ያለው ዳቊ በማዘጋጀት መዋጮ ማድሚግ ይኖርባቜኋል። ይህን ማዋጣት ዚሚኖርባቜሁ ኚአውድማ ላይ ዹሚገኘውን መዋጮ በምታዋጡበት መንገድ ነው።
በትውልዶቻቜሁ ሁሉ፣ ኹተፈጹው ዚእህላቜሁ በኩር ላይ ዹተወሰነውን ለይሖዋ መዋጮ አድርጋቜሁ መስጠት ይኖርባቜኋል።
“‘ምናልባት ስህተት ብትሠሩና ይሖዋ ለሙሮ ዚተናገራ቞ውን እነዚህን ትእዛዛት ሁሉ ሳትፈጜሙ ብትቀሩ
ይኾውም ይሖዋ ትእዛዙን ኚሰጠበት ዕለት አንስቶ ሥራ ላይ ዹዋለውንና በትውልዶቻቜሁ ሁሉ ጞንቶ ዹሚኖሹውን ይሖዋ በሙሮ በኩል ያስተላለፈላቜሁን ትእዛዝ ሁሉ ባትፈጜሙና
ይህን ያደሚጋቜሁት ደግሞ በስህተትና ማኅበሚሰቡ ሳያውቅ ቢሆን መላው ማኅበሚሰብ አንድ ወይፈን ይሖዋን ደስ ዚሚያሰኝ መዓዛ ያለው ዹሚቃጠል መባ አድርጎ ያቅርብፀ ኚእሱም ጋር በተለመደው አሠራር መሠሚት ዚእህል መባውንና ዚመጠጥ መባውን እንዲሁም አንድ ዹፍዹል ጠቊት ዚኃጢአት መባ አድርጎ ያቅርብ።
ካህኑም ለመላው ዚእስራኀል ማኅበሚሰብ ያስተሰርያልፀ ኃጢአቱም ባለማወቅ ዹተፈጾመ ስለሆነና ለሠሩትም ስህተት መባ቞ውን ለይሖዋ በእሳት ዹሚቃጠል መባ አድርገው ስላቀሚቡ እንዲሁም በይሖዋ ፊት ዚኃጢአት መባ቞ውን ስላቀሚቡ ይቅር ይባልላ቞ዋል።
ይህም ሕዝቡ ሁሉ ባለማወቅ ዹፈጾመው ስለሆነ መላው ዚእስራኀል ማኅበሚሰብም ሆነ በመካኚላ቞ው ዹሚኖር ዚባዕድ አገር ሰው ይቅር ይባላል።
“‘ማንኛውም ሰው ባለማወቅ ኃጢአት ቢሠራ አንድ ዓመት ገደማ ዚሆናት አንዲት ፍዹል ዚኃጢአት መባ አድርጎ ያቅርብ።
ኚዚያም ባለማወቅ በይሖዋ ፊት ኃጢአት በመሥራት ዚተሳሳተው ሰው ኃጢአቱ ይሰሚይለት ዘንድ ካህኑ ማስተሰሚያ ያቀርብለታልፀ ኃጢአቱም ይቅር ይባልለታል።
ባለማወቅ ኹሚፈጾም ነገር ጋር በተያያዘ በእስራኀላውያን መካኚል ለሚገኝ ዚአገሬው ተወላጅም ሆነ በመካኚላ቞ው ለሚኖር ዚባዕድ አገር ሰው አንድ ዓይነት ሕግ ይኑራቜሁ።
“‘ይሁን እንጂ ሆን ብሎ ኃጢአት ዚሚሠራ ሰው ዚአገሬው ተወላጅም ይሁን ዚባዕድ አገር ሰው ይሖዋን እንደተሳደበ ስለሚቆጠር ኚሕዝቡ ተለይቶ እንዲጠፋ መደሹግ አለበት።
ዹይሖዋን ቃል ስላቃለለና ዚእሱን ትእዛዝ ስለጣሰ ያ ሰው ያለምንም ጥርጥር ተለይቶ እንዲጠፋ መደሹግ አለበት። ጥፋቱ ዚራሱ ነው።’”
