text stringlengths 4 267 |
|---|
ስለሆነም የዮሴፍ ዘሮች ምናሴና ኤፍሬም ርስታቸው የሆነውን መሬት ወሰዱ። |
የኤፍሬም ዘሮች ወሰን በየቤተሰባቸው የሚከተለው ነው፦ በስተ ምሥራቅ በኩል የርስታቸው ወሰን አጣሮትዓዳር ሲሆን እስከ ላይኛው ቤትሆሮንም ይደርሳል፤ |
ከዚያም እስከ ባሕሩ ድረስ ይዘልቃል። ወሰኑ በስተ ሰሜን ሚክመታት ሲሆን በስተ ምሥራቅ በኩል ዞሮ ወደ ታአናትሺሎ ይሄድና በስተ ምሥራቅ አቅጣጫ ወደ ያኖአህ ይዘልቃል። |
ከያኖአህ ተነስቶም ወደ አጣሮትና ወደ ናዕራ ቁልቁል በመውረድ ኢያሪኮ ይደርስና ወደ ዮርዳኖስ ይዘልቃል። |
ከዚያም ከታጱአ ተነስቶ በስተ ምዕራብ በኩል እስከ ቃና ሸለቆ በመዝለቅ ባሕሩ ጋ ሲደርስ ያበቃል። የኤፍሬም ነገድ በየቤተሰቡ ያገኘው ርስት ይህ ነው፤ |
የኤፍሬም ዘሮች በምናሴ ርስት ውስጥም የተከለሉ ከተሞች ነበሯቸው፤ ከተሞቹ በሙሉ ከነመንደሮቻቸው የእነሱ ነበሩ። |
ሆኖም በጌዜር ይኖሩ የነበሩትን ከነአናውያን አላባረሯቸውም፤ ከነአናውያንም እስከ ዛሬ ድረስ በኤፍሬም መካከል ይኖራሉ፤ የግዳጅ ሥራ የመሥራት ግዴታም ተጥሎባቸዋል። |
ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ የሚገኙት የአሞራውያን ነገሥታት ሁሉ እንዲሁም በባሕሩ አጠገብ ያሉት የከነአናውያን ነገሥታት በሙሉ ይሖዋ እስራኤላውያን ዮርዳኖስን እስኪሻገሩ ድረስ የወንዙን ውኃ በፊታቸው እንዳደረቀው ሲሰሙ ልባቸው ቀለጠ፤ በእስራኤላውያንም የተነሳ ወኔ ከድቷቸው ነበር። |
በዚያን ጊዜ ይሖዋ ኢያሱን “የባልጩት ቢላ ሠርተህ እስራኤላውያን ወንዶችን እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ግረዛቸው” አለው። |
ስለሆነም ኢያሱ የባልጩት ቢላ ሠርቶ እስራኤላውያን ወንዶችን ጊብዓትሃራሎት በተባለ ስፍራ ገረዛቸው። |
ኢያሱ የገረዛቸው በዚህ የተነሳ ነው፦ ከግብፅ በወጣው ሕዝብ መካከል የነበሩት ወንዶች ሁሉ ይኸውም ለውጊያ ብቁ የሆኑት ወንዶች በሙሉ ከግብፅ ከወጡ በኋላ በጉዞ ላይ ሳሉ በምድረ በዳ ሞተዋል። |
ከግብፅ የወጣው ሕዝብ ሁሉ ተገርዞ ነበር፤ ከግብፅ ከወጡ በኋላ በጉዞ ላይ ሳሉ በምድረ በዳ የተወለደው ሕዝብ ግን አልተገረዘም ነበር። |
