text
stringlengths
4
267
እንዲሁም ልጆቻቜሁ፣ ሚስቶቻቜሁና ኚእንጚት ለቃሚዎቻቜሁ አንስቶ እስኚ ውኃ ቀጂዎቻቜሁ ድሚስ፣ በሰፈራቜሁ ዚሚኖሩ ዚባዕድ አገር ሰዎቜ ሁሉ በፊቱ ቆመዋል።
አሁን እዚህ ዹተገኘኾው አምላክህ ይሖዋ በዛሬው ዕለት ኚአንተ ጋር ወደሚገባው ይኾውም በመሐላ ወደሚያጞናው ወደ አምላክህ ወደ ይሖዋ ቃል ኪዳን እንድትገባ ነውፀ
ይህም ለአንተ ቃል በገባውና ለአባቶቜህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ በማለላቾው መሠሚት በዛሬው ዕለት አንተን ሕዝቡ አድርጎ ያጞናህ እንዲሁም አምላክህ ይሆን ዘንድ ነው።
“እኔ አሁን ይህን ቃል ኪዳን ዚምገባውም ሆነ ይህን መሐላ ዹምምለው ለእናንተ ብቻ አይደለምፀ
ኹዚህ ይልቅ በዛሬው ዕለት በይሖዋ ፊት አብሚውን ለቆሙትና በዚህ ዕለት ኚእኛ ጋር ለሌሉት ጭምር ነው።
(በግብፅ እንዎት እንኖር እንደነበሚና በጉዟቜንም ላይ ዚተለያዩ ብሔራትን እንዎት አቋርጠን እንዳለፍን በሚገባ ታውቃላቜሁና።
በመካኚላ቞ው ዚነበሩትን ዚሚያስጠሉ ነገሮቜ እንዲሁም ኚእንጚት፣ ኚድንጋይ፣ ኚብርና ኹወርቅ ዚተሠሩ አስጞያፊ ጣዖቶቻ቞ውንም አይታቜኋል።)
ዚእነዚያን ብሔራት አማልክት ለማገልገል ኚአምላካቜን ኹይሖዋ ልቡ ዚሚሞፍት ወንድ ወይም ሎት ወይም ቀተሰብ አሊያም ነገድ በዛሬው ዕለት በመካኚላቜሁ እንዳይገኝ እንዲሁም መርዛማና መራራ ፍሬ ዚሚያፈራ ሥር በመካኚላቜሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ።
“አንድ ሰው ይህን ዹመሐላ ቃል ቢሰማና በመንገዱ ላይ ያገኘውን ሁሉ ጠራርጎ ለማጥፋት በማሰብ ‘እንዳሻኝ ብሆን እንኳ በሰላም እኖራለሁ’ እያለ በልቡ ቢኩራራ
ይሖዋ ይቅር ሊለው ፈቃደኛ አይሆንም። ኹዚህ ይልቅ ዹይሖዋ ታላቅ ቁጣ በዚያ ሰው ላይ ይነድዳልፀ በዚህ መጜሐፍ ውስጥ ዚተጻፉት እርግማኖቜ በሙሉ ይወርዱበታልፀ ይሖዋም ዹዚህን ሰው ስም ኹሰማይ በታቜ ይደመስሰዋል።
ኚዚያም በዚህ ዹሕግ መጜሐፍ ውስጥ በተጻፈው በቃል ኪዳኑ እርግማን ሁሉ መሠሚት ይሖዋ ኚሌሎቹ ዚእስራኀል ነገዶቜ ሁሉ እሱን ለጥፋት ይለዚዋል።