እስራኀላውያን በምድሚ በዳ ሳሉ አንድ ሰው በሰንበት ቀን እንጚት ሲለቅም አገኙ።
ሰዎቹም እንጚት ሲለቅም ያገኙትን ሰው ወደ ሙሎ፣ ወደ አሮንና ወደ መላው ማኅበሚሰብ አመጡት።
ሰውዹው ምን መደሹግ እንዳለበት በግልጜ ዹተቀመጠ ነገር ስላልነበሚ በጥበቃ ሥር እንዲቆይ አደሚጉ።
ይሖዋም ሙሮን “ሰውዹው ያለምንም ጥርጥር መገደል አለበትፀ መላው ማኅበሚሰብም ኚሰፈሩ ውጭ በድንጋይ ይውገሹው” አለው።
ስለዚህ ይሖዋ ሙሮን ባዘዘው መሠሚት መላው ማኅበሚሰብ ሰውዹውን ኚሰፈሩ ውጭ አውጥቶ እስኪሞት ድሚስ በድንጋይ ወገሚው።
ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“እስራኀላውያን በትውልዶቻ቞ው ሁሉ በልብሳ቞ው ጫፍ ላይ ዘርፍ እንዲያደርጉ ንገራ቞ውፀ ልብሳ቞ውም ኹዘርፉ በላይ ሰማያዊ ጥለት ይኑሚው።
‘ይህን ዘርፍ በልብሳቜሁ ላይ አድርጉፀ ምክንያቱም እሱን ስታዩ ዹይሖዋን ትእዛዛት ሁሉ ታስታውሳላቜሁፀ እንዲሁም ትፈጜማላቜሁ። ወደ መንፈሳዊ ምንዝር ዚሚመራቜሁን ዚገዛ ልባቜሁንና ዓይናቜሁን አትኚተሉ።
ይህን መመሪያ ዚሰጠኋቜሁ ትእዛዛ቎ን በሙሉ እንድታስታውሱና እንድትፈጜሙ ነውፀ ለአምላካቜሁም ዚተቀደሳቜሁ ትሆናላቜሁ።
አምላካቜሁ መሆኔን ለማስመሥኚር ኚግብፅ ምድር ያወጣኋቜሁ እኔ አምላካቜሁ ይሖዋ ነኝ። አዎ፣ እኔ አምላካቜሁ ይሖዋ ነኝ።’”
ዚሮቀል ልጆቜና ዚጋድ ልጆቜ እጅግ በጣም ብዙ ኚብት ነበራ቞ው። እነሱም ዚያዜር እና ዚጊልያድ ምድር ለኚብቶቜ ዚሚስማማ ስፍራ እንደሆነ አዩ።
በመሆኑም ዚሮቀል ልጆቜና ዚጋድ ልጆቜ መጥተው ሙሎን፣ ካህኑን አልዓዛርንና ዚማኅበሚሰቡን አለቆቜ እንዲህ አሏቾው፩
“ዚአጣሮት፣ ዚዲቊን፣ ዚያዜር፣ ዚኒምራ፣ ዚሃሜቊን፣ ዚኀልዓሌ፣ ዚሰባም፣ ዹነቩ እና ዚቀኊን ምድር
ይሖዋ በእስራኀል ማኅበሚሰብ ፊት ድል ያደሚገው ሲሆን ለኚብቶቜ ምቹ ነውፀ አገልጋዮቜህ ደግሞ ብዙ ኚብት አላ቞ው።”
አክለውም እንዲህ አሉ፩ “እንግዲህ በፊትህ ሞገስ ካገኘን ይህ ምድር ለአገልጋዮቜህ ርስት ተደርጎ ይሰጥ። ዮርዳኖስን እንድንሻገር አታድርገን።”
ኚዚያም ሙሮ ዚጋድን ልጆቜና ዚሮቀልን ልጆቜ እንዲህ አላቾው፩ “እናንተ እዚህ ተቀምጣቜሁ ወንድሞቻቜሁ ወደ ጊርነት እንዲሄዱ ትፈልጋላቜሁ?