መላው ብሔር ይኸውም የይሖዋን ቃል ያልታዘዙት ከግብፅ የወጡት ለውጊያ ብቁ የሆኑ ወንዶች ሁሉ ሞተው እስኪያልቁ ድረስ እስራኤላውያን በምድረ በዳ 40 ዓመት ተጓዙ። ይሖዋም ለእኛ ለመስጠት ለአባቶቻቸው የማለላቸውን ምድር ይኸውም ወተትና ማር የምታፈሰውን ምድር እንዲያዩ ፈጽሞ እንደማይፈቅድላቸው ይሖዋ ምሎ ነበር። |
በመሆኑም በእነሱ ምትክ ወንዶች ልጆቻቸውን አስነሳ። ኢያሱም እነዚህን ገረዛቸው፤ ምክንያቱም በጉዞ ላይ ሳሉ ስላልገረዟቸው ከነሸለፈታቸው ነበሩ። |
እነሱም መላውን ብሔር ገርዘው ሲጨርሱ የተገረዙት ከቁስላቸው እስኪያገግሙ ድረስ እዚያው በሰፈሩበት ቦታ ቆዩ። |
ከዚያም ይሖዋ ኢያሱን “በዛሬው ዕለት የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ” አለው። በመሆኑም የዚያ ስፍራ ስም ጊልጋል ተባለ፤ እስከ ዛሬም ድረስ የሚታወቀው በዚሁ ስሙ ነው። |
እስራኤላውያንም በጊልጋል እንደሰፈሩ ቆዩ፤ ወሩ በገባ በ14ኛው ቀን ምሽት ላይም በኢያሪኮ በረሃማ ሜዳ የፋሲካን በዓል አከበሩ። |
ከፋሲካውም ቀን በኋላ በዚያው ዕለት የምድሪቱን ፍሬ ማለትም ቂጣና የተጠበሰ እሸት በሉ። |
ከምድሪቱ ፍሬ በበሉበት ቀን ማግስት መናው ተቋረጠ፤ ከዚያ በኋላ እስራኤላውያን መና አልወረደላቸውም፤ ከዚህ ይልቅ በዚያ ዓመት የከነአንን ምድር ፍሬ መብላት ጀመሩ። |
ኢያሱ በኢያሪኮ አቅራቢያ ሳለ፣ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ፊት ለፊቱ ቆሞ አየ። ኢያሱም ወደ እሱ ሄዶ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው። |
እሱም መልሶ እንዲህ አለው፦ “አይደለሁም፤ እኔ አሁን የመጣሁት የይሖዋ ሠራዊት አለቃ ሆኜ ነው።” በዚህ ጊዜ ኢያሱ በግንባሩ መሬት ላይ ተደፍቶ በመስገድ “ታዲያ ጌታዬ ለአገልጋዩ የሚነግረው ምንድን ነው?” አለው። |
የይሖዋ ሠራዊት አለቃም ኢያሱን “የቆምክበት ስፍራ ቅዱስ ስለሆነ ጫማህን አውልቅ” አለው። ኢያሱም ወዲያውኑ እንደተባለው አደረገ። |
እንግዲህ እስራኤላውያን በከነአን ምድር ርስት አድርገው የወረሱት ይኸውም ካህኑ አልዓዛር፣ የነዌ ልጅ ኢያሱና የእስራኤል ነገዶች የአባቶች ቤት መሪዎች ያወረሷቸው ምድር ይህ ነው። |
ይሖዋ ዘጠኙን ነገድና ግማሹን ነገድ አስመልክቶ በሙሴ አማካኝነት በሰጠው ትእዛዝ መሠረት ርስታቸው የተከፋፈለው በዕጣ ነበር። |