“መጪው ዚልጆቻቜሁ ትውልድና ኚሩቅ ምድር ዚሚመጡት ዚባዕድ አገር ሰዎቜ በምድሪቱ ላይ ዚወሚዱትን መቅሰፍቶቜ ይኾውም ይሖዋ በላይዋ ላይ ያመጣውን በሜታ
እንዲሁም ይሖዋ በቁጣውና በመዓቱ ሰዶምንና ገሞራን፣ አድማህንና ጾቩይምን እንደገለባበጠ ሁሉ መላዋ ምድር እንዳይዘራባት፣ እንዳታቆጠቁጥ ወይም ምንም ዓይነት ተክል እንዳታበቅል ዹላኹውን ድኝ፣ ጹውና እሳት ሲመለኚቱ
እነሱም ሆኑ ሁሉም ብሔራት ‘ይሖዋ በዚህቜ ምድር ላይ እንዲህ ያደሚገው ለምንድን ነው? ይህን ታላቅ ቁጣስ ምን አመጣው?’ ይላሉ።
ኚዚያም እንዲህ ይላሉ፩ ‘ይህ ዚደሚሰባ቞ው ዚአባቶቻ቞ው አምላክ ይሖዋ ኚግብፅ ምድር ባወጣ቞ው ጊዜ ኚእነሱ ጋር ዚገባውን ቃል ኪዳን በማፍሚሳ቞ው ነው።
ሄደውም ሌሎቜን አማልክት ይኾውም ዚማያውቋ቞ውንና እሱ እንዲያመልኳ቞ው ያልፈቀደላ቞ውን አማልክት አገለገሉፀ ደግሞም ሰገዱላ቞ው።
ይሖዋም በዚህ መጜሐፍ ላይ ዚተጻፉትን እርግማኖቜ በሙሉ እስኪያመጣባት ድሚስ ቁጣው በምድሪቱ ላይ ነደደ።
በመሆኑም ይሖዋ በታላቅ ቁጣውና በኃይለኛው ንዎቱ ኚምድራ቞ው ላይ ነቅሎ አሁን ወዳሉበት ሌላ ምድር አፈለሳ቞ው።’
“ዚተሰወሩት ነገሮቜ ዚአምላካቜን ዹይሖዋ ና቞ውፀ ዚተገለጡት ነገሮቜ ግን በዚህ ሕግ ውስጥ ያሉትን ቃላት በሙሉ እንፈጜም ዘንድ ለዘላለም ዚእኛና ዚዘሮቻቜን ና቞ው።
“በሕይወት እንድትኖሩና እንድትበዙ እንዲሁም ይሖዋ ለአባቶቻቜሁ ዹማለላቾውን ምድር ገብታቜሁ እንድትወርሱ ዛሬ ዚማዛቜሁን እያንዳንዱን ትእዛዝ በጥንቃቄ ጠብቁ።
አምላክህ ይሖዋ በልብህ ምን እንዳለ ይኾውም ትእዛዛቱን ትጠብቅ እንደሆነና እንዳልሆነ ለማወቅ ይፈትንህና ትሑት ያደርግህ ዘንድ በእነዚህ 40 ዓመታት በምድሚ በዳ እንድትጓዝበት ያደሚገህን ሹጅሙን መንገድ አስታውስ።
ትሑት እንድትሆን አደሚገህፀ ካስራበህም በኋላ አንተ ዚማታውቀውን፣ አባቶቜህም ዚማያውቁትን መና መገበህፀ ይህን ያደሚገው፣ ሰው ኹይሖዋ አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በምግብ ብቻ ሊኖር እንደማይቜል ሊያሳውቅህ ነው።
በእነዚህ 40 ዓመታት፣ ዚለበስኚው ልብስ አላለቀምፀ እግርህም አላበጠም።