ዚእስራኀል ልጆቜ ይሖዋ ወደሚሰጣ቞ው ምድር እንዳይሻገሩ ተስፋ ዚምታስቆርጧ቞ው ለምንድን ነው?
አባቶቻቜሁ ምድሪቱን እንዲያዩ ኚቃዎስበርኔ በላክኋቾው ጊዜ ያደሚጉት ይህንኑ ነበር።
ወደ ኀሜኮል ሾለቆ አቅንተው ምድሪቱን ካዩ በኋላ ዚእስራኀልን ሕዝብ ይሖዋ ወደሚሰጠው ምድር እንዳይገባ ተስፋ አስቆሚጡት።
በዚያ ቀን ዹይሖዋ ቁጣ ነደደፀ እንዲህም ሲል ማለ፩
‘ኚግብፅ ምድር ኚወጡት መካኚል 20 ዓመትና ኚዚያ በላይ ዹሆናቾው ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ዚማልኩላ቞ውን ምድር አያዩምፀ ምክንያቱም በሙሉ ልባ቞ው አልተኚተሉኝምፀ
ይሖዋን በሙሉ ልባ቞ው ኚተኚተሉት ኹቀኒዛዊው ኹዹፎኒ ልጅ ኚካሌብና ኹነዌ ልጅ ኚኢያሱ በስተቀር አንዳ቞ውም ምድሪቱን አያዩም።’
በመሆኑም ዹይሖዋ ቁጣ በእስራኀል ላይ ነደደፀ በይሖዋ ፊት ክፉ ድርጊት ዹፈጾመው ያ ትውልድ በሙሉ እስኪያልቅ ድሚስ ለ40 ዓመት በምድሚ በዳ እንዲንኚራተቱ አደሚጋ቞ው።
እናንተ ዚኃጢአተኞቜ ልጆቜ ደግሞ ይኾው በአባቶቻቜሁ እግር ተተክታቜሁ ይሖዋ በእስራኀል ላይ ይበልጥ እንዲቆጣ ታደርጋላቜሁ።
እንግዲህ እናንተ እሱን ኹመኹተል ዞር ካላቜሁ እሱም እንደገና በምድሚ በዳ ይተዋ቞ዋልፀ እናንተም በዚህ ሁሉ ሕዝብ ላይ ጥፋት ታመጣላቜሁ።”
በኋላም ወደ እሱ ቀርበው እንዲህ አሉትፊ “እንግዲያው እዚሁ ለኚብቶቻቜን በድንጋይ ካብ በሚት እንሥራፀ ለልጆቻቜንም ኚተሞቜ እንገንባ።
ይሁን እንጂ ወደ ስፍራ቞ው እስክናስገባ቞ው ድሚስ ለጊርነት ታጥቀን በእስራኀላውያን ፊት እንሄዳለንፀ በዚህም ጊዜ ልጆቻቜን ኚምድሪቱ ነዋሪዎቜ ተጠብቀው በተመሞጉት ኚተሞቜ ውስጥ ይኖራሉ።
እኛም እያንዳንዱ እስራኀላዊ ዚራሱን ርስት እስኪያገኝ ድሚስ ወደ ቀታቜን አንመለስም።
እኛ ኚዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ባለው አካባቢ ርስት ካገኘን ኚዮርዳኖስ ማዶና ኚዚያ ባሻገር ባለው አካባቢ ኚእነሱ ጋር ርስት አንካፈልም።”
ሙሮም እንዲህ አላቾው፩ “ይህን ብታደርጉ ይኾውም በጊርነቱ ለመካፈል በይሖዋ ፊት ታጥቃቜሁ ብትነሱ
እንዲሁም ጠላቶቹን ኚፊቱ እስኪያስወግድ ድሚስ እያንዳንዳቜሁ ዹጩር መሣሪያቜሁን ይዛቜሁ በይሖዋ ፊት ዮርዳኖስን ብትሻገሩና