ሙሴ ለሌሎቹ ሁለት ነገዶችና ለሌላኛው ግማሽ ነገድ ከዮርዳኖስ ማዶ ርስት ሰጥቷቸው ነበር፤ ለሌዋውያኑ ግን በእነሱ መካከል ርስት አልሰጣቸውም። |
የዮሴፍ ዘሮች እንደ ሁለት ነገድ ተደርገው ይቆጠሩ የነበረ ሲሆን እነሱም ምናሴና ኤፍሬም ናቸው፤ ለሌዋውያኑም ከሚኖሩባቸው ከተሞች እንዲሁም ለከብቶቻቸውና ለንብረቶቻቸው ከሚሆን መሬት በስተቀር በምድሪቱ ውስጥ ድርሻ አልሰጧቸውም። |
በመሆኑም እስራኤላውያን ይሖዋ ሙሴን ባዘዘው መሠረት ምድሪቱን ተከፋፈሉ። |
ከዚያም የይሁዳ ሰዎች በጊልጋል ወደ ኢያሱ ቀረቡ፤ የቀኒዛዊው የየፎኒ ልጅ ካሌብም እንዲህ አለው፦ “ይሖዋ በቃዴስበርኔ ስለ እኔና ስለ አንተ ለእውነተኛው አምላክ ሰው ለሙሴ ምን እንዳለው በሚገባ ታውቃለህ። |
የይሖዋ አገልጋይ ሙሴ ምድሪቱን እንድሰልል ከቃዴስበርኔ ሲልከኝ የ40 ዓመት ሰው ነበርኩ፤ እኔም ትክክለኛውን መረጃ ይዤ መጣሁ። |
አብረውኝ የወጡት ወንድሞቼ የሕዝቡ ልብ እንዲቀልጥ ቢያደርጉም እኔ ግን አምላኬን ይሖዋን በሙሉ ልቤ ተከተልኩት። |
ሙሴም በዚያ ዕለት ‘አምላኬን ይሖዋን በሙሉ ልብህ ስለተከተልከው እግርህ የረገጣት ምድር ለዘለቄታው የአንተና የልጆችህ ርስት ትሆናለች’ ብሎ ማለ። |
እስራኤል በምድረ በዳ እየተጓዘ ሳለ ይሖዋ ለሙሴ ይህን ቃል ከገባለት ጊዜ አንስቶ ይሖዋ በገባው ቃል መሠረት እነዚህን 45 ዓመታት በሕይወት አቆይቶኛል፤ ይኸው ዛሬ 85 ዓመት ሆኖኛል። |
ደግሞም ሙሴ በላከኝ ጊዜ የነበረኝ ብርታት ዛሬም አለኝ። ልክ እንደዚያን ጊዜ ሁሉ አሁንም ወደ ጦርነት ለመሄድም ሆነ ሌሎች ነገሮችን ለማከናወን የሚያስችል ጥንካሬ አለኝ። |
ስለዚህ ይሖዋ በዚያ ዕለት ቃል የገባውን ይህን ተራራማ አካባቢ ስጠኝ። የተመሸጉ ታላላቅ ከተሞች ያሏቸው ኤናቃውያን በአካባቢው እንደሚኖሩ በዚያ ቀን ሰምተህ የነበረ ቢሆንም ይሖዋ ከእኔ ጋር እንደሚሆን ጥርጥር የለውም፤ ይሖዋም በገባው ቃል መሠረት ድል አድርጌ አባርራቸዋለሁ።” |
በመሆኑም ኢያሱ ባረከው፤ ኬብሮንንም ለየፎኒ ልጅ ለካሌብ ርስት አድርጎ ሰጠው። |
ኬብሮን ለቀኒዛዊው ለየፎኒ ልጅ ለካሌብ እስከ ዛሬ ድረስ ርስት የሆነችው ለዚህ ነው፤ ምክንያቱም እሱ የእስራኤልን አምላክ ይሖዋን በሙሉ ልቡ ተከትሏል። |
ኬብሮን ከዚያ በፊት ቂርያትአርባ ተብላ ትጠራ ነበር (አርባ በኤናቃውያን መካከል ታላቅ ሰው ነበር)። ምድሪቱም ከጦርነት አረፈች። |