አንድ ሰው ለልጁ እርማት እንደሚሰጥ ሁሉ አምላክህ ይሖዋም እርማት ይሰጥህ እንደነበር ልብህ በሚገባ ያውቃል።
“እንግዲህ አንተ በመንገዶቹ በመሄድና እሱን በመፍራት ዹአምላክህን ዹይሖዋን ትእዛዛት ጠብቅ።
ምክንያቱም አምላክህ ይሖዋ መልካም ወደሆነቜ ምድር ሊያስገባህ ነውፀ ይህቜ ምድር ጅሚቶቜ ያሏት፣ በሾለቋማ ሜዳዋና በተራራማ አካባቢዋ ምንጮቜ ዚሚፈልቁባትና ውኃዎቜ ዚሚንዶለዶሉባት፣
ስንዎ፣ ገብስ፣ ወይን፣ በለስና ሮማን ዚሚበቅልባት፣ ዚወይራ ዘይትና ማር ዚሚገኝባት፣
ዚምግብ እጥሚት ዚሌለባት፣ ምንም ነገር ዚማታጣባት፣ ብሚት ያለባ቞ው ድንጋዮቜ ዚሚገኙባት እንዲሁም ኚተራሮቿ መዳብ ቆፍሹህ ዚምታወጣባት ምድር ናት።
“በልተህ በምትጠግብበት ጊዜ ስለሰጠህ ስለ መልካሚቱ ምድር አምላክህን ይሖዋን አመስግነው።
እኔ ዛሬ ዹማዝህን ዚእሱን ትእዛዛት፣ ድንጋጌዎቜና ደንቊቜ ቜላ በማለት አምላክህን ይሖዋን እንዳትሚሳው ተጠንቀቅ።
በልተህ ስትጠግብ፣ ጥሩ ጥሩ ቀቶቜን ሠርተህ በዚያ መኖር ስትጀምር፣
ኚብትህና መንጋህ ሲበዛ፣ ብርህና ወርቅህ ሲበራኚት እንዲሁም ዹአንተ ዹሆነው ሁሉ እዚበዛ ሲሄድ
ልብህ እንዳይታበይና ኚግብፅ ምድር ይኾውም ኚባርነት ቀት ያወጣህን አምላክህን ይሖዋን እንዳያስሚሳህ ተጠንቀቅፀ
መርዛማ እባቊቜና ጊንጊቜ በሞሉበት እንዲሁም ውኃ ዹተጠማ ደሚቅ ምድር ባለበት በዚያ ጭልጥ ያለና ዚሚያስፈራ ምድሚ በዳ አቋርጠህ እንድታልፍ ያደሚገህን አምላክህን እንዳያስሚሳህ ተጠንቀቅ። እሱ ኚጠንካራ ዓለት ውኃ አፍልቆልሃልፀ
እንዲሁም ወደፊት መልካም እንዲሆንልህ አንተን ትሑት ለማድሚግና ለመፈተን ሲል አባቶቜህ ዚማያውቁትን መና በምድሚ በዳ መግቊሃል።
በልብህም ‘ይህን ሀብት ያፈራሁት በራሎ ኃይልና በእጄ ብርታት ነው’ ብለህ ብታስብ
ሀብት እንድታፈራ ኃይል ዹሰጠህ አምላክህ ይሖዋ መሆኑን አስታውስፀ ይህን ያደሚገው ዛሬ እንደሆነው ሁሉ ለአባቶቜህ በመሐላ ዚገባውን ቃል ኪዳን ለመፈጾም ነው።
“አምላክህን ይሖዋን ብትሚሳና ሌሎቜ አማልክትን ብትኚተል እንዲሁም እነሱን ብታገለግልና ለእነሱ ብትሰግድ፣ በእርግጥ እንደምትጠፉ እኔ ዛሬ እመሠክርባቜኋለሁ።
ዚአምላካቜሁን ዹይሖዋን ቃል ስላልሰማቜሁ ይሖዋ ኚፊታቜሁ እንደሚያጠፋ቞ው ብሔራት እናንተም እንዲሁ ትጠፋላቜሁ።