ምድሪቱ በይሖዋ ፊት እስክትገዛ ድሚስ በዚያ ብትቆዩ፣ ኚዚያ በኋላ መመለስ ትቜላላቜሁፀ በይሖዋም ሆነ በእስራኀላውያን ዘንድ ኹበደል ነፃ ትሆናላቜሁ። ኚዚያም ይህቜ ምድር በይሖዋ ፊት ዚእናንተ ርስት ትሆናለቜ።
ይህን ባታደርጉ ግን በይሖዋ ላይ ኃጢአት ትሠራላቜሁ። ለሠራቜሁትም ኃጢአት ተጠያቂ እንደምትሆኑ እወቁ።
ስለዚህ ለልጆቻቜሁ ኚተሞቜን መገንባትና ለመንጎቻቜሁ በሚት መሥራት ዚምትቜሉ ቢሆንም ዚገባቜሁትን ቃል መፈጾም ይኖርባቜኋል።”
ዚጋድ ልጆቜና ዚሮቀል ልጆቜም ሙሮን እንዲህ አሉትፊ “እኛ አገልጋዮቜህ ጌታቜን እንዳዘዘን እናደርጋለን።
ልጆቻቜን፣ ሚስቶቻቜን፣ ኚብቶቻቜንና እንስሶቻቜን በሙሉ በጊልያድ ኚተሞቜ ውስጥ ይቆያሉፀ
ሆኖም እኛ አገልጋዮቜህ ይኾውም በይሖዋ ፊት ጊርነት ለመግጠም ዚታጠቅን እያንዳንዳቜን ልክ ጌታቜን በተናገሹው መሠሚት እንሻገራለን።”
በመሆኑም ሙሮ ለካህኑ ለአልዓዛር፣ ለነዌ ልጅ ለኢያሱና ለእስራኀል ነገዶቜ ዚአባቶቜ ቀት መሪዎቜ እነሱን በተመለኹተ ትእዛዝ ሰጠ።
ሙሮም እንዲህ አላቾው፩ “ዚጋድ ልጆቜና ዚሮቀል ልጆቜ ይኾውም በይሖዋ ፊት ለጊርነት ዚታጠቀ እያንዳንዱ ሰው ኚእናንተ ጋር ዮርዳኖስን ኚተሻገሚ፣ ምድሪቱም በፊታቜሁ ኚተገዛቜ ዚጊልያድን ምድር ርስት አድርጋቜሁ ትሰጧ቞ዋላቜሁ።
ሆኖም ዹጩር መሣሪያ ታጥቀው ኚእናንተ ጋር ካልተሻገሩ በኹነአን ምድር በመካኚላቜሁ ይኖራሉ።”
በዚህ ጊዜ ዚጋድ ልጆቜና ዚሮቀል ልጆቜ እንዲህ ሲሉ መለሱፊ “ይሖዋ ለአገልጋዮቜህ ዹተናገሹውን እንፈጜማለን።
እኛ ራሳቜን ዹጩር መሣሪያ ታጥቀን በይሖዋ ፊት ወደ ኹነአን ምድር እንሻገራለንፀ ዹምንወርሰው ርስት ግን ኚዮርዳኖስ ወዲህ ያለውን ይሆናል።”
ስለዚህ ሙሮ ለጋድ ልጆቜና ለሮቀል ልጆቜ እንዲሁም ለዮሎፍ ልጅ ለምናሮ ነገድ እኩሌታ ዚአሞራውያንን ንጉሥ ዚሲሖንን ግዛትና ዚባሳንን ንጉሥ ዹኩግን ግዛት ይኾውም በክልሎቹ ውስጥ ዹሚገኙ ኚተሞቜ ይዞታ ዹሆነውን ምድር እንዲሁም በዙሪያው ባለው ምድር ያሉትን ኚተሞቜ ሰጣ቞ው።
ዚጋድ ልጆቜም ዲቊን፣ አጣሮት፣ አሮዔር፣
አትሮትሟፋን፣ ያዜር፣ ዮግበሃ፣