ከዚያም ኢያሱ ሮቤላውያንን፣ ጋዳውያንንና የምናሴን ነገድ እኩሌታ ጠርቶ |
እንዲህ አላቸው፦ “የይሖዋ አገልጋይ ሙሴ ያዘዛችሁን ሁሉ ፈጽማችኋል፤ እኔም ባዘዝኳችሁ ነገር ሁሉ ቃሌን ሰምታችኋል። |
በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት እስከ ዛሬ ድረስ ወንድሞቻችሁን አልተዋችሁም፤ አምላካችሁ ይሖዋ ከሰጣችሁ ትእዛዝ ጋር በተያያዘ ግዴታችሁን ተወጥታችኋል። |
እንግዲህ አሁን አምላካችሁ ይሖዋ ለወንድሞቻችሁ ቃል በገባላቸው መሠረት እረፍት ሰጥቷቸዋል። በመሆኑም የይሖዋ አገልጋይ ሙሴ ከዮርዳኖስ ማዶ ርስት አድርጎ በሰጣችሁ ምድር ወደሚገኙት ድንኳኖቻችሁ መመለስ ትችላላችሁ። |
ብቻ እናንተ አምላካችሁን ይሖዋን በመውደድ፣ በመንገዶቹ ሁሉ በመሄድ፣ ትእዛዛቱን በመጠበቅ፣ ከእሱ ጋር በመጣበቅ እንዲሁም በሙሉ ልባችሁና በሙሉ ነፍሳችሁ እሱን በማገልገል የይሖዋ አገልጋይ ሙሴ የሰጣችሁን ትእዛዝና ሕግ በጥንቃቄ ፈጽሙ።” |
ከዚያም ኢያሱ ባረካቸውና አሰናበታቸው፤ እነሱም ወደ ድንኳኖቻቸው ሄዱ። |
ሙሴ ለምናሴ ነገድ እኩሌታ በባሳን ርስት ሰጥቶ ነበር፤ ኢያሱ ደግሞ ለቀረው የነገዱ እኩሌታ ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ከወንድሞቻቸው ጋር መሬት ሰጣቸው። በተጨማሪም ኢያሱ ወደ ድንኳኖቻቸው እንዲሄዱ ባሰናበታቸው ጊዜ ባረካቸው፤ |
እንዲህም አላቸው፦ “ብዙ ሀብት፣ እጅግ ብዙ ከብት፣ ብር፣ ወርቅ፣ መዳብ፣ ብረትና እጅግ ብዙ ልብስ ይዛችሁ ወደየድንኳኖቻችሁ ተመለሱ። ከጠላቶቻችሁ ያገኛችሁትን ምርኮ ወስዳችሁ ከወንድሞቻችሁ ጋር ተካፈሉ።” |
ከዚህ በኋላ ሮቤላውያን፣ ጋዳውያንና የምናሴ ነገድ እኩሌታ በከነአን ምድር በምትገኘው በሴሎ ከነበሩት ከሌሎቹ እስራኤላውያን ተለይተው ወደ ጊልያድ ምድር ይኸውም ይሖዋ በሙሴ አማካኝነት በሰጠው ትእዛዝ መሠረት ርስት አድርገው ወደሰፈሩባት ምድር ተመለሱ። |
ሮቤላውያን፣ ጋዳውያንና የምናሴ ነገድ እኩሌታ በከነአን ምድር ወዳለው የዮርዳኖስ ክልል ሲደርሱ በዮርዳኖስ አጠገብ ግዙፍ የሆነ አስደናቂ መሠዊያ ሠሩ። |
በኋላም ሌሎቹ እስራኤላውያን ይህን ሲሰሙ “ሮቤላውያን፣ ጋዳውያንና የምናሴ ነገድ እኩሌታ የእስራኤላውያን ክልል በሆነው በከነአን ምድር ወሰን ላይ በሚገኘው የዮርዳኖስ ክልል መሠዊያ ሠርተዋል” አሉ። |