ኚዚያም ዕጣው ለምናሮ ነገድ ወጣፀ ምክንያቱም እሱ ዚዮሎፍ ዚበኩር ልጅ ነበር። ዚጊልያድ አባት ዹሆነው ዹምናሮ ዚበኩር ልጅ ማኪር ጩሹኛ ሰው ስለነበር ጊልያድን እና ባሳንን ወሰደ።
ለቀሩት ዹምናሮ ዘሮቜም በዚቀተሰባ቞ው ይኾውም ለአቢዔዜር ልጆቜ፣ ለሄሌቅ ልጆቜ፣ ለአስሪዔል ልጆቜ፣ ለሎኬም ልጆቜ፣ ለሄፌር ልጆቜና ለሞሚዳ ልጆቜ ዕጣ ወጣ። ዚዮሎፍ ልጅ ዹምናሮ ዘሮቜ ወንዶቹ በዚቀተሰባ቞ው እነዚህ ነበሩ።
ሆኖም ዹምናሮ ልጅ፣ ዚማኪር ልጅ፣ ዚጊልያድ ልጅ፣ ዹሄፌር ልጅ ሰለጰአድ ሎቶቜ እንጂ ወንዶቜ ልጆቜ አልነበሩትምፀ ዚሎቶቜ ልጆቹም ስም ማህላ፣ ኖኅ፣ ሆግላ፣ ሚልካ እና ቲርጻ ነበር።
እነሱም ወደ ካህኑ አልዓዛር፣ ወደ ነዌ ልጅ ወደ ኢያሱና ወደ አለቆቹ ቀርበው “ይሖዋ በወንድሞቻቜን መካኚል ርስት እንዲሰጠን ሙሮን አዞት ነበር” አሏ቞ው። ስለዚህ ኢያሱ ይሖዋ በሰጠው ትእዛዝ መሠሚት በአባታ቞ው ወንድሞቜ መካኚል ርስት ሰጣ቞ው።
ምናሮ በዮርዳኖስ ማዶ ኚነበሩት ኚጊልያድና ኚባሳን በተጚማሪ አሥር ድርሻዎቜ ወጡለትፀ
ምክንያቱም ዹምናሮ ሎቶቜ ልጆቜ በወንዶቜ ልጆቹ መካኚል ርስት ተሰጥቷ቞ው ነበርፀ ዚጊልያድም ምድር ዚቀሩት ዹምናሮ ዘሮቜ ርስት ሆነ።
ዹምናሮ ወሰን ኹአሮር አንስቶ ኚሎኬም ፊት ለፊት እስኚምትገኘው እስኚ ሚክመታት ድሚስ ነበርፀ ወሰኑ በስተ ደቡብ በኩል ዚኀንታጱአ ነዋሪዎቜ እስኚሚገኙበት ምድር ይዘልቃል።
ዚታጱአ ምድር ዹምናሮ ሆነቜፀ በምናሮ ወሰን ላይ ዚምትገኘው ዚታጱአ ኹተማ ግን ዚኀፍሬም ዘሮቜ ነበሚቜ።
ወሰኑ ወደ ቃና ሾለቆ ይኾውም በስተ ደቡብ አቅጣጫ ወደ ሾለቆው ቁልቁል ይወርዳል። በምናሮ ኚተሞቜ መካኚል ዹሚገኙ ዚኀፍሬም ኚተሞቜ ዚነበሩ ሲሆን ዹምናሮ ወሰን በሾለቆው ሰሜናዊ ክፍል አድርጎ ባሕሩ ጋ ሲደርስ ያበቃል።
በስተ ደቡብ በኩል ያለው ዚኀፍሬም፣ በስተ ሰሜን በኩል ያለው ደግሞ ዹምናሮ ነበርፀ ባሕሩም ዚእሱ ወሰን ነበርፀ እነሱም በስተ ሰሜን እስኚ አሎር፣ በስተ ምሥራቅ ደግሞ እስኚ ይሳኮር ይደርሱ ነበር።