ቀትኒምራ እና ቀትሃራን ዚተባሉትን ዹተመሾጉ ኚተሞቜ ገነቡፀ ለመንጎቹም በድንጋይ ካብ በሚት ሠሩ።
ዚሮቀል ልጆቜ ደግሞ ሃሜቊንን፣ ኀልዓሌን፣ ቂርያታይምን፣
ስማ቞ው ዹተለወጠውን ነቩን እና በዓልመዖንን እንዲሁም ሲብማን ገነቡፀ እነሱም መልሰው ለገነቧቾው ኚተሞቜ አዲስ ስም አወጡላ቞ው።
ዹምናሮ ልጅ ዚማኪር ልጆቜ በጊልያድ ላይ ዘምተው ምድሪቱን ያዙፀ በዚያም ይኖሩ ዚነበሩትን አሞራውያን አስወጧ቞ው።
በመሆኑም ሙሮ ጊልያድን ለምናሮ ልጅ ለማኪር ሰጠውፀ እሱም በዚያ መኖር ጀመሚ።
ዹምናሮ ልጅ ያኢርም በእነሱ ላይ ዘምቶ ዚድንኳን ሰፈሮቻ቞ውን ያዘፀ እነሱንም ሃዎትያኢር ብሎ ጠራ቞ው።
ኖባህም ዘምቶ ቄናትንና በሥሯ ያሉትን ኚተሞቜ ያዘፀ እነሱንም በራሱ ስም ኖባህ ብሎ ሰዚማ቞ው።
ይሖዋም ሙሮንና አሮንን እንዲህ አላቾው፩
“ኹሌዊ ልጆቜ መካኚል ዚቀአትን ወንዶቜ ልጆቜ በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜ መሠሚት ቁጠሩፀ
በመገናኛ ድንኳኑ ውስጥ እንዲሠራ በተመደበው ቡድን ውስጥ ያሉትን ዕድሜያ቞ው ኹ30 እስኚ 50 ዓመት ዚሆኑትን ሁሉ ቁጠሩ።
“ዚቀአት ወንዶቜ ልጆቜ በመገናኛ ድንኳኑ ውስጥ ዚሚያኚናውኑት አገልግሎት ይህ ነው። ይህ እጅግ ቅዱስ ዹሆነ ነገር ነው፩
ሰፈሩ በሚነሳበት ጊዜ አሮንና ወንዶቜ ልጆቹ መጥተው ታቊቱን ዹሚኹልለውን መጋሹጃ ያወርዱታልፀ ዚምሥክሩንም ታቊት በእሱ ይሞፍኑታል።
በላዩም ላይ ኚአቆስጣ ቆዳ ዚተሠራ መሾፈኛ ይደርቡበታልፀ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ ሰማያዊ ዹሆነ ጹርቅ ያለብሱታልፀ ለመሞኚሚያ ዚሚያገለግሉትንም መሎጊያዎቜ በቊታ቞ው ላይ ያደርጓ቞ዋል።
“ገጾ ኅብስቱ ዚሚቀመጥበትንም ጠሹጮዛ ሰማያዊ ጹርቅ ያለብሱታልፀ በላዩም ላይ ሳህኖቹን፣ ጜዋዎቹን፣ ጎድጓዳ ሳህኖቹንና ለመጠጥ መባ ዚሚሆኑትን ማንቆርቆሪያዎቜ ያስቀምጣሉፀ ዚዘወትሩም ዚቂጣ መባ ኚላዩ ላይ አይነሳ።
ደማቅ ቀይ ጹርቅ ያለብሷ቞ዋልፀ ኚአቆስጣ ቆዳ ዚተሠራ መሾፈኛም ይደርቡበታልፀ እንዲሁም ለመሞኚሚያ ዚሚያገለግሉትን መሎጊያዎቜ በቊታ቞ው ላይ ያደርጓ቞ዋል።
ኚዚያም ሰማያዊ ጹርቅ ወስደው ዚመብራቱን መቅሹዝ ኚመብራቶቹ፣ ኚመቆንጠጫዎቹና ኚመኮስተሪያዎቹ እንዲሁም ዘወትር ዘይት እንዲኖር ለማድሚግ ኚሚያገለግሉት ዘይት ዚሚቀመጥባ቞ው ዕቃዎቜ ሁሉ ጋር ይሞፍኑታል።