እስራኤላውያንም ይህን በሰሙ ጊዜ መላው የእስራኤላውያን ማኅበረሰብ እነሱን ለመውጋት በሴሎ ተሰበሰበ። |
ከዚያም እስራኤላውያን የካህኑን የአልዓዛርን ልጅ ፊንሃስን በጊልያድ ምድር ወዳሉት ወደ ሮቤላውያን፣ ወደ ጋዳውያን እና ወደ ምናሴ ነገድ እኩሌታ ላኩት፤ |
ከእሱም ጋር አሥር አለቆችን ይኸውም ከሁሉም የእስራኤል ነገዶች ከእያንዳንዱ የአባቶች ቤት አንድ አንድ አለቃ አብረው ላኩ፤ እነዚህም እያንዳንዳቸው ከእስራኤል የሺህ አለቆች መካከል የሆኑ የአባቶች ቤት መሪዎች ነበሩ። |
እነሱም በጊልያድ ምድር ወዳሉት ወደ ሮቤላውያን፣ ወደ ጋዳውያንና ወደ ምናሴ ነገድ እኩሌታ መጥተው እንዲህ አሏቸው፦ |
“መላው የይሖዋ ጉባኤ እንዲህ ይላል፦ ‘በእስራኤል አምላክ ላይ እንዲህ ያለ ታማኝነት የጎደለው ድርጊት የፈጸማችሁት ለምንድን ነው? ለራሳችሁ መሠዊያ በመሥራትና በይሖዋ ላይ በማመፅ ይኸው ዛሬ ይሖዋን ከመከተል ዞር ብላችኋል። |
በፌጎር የሠራነው ስህተት አንሶ ነው? ምንም እንኳ ያኔ በይሖዋ ጉባኤ ላይ መቅሰፍት ቢወርድም ይኸው እስከ ዛሬ ድረስ ከዚህ ነገር ራሳችንን አላነጻንም። |
እናንተ ደግሞ ዛሬ ይሖዋን ከመከተል ዞር ትላላችሁ! ዛሬ እናንተ በይሖዋ ላይ ብታምፁ ነገ ደግሞ እሱ በመላው የእስራኤል ማኅበረሰብ ላይ ይቆጣል። |
የወረሳችኋት ምድር ረክሳ ከሆነ የይሖዋ የማደሪያ ድንኳን ወደሚገኝበት የይሖዋ ርስት ወደሆነው ምድር ተሻግራችሁ በመካከላችን ኑሩ፤ ሆኖም ከአምላካችን ከይሖዋ መሠዊያ ሌላ ለራሳችሁ መሠዊያ በመሥራት በይሖዋ ላይ አታምፁ፣ እኛንም ዓመፀኞች አታድርጉን። |
የዛራ ልጅ አካን ለጥፋት ከተለየው ነገር ጋር በተያያዘ ታማኝነት የጎደለው ድርጊት በፈጸመ ጊዜ በመላው የእስራኤል ማኅበረሰብ ላይ ቁጣ አልወረደም? በሠራው ስህተት የሞተው እሱ ብቻ አልነበረም።’” |
በዚህ ጊዜ ሮቤላውያን፣ ጋዳውያንና የምናሴ ነገድ እኩሌታ ለእስራኤል የሺህ አለቆች እንዲህ ሲሉ መለሱላቸው፦ |
“የአማልክት አምላክ፣ ይሖዋ! የአማልክት አምላክ፣ ይሖዋ! እሱ ያውቃል፤ እስራኤልም ቢሆን ያውቃል። በይሖዋ ላይ ዓምፀንና ታማኝነት የጎደለው ድርጊት ፈጽመን ከሆነ ዛሬ አይታደገን። |
ለራሳችን መሠዊያ የሠራነው ይሖዋን ከመከተል ዞር ለማለት ወይም በላዩ ላይ የሚቃጠሉ መባዎችንና የእህል መባዎችን ለማቅረብ አሊያም የኅብረት መሥዋዕቶችን ለመሠዋት ብለን ከሆነ ይሖዋ ይቅጣን። |