በይሳኮርና በአሮር ግዛቶቜ ውስጥ ለምናሮ ዚተሰጡት ዚሚኚተሉት ናቾው፩ ቀትሌንና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ ይብለአምና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ ዚዶር ነዋሪዎቜና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ እንዲሁም ዚኀንዶር ነዋሪዎቜና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ ዚታአናክ ነዋሪዎቜና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ ዚመጊዶ ነዋሪዎቜና በሥሯ ያሉት ኚተሞቜ፣ ሊስቱ ኮሚብታማ አካባቢዎቜ።
ሆኖም ዹምናሮ ዘሮቜ እነዚህን ኚተሞቜ መውሚስ አልቻሉምፀ ኚነአናውያን ይህን ምድር ላለመልቀቅ ቆርጠው ነበር።
እስራኀላውያን እያዚሉ በሄዱ ጊዜ ኚነአናውያንን ዚግዳጅ ሥራ እንዲሠሩ አስገደዷ቞ውፀ ይሁን እንጂ ሙሉ በሙሉ አላባሚሯ቞ውም።
ዚዮሎፍ ዘሮቜም ኢያሱን “አንድ ዕጣና አንድ ድርሻ ብቻ ርስት አድርገህ ዹሰጠኾን ለምንድን ነው? ይሖዋ እስካሁን ድሚስ ስለባሚኚን ዚሕዝባቜን ቁጥር በዝቷል” አሉት።
ኢያሱም “ቁጥራቜሁ ይህን ያህል ብዙ ኹሆነ ዚኀፍሬም ተራራማ አካባቢ በጣም ስለሚጠብባቜሁ ወደ ጫካው በመውጣት በፈሪዛውያንና በሹፋይም ምድር ዹሚገኘውን አካባቢ ለራሳቜሁ መንጥሩ” አላ቞ው።
ኚዚያም ዚዮሎፍ ዘሮቜ እንዲህ አሉትፊ “ተራራማው አካባቢ አይበቃንምፀ ደግሞም በሾለቆው ምድር ማለትም በቀትሌን እና በሥሯ በሚገኙት ኚተሞቜ እንዲሁም በኢይዝራኀል ሾለቆ ውስጥ ዚሚኖሩት ኚነአናውያን በሙሉ ዚብሚት ማጭድ ዹተገጠመላቾው ዹጩር ሠሚገሎቜ አሏ቞ው።”
በመሆኑም ኢያሱ ለዮሎፍ ቀት ይኾውም ለኀፍሬምና ለምናሮ እንዲህ አለ፩ “እናንተ ብዙ ሕዝብ ናቜሁፀ ታላቅ ኃይልም አላቜሁ። ድርሻቜሁ አንድ ዕጣ ብቻ አይሆንምፀ
ኹዚህ ይልቅ ተራራማው አካባቢ ዚእናንተ ይሆናል። አካባቢው ጫካ ቢሆንም ትመነጥሩታላቜሁፀ ዚግዛታቜሁም ወሰን ይሆናል። ምክንያቱም ኚነአናውያን ዚብሚት ማጭድ ዹተገጠመላቾው ዹጩር ሠሚገሎቜ ያሏ቞ውና ብርቱዎቜ ቢሆኑም እንኳ ኚምድሩ ታባርሯ቞ዋላቜሁ።”
ኚዚያም ሁለተኛው ዕጣ ለስምዖን ይኾውም ለስምዖን ነገድ በዚቀተሰቡ ወጣ። ርስታ቞ውም በይሁዳ ርስት መካኚል ነበር።