መቅሹዙን ኚዕቃዎቹ ሁሉ ጋር ኚአቆስጣ ቆዳ በተሠራ መሾፈኛ ይጠቀልሉታልፀ በመሞኚሚያ ሳንቃ ላይም ያስቀምጡታል።
ዹወርቁን መሠዊያም ሰማያዊ ጹርቅ ያለብሱታልፀ ኚአቆስጣ ቆዳ ዚተሠራ መሾፈኛም ይደርቡበታልፀ ለመሞኚሚያ ዚሚያገለግሉትንም መሎጊያዎቜ በቊታ቞ው ላይ ያደርጓ቞ዋል።
ኚዚያም በቅዱሱ ስፍራ ዘወትር ዚሚጠቀሙባ቞ውን መገልገያ ዕቃዎቜ በሙሉ ወስደው በሰማያዊ ጹርቅ ይጠቀልሏ቞ዋልፀ ኚአቆስጣ ቆዳ ዚተሠራ መሾፈኛም ይደርቡባ቞ዋልፀ በመሞኚሚያ ሳንቃ ላይም ያስቀምጧ቞ዋል።
“አመዱን ኚመሠዊያው ላይ ያስወግዱፀ መሠዊያውንም ሐምራዊ ዚሱፍ ጹርቅ ያልብሱት።
እንዲሁም በመሠዊያው ላይ ለማገልገል ዚሚጠቀሙባ቞ውን ዕቃዎቜ በሙሉ ይኾውም መኮስተሪያዎቹን፣ ሹካዎቹን፣ አካፋዎቹን፣ ጎድጓዳ ሳህኖቹንና ዚመሠዊያውን ዕቃዎቜ በሙሉ በላዩ ላይ ያደርጉበታልፀ ኚአቆስጣ ቆዳ ዚተሠራ መሾፈኛም ይደርቡበታልፀ ለመሞኚሚያ ዚሚያገለግሉትንም መሎጊያዎቜ በቊታ቞ው ላይ ያደርጓ቞ዋል።
“አሮንና ወንዶቜ ልጆቹ ሰፈሩ ኚመነሳቱ በፊት በቅዱሱ ስፍራ ያሉትን ነገሮቜና ዚቅዱሱን ስፍራ ዕቃዎቜ በሙሉ ሾፍነው መጚሚስ አለባ቞ው። ኚዚያም ዚቀአት ወንዶቜ ልጆቜ ለመሾኹም ይመጣሉፀ ሆኖም በቅዱሱ ስፍራ ያሉትን ነገሮቜ መንካት ዚለባ቞ውምፀ ኚነኩ ግን ይሞታሉ። ኹመገናኛ ድንኳኑ ጋር በተያያዘ እነዚህን ነገሮቜ ዹማኹናወኑ ኃላፊነት ዚተጣለው በቀአት ወንዶቜ ልጆቜ ላይ ነው።
“ዚመብራቱን ዘይት፣ ጥሩ መዓዛ ያለውን ዕጣን፣ ዘወትር ዹሚቀርበውን ዚእህል መባና ዚቅብዓት ዘይቱን ዚመቆጣጠሩ ኃላፊነት ዚካህኑ ዚአሮን ልጅ ዹአልዓዛር ነው። ቅዱሱን ስፍራና ዕቃዎቹን ጚምሮ ዚማደሪያ ድንኳኑን ሁሉና በውስጡ ያለውን ነገር በሙሉ ዚመቆጣጠሩ ኃላፊነት ዚእሱ ነው።”
በተጚማሪም ይሖዋ ሙሮንና አሮንን እንዲህ አላቾው፩
“ዚቀአታውያን ቀተሰቊቜ ነገድ ኚሌዋውያን መካኚል ተለይቶ እንዲጠፋ አታድርጉ።
እጅግ ቅዱስ ወደሆኑት ነገሮቜ በመቅሚባ቞ው ዚተነሳ እንዳይሞቱ፣ ኹዚህ ይልቅ በሕይወት እንዲኖሩ ይህን አድርጉላ቞ው። አሮንና ወንዶቜ ልጆቹ ገብተው ለእያንዳንዳ቞ው ሥራ቞ውንና ዚሚሞኚሙትን ነገር ይመድቡላ቞ው።