እኛ ግን ይህን ያደረግነው ወደፊት ልጆቻችሁ ልጆቻችንን እንዲህ ማለታቸው አይቀርም ብለን ስለሰጋን ነው፦ ‘ከእስራኤል አምላክ ከይሖዋ ጋር ምን ግንኙነት አላችሁ? |
ይሖዋ ሮቤላውያንና ጋዳውያን በሆናችሁት በእናንተና በእኛ መካከል ዮርዳኖስን ድንበር አድርጓል። እናንተ በይሖዋ ዘንድ ምንም ድርሻ የላችሁም።’ ልጆቻችሁም ልጆቻችን ይሖዋን እንዳያመልኩ እንቅፋት ይሆኑባቸዋል።” |
“በመሆኑም እንዲህ አልን፦ ‘እንግዲህ አንድ እርምጃ መውሰድ አለብን፤ መሠዊያ እንሥራ፤ ይህም የሚቃጠል መባ ወይም መሥዋዕት የሚቀርብበት አይደለም፤ |
ከዚህ ይልቅ የሚቃጠሉ መባዎቻችንን፣ መሥዋዕቶቻችንንና የኅብረት መሥዋዕቶቻችንን ይዘን በመምጣት በይሖዋ ፊት አገልግሎት እንደምናቀርብ ለማሳየት በእኛና በእናንተ እንዲሁም ከእኛ በኋላ በሚመጡት ዘሮቻችን መካከል ምሥክር የሚሆን ነው፤ ስለዚህ ወደፊት ልጆቻችሁ ልጆቻችንን “እናንተ በይሖዋ ዘንድ ምንም ድርሻ የላችሁም” አይሏቸውም።’ |
ስለዚህ እኛ እንዲህ አልን፦ ‘ወደፊት እኛንም ሆነ ዘሮቻችንን እንዲህ ቢሉ እኛ ደግሞ “የሚቃጠል መባ ወይም መሥዋዕት የሚቀርብበት ሳይሆን በእኛና በእናንተ መካከል ምሥክር እንዲሆን አባቶቻችን የይሖዋን መሠዊያ አስመስለው የሠሩት መሠዊያ ይኸውና” እንላቸዋለን።’ |
በማደሪያ ድንኳኑ ፊት ካለው ከአምላካችን ከይሖዋ መሠዊያ ሌላ የሚቃጠል መባ፣ የእህል መባና መሥዋዕት የሚቀርብበት መሠዊያ በመሥራት ዛሬ በይሖዋ ላይ ማመፅና ይሖዋን ከመከተል ወደኋላ ማለት በእኛ በኩል ፈጽሞ የማይታሰብ ነገር ነው!” |
ካህኑ ፊንሃስና ከእሱ ጋር የነበሩት የማኅበረሰቡ አለቆች ይኸውም የእስራኤል የሺህ አለቆች የሮቤል፣ የጋድና የምናሴ ዘሮች የተናገሩትን በሰሙ ጊዜ ነገሩን አሳማኝ ሆኖ አገኙት። |
በመሆኑም የካህኑ የአልዓዛር ልጅ ፊንሃስ የሮቤልን፣ የጋድንና የምናሴን ዘሮች እንዲህ አላቸው፦ “በይሖዋ ላይ እንዲህ ያለ ታማኝነት የጎደለው ድርጊት ስላልፈጸማችሁ ይሖዋ በመካከላችን እንዳለ ዛሬ አውቀናል። እነሆ እስራኤላውያንን ከይሖዋ እጅ ታድጋችኋል።” |
ከዚያም የካህኑ የአልዓዛር ልጅ ፊንሃስና አለቆቹ በጊልያድ ምድር ከሰፈሩት ከሮቤላውያንና ከጋዳውያን ዘንድ ተመልሰው በከነአን ምድር ወደሚገኙት ወደ ሌሎቹ እስራኤላውያን በመምጣት ስለ ሁኔታው ነገሯቸው። |