ርስታ቞ውም ዹሚኹተለው ነበር፩ ቀርሳቀህ ኚሳባ ጋር፣ ሞላዳ፣
ሃጻርሹአል፣ ባላህ፣ ኀጌም፣
ኀልቶላድ፣ በቱል፣ ሆርማ፣
ጺቅላግ፣ ቀትማርካቊት፣ ሃጻርሱሳ፣
ቀትለባኊት እና ሻሩሄንፀ በአጠቃላይ 13 ኚተሞቜ ኚነመንደሮቻ቞ውፀ
አይን፣ ሪሞን፣ ኀ቎ር እና አሻንፀ በአጠቃላይ አራት ኚተሞቜ ኚነመንደሮቻ቞ውፀ
እንዲሁም በእነዚህ ኚተሞቜ ዙሪያ ዚነበሩትን መንደሮቜ በሙሉ እስኚ ባዓላትበኀር ይኾውም በስተ ደቡብ እስኚምትገኘው እስኚ ራማ ድሚስ ያሉትን አካባቢዎቜ ይጚምራል። ዚስምዖን ነገድ ርስት በዚቀተሰቡ ይህ ነበር።
ለስምዖን ዘሮቜ ርስት ዹተሰጠው ኚይሁዳ ልጆቜ ድርሻ ላይ ተወስዶ ነበርፀ ምክንያቱም ዚይሁዳ ዘሮቜ ድርሻ቞ው በጣም በዝቶባ቞ው ነበር። በመሆኑም ዚስምዖን ልጆቜ ርስት ያገኙት በእነሱ ርስት መካኚል ነው።
በመቀጠል ሊስተኛው ዕጣ ለዛብሎን ዘሮቜ በዚቀተሰባ቞ው ወጣፀ ዚርስታ቞ውም ወሰን እስኚ ሳሪድ ድሚስ ይዘልቃል።
በስተ ምዕራብም ወደ ማሹአል ይወጣና እስኚ ዳባሌት ይደርሳልፀ ኚዚያም በዮቅነአም ፊት ለፊት እስካለው ሾለቆ ድሚስ ይሄዳል።
ኚሳሪድ ተነስቶ በስተ ምሥራቅ ወደ ፀሐይ መውጫ አቅጣጫ እስኚ ኪስሎትታቊር ድንበር ድሚስ ይሄድና ወደ ዳብራት ኚዚያም ወደ ያፊአ ይወጣል።
ኚዚያም ተነስቶ በስተ ምሥራቅ በፀሐይ መውጫ አቅጣጫ ወደ ጋትሔፌር፣ ወደ ኢትቃጺን ኹሄደ በኋላ ወደ ሪሞን ወጥቶ እስኚ ኒአ ይዘልቃል።
በመቀጠልም በስተ ሰሜን ዞሮት ወደ ሃናቶን ያመራልፀ ወሰኑ ዚሚያበቃው ይፍታህኀል ሞለቆ፣
ቃጣት፣ ናሃላል፣ ሺምሮን፣ ይዳላ እና ቀተልሔም ጋ ሲደርስ ነውፀ በአጠቃላይ 12 ኚተሞቜ ኚነመንደሮቻ቞ው ነበሩ።
ዚዛብሎን ዘሮቜ ርስት በዚቀተሰባ቞ው ይህ ነበር። ኚተሞቹና መንደሮቻ቞ው እነዚህ ነበሩ።
አራተኛው ዕጣ ዚወጣው ለይሳኮር ይኾውም ለይሳኮር ዘሮቜ በዚቀተሰባ቞ው ነበር።
ወሰናቾውም እስኚ ኢይዝራኀል፣ ኚሱሎት፣ ሹነም፣
ሃፋራይም፣ ሺኊን፣ አናሃራት፣
ራቢት፣ ቂሟን፣ ኀቀጜ፣
ሚመት፣ ኀንጋኒም፣ ኀንሃዳ እና ቀትጳጌጜ ድሚስ ነበር።
ኚዚያም እስኚ ታቊር፣ ሻሃጺማ እና ቀትሌሜሜ ይዘልቅ ነበርፀ ወሰናቾውም ዮርዳኖስ ጋ ሲደርስ ያበቃልፀ በአጠቃላይ 16 ኚተሞቜ ኚነመንደሮቻ቞ው ነበሩ።