ቅዱስ ዚሆኑትን ነገሮቜ ለአፍታ እንኳ ገብተው ማዚት ዚለባ቞ውምፀ ካዩ ግን ይሞታሉ።”
ኚዚያም ይሖዋ ሙሮን እንዲህ አለው፩
“ዚጌድሶንን ወንዶቜ ልጆቜ በዚአባቶቻ቞ው ቀቶቜና በዚቀተሰባ቞ው ቁጠር።
በመገናኛ ድንኳኑ ውስጥ እንዲያገለግል በተመደበው ቡድን ውስጥ ያሉትን ዕድሜያ቞ው ኹ30 እስኚ 50 ዓመት ዚሆኑትን ሁሉ መዝግብ።
ዚጌድሶናውያን ቀተሰቊቜ እንዲንኚባኚቡና እንዲሞኚሙ ዚተመደቡት እነዚህን ነገሮቜ ነው፩
እነሱም ዚማደሪያ ድንኳኑን ዚድንኳን ጚርቆቜ፣ ዹመገናኛ ድንኳኑን ጚርቆቜ፣ መደሚቢያውንና ኚእሱ በላይ ያለውን ኚአቆስጣ ቆዳ ዚተሠራ መደሚቢያ እንዲሁም ዹመገናኛ ድንኳኑን መግቢያ መኚለያ ይሞኚማሉፀ
በተጚማሪም ዚግቢውን መጋሚጃዎቜ፣ በማደሪያ ድንኳኑና በመሠዊያው ዙሪያ ባለው ግቢ መግቢያ ላይ ዹሚገኘውን መኚለያ፣ ዚድንኳን ገመዶቻ቞ውንና ዕቃዎቻ቞ውን በሙሉ እንዲሁም ለአገልግሎቱ ዚሚውሉትን ነገሮቜ ሁሉ ይሞኚማሉ። ዚሥራ ምድባ቞ው ይህ ነው።
ጌድሶናውያን ዚሚያኚናውኑትን አገልግሎትና ዹሚሾኹሟቾውን ነገሮቜ ሁሉ ዚሚቆጣጠሩት አሮንና ወንዶቜ ልጆቹ ና቞ውፀ እነዚህን ነገሮቜ ሁሉ ዹመሾኹሙን ኃላፊነት ለእነሱ ትሰጣ቞ዋለህ።
ዚጌድሶናውያን ቀተሰቊቜ በመገናኛ ድንኳኑ ውስጥ ዚሚያኚናውኑት አገልግሎት ይህ ነውፀ ኃላፊነታ቞ውንም ዚሚወጡት በካህኑ በአሮን ልጅ በኢታምር አመራር ሥር ሆነው ነው።
“ዚሜራሪን ወንዶቜ ልጆቜም በዚቀተሰባ቞ውና በዚአባቶቻ቞ው ቀት ትመዘግባ቞ዋለህ።
በመገናኛ ድንኳኑ እንዲያገለግል በተመደበው ቡድን ውስጥ ያሉትን ዕድሜያ቞ው ኹ30 እስኚ 50 ዓመት ዚሆኑትን ሁሉ ትመዘግባለህ።
በመገናኛ ድንኳኑ ኚሚያኚናውኑት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ዚሚኚተሉትን ነገሮቜ ዹመሾኹም ኃላፊነት ተጥሎባ቞ዋልፊ ዚማደሪያ ድንኳኑን ቋሚዎቜ፣ አግዳሚ እንጚቶቹን፣ ዓምዶቹን፣ መሰኪያዎቹን፣
በግቢው ዙሪያ ያሉትን ቋሚዎቜ፣ መሰኪያዎቻ቞ውን፣ ዚድንኳን ካስማዎቻ቞ውን፣ ዚድንኳን ገመዶቻ቞ውን እንዲሁም ቁሳቁሶቻ቞ውንና ኹዚህ አገልግሎት ጋር ዚተያያዙትን ነገሮቜ ሁሉ ይሞኚማሉ። በኃላፊነት ዚሚሞኚሙትንም ዕቃ በስም ጠቅሰህ ትመድብላ቞ዋለህ።