እስራኤላውያንም ነገሩን አሳማኝ ሆኖ አገኙት። ከዚያም እስራኤላውያን አምላክን ባረኩ፤ ከዚያ በኋላም በሮቤላውያንና በጋዳውያን ላይ ስለመዝመትም ሆነ የሚኖሩባትን ምድር ስለማጥፋት አንስተው አያውቁም። |
ስለሆነም ሮቤላውያንና ጋዳውያን “ይህ መሠዊያ ይሖዋ እውነተኛ አምላክ ስለመሆኑ በመካከላችን ያለ ምሥክር ነው” በማለት ለመሠዊያው ስም አወጡለት። |
ለይሁዳ ነገድ ለየቤተሰቡ በዕጣ የተሰጠው ርስት እስከ ኤዶም ይኸውም እስከ ጺን ምድረ በዳና እስከ ኔጌብ ደቡባዊ ጫፍ ድረስ ይዘልቃል። |
ደቡባዊው ወሰናቸው ከጨው ባሕር ዳርቻ ይኸውም ከባሕሩ ደቡባዊ ወሽመጥ ይነሳል። |
ከዚያም በስተ ደቡብ እስከ አቅራቢም አቀበት ድረስ ይዘልቅና ወደ ጺን ይሻገራል፤ በመቀጠልም ከደቡብ ወደ ቃዴስበርኔ ይወጣና በኤስሮን በኩል አልፎ ወደ አዳር ከሄደ በኋላ ወደ ቃርቃ ይዞራል። |
ከዚያም ወደ አጽሞን ይዘልቅና ወደ ግብፅ ሸለቆ ይቀጥላል፤ ወሰኑም ባሕሩ ጋ ሲደርስ ያበቃል። ደቡባዊ ወሰናቸው ይህ ነበር። |
ምሥራቃዊው ወሰን ደግሞ ጨው ባሕር ሲሆን ይህም እስከ ዮርዳኖስ ጫፍ ይደርሳል፤ በስተ ሰሜን በኩል ያለው ወሰን በዮርዳኖስ ጫፍ ላይ የሚገኘው የባሕሩ ወሽመጥ ነበር። |
ከዚያም ወሰኑ ወደ ቤትሆግላ ይወጣና ከቤትአረባ በስተ ሰሜን በኩል ያልፋል፤ የሮቤል ልጅ የቦሃን ድንጋይ እስካለበትም ድረስ ይዘልቃል። |
በመቀጠልም በአኮር ሸለቆ ወደምትገኘው ወደ ደቢር ይወጣና በስተ ሰሜን ወደ ጊልጋል ይኸውም ከሸለቆው በስተ ደቡብ ከሚገኘው ከአዱሚም አቀበት ፊት ለፊት ወዳለው ቦታ ይታጠፋል፤ ከዚያም ወደ ኤንሼሜሽ ውኃዎች ይሄድና ኤንሮጌል ላይ ያበቃል። |
ወሰኑ እስከ ሂኖም ልጅ ሸለቆ ይኸውም በስተ ደቡብ እስከሚገኘው እስከ ኢያቡሳውያን ሸንተረር ማለትም እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ይወጣል፤ በተጨማሪም በረፋይም ሸለቆ ሰሜናዊ ጫፍ ላይ እስከሚገኘውና ከሂኖም ሸለቆ ምዕራባዊ ክፍል ትይዩ እስካለው ተራራ አናት ድረስ ይዘልቃል። |
ከዚያም ከተራራው አናት ተነስቶ እስከ ነፍቶአ የውኃ ምንጮች ድረስ ይሄዳል፤ እንዲሁም በኤፍሮን ተራራ ላይ እስካሉት ከተሞች ይዘልቃል፤ በመቀጠልም እስከ ባዓላ ማለትም እስከ ቂርያትየአሪም ይሄዳል። |