ዚይሳኮር ነገድ ርስት በዚቀተሰቡ ይህ ነበርፀ ኚተሞቹና መንደሮቻ቞ው እነዚህ ነበሩ።
ኚዚያም አምስተኛው ዕጣ ለአሮር ነገድ በዚቀተሰቡ ወጣ።
ወሰናቾውም ሄልቃት፣ ሃሊ፣ ቀጀን፣ አክሻፍ፣
አላሜሌክ፣ አምዓድ እና ሚሜአል ነበር። በስተ ምዕራብም እስኚ ቀርሜሎስና እስኚ ሺሆርሊብናት ይደርስ ነበርፀ
ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ወደ ቀትዳጎን ተመልሶ እስኚ ዛብሎን እንዲሁም በስተ ሰሜን እስኚ ይፍታህኀል ሾለቆ ይደርስና እስኚ ቀትኀሜቅ እንዲሁም እስኚ ነኢኀል ይዘልቃልፀ በመቀጠልም በስተ ግራ በኩል ወደ ካቡል ይሄዳልፀ
ኚዚያም ወደ ኀብሮን፣ ሬሆብ፣ ሃሞን እና ቃና ሄዶ እስኚ ታላቋ ሲዶና ድሚስ ይደርሳል።
ወሰኑ ወደ ራማ ተመልሶ እስኚተመሞገቜው ኹተማ እስኚ ጢሮስ ይዘልቃል። ኚዚያም ወደ ሆሳ ይመለስና በአክዚብ ክልል ዹሚገኘው ባሕር፣
ዑማ፣ አፌቅ እና ሬሆብ ጋ ሲደርስ ያበቃልፀ በአጠቃላይ 22 ኚተሞቜ ኚነመንደሮቻ቞ው ነበሩ።
ዹአሮር ነገድ ርስት በዚቀተሰቡ ይህ ነው። ኚተሞቹና መንደሮቻ቞ው እነዚህ ነበሩ።
ስድስተኛው ዕጣ ዚወጣው ለንፍታሌም ዘሮቜ ይኾውም ለንፍታሌም ዘሮቜ በዚቀተሰባ቞ው ነበር።
ወሰናቾውም ኚሄሌፍ፣ በጻናኒም ኹሚገኘው ትልቅ ዛፍ፣ ኚአዳሚኔቄብ እና ኚያብነኀል አንስቶ እስኚ ላቁም ይደርሳልፀ ዮርዳኖስ ጋ ሲደርስም ያበቃል።
ወሰኑ በስተ ምዕራብ ወደ አዝኖትታቊር ይመለሳልፀ ኚዚያም በመነሳት ወደ ሁቆቃ ይሄድና በስተ ደቡብ እስኚ ዛብሎን፣ በስተ ምዕራብ እስኚ አሎር፣ በስተ ምሥራቅ ደግሞ በዮርዳኖስ እስኚሚገኘው እስኚ ይሁዳ ይደርሳል።
ዚተመሞጉት ኚተሞቜ እነዚህ ነበሩፊ ጺዲም፣ ጞር፣ ሃማት፣ ራቃት፣ ኪኔሬት፣
አዳማ፣ ራማ፣ ሃጟር፣
ቃዎሜ፣ ኀድራይ፣ ኀንሃጟር፣
ይርኊን፣ ሚግዳልኀል፣ ሆሬም፣ ቀትአናት እና ቀትሌሜሜፀ በአጠቃላይ 19 ኚተሞቜ ኚነመንደሮቻ቞ው ነበሩ።
ዚንፍታሌም ነገድ ርስት በዚቀተሰቡ ይህ ነበርፀ ኚተሞቹና መንደሮቻ቞ው እነዚህ ነበሩ።
ሰባተኛው ዕጣ ለዳን ነገድ በዚቀተሰቡ ወጣ።
ዚርስታ቞ውም ወሰን ጟራ፣ ኀሜታዖል፣ ኢርሻሜሜ፣
ሻአላቢን፣ አይሎን፣ ይትላ፣
ኀሎን፣ ቲምና፣ ኀቅሮን፣