ወሰኑ ከባዓላ ተነስቶ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ በመዞር ወደ ሴይር ተራራ ይሄዳል፤ ከዚያም በስተ ሰሜን ወደ የአሪም ተራራ ሸንተረር ማለትም ወደ ከሳሎን ያልፋል፤ በመቀጠልም ወደ ቤትሼሜሽ በመውረድ ወደ ቲምና ይዘልቃል። |
ወደ ሰሜን አቅጣጫ ወደ ኤቅሮን ሸንተረር ከወጣም በኋላ ወደ ሺከሮን ይሄዳል፤ ከዚያም ባዓላ ተራራን አልፎ ወደ ያብነኤል ይወጣል፤ ባሕሩም ጋ ሲደርስ ያበቃል። |
ምዕራባዊው ወሰን ታላቁ ባሕርና ዳርቻው ነበር። እንግዲህ የይሁዳ ዘሮች በየቤተሰባቸው ወሰናቸው ዙሪያውን ይህ ነበር። |
ኢያሱ ይሖዋ ባዘዘው መሠረት ለየፎኒ ልጅ ለካሌብ በይሁዳ ዘሮች መካከል የምትገኘውን ኬብሮን የተባለችውን ቂርያትአርባን ድርሻ አድርጎ ሰጠው (አርባ የኤናቅ አባት ነበር)። |
በመሆኑም ካሌብ የኤናቅ ዘሮች የሆኑትን ሦስቱን የኤናቅ ልጆች ማለትም ሸሻይን፣ አሂማንን እና ታልማይን ከዚያ አባረራቸው። |
ከዚያ ተነስቶም በደቢር ነዋሪዎች ላይ ዘመተ። (ደቢር ቀደም ሲል ቂርያትሰፈር ትባል ነበር።) |
ካሌብም “ቂርያትሰፈርን መትቶ በቁጥጥር ሥር ላደረጋት ሰው ሴት ልጄን አክሳን እድርለታለሁ” አለ። |
የካሌብ ወንድም የሆነው የቀናዝ ልጅ ኦትኒኤልም ከተማዋን በቁጥጥር ሥር አደረጋት። ስለሆነም ካሌብ ሴት ልጁን አክሳን ዳረለት። |
እሷም ወደ ባሏ ቤት እየሄደች ሳለ ባሏን ከአባቷ መሬት እንዲጠይቅ ወተወተችው። ከዚያም ከአህያዋ ላይ ወረደች። በዚህ ጊዜ ካሌብ “ምን ፈለግሽ?” ሲል ጠየቃት። |
እሷም “የሰጠኸኝ በስተ ደቡብ ያለ ቁራሽ መሬት ስለሆነ እባክህ ባርከኝ፤ ጉሎትማይምንም ስጠኝ” አለችው። ስለዚህ ላይኛውን ጉሎት እና ታችኛውን ጉሎት ሰጣት። |
የይሁዳ ነገድ በየቤተሰባቸው የተሰጣቸው ርስት ይህ ነበር። |
በኤዶም ወሰን በኩል ባለው የይሁዳ ነገድ ክልል ደቡባዊ ጫፍ ላይ የሚገኙት ከተሞች እነዚህ ናቸው፦ ቃብጽኤል፣ ኤዴር፣ ያጉር፣ |
ቂና፣ ዲሞና፣ አድዓዳ፣ |
ቃዴሽ፣ ሃጾር፣ ይትናን፣ |
ዚፍ፣ ተሌም፣ በዓሎት፣ |
ሃጾርሃዳታ፣ ቀሪዮትሄጽሮን ማለትም ሃጾር፣ |
አማም፣ ሼማ፣ ሞላዳ፣ |
ሃጻርጋዳ፣ ሄሽሞን፣ ቤትጳሌጥ፣ |
ሃጻርሹአል፣ ቤርሳቤህ፣ ቢዝዮትያ፣ |
ባዓላ፣ ኢዪም፣ ኤጼም፣ |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.